cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

𝘚𝘶𝘯𝘢 𝘪𝘴𝘭𝘢𝘮𝘪𝘤 𝘭𝘪𝘣𝘳𝘢𝘳𝘺

"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታህ ሥም" ቁርዓን96:1

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
238
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-47 أيام
-430 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

የመንገድ ላይ ዳዕዋ.aac2.49 MB
የመንገድ ላይ ዳዕዋ.m4a4.37 MB
Repost from "ANTi ቢድዓ"
🗞ከምርጦቹ አንደበት🗞⑧⑨ {የሰውን ውስጥ አትፈላፈል} "አንድ ሰውዬ ሰላት ውስጥ ሲያለቅስ ተመለከትኩ ከዚያም እኔ ይዩልኝ ይሆናል ብዬ ጠረጠርኩት ከዚያ በሗላ ለአመት ያክል ለአላህ ብሎ ማልቀስን ተከለከልኩኝ" መክሁል 📖አልዑቁባት ሊብኒ አቢ ዱንያ (83) በየቀኑ መሰል መልእክቶች እንዲደርስዎ ሊንኩን ይርገጡ  👇 T.me/anti_beda
إظهار الكل...
"ለኒቃብ ግር ግር ሰዋቡ ንግግር" በሚል የተዘጋጀ የኒቃብን ዋጂብነት አስመልክቶ የተለያዩ መረጃዎችን ያካተተ እንዲሁም ዋጂብ አይደለም ለሚሉት በቂ መልስ የተሰጠበት አጭር ሪሳላ መፅሀፍ ነው። በሰዑድ ጀማል T.me/anti_bed t.me/anti_beda
إظهار الكل...
ለኒቃብ ግር ግር ሰዋቡ ንግግር.pdf3.93 MB
አባ ቅጣው ኻሊድ! ~ በፋርስ ኤምፓየር እና በሮማ ኤምፓየር መካከል የተካሄደው ጦርነት 700 ዓመታት ዘልቋል። በዚህ ረጅም ዘመን ውስጥ ከ1000 በላይ ጦርነቶችን አካሂደዋል። ኻሊድ ብኑል ወሊድ ግን ሁለቱንም ኤምፓየሮች በ4 ዓመታት ብቻ ነበር ያንኮታኮታቸው። ፋርሶችን በ15 ጦርነት ድል አድርጎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ኃያልና ገናና ሆኖ ለረጅም ዘመናት የዘለቀውን መንግስታቸውን ሙሉ በሙሉ ከምድረ ገፅ አጠፋው። ለአንድ ሺህ አመታት ምስራቅ ላይ የነገሰውን የሮማ ቁጥጥር በዘጠኝ ጦርነቶች ቋጨው። በተናጠል ቢያቅታቸው ጊዜ የዘመናት ባላንጣዎቹ ፋርስና ሮማ ኻሊድ ብኑል ወሊድን ለመውጋት ህብረት ፈጥረው የፊራድ ጦርነት ላይ ገጥመው ነበር። ያም ሆኖ የዘመኑ ኃያላን ህብረት የኻሊድን ጦር መቋቋም አልቻለም። ይልቁንም ፍፁም በሆነ የበላይነት መራር የሆነ የሽንፈት ጽዋን ነበር ያቀመሳቸው። እኚህ ናቸው አባቶቼ - አምሳያ ካለህ ዝከር በሰው ልጅ ረጅም ታሪክ - የማይገኝላቸው ወደር የፍትህ የጀግንነት - ጫፍ የተቆናጠጡ ለጨካኞች ተንበርክከው - ፍፁም እጅ የማይሰጡ። Ibnu Munewor = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

ለዒልም ተማሪዎች ጉርሻ ~ ኪታብ ከሚቀሩ ተማሪዎች ውስጥ ብዙዎቹ ለልፋታቸው የሚመጥን በቂ ግንዛቤ አይጨብጡም። ከነዚህ በተቃራኒ ደግሞ በቂራአት ማእድ ላይ ያላቸው ቆይታ አነስተኛ ሆኖ የተሻለ የሚጠቀሙ አሉ። ልዩነቱ ከምን የመነጨ ነው? ለዚህ ልዩነት ብዙ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። ከነዚህ ውስጥ አንዱ አድምቶ አለመቅራት የሚያመጣው ክፍተት ነው። የብዙ ተማሪዎች አያያዝ የለብ ለብ ነው። አንዱን ኪታብ ጥንቅቅ አድርገን ሳንይዝ ከፍ ወዳለው ለመግባት ያለን ጉጉት ብዙ ቀርተናል የሚል ጉጉታችንን ከማርካት ባለፈ ብስለት እንዳይኖረን ሊያደርገን ይችላል። ይህንን ክፍተታችንን ለመድፈን ከሚያግዙ መንገዶች ውስጥ ሶስቱን ላንሳ፦ 1- ቃላት ለቀማ 2- መልእክቱን መጨበጥ 3- ነጠብጣቦችን ማገናኘት ላብራራቸው። 1- ቃላት ለቀማ፦ ከምንቀራው ኪታብ ውስጥ አንድ የማናውቀው ቃል መኖር የለበትም። በተቻለ መጠን ሁሉንም ልቅም አድርገን ልንይዝ ይገባል። በዚህ መልኩ ስንሄድ ደርስ በጣም እየቀለለን ነው የሚሄደው። ቃላት በቅጡ ሳንይዝ የምንጓዝ ከሆነ ግን ወደላይ በገፋን ቁጥር ይበልጥ እየከበደን ይሄዳል። በዚያ ላይ ቃላት የማንይዝ ከሆነ አጠቃላይ የደርሱን ጭብጥ የመያዝ እድላችን እያነሰ ነው የሚሄደው። 2- መልእክቱን መጨበጥ:- ከኪታብ ትምህርት ዋናው የሚፈለገው አላማ መልእክቱን መጨበጥ ነው። ቁርኣን የወረደው፣ ሐዲሥ የተላለፈው የቃላት ትርጉም ለማስተማር ሳይሆን ለሰዎች የሚበጃቸውን መልእክት ለማስተላለፍ ነው። በብዛት በሃገራችን የተለመደው የቃል በቃል ትርጉም የማስተማር ዘዴ በዚህ በኩል ጉልህ ክፍተት አለበት። ስለዚህ ለመልእክት በቂ ትኩረት መስጠት ይገባል። እዚህ ላይ አንድ ወሳኝ ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። "የተማርነውን ኪታብ በበቂ ሁኔታ እንደተገነዘብነው መለኪያው ምንድነው?" የሚል። መለኪያው የተማርነውን ኪታብ ለሌላ ማስተማር በሚያስችል መጠን ይዘነዋል ወይ?" ብለን ራሳችንን መጠየቅ ነው። ለራሳችን እውነተኛ ሆነን እንመልስ። አንዳንዴ አስተማሪዎች ሲሳሳቱ "ማግኘታችን" የራስ ሽንገላ ውስጥ እንዳይከተን ልንጠነቀቅ ይገባል። የእውነት ኪታቡን በስርአት ቁጭ ብለን ማስተማር እንችላለን? ካልሆነ ወደሌላ ኪታብ ለመቀጠል ከመጓጓታችን በፊት አጥርተን እንማር። "ይህንን ኪታብ ቀርተነዋል፤ ሌላ ይሁንልን" ከማለታችን በፊት ራሳችንን እንገምግም። 3- ነጠብጣቦችን ማገናኘት:- በዚህ ክፍል ሁለት ነጥቦችን ነው መጠቆም የፈለግኩት። 1ኛ፦ ማስረጃን ከነጥቡ ጋር፣ በአንድ ባብ (ርእስ) ስር የተደረደሩ የቁርኣን አንቀፆችንና ሐዲሦችን ከርእሱ ጋር ማገናዘብ። እየነጠሉ መረዳት በቂ አይደለም። ይሄ ሐዲሥ እንዴት ነው ማስረጃ የሚሆነው? ይሄ መልእክት ከርእሱ ጋር እንዴት ነው የሚናኘው? እያልን ማስተዋል ይኖርብናል። 2ኛ፦ ከራሳችንና ከህዝባችን ተጨባጭ ጋር ማገናኘት። ይህም የምንማረው ትምህርት ራስንም ወገንንም ለመለወጥ እንዲያግዘን ይረዳናል። ወላሁ አዕለም Ibnu Munewor = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

📌 قال الله تعالى: {وأن استغفروا ربكم ثم توبوا إليه يمتعكم متاعا حسنا إلى أجل مسمى} [هود:3] ▪️العمر يطول، والرزق يبسط بالتوبة، والاستغفار، والعمل الصالح. ▪️قال ﷺ: {من أحب أن يبسط له في رزقه، وينسأ له في أثره؛ فليصل رحمه} [أخرجه البخاري ومسلم]. 📚t/me.mesunatube
إظهار الكل...
🔖ወርቃማ ምክሮች🙏                🖍8⃣ 👉🏾 እውር እንዳይሉህ ያልታየኽን አያለሁ አትበል ። ጨካኝ እንዳይሉህ ያልተሰማህን ጩኸት እሰማለሁ አትበል ። ንፉግ እንዳይሉህ ያለ አቅምህ እረዳለሁ አትበል ። ነገር አይገባውም እንዳይሉህ ያልገባህን እንደገባህ አድርገህ አትለፍ ። አንድ በጎ ዕውቀት ሳትጨብጥ የዋልክበትን ቀን እንደ ኖርክበት አትቁጠረው ፣ ስለዚህ መፅሐፍትን አንብብ ፣ አዋቂዎችን ጠይቅ ፣ ሁሉን ሳትንቅ ስማ ።
إظهار الكل...
عن أنس بن مالك رضي الله عنه قال : قال رسول الله ﷺ : ((مَنْ صَلَّى عَلَيَّ صَلَاةً وَاحِدَةً صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ عَشْرَ صَلَوَاتٍ ، وَحُطَّتْ عَنْهُ عَشْرُ خَطِيئَاتٍ ، وَرُفِعَتْ لَهُ عَشْرُ دَرَجَاتٍ)) رواه النسائي. «اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ» Hadith حَدَّثَنَا قَيْسُ بْنُ حَفْصٍ، وَمُوسَى بْنُ إِسْمَاعِيلَ، قَالاَ حَدَّثَنَا عَبْدُ الْوَاحِدِ بْنُ زِيَادٍ، حَدَّثَنَا أَبُو قُرَّةَ، مُسْلِمُ بْنُ سَالِمٍ الْهَمْدَانِيُّ قَالَ حَدَّثَنِي عَبْدُ اللَّهِ بْنُ عِيسَى، سَمِعَ عَبْدَ الرَّحْمَنِ بْنَ أَبِي لَيْلَى، قَالَ لَقِيَنِي كَعْبُ بْنُ عُجْرَةَ فَقَالَ أَلاَ أُهْدِي لَكَ هَدِيَّةً سَمِعْتُهَا مِنَ النَّبِيِّ، صلى الله عليه وسلم فَقُلْتُ بَلَى، فَأَهْدِهَا لِي‏.‏ فَقَالَ سَأَلْنَا رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَقُلْنَا يَا رَسُولَ اللَّهِ كَيْفَ الصَّلاَةُ عَلَيْكُمْ أَهْلَ الْبَيْتِ فَإِنَّ اللَّهَ قَدْ عَلَّمَنَا كَيْفَ نُسَلِّمُ‏.‏ قَالَ ‏ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ‏ قُولُوا اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ ‏" ‌‌‏ Narrated Abdur-Rahman bin Abi Laila: Kab bin Ujrah met me and said, "Shall I not give you a present I got from the Prophet?" `Abdur- Rahman said, "Yes, give it to me." I said, "We asked Allah's Messenger (ﷺ) saying, 'O Allah's Messenger (ﷺ)! How should one (ask Allah to) send blessings on you, the members of the family, for Allah has taught us how to salute you (in the prayer)?' He said, 'Say: O Allah! Send Your Mercy on Muhammad and on the family of Muhammad, as You sent Your Mercy on Abraham and on the family of Abraham, for You are the Most Praise-worthy, the Most Glorious. O Allah! Send Your Blessings on Muhammad and the family of Muhammad, as You sent your Blessings on Abraham and on the family of Abraham, for You are the Most Praise-worthy, the Most Glorious.' " Sahih al-Bukhari 3370 In-book : Book 60, Hadith 49 USC-MSA web (English) : Vol. 4, Book 55, Hadith 589  (deprecated) Sahih Bukhari ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 60, ሐዲስ 48 አቡ ሑመይድ አሥ-ሣዒዲይ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ *”ሰዎች፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ሆይ! በእርሶ ላይ እንዴት ሰለዋት እናውርድ? አሉ፤ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “አላህ ሆይ! ሰለዋትን በሙሐመድ፣ በባልተቤቶቹ እና በዝርዮቹ ላይ አውርድ፥ ሰለዋትን በኢብራሂም ቤተሰብ ላይ እንዳወረድክ በረካትን በሙሐመድ፣ በባልተቤቶቹ እና በዝርዮቹ ላይ አውርድ ልክ በኢብራሂም ቤተሰብ ላይ እንዳወረድክ፤ አንተ የተመሰገንክ እና የተከበርክ ነህ*። أَخْبَرَنِي أَبُو حُمَيْدٍ السَّاعِدِيُّ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّهُمْ قَالُوا يَا رَسُولَ اللَّهِ كَيْفَ نُصَلِّي عَلَيْكَ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ قُولُوا اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَأَزْوَاجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، وَبَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَأَزْوَاجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ ‏”‌‏.‏ T.me/sunatube
إظهار الكل...
𝘚𝘶𝘯𝘢 𝘪𝘴𝘭𝘢𝘮𝘪𝘤 𝘭𝘪𝘣𝘳𝘢𝘳𝘺

"አንብብ በዚያ(ሁሉን)በፈጠረው ጌታህ ሥም" ቁርዓን96:1

በትክክለኛ ሰነድ ፀድቀው የመጡ 14 የጁምዓ ቀን ሱናዎች 1 ገላን መታጠብ። 2. ሽቶን መቀባባት እና መዋብ። 3. ሲዋክን መጠቀም። 4. የክት ልብስ መልበስ። 5. በጊዜ መስጂድ መጓዝ። 6. በእግር እየተጓዙ ወደ መስጅድ መሄድ። 7. መስጂድ ከደረሱ በኋላ የሰዎችን ትከሻ በመረማመድ ሰዉን አለማስቸገር። 8. ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ ቢሆንም ተህየቱ መስጂድ መስገድ። 9. ኹጥባ ወደ የሚያደርገው ኢማም መዞርና እሱን እያዩ ኹጥባ ማድመጥ። 10. ኹጥባ በሚደረግበት ሰዓት ፀጥታን መላበስ። 11. ሰደቃን ማብዛት። 12. ከሀሙስ ማታ ጀምሮ እሰከ ጁምዓ ዐስር ድረስ ሱረቱ ከሕፍ መቅራት። 13. ድዓ ተቀባይነት የሚያገኝበት ሰዓትን መጠባበቅ። 14. በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን በብዛት ማውረድ።👇👇👇👇👇 ﴿ إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ ۚ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ﴾ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 اللهمَّ صلِّ على محمَّد وعلى آل محمَّد، كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم، إنَّك حميدٌ مجيد. اللهمَّ بارِك على محمَّد وعلى آل محمَّد، كما باركتَ على إبراهيم وعلى آل إبراهيم، إنَّك حميدٌ مجيد. T.me/sunatube
إظهار الكل...
4_5800828764652833967.mp310.67 MB
Photo unavailableShow in Telegram
🚿 يوم الجمعة 🚿የውመል ጁምዓ ➖عن ابي هريرة رضي الله عنه قال:قال رسول الله صلى الله عليه وسلم :(( خيرُ يوم طلعت عليه الشمسُ يوم الجمعة: فيه خلق آدم، وفيه أدخل الجنة، وفيه أخرج منها، ولا تقومُ الساعة إلاً يوم الجمعة)) [مسلم]. 🍀 የአላህ መልእክተኛ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ብለዋል. 🌅 " ፀሀይ ከወጣችበት ቀናቶች በላጯ ቀን የጁምአ ቀን ነው፡ በሷ (በጁምአ) አደም ተፈጥሯል ፡ ጀነት እንዲገባ ተደርገዋል ፡በሷም ቀን ከጀነት እንዲወጣም ተደርጓል ፡ ቂያማም አትቆምም በሷ ቀን ቢሆን እንጂ". 📚 [ ሙስሊም ዘግቦታል ].
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.