- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
جاري تحميل البيانات...
የፌዴራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት ለሶማሌ ክልል ፍትሕ አካላት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ዛሬ ፍጻሜውን አገኘ፡፡ (ሰኔ 8/2016 ዓ.ም) የፌዴራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት ለሶማሌ ክልል ፍትሕ አካላት ላለፉት ስድስት ቀናት በጅግጅጋ ከተማ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ዛሬ ፍጻሜውን አገኘ፡፡ በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ በመገኘት የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የተወካዮች ምክር ቤት አባልና በሚስቴር ዴዔታ ማዕረግ የፌዴራል የፍሕና ሕግ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ አቶ ዘካሪስ ኤርኮላ በንግግራቸው ጠንካራ የፍትሕ ሥርዓት መኖር የሕግ የበላይነት የሚከበርበት፣ ዜጎች በእኩል አይን የሚታዩበት፣ ለሕግ ተገዢና በሕግ ተጠያቂነት የሚኖርበትና ዜጎችን በፍትሃዊነት ማስተናገድ የሚቻልበትን ከዚህም አልፎ ደግሞ ሁሉም ዘርፎች የሚደገፉበትን መንገድ መፍጠር ማለት ነው ያሉ ሲሆን ከዚህ ረገድ ተቋማችን የተሰጡትን ተግባርና ሃላፊነቶች እየተወጣ ነው ማለት ይቻላል ብለዋል፡፡ የፍትሕ ተቋመት ጠንካራ መሆን በዜጎች መካከል የሚኖረው ማህበራዊና ኢኮኖሚዊ መስተጋብር ዋስትና እንዲኖረው ያደርጋል ያሉት ሚንስቴር ዴዔታው ባለፉት አምስት አመታት እየተካሄደ ባለው ለውጥ ሂደት ውስጥ ለፍትሕ ተቋማት በነጻነትን፣ በህግና ሕግ ላይ ብቻ ተንተርሰው እንዲሰሩ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፤ በርካታ አሳሪና አስከፊ የነበሩ ሕጎችን የማቻቻል ስራ ተሰርቷል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ የዳኝነት ነጻነት እንዲከበር ተጠያቂነት ላይ ያለው ስርዓትም የተመቻቸ እንዲሆን ለማስቻል እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም የሶማሌ ክልል ከሰላም አንጻር በርካታ ስራዎችን በመስራት የክልሉን አንጻራዊ ሰላምና ልማት እያረጋገጠ ይገኛል ያሉት አቶ ዘካርያስ ለዚህም የፍትሕ ተቋማት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ እምነት አለን ብለዋል፡፡ በዕለቱስልጠናው ከስራቸው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው እደሆነና በስራ ቦታቸውም ላይ እንደሚጠቅማቸው በመግለጽ ነገር ግን ቢያንስ በዬ ስድስት ወሩ ስልጠና የሚገኙነትንና ለወረዳና ለዞን ሰልጣኞች ጭምር የሚመቻችበት መንገድ መቀየስ አለበት ያሉት አስተያዬት የሰጡ ሰልጣኞች ለተደረገላቸው ገነር ምስጋናቸውን አቅርበዋ፡፡ መረጃው፡- የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ነው!
تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.