Mezimure✝✝✝
🙏🙏🙏 Mezimure From axumawit
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
200
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
፨በደሙ አተመኝ፨
ለሌባ ዋስ የለው
ለቀማኛ ዘመድ
ከጓደኛዬ ጋር
ተቀብለን የሞት ፍርድ
ተገልጾ ሲታየኝ
በደሉና ጽድቁ
የጸጸትን እንባ
ዓይኖቼ አፈለቁ
ለካስ ከሞት ሀገር
ሕይወትም ይገኛል
የዕድሜ ልክን ኃጢአት
ንስሐ ያጠራል
ዕንባዬን አብሶ
የተስፋ ቃል ሰጠኝ
ዳግም እንዳልጠፋ
በደሙ አተመኝ
ቁልፉን ተረክቤ
ከሕይወት ባለቤት
አዳምን ቀድሜ
ገባሁ ወደ ገነት።
#ቀዳም_ሥዑር (የተሻረች ቅዳሜ)
የዐቢይ ጾም የመጨረሻዋ ቅዳሜ ብዙ ስያሜዎች አሏት፦
#ቀዳም_ሥዑር፡-
በዚች ዕለች ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው ቅዳሜ ትባላለች፡፡ የማትጾመዋ ቅዳሜ ስለምትጾም ስዑር /የተሻረች/ ተብላለች በዓል መሻርን አይመለከትም በቀዳም ሥዑር ሌሊት ሥርዓቱ የሚጀመረው በመኀልየ ሰሎሞን ምንባብ ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጥዋት አቡን መዋሥዕት ውዳሴ ማርያም ዜማ ተደርሶ ወለመልአከ ሕይወትሰ ሰቀልዎ በሚለው ሰላም ይጠናቀቃል፡፡በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡
#ለምለም_ቅዳሜ፡-
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ በዚህ ተሰይሟል፡፡ ቀጤማውንም ምእመናን እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል፡፡ በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሠሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡
(የቀጤማው አመጣጥና ምስጢርም ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቀጤማ ይዛ በመግባት ነው፡፡ ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት ካህናት ቄጠማ ይዘው ምእመናንን ያበሥሩበታል፡፡)
#ቅዱስ_ቅዳሜ፡-
ቅዱስ ቅዳሜ መባሉ ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ከፈጠረ በኋላ በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ ያረፈበት ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ፣ በነፍሱ ሲዖልን በርብሮ ባዶዋን አስቀርቷታል፡፡ በዚያ ለነበሩት ነፍሳትም የዘለዓለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ከሌሎቹ ዕለታት የተለየ ዕለት ለማለት ቅዱስ ቅዳሜ ተብሏል፡፡
(ስምዐ ተዋሕዶ የስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ዘሰሙነ ሕማማት ሚያዝያ 2004 ዓም)
@beteafework @beteafework
@beteafework @beteafework
@beteafework @beteafework
ሕማማት ክፍል 19
👉 ለንስሐ የሚቀሰቅስ ዶሮ
✍ ጸሐፊ ፦ ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
🎤 ተራኩ ፦ ኢዮብ ዮናስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ዘሕፅበተ እግር ምስባክ
ትነዝሐኒ በአዛብ ወእነጽሕ
ተሐፅበኒ እምበረድ ወእፃዓዱ
ታሰምአኒ ትፍሥሕተ ወሐሤተ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
በስህተት ክፍል 17ትን ሳንለቅ ነበር ክፍል 18ትን የለቀቅነው ክፍል 17 እነሆ
ሕማማት ክፍል 17
👉 ብርድ የማይችለው ዓለት
✍ ጸሐፊ ፦ ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
🎤 ተራኩ ፦ ኢዮብ ዮናስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
21/08/2013
ጸሎተ ሐሙስ
በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበ
መልዕክታት ወንጌልና ምስባክ፡፡
ዲ/ን:- ዕብ 12÷2-18
ን/ዲ:- 1ጴጥ 3÷15-20
ን/ካ:- ግብ.ሐዋ 10÷30-40
የዕለቱ ምስባክ :- መዝ 20÷5
ወሠራዕከ ማዕደ በቅድሜየ
በአንፃሪሆሙ ለእለ ይሣቅዩኒ
ጽዋዕከኒ ጽኑዕ ወያረዊ
ትርጒም፦
በፊቴ ማዕድን አዘጋጀህልኝ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ።
የዕለቱ ወንጌል፦ ማቴ 26፥20 -30
ቅዳሴ፦ ዘዮሐንስ አፈ ወርቅ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አማኑኤል ፍቅርህ ይማርካል
አማኑኤል ፍቅርህ ይማርካል
አማኑኤል ፍቅርህ ይማርካል/2/
በመስቀል ተሰቅለህ መድኃኒት ሆነሃል
አማኑኤል ፍቅርህ ይማርካል
ሳታቆስል በፍቅርህ ማርከኸን
ከፊት ቀድመህ በድል አስከተልከን
በደለኞች እኛ ሆነን ሳለ
አንተ ከፍለህ ክሳችን ተጣለ
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን
#አዝ
እንደሰማን እንዲሁ አይተናል
ማዳንህን ቀምሰን መስክረናል
የእግዚአብሔር በግ ቆስለህ የፈወስከን
ወደ ድንቁ ብርሃን ያሻገርከን
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን
#አዝ
አፅናንተኸን ሞትን አስተከዝከው
ወደ ጥልቁ እንዲወርድ አዘዝከው
ባንተ ፍቅር ምርኮ በዝቶልናል
ማማ ሆነህ ከፍ ከፍ ብለናል
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን
#አዝ
ስንሸሽህ እየተከተልከን
ልጆች አርገህ በክብር አስጌጥከን
ተቅበዝባዡን ሰብስበሃልና
ከማደሪያህ ይፈልቃል ምስጋና
ኪርያላይሶን ኪርያላሶን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
إظهار الكل...