cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ሰፋኒት ሚዲያ-Sefanit Media

በሃይማኖታችን ጸንተን በመንፈሳዊ ሕይወታችን እንበርታ! Let us stand firm in our faith and be strong in our spiritual life.

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
556
المشتركون
+224 ساعات
-17 أيام
-1230 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

#ብቸኝነትን አትቃወሙት በውስጡ ጥልቅ መረጋጋት አለ ። አትሽሹት በብቻ መንገድ ውስጥ ብዙ የምታውቁት አለም አለ። ከተበጠበጠው የሰው ሁካታ መሀል ለብቻ ህይወትን መምራት፣ በብቸኝነት መጽናት  በእግዚአብሔር እና በራስ መሀከል ስላለው ድልድይ የሌሎች ግፊት እንዳይጎረብጠን ምቹ ምንጣፍ መዘርጋት ነው። ብቸኝነት  ከእግዚአብሔር ጋር መጣበቅ ነው ።ብቸኛ ስትሆኑ እርሱን ታስተውሉታላችሁ ፣ታፈቅሩታላችሁ፣ ታመሠግኑታላችሁ  ስለዚህ  ከአምላካችሁ ጋር ለመቆራኘት የብቻ አጸድን  ፈልጉ ከዝሙት፣ከሱስ፣ ከበቀል ፣ቁልቁል ከሚገፏችሁ ሰዎች ብቸኛ ሁኑ ያኔ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሆናል! ብቸኝነትን ውደዱ "
إظهار الكل...
🥰 2
"እንደ ማመስገንና ይቅርታን እንደ ማድረግ ያለ ዕረፍትን አላየሁም። ፤ከሰው ነገር እንደ መራቅ ያለ ነጻነት፣ ሞትን እንደማሰብ ያለ ሥጋን (ራስን) መናቅ፣ ሰውን እንደማስደሰት ያለ ፍቅርን መዝራት ከቶ አላየሁም።" #ሰፋኒት
إظهار الكل...
🙏 2🥰 1
"በታላላቅ ሐሳቦች የሚታጀቡት ሁሉ ብቸኞች አይደሉም።"
إظهار الكل...
👍 2
በዕቅበተ እምነት ጥንቃቄ የሚሹ ተግባራት (ከብርሃኑ አድማስ ጽሑፍ በምኅጻር የተወሰደ) -- 1.የዕቅበተ አምነትን ሁለት ዋና ጠባያት መረዳት፡- (1) ሃይማኖት/እምነት ከአምላክ የተገለጠ እውነት መሆኑን ተረድቶ ለማጽናት መታገልና (2) በእምነት የደከሙትን/የሳቱትን ሰዎች ራሳን እንደ ደጉ ሳምራዊ አድርጎ በርኅራኄ ቁስላቸውን አክሞ ለማዳን መፋጠን ሁለቱ የቅበተ እምነት መሠረታውያን ጠባዕያት ናቸው፡፡ -- 2.በዕቅበተ እምነት ውስጥ የማይታለፉ ጉዳዮች፡- (1)ዐቂበ እምነት፡- የሃይማኖትን ምንነት በቤተ ክርስቲያናዊ አስተምህሮ ላይ ተመሥርቶ መግለጥና ያንን የሚቃወም ስሑት ትምህርት በየዘመናቱ ሲመጣ ትምህርቱ የአባቶች አለመሆኑን ማሳየት፡፡ (2)እውነት ላይ ማተኮር፡- ዐቃቤ እምነት ትኩረቱ እውነት እንጂ አሸናፊነት አይደለም፣ ትኩረቱ ወደተሳሳተው አስተምህሮ እንጂ ወደተሳሳተው ግለሰብ አይደለም- ልክ መድኃኒት በሽታን እንጂ በሽተኛን ለማጥቃት እንደማይሰጠው፡፡ (3)አሳማኝነት፡- ጭብጥ አቀራረጹና አቀራረቡ ሐሳብን ሊያስተላልፍና የተለያየ ዕውቀትና ግንዛቤ ላላላቸው ሰዎች ተደራሽና ሰዎች ሐሳቡን ሊጋሩት በሚችል መመልኩ መቅረብ አለበት፡፡ (4)ክርክርን በተገቢው መንገድ ማቅረብ፡- የዕቅበተ እምነት ሥራ ዐላማው አማኞች ከመጠራጠር መጠበቅና የሔዱትን መመለስ እንደመሆኑ መጠን አቀራረቡ የሚያቀርቡትን ጭብጥ መረዳት (understanding)ንና ተደራስያን ሊረዱ በሚችሉበት ቋንቋ የማቅረብ አቅም፣ ያልተድበሰበሰ ውሳኔን (judgment)ና የሚሟገታቸውን ሐሳቦች ስሑትነት የሚያሳይና የሚያቀርበውን ሐሳብ ከትችት ያራቀ አጠይቆት(reasoning)ን ማማከል ይገባዋል፡፡ -- 3.የዕቅበተ እምነት ጸያፎች፡- (1)ሐሰተኛ ትርጉም መስጠት (Proselytism)፡- ማለትም የምንሞግተውን ሐሳብ ተሞጋቹ በሚለው ሳይሆን እኛ በሰጠነው ትርጉም ሰይሞ ምላሽ ለማዘጋጀት መሞከር፡፡ ለምሳሌ፡- ኦርቶዶክሳውያን እመቤታችንን እናከብራታለን እንጂ አናመልካትም፡፡ ተቃዋሚዎች ግን ማክነራችንን ማምለክ ብለው ተርጉመው የዕቅበተ እምነት ሥራ ሠራን ይላሉ፡፡ በእኛም ቤት ካቶሊካውያን እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ይላሉ የሚል ልማድ ያገነነው ስሑት አበባል አለ፡፡ ሐሰተኛ ትርጉም መስጠጥ ይባላል፡፡ (2)ሥነ ልቡናዊ ርግጠኝነት (Psychological Certainity)፡- የሰማዕያን/አንባብያንን ድክመት ተጠቅሞ የማያውቁትን ሐሳብ ወይም ቋንቋ ከዐውድ ውጪ በመውሰድ ለማሳመን መሞከር ነው፡፡ ምሳሌ፡- ኦርቶዶክሳውያን ለሥዕል የምንሰጠውን ክብር ዘፀ.20፡4 ላይ ያለውን ‹‹የተቀረጸውን ምስል ለአንተ አታድርግ›› የሚል ጥቅስ ተጠቅሞ ቅዱሳት ሥዕላትን ጣኦት አድርጎና የጥቅሱ መተርጎሚያ አድርጎ መጠቀም፡፡ ያላነበቡትን እንዳነበቡ፣ የማያውቁትን ግእዝ ወይም እንግሊዝኛ ወይም ደግሞ ሌላ ቋቋ የሚያውቁ መስሎ ለማሳመን መሞከርም በሰማዒው/አንባቢው ላይ የሥነ ልቡና ርግጠኝነትን ፈጥሮ ለመቀሰጥ ሙከራ የሚደረግበት የዕቅበተ እምነት ጸያፍ ነው፡፡ (3)መንሸራተት (Deviation)፡- ከጭብጥ መሸሽ ወይም ጭብጥን ለራስ በሚመች መልኩ ቀርጾ መዳከር፡፡ (4)ከአመክንዮ በተቃርኖ መቆም (Logical fallacy)፡- ምንም እንኳ ነገረ ሃይማኖት ከአመክንዮ ባሻገር ቢሆንም አንድን የፍሬ ነገር መለኪያ ለተለያየ መደምደሚያ መጠቀም፡፡ ምሳሌ፡- ተሐድሶዎች የደቂቀ እስጢፋስ ገድላት ላይ መፍቀርያነ ገድል መስለው ሲያበቁ በሌሎች ቅዱሳን ላይ ሲሆን የምናውቀውንና እዚህ የማንናገረውን ጸያፍ አንደበት እንደሚጠቀሙት፡፡ (5)ሁሉን ጠልነት (Negativism)፡- የሚቃወሙት ሰው/ቡድን የተናገረውን ሁሉ በጅምላ ማነወር፡፡ አውንታዊ ምሳሌ ብንጠቅስ፡- መልአከ ብርሃን አድማሱ ምላሽ የጻፉላቸው ሰዎች ትክክለኛ ነገር ሲጽፉ እንዳላዩ አያልፉም፤ እዚህ ላይ ትክክል ነህ ይላሉ፡፡ (6)አድሏዊነት (Inclination/Bias)፡- በአንድ ስሕተት የሚያውቁትን ሰው እንደሚሳሳት አስቦ ሥራዎቹን ማየት ወይም በስሕተት የወደቁ ሰዎችን በአካባቢ ወይም በተማሩበት ት/ቤት ፈርጆ ‹‹ወትሮስ ከዚያ የወጡ!›› እያሉ መፈረጅ ጸያፍ ነው፡፡ -- ምንጭ፡- አድማሱ ጀንበሬ፡ ሕይወቱ ወሐተታ መጻሕፍቱ፣ 2011፣ ገጽ 12-39 (በምኅፃር ተጨምቆ የቀረበ፡፡)
إظهار الكل...
👍 1
ጥያቄ ብቻ ነው። በዚህ የምትቀየሙ ሁሉ፣ ሳላውቅ የበደልኳቸሁ ካላችሁም ይቅር በሉኝ፣ እንድትድን ለምን ትጠይቃለህ ግን አትበሉኝ። እንድድን በወልደ እግዚአብሔር ሞት ተጠርቻለሁና። Dn. Birhanu Admas
إظهار الكل...
👌 1
ከሲኖዶስ የምጠብቀው እና የምጠይቀው አቤቱ ጌታዬ እና መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ሳላውቅ በድፍረት አውቄ በትዕቢት ከመናገር እንድትጠብቀኝ እለምንሃለሁ። ጌታዬ መድኃኒቴ ኢይሱስ ክርስቶስ ሆይ አንተ በደምህ ከመሠርትሃት በኪዳንህም ካቆምካት፣ አካልህ ከሆነች፣ ብልት አድርጋ ከምትሰበስበን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኅብረት ከሚያወጣ ድፍረት፣ ምን አገባኝም ከሚል ፍርኅት እንድትጠብቀኝ እኔ ከሁሉ የማንሰው ኃጢአተኛ ልጅህ እለምንሃለሁ። ጌታዬ ሆይ ከእንግዲህስ ወዳጆቼ እንጂ ባሪያዎቼ አልላችሁም ብለህ ባከበርሃቸው፣ ምሥጢራትህንም ሁሉ በገለጽህላቸው ፍጹማን ወዳጆችህ፣ አንተ ታማኝ መልካም ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ብለህ በምታከብራቸው ትጉኃን አገልጋዮችህ፣  ለባሕርይህ ለማይስማማ ሞት ራስህን አሳልፈህ በሰጠህላቸው ንጹሐን ምእመናን በጎችህ ብለህ እንኳን የአባቶቼን የየትኛውንም ሰው ኅሊና ሊጎዳ ከሚችል ክፉ ሐሳብም ሆነ ንግግር ትጠበቀኝ ዘንድ እለምንሃለሁ። ጌታ ሆይ ከግብዝነት፣ ከአድርባይነት እና ከሚታወቅም ከማይታወቅም ጥፋት እንድትጠብቀን በጎውን እና እውነተኛውን ነገር ብቻም ለመናገር ከአንተ ውጭ እንኳን እኛ የበቁትም ቢሆኑ አይቻላቸውምና ስለቅዱሳንህ ሁሉ ይልቁንም የባሕርያችን መመኪያ የደኅንነታችን ዘውድ ስለምትሆን ንጽሕት እናትህ ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ብለህ በመልካሙ መንገድ ብቻ ምራን፣ እኔንም ከዚህ መንገድ አታውጣኝ አሜን። ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ፤  አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ አሜን። አንዳንድ ሰዎች ስለሲኖዶስ በጻፍናቸው ተነሥተው ጉዳዩን ለመጠምዘዝ ከተቻለም መለያየት እና ጸብ በመፍጠር የሚፈልጉትን ለማሳካት እንደሚጥሩ ስለተሰማኝ፣ በቅንነት ሆነው ጥያቄያችንም የመብት ጥያቄ የመሰላቸው እና እራሳቸውንም የሆነ አካባቢ ተወካይ አድርገው የመብት ጥያቄ ጠያቂ እና አስተባባሪ ሆነው ስላየሁ የእኔ እና እኔንም የሚመስሉ ወንድሞቼ ጥያቄ ምን ዓይነት ጥያቄ እንደሆነ ስለቅዱስ ሲኖዶስ ያለኝን እምነት በማስቀደም በመግለጽ ጥያቄዬን በድጋሜ አቀርባለሁ። ቅዱስ ሲኖዶስ ፦ ቅዱስ ሲኖዶስ የእግዚአብሔር መንግሥት አስፋፊዎች የመላእክት ወንድሞች የሰማያዊ ዜጎች አንድነት እንጂ የከርስቲያኖች የየአካባቢው ተወካዮች የሚሰበስቡበት ምክር ቤት እንዳለሆነ በደንብ አዋቃለሁ። ቅዱስ ሲኖዶስ ከብዙ ቋንቋ ተናጋሪዎች የመጡ አባቶች ቢገኙበትም የየቋንቋቸው ወኪሎች ስብስብ እንዳልሆነም በደንብ አውቃለሁ። ቅዱስ ሲኖዶስ ከየአካባቢው ተወልደው አድገው በመጡ አባቶች የተመላ ቢሆንም የየተገኙበትና የየመጡበት አካባቢ ተወካዮች እና የወንበር ምድብ ቆጣሪዎች ስብስብ እንዳልሆነና ሊሆንም እንደማይችል፣ እንደማይገባውም በደንብ አውቃለሁ። ቅዱስ ሲኖዶስ በሰማይ ያለች የእግዚአብሔርን መንግሥት በምድር ሆነው ያገለግሉ ዘንድ የሚላኩ የእግዚአብሔር አምባሳደሮች ስብስብ እና ለላካቸው ለእግዚአብሔር መንግሥት ፍላጎት ብቻ የሚሠሩ በተፈጥሮ ከሰው ወገን ቢሆኑም በክህነት ምክንያት ከመላእክት ወገን የሆኑ እና እንደ መላእክትም ለሁሉም እኩል ቅርብ የሆኑ ሊሆኑም የሚገባቸው አባቶች ስብስብ እንደሆነ አምናለሁ። ከዚህም የተነሣ ከመካከላቸው ከላከው ከእግዚአብሔር እና ከሾመችው ከአካሉ ከቤተ ክርስቲያን ፈቃድ ወጥቶ የራሱን ፈቃድ የሚከተል፣ የምድራዊ መንግሥታትን ፈቃድ ለመፈጸም እና ለማስፈጸም የሚሠራ አካል ቢገኝ ከማኅበረ መላእክት ወገን ሳለ የራሱን ሌላ መንግሥት ማቋቋም ከፈለገ ከዲያብሎስ እና እርሱን እሺ በጄ ካሉት ከሠራዊቱ የሚመደብ እንደሆነ አምናለሁ፤ አውቃለሁም። በሐዋርያት መዓርግ ተሹሞና እና ተሰይሞ በጉባኤያቸውም ተገኝቶ እውጭ ላሉት ምሥጢር የሚሰጥ፣ ከእነርሱም ጋር የጥቅም ውል ያለው ቢኖር አልደነቅም። እንዲህ ያለው ከሐዋርያት ሲኖዶስ እያለ ከአይሁድ ጋር የጥቅም ውል የተዋዋለ እና ከጉባኤያቸውም የተሰናበተውን ይሁዳን እንደሚመስል እና በእርሱ ምክንያትም ሌሎች እንደማይተቹ በደንብ ተምሬያለሁና። ረቂቅ ባሕርይ በነበረው በሳጥናኤል ምትክ ከመሬት አፈር የተፈጥረው አዳም እንደተተካ፤ በይሁዳም ምትክ ማትያስ በሐዋርያት እጩነት ቀርቦ በዕጣ እንደገባ ከአባቶቼ ተምሬያለሁ፣ አዋቃለሁምና የሚወጣ ቢኖር አልደነግጥም አልረበሽምም። እንዲህ ባላው ሰው ምክን ያት ቤተ ክርስቲያን ስሟ እንደማይጎድፍ ክብሯ እንደማይቀንስ ሁሉን የሚያውቅ ጌታ አስቀድሞ አለማስገባት እየተቻለው ለይሁዳ እድሉን በመስጠት አስተምሮናልና።  ቅዱስ ሲኖዶስ ለእጃችሁ በትር አትያዙ የተባሉ ሐዋርያት ወራሽ እንጂ ሰይፍ፣ ጎራዴና እና ዱላ ይዘው ክርስቶስን ለመያዝ የመጡ፣ ዳዊት በመዝሙሩ አገቱኒ ከለባት ያላቸው ለምድራዊ ገዥዎች ፍላጎት የሚጮሁ የዚያ ዘመን አይሁድ ወራሽ እንዳልሆነ አውቃለሁ፣ አምናለሁም። ቅዱስ ሲኖዶስ በዐመጻው ምክንያት መልአከ እግዚአብሔር በሰይፍ እጁን የቀጣውን ታውፋንያን ንስሐውን ተቀብሎ በተአምራት እጁን መልሶ ዐመጸኛውንም ወደ ትሕትና እና መታዘዝ የሚመልሱ የቅዱስ ጴጥሮስ ልጆች ስብስብ እንጂ እንደ አውሳብዮስ እና ጓደኞቹ የመንግሥታትን ጉልበት ተጠቅሞ ቤተ ክርስቲያንን የሚከፋፍሉ ሰዎች ስብስብ እንዳለሆነ አውቃለሁ፣ እንዲህ ሆኖ እንዲኖርም እጠብቃለሁ። ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት  እንደ ጠቢቡ ሰሎሞን ረቂቅ ፍርድ ፈርዶ ሕዝቡን የእግዚአብሔርን መጋቢነት የሲኖዶስን መንፈስንቅዱሳዊነት ሊያሳይ እንደሚተጋ እንጂ እንደ ኢሳይያስ የንጉሥ ድምፅ ፈርቶ እኔ ምን አገባኝ ብሎ ቤተ ክርስቲያንን ለዖዝያን ፍላጎት አሳልፎ በመስጠት ለምጻም የሆኑ ሰዎች ስብስብ እንዳልሆነ ፣ እንደማይሆን፣ ሊሆንም እንደማይገባው አምናለሁ፤ እጠብቃለሁም። ቅዱስ ሲኖዶስ የእግዚአብሔር መንግሥት ለሁሉም ይዳረስ ዘንድ ተጭንቆና ተጠብቦ እንደ ጳውሎስ እስከ ዕልዋሪቆን እንደ በረተሎሜዎስም በላእተ ሰብእ ያሉበት ድረስ ሔዶ ለመስተማር የሚያስቡ አባቶች ስብስብ እንጂ እንደ አካባቢ የልማት ድርጅቶች በየአካባቢው ሕንፃ ለመሥራት ግንብ ለማቆም የሚሯሯጡ ዉሉደ ባቤል ደቂቀ ናምሩድ ስብስብ እንዳልሆነ አምናለሁ፣ ተስፋም አደርጋለሁ። ቅዱስ ሲኖዶስ እቄሣር ግቢ ቢገባ እዚያ ያሉትን ለውጦ እንደ ጳውሎስ ከቄሳር ቤት የሆኑት ሰላምታ ያቀርቡላችኋል የሚሉ ጥቡዓን ስብስብ እንጂ እንደ ዴማስ በከተማ ውበት በቤተ መንግሥት ግርማ ተሰልቦ አላማውን ለውጦ የሚኖር ከተሜዎች ስብስብ እንዳለሆነ እረዳለሁ። ቅዱስ ሲኖዶስ እንደ ዲዮስቆሮስ ጥርሱ እስኪረግፍ ቢደበደብ እንደ አትናቴዎስ አምስት ጊዜ ቢሰደድ በትዕግሥት መከራውን ተቀብለው ቤተ ክርስቲያንን የሚያሻግሩ ፣ ዐለም ትቷችኋል ቢባሉ ልክ እነደ አትናቴዎስ እኔም ዐለምን አልፈልገውም የሚሉ ልበ ሙሉዎች ስብስብ እንጂ በቤተ መንግሥት ማዕድ እና ሺንገላ ልባቸው የሚማልል አባቶች ስብስብ እንዳልሆነ አውቃለሁ፣ እጠብቃለሁም። ቅዱስ ሲኖዶስ እንደ ሲሞን ገንዘባቸውን ይዘው እናንተ የያዛችሁትን መዓርግ  ልያዝ፣ ጓደኞቼ ከደረሱበት ልድረስ ብለው በእኔ ጊዜ ነው ወይ መመሪያ የሚወጣው እያሉ ዘመድ አዝማድ ስጦታ አስይዘው በመላክ፣ ውለታ ቆጥረው በማስታወስ  የሚወተውቱ ሲሞናዊያንን ገንዘብህ ይጥፋ፣ ሀሳብህም አይፈጸም እያለ እነርሱን ትቶ ማትያስን በይሁዳ ፈንታ በተካበት መንገድ ለመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሚሆኑትን የሚሾም ወራሴ ጰጥሮስ ወሐዋርያት እንደሆነ አውቃለሁ አምናለሁም።
إظهار الكل...
👍 1
ቅዱስ ሲኖዶስ ሠራኤ ሕግ ወፈጻሜ ሕግ የሆነውን ጌታቸውን የተከተሉ፣ ሙጽአ ሕግ የሆነችውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተልእኮ በሕገ እግዚአብሔር በቀኖና ቤተ ክርስቲያን የሚያስፈጽሙ አባቶች ስብስብ እንደሆነ አምናለሁ፣ አውቃለሁም። ለዚህም ነው በዘወትር ጸሎታችን ያለውን እንደ ሁሉም ክርስቲያኖች ሁሉ ዕለት ዕለት “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት” ብለው ያስተማሩኝን የማምነው፣ የምመሰክረው፣ የምጸልየውም። ቤተ ክርስቲያን ከጉባኤያት ፣ ከምክር ቤቶች፣ ከስብሰባዎች ሁሉ በላይ የሆነችውም በተፈጥሮዋም፣ በአሠራሯም፣ በሒደቷም ከሁሉም በላይ በሆነው በጌታዋ በቤዛዋ በመድኃኒቷ እንዲህ ጸንታ የምትኖር ስለሆነች እና መሆንም ስላለባት እንደሆነ አውቃለሁ፣ አምናለሁም። አንዳንድ ሰዎች ዘመን ሰጠን፣ ጉልበት አገኘን ብለው ይህን አስትተው እንደ ጎሣ ምክር ቤት፣ እንደ ፌዴሪሽን ምክር ቤት፣ እንደ ወንድማማቾች እድር፣ እንደ ተወላጆች ማኅበር፣ እንደ መሳሰሉት ቅርጽ እና መልክ ይዛ እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ መሆኗ ቀርቶ እንተ ታሕተ ኩሉ መንግሥታት፣ ፓርቲያት ፣ ብሔር ወጎሣ ወመማክርት እንድትሆን የሚፈልጉትን ሁሉ ነፍሴ አጥብቃ ትጸየፋለች፣ በሚቻለኝም ሁሉ እንደ አባቶቼ ይህን እቃወመዋለሁ። እንዲህ እንዲሆን የሚመኝ የሚሠራ ካለም ክርስቶስን ረዳቴ እና ጌታየ አድርጌ ቅዱስ ጴጥሮስ ሲሞንን እንደረገመው እረግመዋለሁ፣ ከኅብረቱ እንደለየውም ቢያንስ ራሴን ከእንዲህ ያለው እለያለሁ። የእኔ ጥያቄ ለሲኖዶስ፦ እኔ ቅዱስ ሲኖዶስን የምጠይቀው የመብት ጥያቄ የለኝም። ቅዱስ ሲኖዶስ የታዛዦች የአገልጋዮች ጉባኤ እንጂ የባላ ሥልጣናት ምክር ቤት አይደለምና። እኔ ቅዱስ ሲኖዶስን የምጠይቀው የአካባቢ፣ የጎሳ፣ የቋንቋ፣ ... የመሳሰሉት የውክልና ጥያቄም የለኝም። የሰማያውያን የመላእክት ወንድሞች የሆኑ ይህን ዐለም የካዱ አባቶች ጉባኤ ነውና። ቅዱስ ሲኖዶስን የምጠይቀው የእገሌ ይሾም የእገሌ አይሾም ጥያቄም የለኝም።  ጥያቂዬ የሕግ እና የሥርዓት እንጂ የመብት እና የፖለቲካ አይደለምና። ቅዱስ ሲኖዶስ አማኞች እንደ ፓርቲ ያቋቋሙት በፈለጉ ጊዜ ሕጉን ቀይረው ዘመን የወለደውን ንጉሥ የወደደውን አስመስለው የሚሠሩት ተራ ተቋም እንዳልሆነ ስማር ኖሪያለሁ፣ በዐለም ባሉት ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያን ሁሉም እንዲህ እንዳልሆነ አውቃለሁ፣ አያለሁምና ምንም ዐይነት የመብት ጥያቄ የለኝም። የመብት ጥያቄ ያለው ክርስቲያን ሆኖ ሊኖር የሚችልም የለምና። የእኔ ጥያቄ መዳኑ በቤተ ክርስቲያን ሊፈጸምለት እንደሚሻ አንድ ኃጢአተኛ እና ደካማ ሲኖዶሴ ሲኖዶስ  ቤተ ክርስቲያኔም ቤተ ክርስቲያን ሆና ማየት ብቻ ነው። ቤተ ክርስቲያንን መገለጫዋን ቅዱስ ሲኖዶስን በሌላው እንዳደረጉት ኢትዮጵያን ይምሰል በሚል ሽፋን ምክር ቤት ይምስል፣ የጎሳ ውክልና ምጥጥን ስሌት ይጠቀም የሚሉትን የምቃወመው ቤተ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን እንድትሆን የልጅነት ድምፄን፣ ክርስቲያናዊ ግዴታዬን ለመወጣት ብቻ ነው። መብት በሚል አደገኛ የፖለቲካ ቃል በር አስከፍቶ ሲኖዶስን የጎሳ ምክር ቤት፣ ቤተ ክርስቲያንም የድኅነት ቤት የፍጥረት ሁሉ መጠጊያ ሐመረ ኖኅ መሆኗን አስጥሎ ጥቅመ ሰናዖር፣ ሐይመተ ፈርዖን ሆና እንድትቆጠር እና ራሷ ከሆነው ከጌታ ከክርስቶስ ከብልቶቿ ከንጹሐን ምእመናን ለመለየት የሚደረገውን ጥረት የምቃወመው ሊቀርብ የሚገባው ጥያቄ የሕግ እና የሥርዓት እንጂ የመብት እና የፖለቲካ አይደለም ብዬ ስለማምን ነው። ባለፈው ጊዜ በሻሸመኔ እና በተለያዩ አካባቢዎች የተገደሉ፣ አካላቸው የጎደለ፣ የታሠሩ የተገርፉ እና አሁንም የሚታሠሩ፣ ቤተ ክርስቲያናቸው እስካሁን የተዘጋባቸው፣ በአዲስ አበባ እንኳ ከሥራቸው ተፈናቅለው በደስታ የተቀበሉት ጥያቄያቸው የድኅነት የሕግ የሥርዓት ይከበር ጥያቄ ስለሆነ እንጂ የመብትማ ቢሆን እንዲህ አይሆንም ነበር። እነዚህ ሁሉ ጥያቄያቸው ቤተ ክርስቲያናቸውን ከወንበዴዎች፣ በጎቹንም ከተኩላ ጠብቃችሁ አድኑን የሚል ትሑት እና የመጨረሻ አነሥተኛ ጥያቄ ነው። የእኔም ጥያቄ ድኅነት ፈለገው የመጡ ምእመናን የጌታን ደም በቁርባን ሰጥተው በማዳን ፈንታ የምእመናን ደም ላፈሰሱ፣ በልተው ላልጠገቡ ለተራቡ ተኩላዎች ሰጥታችሁ አታስበሉን፣ ይልቁንም ድኅነታቸውን ሽተው ለሚያድኑን እረኞች አብቁን የሚል ብቻ ነው። ይህ ካልሆነ ሲኖዶሱ ሲኖዶስ አይደለም ያሰኝና ብዙዎችን ሊያስወጣ፣ ምእመናን ሊከፋፍል፣ ... ሌላም ሌላም ችግር ሊያስከትል ስለሚችል የእነዚያ ሰዎች የድኅነት ጥያቄ የእኔም ልባዊ ጥያቄ ነው። አባቶቼ የምታመልኩት የምታገለግሉት፣ እኔም ኃጢአተኛው እና ደካማው የማመልከው ላገለግለውም የምመኘው ሕያው እግዚአብሔር በሚያውቀው ጥያቄዬ አንድ እና አንድ ብቻ ነው። ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትም ሆነ ማንኛውም ነገር በሕግ እና በሥርዓት ፣ ቀኖናውን መሠረት ባደረገ ለማንም በማያዘነብል፣ ለምእመናን ድኅነት እና ለቤተ ክርስቲያን እድገት እንጂ ለፓርቲዎችና እና ለፖለቲከኞች መሣሪያ ባልሆነ ግልጽ እና ሁሉም ሊያውቀው በሚችል በሲኖዶስ በጸደቀ የምርጫ መመሪያ እና ባለማድላት በተመሰከረላቸው አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ሲፈጸም ሕግ ሥርዓት ሲተገበር የማየት የልጅነት ጥያቄ ብቻ ነው። በእኛ ዘመን ለምን ሕግ ይወጣል? ቀኖናስ ለምን ይጠበቃል የሚል ድምጽ ለሚሰሙት እንዴት ይረብሻል በእውነት። ይህ ድምፅ ይሰማል የሚል እምነት ባይኖረኝም መረበሹን አለመናገር ግን ድምፃቸውን እንደ አማራጭ ማስቆጠር መስሎ ስለተሰማኝ ከፊል የተስማማሁ ስለመሰለኝ ነው ያነሣሁት እንጂ ይደረጋል ብዬ አላስብም። ጥያቄዬ ቅዱስ ሲኖዶስ በዓላማው በክብሩ ጸንቶ እንዲኖር ቅዱስ ጳውሎስ የሚያውኳችሁ ይቆረጡ እንዳለው ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ለመጣል እና ቤተ ክርስቲያንን ለማወክ ያሰፈሰፉ ሁሉ በሕግ ተቆርጠው እንዲወድቁ ብቻ ነው። ጥያቄዬ ቤተ ክርስቲያንን ተሳታፊዎች የሚዘውሯት ተራ ምድራዊ ተቋም ሳትሆን ሰማያዊ መልኳን ይዛ እንድትጸና ሕግ ሥርዓቷ ይከበር የሚል ብቻ ነው። ጥያቄዬ አሳሳቾች በሚፈጽሙት ችግር ምእመናን እንዳይረበሹ ለድኅነታቸውም መሰናክል እንዳይበዛ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን ይከበር የሚል የልጅነት ጥያቄ ብቻ ነው። ይህን መጥየቅ ካልቻልኩማ ምኑን ልጇ ሆንኩት፣ ስማረው የኖሩክትስ ምን ይጠቅመኛል። ለድኅነት ካልሆነስ ምን ይረዳኛል። ቤተ ክርስቲያኔ ቤተ ክርስቲያን ካልሆነችስ ምን ይጠቅመኛል። ፓርቲማ መች ቸገረኝ፣ ሕግ ጥሰት እና ድፈረትማ በዓለም ሁሉ ሞልቶ የለ። ከዚህ ሁሉ የጥፋት ባሕር ቀዝፋ የምታሽግር መርከቤን ሽንቁረው ውኃውን አስገብትው አብረን እናስጥምህ ሲሉኝ ዝም ካልኩኝማ ምኑን ሰው ሆንኩ? የተርሴስ ተጓዦች የተጨነቁትን ያህል ካልተጨነቅሁ ምን እጠቅማለሁ? እነሱ እንዳደረጉት ለመርከቢቱ የከበደውን ነገር ባላውቀው እንኳ ሸክም ካልቀነስኩ ምን ረባሁ? የተኛውን ካልቀሰቀስኩ ወደ አምላክህ ጩህ ካላልኩ ከእነዚያ ተጓዦች የማንስ እጅግ ምስኪን አልሆንምን? ስለዚህ የእኔ ጥያቄ የድኅነት እንጂ የመብት ጥያቄ አይደለም። የመብት ጠያቂዎችንም መስማት አልፈልግም። እርሱ ለፖለቲካ ፣ ለድርጅት፣ ለዚህ ዓለም ሰው ሰራሽ ተቋም እንጂ እግዚአብሔር ለመሠረታት፣ ፍጽምት እና አለነውር እንድትሆን ላደረጋት ቤተ ክርስቲያን የመብት ጥያቄ የለኝም፣ ሊኖረኝም አይችልም። የእኔ ጥያቄ እንተ ላዕኩሉን እንተ ታሕተ ኩሉ ሊያደርጉ የመጡትን በሕግ በሥርዓት ቆርጣችሁ፣ መርከባችን ከሚያናውጥ ማዕበል ቀዝፋችሁ አድኑን የሚል የድኅነት የሕግ የሥርዓት
إظهار الكل...
👍 1
“ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን? እንኪያስ በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፡፡ ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አድርጉት፡፡ በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፡፡ ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት፡፡ ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፡፡ ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው፡፡" ( ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
إظهار الكل...
✝ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮችን በድምፅ / በኦድዮ ለማግኘት ከስር ( ክፈት ) ሚለውን ይጫኑ።
إظهار الكل...
ክፈት
ለመ🀄️ላ🀄️ል
Free FaceSwap🤖
Best DeepNude🙈
Photo unavailableShow in Telegram
❝ጌታ በእውነት ተነሥቶአል።❞ (ሉቃስ ፳፬÷፴፬) "The Lord is risen indeed." (Luke 24:34) እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ! መልካም በዓል ይሁንላችሁ! #ሰፋኒት ~~~~~~ በሃይማኖታችን ጸንተን በመንፈሳዊ ሕይወታችን እንበርታ! Let us stand firm in our faith and be strong in our spiritual life.
إظهار الكل...
👍 1