Ethiopian Law
الذهاب إلى القناة على Telegram
ዳንኤል ፍቃዱ ተስፋዬ በሁሉም የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጠበቃና የህግ አማካሪ ስልክ - 0913158507 ወይም 0978554559 Daniel Fikadu Tesfaye Certified Attorney of law at all Federal Courts of Ethiopia. Email- nurotekore@gmail. Com ⚖⚖Ethiopian Law by Daniel Fikadu channel ⚖⚖⚖
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
583
المشتركون
+1824 ساعات
+1167 أيام
+52030 أيام
أرشيف المشاركات
የ/ፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሕግ ትርጉም የሰጠባቸዉ ዉሳኔዎች ማዉጫ - ከቅጽ 01-25
ማውጫው ዉሳኔዎችን በዙርፍ በዘርፍ ተከፋፍሎ ተመሳሳይ ጉዳይን የሚመለከቱ ዉሳኔዎችን በአንድ ላይ ተደራጅቶ በሕግ ባለሙያ አቶ አረጋይ ገ/እግዚአብሄር ተዘጋጅቶ ቀርቧል::
Case No. 164649.doc0.42 KB
Case No. 160409 R.doc0.32 KB
Case No. 159195.doc0.34 KB
Case No. 124316.doc0.38 KB
Case No. 123526.doc0.42 KB
የተመረጡ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የወንጀል ውሳኔዎች
የህገመንግስት አጣሪ ጉባኤ የ40/60 የኮንዶሚኒየም ቤት መርሃ ግብር እጣ አወጣጥ ጉዳይን በተመለከተ የመስማት /Hearing/ እንዲካሄድ ውሳኔ ሰጠ
***
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ባካሄደው መደበኛ ጉባዔ ቀደም ሲል በተለያዩ ጊዜያት በዋና ጉባዔና በንዑስ ጉባዔ ደረጃ ሲመረምራቸው ከቆያቸው አቤቱታዎች መካከል በ28 ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።
አጣሪ ጉባዔው ሐሙስ መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ጉባዔ 28 ጉዳዮችን በመመርመር 26 ጉዳዮች ምንም አይነት የሕገ መንግሥት ጥሰት ስላላገኘባቸው የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልጋቸውም ብሎ ውሳኔ በመስጠት ሲዘጋቸው አንድ ጉዳይ ላይ ግን ተጨማሪ ማብራሪያ ተደርጎበት ግልፅ ሆኖ እንዲቀርብ አቅጣጫ ሰጥቶበታል፡፡
በጉባዔው ሰፊ ውይይት ያደረገበት ሌላኛው አንድ ጉዳይ ደግሞ በመዝገብ ቁጥር 6690/14 የቀረበና ከ40/60 የኮንዶሚኒየም ቤት መርሃ ግብር እጣ አወጣጥ ጋር የተያያዘ ሲሆን ጉዳዩ ወደ ጉባዔው የቀረበው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ አመልካችነትና በ761 ሰዎች ተጠሪነት ነው፡፡ ጉባዔውም ቀደም ሲል በአቤቱታውና በተጠሪዎች በቀረቡ መልሶች እንዲሁም በጉባዔው የጉዳዮች አቀራረብና አወሳሰን መመሪያ አንቀፅ 26 መሰረት ከጉዳዩ ጋር ተዛማጅነት ያላቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትንና የዘርፉ ምሁራን ባቀረቡት ምክረ ሀሳብ ላይ ሰፊ ውይይት ካካሄደ በኋላ የሕገ መንግሥት ትርጉም ምርመራ ስራውን በተሻለ ለመፈፀም ይረዳው ዘንድ ሌሎች ተጨማሪ የዘርፉ ምሁራንን ምክረ ሃሳብ ለመስማት ጭብጦችን ለይቶ በጥቂት ቀናት ውስጥ አጠቃላይ ዝግጅቱ እንዲጠናቀቅና የመሰማት ፕሮግራሙ /Hearing/ እንዲካሄድ አቅጣጫ አስቀምጦ የእለቱ ጉባዔ ተጠናቋል፡፡
ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ ከእስር ተፈቱ
በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እና በሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ መዝገብ ተከስሰው በእስር ላይ የነበሩ የህወሓት ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮች ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 21፤ 2015 አመሻሽ ላይ ከእስር መፈታታቸውን የተከሳሾቹ ጠበቆች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሃፍቶም ከሰተ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በዛሬው ዕለት ከእስር ተለቅቀው ወደ ቤታቸው መግባታቸው ከተረጋገጡ ተከሳሾች ውስጥ፤ የህወሓት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ እንደሚገኙበት ጠበቃው አስታውቀዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
የክስ መነሳትን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
በፌዴራል መንግስት እና በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) መሃከል በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረት ከግጭቱ ጋር ተያያዥ የሆኑ ወንጀሎች ተጠያቂነት በተመለከተ ያለውን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ ሊታዩ እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ስለሆነም በወንጀል ተጠርጥረዉ ክስ ቀርቦባቸዉ የነበሩ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮችን ክስ በማቋረጥ ጉዳያቸዉ በቀጣይ በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ እንዲታይ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
ስለዚህ በተገለፀው አግባብ ከዚህ ጋር በተያያዘ ቀርቦ በክርክር ሂደት ላይ ይገኙ የነበሩ የወንጀል ክሶች በአዋጅ 943/2008 አንቀጽ 6 (3) (ሠ) መሰረት የተነሱ መሆኑን እናሳዉቃለን።
#ፍትህ ሚኒስቴር
የኢትዮጵያ_ብሔራዊ_መታወቂያ_ረቂቅ_አዋጅ.pdf6.39 KB
Draft-Digital-ID-LAW-English-Version.pdf
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የዲጂታል መታወቂያ አዋጅ በዛሬው ዕለት በአዋጅ ቁጥር 1284/2015 ሆኖ ጸድቋል።
The National ID Program is delighted to announce the adoption of the #DigitalID Proclamation (Proclamation No. 1284/2015) officially passed into law today by the parliament House of Peoples Representatives of FDRE
* you can find the final draft below
ምክር ቤቱ የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ዳኛ የነበሩትን አቶ ፋንታሁን ደለለውን ከስራ አሰናበተ
********
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ዓመት 12ኛ መደበኛ ስብሰባው የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ዳኛ የነበሩትን አቶ ፋንታሁን ደለለው ሽፈራውን ከስራ አሰናብቷል።
የስራ ስንብት ውሳኔ ሃሳቡን ያቀረቡት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ እና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ እፀገነት መንግስቱ፤ አቶ ፋንታሁን የዳኞች የስነ-ምግባርና የዲሲፕሊን ክስ ስነ-ስርዓት ደንብ በመተላለፍና የሐቀኝነት ተነጻጻሪ ግዴታ በመተላለፍ ከአመልካች ብር 100ሺህ መደለያ መቀበላቸው በማስረጃ ተረጋግጧል ብለዋል።
ምክር ቤቱም የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ ሪፖርት ካዳመጠ በኋላ የአቶ ፋንታሁን ደለለው ሽፈራውን የስራ ስንብት የውሳኔ ሃሳብ ቁጥር 13/2015 አድርጎ በሙሉ ድምጽ ማጽደቁን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መረጃ ያመለክታል።
#EBC
Repost from Harmeejobs.com
New vacancies at Zemen Bank
🔰 Zemen Bank wants to recruit employees in the following vacant positions 👇👇
🔰 Professions: Accounting, Banking & Insurance, Management, Economics, Law, Accounting & Finance, Marketing, in Human Resources Management, Management, Business Administration, Administrative Management, Office Management , Public Administration and related.
📌 Deadline : April 7, 2023
📌ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇
👉 Read Detail:- https://bit.ly/3jTya7z
📌ዛሬ የወጡ የስራ ማስታወቂያዎች ሁሉም በአንድ ቦታ በዚህ ሊንክ ዌብሳይቱ ላይ ይመልከቱት👇👇👉 www.harmeejobs.com
🔰Telegram:- https://t.me/harmeeJobs
🔰Please Don't forget to share/ወዳጅ ዘመድዎ እንዲደርሰው ሼር ያድርጉ
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪን ለ90 ቀናት ለማገድ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የወጣ ማሻሻያ ደንብ ቁጥር 145/2015
A Regulation to provide for the amendment for the suspension of residential housing rental increment for 90 days
Regulation no. 145/2015
የጠበቆች ማህበር በካፒታል ማርኬት ላይ የስልጠና መርሃ-ግብር ዝግጅቱን እያጠናቀቀ ነው
********
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር በአዋጅ ከወሰዳቸው ሀላፊነቶች አንዱ ጠበቆች ከአዳዲስ የህግ ማዕቀፎችና ማሻሻያዎች ላይ ግንዛቤዎችን መፍጠር ስልጠናዎችን መስጠት በውጤቱም ጠበቆች ወቅቱን የዋጀ የህግ ግንዛቤ ኖሮአቸው የሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል ማስቻል ነው፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ከ አለማየሁ ሀይሌ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር መቀመጫቸውን ናይጄሪያ ካደረጉት ፕራይስ ዋተር ሀውስ ኮፐርስ እና ኤን.ጂ.ኤክስ ሬጉሌሽን ሊሚትድ (PricewaterhouseCoopers and NGX Regulation Limited) ከተባሉ ሁለት የውጭ ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን በካፒታል ማርኬት ላይ ስልጠና ለመስጠት ቅድመ ዝግጅቶችን አጠናቋል፡፡
ስልጠናው እ.ኤ.አ April 06 2023 ማለትም በመጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ.ም ሀሙስ ከቀኑ 5፡00 እስከ 7፡15 ሰአት Virtual በበይነ-መረብ ይሰጣል፡፡ በስልጠናው ከፌደራል ጠበቆች በተጨማሪ ከተለያዩ ሚኒስትር መ/ቤቶች፤ ኮሚሽንና ባለስልጣን መ/ቤቶች፤ ከባንኮች የተውጣቱ የህግ አማካሪዎች In- house counselors፤ ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጠበቆችና የህግ አማካሪ ባለሙያዎችን ለማሳተፍ ታቅዷል፡፡ በመሆኑም ለስልጠናው ፍላጎት ያላችሁ በሙሉ ከዚህ በታች ከተያያዘው link ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቀድማችሁ እንድትመዘገቡ ማህበሩ ያሳስባል፡፡
ሙሉ መርሃ- ግብሩን በቀጣይ የምናሳውቅ ይሆናል::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
መጋቢት 18 ቀን 2015ዓ.ም
አዲስ አበባ፤
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScm2V-a2DkrqB4YnR1570UEcjDn2CbvwE9BxC4OjyWadNuqjw/viewform?fbzx=-2205564144719468411
