የኦርቶዶክስ አገልግሎቶች
"እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ፤ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ፥ ወደ እርሱ እገባለሁ ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል።" (የዮሐንስ ራእይ 3:20፤) https://t.me/+eap0Rp_ezchmNDU0
إظهار المزيد268
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
11420
Photo unavailable
#እንሂድ_ተነሺ
እንሂድ ተነሺ ሕፃኑን ይዘሽ
ዮሴፍ ሲልሽ /ምናለ ሆድሽ/(፪)
ድንግል ሆይ(፪)ምን አለ ሆድሽ
ስለ ሰማ ሔሮድስ የሕፃኑን ዜና
በግፍ ሊያስገድለው /ይፈልጋልና/(፪)
መልአኩ ለዮሴፍ በህልሙ ነገረው
ድንግልን ወደ ግብፅ /ይዘሃት ሽሽ አለው/(፪)
አሳስቢ ድንግል ሆይ የስደት ጉዞሽን
በልጅሽ ምክንያት/የደረሰብሽን/(፪)
በግብፅ በረሃ ስትንከራተቺ
አጣሽ ዘመድ አዝማድ /የሚያዝንልሽ ላንቺ/(፪)
ድንግል እንዴት ቻልሽው ሕፃን ይዘሽ ስደት
ለአንድ ቀን ይከብዳል /እንኳን ለአመታት/(፪)
ሽፍቶች ሲማከሩ እነሱን ለመያዝ
የድንግል እንባዋ/ሆነ እንደ አባይ ወንዝ/(፪)
በጣለችው ጊዜ ሕፃኑን ኮቲባ
ልቦናን ይከፍላል /ያነባሽው እንባ/(፪)
አይዞሽ እናቴ ሆይ አታልቅሽ አትዘኝ
ጊዜዬ ገና ነው /ሔሮድስም አይገድለኝ/(፪)
ሕፃኑ እንዲህ ብሎ እናቱን አጽናናት
የአምላክነቱን/ምስጢር ሲገልጽላት/(፪)
በሕፃንነቱ ልጅሽ የረገጣት
የአስራት ሀገርሽ /ኢትዮጵያ ናት/(፪)
የሔሮድስን መሞት መልአኩ ሲያበስራት
ድንግል ተመለሰች /ወደ ሀገሯ ናዝሬት/(፪)
መዝሙር
ዘማሪት ማርታ ኃይሉ
12410
12330