HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
الذهاب إلى القناة على Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
إظهار المزيد2 277
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+47 أيام
+2930 أيام
أرشيف المشاركات
◈ ህዳር 7 የዛሬ 20 ዓመት ጻድቃኔ ማርያም ከቦንብ የዳንኩበት ቀን 🙏
በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
ተወዳጆች ሆይ ቀኑ ወሩ ዓመቱ ዓመታቱ እንደ ዋዛ እንደ ፈጣን ባቡር እልም እያለ ይሄዳል ይነጉዳል፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች እየዳኑ ምስክርነታቸው ሰምቻለሁ አሰምቻለሁ፡፡ እስኪ እኔም የዛሬ 20 ዓመት አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ያደረጉልኝ፣ ከሞት የታደጉኙን እና ዳግም የመኖር ዕድል የሰጡኝን በእለተ ቀናቸው ልናገር፡፡
መቼን ጻድቃኔ ማርያምን የማያውቅ ኦርቶዶክሳዊ አለ ብዬ አላምንም፡፡ የተፈቀደላቸው የተቀደሰ ደጇን ረግጠው በሥጋም በነፍስም የተጠቀሙ ሚሊዮኖች ናቸው፡፡ ከእነዛ ውስጥ አንዱ እኔ ነኝ፡፡ እዚህ ለመድረሴ መሠረቴ ጻድቃኔ ማርያም ነች፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው ጻድኔ ማርያም አንድ ዓመት ተቀምጬ ሁለተኛ ዓመቴን እንዳገባደድኩ ልክ የዛሬዋ ቀን ህዳር 7 በ1996 ዓ.ም በርዕሱ የገለጽኩላችሁ ነገር ተፈጠረ፡፡ ጻደቃኔ ማርያም ገደም ውስጥ በተለይም ከኪዳን ማድረሻው ዋሻ አናቱ ላይ አንድ ትልቅ እና ሰፊ ጎጆ ቤት ነበር፡፡
በዚህች ጎጆ ቤት ከአዲስ አበባ እና ከለተያዩ ቦታዎች የሚመጡ የቦታው አፈር አይንካኝ፣ ደረቅ የሲሚንቶ አዳራሽ ውስጥ አታስተኙኝ የሚሉ የቀበጡ፣ ከመንፈሳዊ ሕይወት የወጡ፣ በገዳም ስለሚኖረው የሥጋ ፈተና እውቀት ያልጨበጡ፣ ሐብታም ጠብታም የሚጫወቱ መንፈሳዊ ቀለብ ሳይሆን ገንዘብ ያላቸው ሰዎች እየመጡ የደጇን እምነት እና ወለሉ ሲሚንቶ ሆኖ የሚቀዘቅዘውን አዳራሽ ሽሽት በዋሻው አናት ላይ በተሠራው ንብረትነቱ የአንድ ሰው ጎጆ ቤት ውስጥ በተለይ ለጾመ ለፍለሰታ ገንዘብ እየከፈሉ ያድራሉ፡፡ እኛ ደግሞ የሲሚንቶውን ቅዝቃዜ ችለን፣ አንድ ፎጣ ለብሰን እመቤታችንን ሙጥኝ ብለን ደጅ እንጸናለን፡፡
እንደ ነገርኳችሁ ጎጆ ቤቱ ከኪዳን ማድረሻው አናት ላይ ስላለ ከታች ሌሊት ሰዓታቱ ይቆማል፣ ጠዋት ኪዳን ይደረሳል፤ ከላይ ደግሞ ባለ ገንዘቦቹ ጎጆ ቤት የተከራዩት ኪዳን አያደርሱ ወሬ ሲለውሱ፣ ያለ ሰዓቱ እንደ ልባቸው ያገኙትን ሲያግበሰብሱ ይውላሉ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ቀንም ማታው ጨዋታ ሁካታ ያበዛሉ፡፡
ቦታው ደግሞ የአርምሞ፣ የጥሞና፣ የሱባኤ እና የጸሎት ቦታ ስለሆነ በቦታው ላይ ያሉት የተሰወሩት ቅዱሳን አዘኑ፣ እመቤታችንም አዘነች፡፡ በተለይ የተሰውሩት ቅዱሳን ለእመቤታችን መጸለይ አልቻልንም ጫጫታው በዛብን ብለው አመለከቱ፡፡
እመቤታችን ወትሮም ቅይም ብላቸው ስለነበር በሕልም እና በራዕይ በገዳሙ ላሉት እናቶች እና አባቶች ‹‹ቦታዬ የሳቅ የስላቅ፣ የጨዋታ የሆካታ ሆነ፡፡ ቅዱሳን ልጆቼም እኔም አዘንኩ፣ ከቤተ መቅደሴ አናት ላይ ሆነው ረበሹኝ›› ብላ መልእክት ተናገረች፡፡
ይህንን የእመቤታችንን መልእክት የሰሙት አባቶች እና እናቶች ለጎጆ ቤቱ ባለቤት ነገሩት አልሰማም፡፡ ‹‹ጎጆ ቤቱ ዋሻው አናት ላይ ስላለ የቤቱን ግምት እንስጥህ እና ይፍረስ ገዳሙም ቅዱሳኑም እየታወኩ ነው›› ተባለ፡፡ ሰውዬው እንቢኝ አሻፈረኝ አለ፡፡
በዚህ ጊዜ ገዳሙ ሰውየውን ፍርድ ቤት ከሰሰው፡፡ ፍርድ ቤቱም ጎጆ ቤቱ የተሠራው ገዳም ውስጥ ነው። ይባስ ብሎ የዋሻው አናት ላይ ነውና ጎጆ ቤትህ ይፍረስ አሥር ሺ ብር ካሳህን ጉረስ›› ብሎ በባለ ሙያ አስገምቶ ወሰነ፡፡ ሰውየውም እሺ ብሎ ተስማማ፡፡ ከፍርድ ቤት ከተመለሰ በኋላ ገዳሙን ‹‹አሥር ሺ ብር የጎጆ ቤቱ ካሳ ያንሰኛል አሥራ አራት ሺ ብር ካልከፈላችሁኝ አይፈርስም›› አለ፡፡
አስቡት የዛሬ 20 ዓመት አሥር ሺ ብር ያለውን የመግዛት ጉልበት! ጉዳዩ በድጋሚ ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡ የሰላ ድንጋይ ፍርድ ቤትም ‹‹ህዳር 6 የማያፈርስ ከሆነ ህዳር 7 በራሱ ኪሳራ እናንተ አፍርሱት›› ብሎ ወሰነ፡፡
ይህንን ዜና ህዳር 6 ማታ ሰላም እለኪ አዳራሽ የገዳሙ አበ ምኔት መጥተው ነገሩን፡፡ ‹‹ዛሬ ህዳር 6 ስላላፈረሰ ነገ ጠዋት እናንተ ተባብራችሁ አፍርሱት›› ብለው ወጥተው ሄዱ፡፡ እኛም እመቤታችን አሥር ሺ ብር ካሳ ከፍላው እንዴት እንቢ ይላል፣ በዛ ላይ ገዳም ውስጥ፣ ይባስ ብሎ ዋሻዋ አናት ላይ ሠርቶ ብለን፣ በጠዋት ጎጆ ቤቷን ለማፍረስ ከሱባኤተኛው ጋር ቀጠሮ ይዘን ተኛን፡፡
ጠዋት እኔ አንድ ችግር ገጠኝ፡፡ ከማስታምማቸው ልጆች ውስጥ አንዱ ልብሱ ላይ ሽንቱን ሸንቶ ተጸዳድቶ አደረ፡፡ እሱን ሰውነቱን ላጥበው፣ ልብሱንም ልቀይርለት ወደ ወንዝ ይዤው ሄድኩኝ፡፡ አጣጥቤው ተመለስኩ እና እስኪ በረከቱ ይድረሰኝ ብዬ ወደ ጎጆዋ ስሄድ ሱባኤተኛው ጎጆ ቤቷን ከላይ ከታች እንደ ንብ ወረዋት በሞራል ያፈርሳሉ፡፡
ጎጆዋ ጋር እንደ ተጠጋሁ የቀኝ ተረከዜን የሆነ ነገር ሲመታኝ ታወቀኝ፡፡ ዞር ብዬ ስመለከት ቦምብ ነው፡፡ ችስስ … እያለ ተረከዜ ስር ይዞራል፡፡ በጣም ደነገጥቱ ወዴት እንደምሄድ ግራ ገባኝ፡፡ ቦምቡም ጊዜ አልሰጠኝም፡፡ እልም ብሎ ፈነዳ! ቦምቡ ከፈነዳ።
በኃላ ምን እንደተፈጠረ፣ ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ ብቻ ስነቃ እኔ አዋራ ጠጥቼ፣ መሬቱ ላይ በጀርባዬ ተኝቼ፣ የማስታምመው ልጅ ደግሞ እኔ ላይ ወድቋል፣ ጆሮዬም በቦንቡ ፍንዳታ ተደናቁራል፡፡
አዋራው ይጨሳል፣ ጎጆ ቤቱን የሚያፈርሱት ሱባኤተኞች ጩኸታው ይሰማል፡፡ ደነገጥኩ ሕልምም ሰመለኝ ግን እውነታ ነው፡፡
የማስታምመውን ልጅ ከላዬ ላይ አንስቴ ምን እንደተፈጠረ ግራ ቀኝ ስቃኝ አንድ ሰው ከፊት ለፊቴ ወድቋል። ደሙ እንደ ጅረት ወንዝ ይፈሳል፡፡ ‹‹ኸረ ባካችሁ ሰው ወድቋል ሰው ሞቷል እያልኩ›› ስጮህ ሱባኤተኛው ግር ብሎ መጣ፡፡ በእውነትም የወደቀው ሰው በጀርባው ተኝቶ ደሙ በሥሩ ይፈሳል፡፡
ሰውየውን ለማንሳት እና ወደ ሕክምና ተቋል ለመውስድ ሰው ሲሯሯጥ ስማቸው ለጊዜው ይቅርና እንድ እማሆ ጠጋ በለው ‹‹እናንተ ቦምቡን ያፈነዳው ይሄው ሰውዬ ነው፣ ከቦንቡ ላይ የሆነ ነገር ነቅሎ ልጁ ላይ /እኔ ላይ/ ጥሎ እግሩ ሥር ሲወረውረው አይቻለሁ አታንሱት ፈትሹት›› አሉ፡፡
አንድ ወጣት ልጅ የወደቀውን ሰውዬ ከጨርቅ የተሰፋ ቦርሳውን ሲፈትሽ አንድ ያልፈነዳ ቦምብ አገኘ፡፡ ጉድ ተባለ፡፡ ወዲያው ፓሊስ መጣ የወደቀውን ሰውዬ አገላብጠው ሲያዩት ከጀርባው እስከ መቀመጫው ለሁለት ተሰንጥቋል፡፡
ለካ እኔ ላይ የወረወረው ቦንብ ሲፈነዳ እሱን ነው የመታው፡፡ ፖሊሱ ሲናገር እንደሰማሁት ቦንቡ እጅግ ገዳይ እና ብዙ ሜትሮችን የሚያካልልና ኤፍ ዋን ግሪናዴ/F1 grenade/ የሚባል ቦንብ ነው፡፡
እኔም የማስታምመው ልጅ ምንም አልሆንም። ፍንጣሪውም አልነካንም። የማስታምመው ልጅ ትንሽ ድንጋይ እግሩን በስቶታል፡፡
ወዳጆቼ እስከ ዛሬ ድረስ እንቆቅልሽ የሚሆንብኝ እና ሳስበው ድክም የሚለኝ ቦንቡ ሲፈነዳ ቆሜ ነበር። እራሴን ያገኘሁት ግን ቦንቡ ከፈነዳበት ቦታ ርቄ በጀርባዬ ተኝቼ ነው፡፡ በአየር ላይ ልሂድ፣ ልገልበጥ፣ ልንሳፈፍ አላውቅም፡፡ ይህ የሆነው ህዳር 7 በ1996 ዓ.ም የአጋዕዝተ ዓለም የሥላሴ ቀን የዛሬ ሃያ ዓመት ነው፡፡
ልክ ይሄ ነገር ሊፈጠር አንድ ቀን ሲቀረው አንዲት ልጅ ሱባኤ ግብታ ጨርሳ ልትወጣ ስትል እመቤታችን በሕልሟ ‹‹ዛሬ አንድ ተአምር በገዳሜ ላይ ታያለሽ ዛሬን ውለሽ ነገ ትሄጃለሽ ብላኝ ነበር ለካ ይሄንን ልታሳየኝ ነው›› ብላ ህዳር 7 ቀን እዛው ገዳም ምስክርነቷን ሰጥታለች፡፡
🛑የሰይፉ ጨንገር፣ የራሔሎ፣ የአዳልሞቴ፣ የአዮ ሞምና፣ የእስላም ዛር መናፈስቶች ፈተና አሁንም ይሄን እየሰማን እንኳን አናምንም ተሞክሮ ክፍል 24 😭
https://youtu.be/9Ima9K4f0nY
🛑በእውነት ይገርማል! በሁላችን ቤት ያለ ጣጣ ቤተሰቦቼ የማያመልኩት የባዕድ አምልኮ የለም ምዕመናን ሰባኪ ሆነው ሲያስተምሩን | ተሞክሮ ክፍል 23 😭
https://youtu.be/DH50RTZIaAc
🛑መቁጠሪያን በእምነት እንዴት እንጠቀም በ7 ዓመቱ የገባ ዘማዊ፣ ሰሴኛ ያደረገ መንፈስ ፈተና የቅዱስ ቁርባን ነገር በዲያቆን ሆኖክ #ethiopia 😰
https://youtu.be/yKhr_Aftnfo
🙏 ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች እንደምን አደራቹ ሰላማቹ በያላችሁበት በእግዚአብሔር መሀሪነት በድንግል ማርያም አማላጅነት ይብዛ እያልን ለዛሬ ይችን አጭር ፅሁፍ ግን ብዙ የምታስተምር ቃል ልናጋራቹ ወደድን
"በድህነት እና በረሃብ የሚሰቃዩ ሰዎች እንደ ሠለስቱ ደቂቅ ናቸው:: ከድህነት የበለጠ ምን እሳት አለ? ከረሃብስ የሚበልጥ ምን ነበልባል አለ? ሦስቱ ወጣቶች እሳት ውስጥ ሆነው እንደዘመሩ በመከራ ውስጥ ሆኖ ፈጣሪን የሚያመሰግን ሰው የመከራው እሳት ውኃ ይሆንለታል:: ለድሆች ምጽዋትን የሚሠጥ ሰው ደግሞ ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት የታደገውን የእግዚአብሔር መልአክን ይመስለዋል"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
🙏 ለሁላችሁ መልካም ቀን ይሁን እያልኩኝ እንደምታወቀው የበረከት ሥራ መሥራት ጀምረን ብዙ እህቶች እንዲሁም ማህበራት እየተሳተፋችሁ እንደሆነ አውቃለሁ። አሁንም ለብዙ አቅሜ ደካማዎች ለመድረስ ይመቸን ዘንድ በተቻላችሁ አቅም በዚህ የበረከት ሥራ ላይ ተሳተፉ። ለአንድ እናት በችግሯ መድረስ፣ ለአንድ አባት በፈተናው ወቅት ማገዝ ትልቅ በረከት ነውና የአቅማችንን እናግዝ።
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🛑አውድሙ፣ አባክኑ፣ አስጨንቁ ተብለው የተላኩ የሰላቢ እና የመተት መንፈስ ፈተና የሰላቢ መንፈስ የመተት መንፈስ || ተሞክሮ ክፍል 22 #eotc 😰😭
https://youtu.be/4wk48CiO7Yc
🌹 ሱላማጢስ ከስደት ተመልሳለች፤ የኛስ መመለሻችን መቼ ይሆን? 🌹
🌹 ኅዳር ስድስት ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አዝላ ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ሦስት ዓመት ከመንፈቅ በስደት ከኖሩ በኋላ ቅዱስ ገብርኤል ለዮሴፍ እንዲህ አለው
🌹 ❝ሕፃኑን የሚሹት ሄሮድስና ሠራዊቱ ሞተዋልና እናቱንና ሕፃኑን ይዘህ ወደ ሀገርህ ተመለስ ❞ (ማቴ 2 ፥ 19) ባለው ጊዜ አረጋዊ ዮሴፍ እናትና ልጁን ይዞ ሰሎሜን አስከትሎ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ከስደት ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሱ ደብረ ቁስቋም በተባለ ቦታ ያረፉበት ተራራ ነው።
🌹 ዐምስት ሺ ዐምስት መቶ ዘመን ሙሉ ሰላም ላጣ ለአዳም ሰላም የሆነች ❝ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ❞ ተብሎ እንዲመሰገን ምክንያት የሆነች የሰላም አናት የሰላም እመቤት ድንግል ማርያም ሱላማጢስ ከስደት ተመልሳለች።
🌹 እኛስ መቼ ይሆን ዛሬ በኀጢአት ስደት ያለን ብዙዎች ነን የሠራነው ኀጢአት ከእግዚአብሔር ፊት ከቤተ ክርስቲያን ደጅ ያሳደደን ብዙዎች ነን በትዕቢት ልብ ተይዘን ትላንት ካስቀደስንባት፣ ከቆረብንባት ከቀደስንባት ከተማርንባት ካስተማርንባት ደጅ የተሰደድን መመለሳችን መቼ ይሆን?
🌹 መቼ ይሆን? ከሥጋ ወደሙ የተሰደድን ከልጅነት ጊዜያችን በኋላ፣ ከትዳራችን በኋላ፣ ከአገልግሎታችን በኋላ ሥጋ ወደሙን መቀበል ያቆምን ከሕይወት ምግብ የተሰደድን ሥጋችን እየደለበ ነፍሳችን የቀጨጨችብን መመለሳችን መቼ ይሆን? ከአገልግሎት የተሰደድን ትላንት እንዘምር፣ እንማር እናስተባብር የነበርን አገልጋዮች ዛሬ የት ነን? መመለሳችን መቼ ይሆን? ወዳጄ በቤተ ክርስቲያን አለሁ እንጂ ነበርኩ አያድንምና ያለነው የነበርንበት ቦታ ካልሆነ ወደ ነበርንበት እንመለስ በደልን እንጂ በደለኛን ወደ ማይጠላ አምላክ እንመለስ የት ናችሁ ስንባል ከምናፍርበት ቦታ እንዳንገኝ ወደ ደገኛይቱ ቤት ወደ ቤተ ክርስቲያን እንመለስ።
ሠዐሊ ቀሲስ አማረ ክብረት እንደሣሉት
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🛑ዘፈን፣ ዝሙት፣ ጭፈራ የኃጢአት ነገሮችን ማቆም አቃተኝ ራስን መግዛት በመንፈሳዊ ሕይወት ጉዞ ገድላትና ድርሳናትን የማንበብ ጥቅም #ethiopia 😰
https://youtu.be/fNmgxrZeObU?si=d-JaW_WKM8q9ZwYH
🛑የሙታን ሳቢ፣ የአንደርቢ፣ የቁራኛ፣ የፍልስፍና፣ የከልከልዮስ የሌብነት እና የአፍዝ አደንግዝ መንፈሶች ፈተና #በማለዳ_ንቁ_2023 #ethiopia 😭😰🙏
https://youtu.be/EQCbEjR1xgw
◈ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሆይ አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ዘመን በገዳም ስትቀመጥ እግዚአብሔር በጸጋ የሰጠህ በመላ አካልህ የበቀለው ጸጉር ልብስ ሆኖህ ኖርህ። ክቡር አባት ሆይ ሥጋዊና መንፈሳዊ ጥበብን ግለጽልኝ ይልቁንም የጸሎትህ ኃይለ ቃል ረዳቴ በመሆን ዓሥራት በኩራት አድርጎ ይጠብቀኝ።
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🛑ብዙዎች የሚሰቃዩበት አላስፈላጊ ጸጸት ከንስሐ በኋላ በተመሳሳይ ኃጢአት ደጋግሞ መውደቅ እንኳን ዘፈን ሞቅ ያለ መዝሙርም አይፈቀድም #sibket 😰😭
https://youtu.be/alVaL5fksDM?si=SHLbED9AvsYRrbVm
✍️''አቤቱ አምላኬ የሕይወቴ ጌታ ሆይ የስንፍናን መንፈስ፣ ተስፋ መቁረጥን፣ ስልጣን መሻትንና ከንቱ ወሬን ከእኔ አርቅልኝ ነገር ግን በምትኩ የንጽሕናን፣ የትሕትናን፣ የትዕግስትንና የፍቅርን መንፈስ ለእኔ ለባሪያህ አድለኝ አዎን፣ ጌታዬና ንጉሥ ሆይ የራሴን መተላለፍ እንድመለከት እንጂ በወንድሜ ላይ እንዳልፈርድ አድርገኝ አንተ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ሁለም ምስጉን ነህና''
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
👇👇👇👇
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
◈ ምክር እና ቡጢ ◈
◈ አንዳንዴ ሰው ተቸግሮ ወደ እኛ መጥቶ ሲያወያየን ከግለሰቡ በላይ የምንሰጠውን ምክር የምንወድ ሰዎች አለን። ያ ሰው ምን ሁኔታ ላይ ነው? ምን ይሰማዋል? ብሎ ለመረዳት ከመጣር ይልቅ ልንነግረው ባሰብነው ምክር ቀድሞ ደስ መሰኘት። አውርቶ እስኪጨርስ ትዕግሥት ማጣት። እንዴት ሰምቼ ላሳርፈው ከማለት ይልቅ ከመቼው ነግሬው ላስደንቀው (ይደነቅብኝ) የሚል ጉጉት።
◈ መፍትሔ ብለን የምንነግረው ደግሞ ሸክም ያደከመው ሰውነቱን ጨርሶ ያላገናዘበ የሚሆንበት አጋጣሚ በጣም ብዙ ነው።
◈ አንድ በchildhood psychology የተመረቀ አንድ ወጣት ሰው ነው አሉ። ወላጆች በተሰበሰቡበት የመጀመሪያውን ሥልጠና ሲሰጥ ለጥናቱ የመረጠው ርእስ "ዐሥርቱ ትእዛዛት ለወላጆች"/Ten commandments for parent" በሚል ነበር። ታዲያ እርሱም እንደ ሌሎች የትዳር ወጉ ደርሶት ልክ አንድ ልጅ ወልዶ ማሳደግ እንደ ጀመረ ያ ይሰጠው የነበረውን የሥልጠና ርእስ መቀየር እንዳለበት ተሰማውና "ዐሥር ማሳሰቢያ ለወላጆች" አለው። ቀጥሎ ሁለተኛ ልጅ ወልዶ ሲያሳድግ አሁንም የቀየረው የሥልጠና ርእስ ድጋሚ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው ተረዳ። ስለዚህ በስተመጨረሻ ርእሱን "ዐሥር ጥቆማ ለወላጆች" አለው ይባላል። አንዳንዴ ለሰዎች የምንሰጠው ምክር ምን ያህል ከባድ እንደ ሆነ ሕይወት እስክታስተምረን ድረስ የምንጨክን እንኖራለን።
◈ አንዳንድ ጊዜ ሰው ጨንቆት ወደ አንተ ሲመጣ ግዴታ የሆነ ወርቃማ አባባል እንድትነግረው ወይም በአነቃቂ ቃላት እንድታግለው ላይሆን ይችላል። ያን ሰው በዝምታ መስማት እና የተዘበራረቀው ሐሳቡን ጊዜ ወስዶ ለአንተ በመናገር እንዲያጠራ ማድረግም ትልቅ እርዳታ ነው።
በዲያቆን አቤል ካሳሁን
👇👇👇👇
#ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🛑መናፍስት እና የአካል ክፍሎቻችን ክፍል 1 የጭንቅላት ክፍላችን በመናፍስት ሲያዝ ምልክቶቹና መፍትሄዎቹ || በማለዳ ንቁ 2023 #ethiopia 😰😭
https://youtu.be/OFawyK0Mpp4
🛑ለ12 ዓመታት ደም ይፈሳት የነበረች እናት ታርክ የደም ግብር ፈላጊ ክፉ መናፈስቶች የጬሌ፣ የራሔሎና የአቴተ መናፍስቶች #ethiopia 🙏😰😭🙄
https://youtu.be/dM7cUCOGmrw
