HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
الذهاب إلى القناة على Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
إظهار المزيد2 278
المشتركون
+324 ساعات
+137 أيام
+3830 أيام
أرشيف المشاركات
+++ የሰይጣን ወጥመድ +++
=> አባ ኔቅጣስ ስለ ኹለት ወንድሞች የሚከተለውን ተናግረዋል። አንድ ጊዜ ኹለት መነኮሳት በአንድነት ለመኖር ወሰኑ። አንደኛው በልቡ "ወንድሜ የሚፈልገውን ኹሉ አደርግለታለሁኝ" ሲል ቃል ገባ። ሌላኛውም "የወንድሜን ፈቃድ እፈጽምለታለሁ" ሲል በልቡ ወሰነ። በዚህ ውሳኔያቸው ለብዙ ዘመናት በለጋሥነት ኖሩ። በዚህ ፍቅራቸው የቀና ሰይጣን ሊለያያቸው ተነሣ። በበኣታቸው በር ላይ ቆመና ለአንደኛው ርግብ ለሌላኛው ቍራ መስሎ ታያቸው። በዚህ ጊዜ አንደኛው መነኩሴ "ርግቧን አየሃት?" ሲለው ሌላኛው ደግሞ "ርግብ አይደለችም ቍራ ናት" ሲል መለሰ። "ርግብ ናት"፣ "ቍራ ነው" ክርክር ጀመሩ። ክርክሩ ወደ ጭቅጭቅ፣ ጭቅጭቁ ወደ ድብድብ አመራና ደም በደም እስኪ ኾኑ ድረስ ተደባደቡ። በመጨረሻም ተለያዩ። ከሦስት ቀናት በኋላ ወደ ልባቸው ተመልሰው ኹለቱም ተፀፀቱ። ይቅርታም ተጠያየቁ። ኹለቱም በተለያየ መልክ አንድ ዓይነት ነገር ማየታቸውንና ልዩነታቸው የመጣው ከነገሩ ሳይኾን ከዲያብሎስ መኾኑን ተረዱ። እስከ ዕለተ ሞታቸውም ድረስ አብረው ያለ ፀብ ኖሩ። (ዳንኤል ክብረት (ዲ/ን፣ አርተር)፣ በበረሓው ጉያ ውስጥ፣ ሦስተኛ ዕትም 2004 ዓ.ም፣ ገጽ 57-58)።
=> ብዙ ጊዜ መንፈሳዊ ሕይወታችን ምስቅልቅል የሚልብን በእንዲህ ዓይነት ስውር የሰይጣን ወጥመድ ነው። አንድን ነገር በእርጋታ ከመመርመር ይልቅ ያየነውን ብቻ መሠረት አድርገን ወደ ተሳሳተ ውሳኔ የምንገባም እና የእግዚአብሔርን መግቦት የምንጠራጠር ብዙ ሰዎች አለን። ከሌሎች ጋር በፍቅር ለመኖር የወሰነውን ውሳኔ ድንገት በአንዲት ተራ ምክንያት የምናፈርስ መኾኑን እናስተውል። የገመጠንን ነገር በልቡናችን ከገባነው ቃል ኪዳን ጋር እያስተያየን በትዕግሥት ልንጸናና ረጋ ልንል ሲገባን በጥድፊና ተቃራኒ መልስ እየመለስን ወደ ጥልና ፀብ የምንገባ ልንጠነቀቅ ይገባናል። የልቡናችንን ዐይን ስሜታዊነታችንን አንጫነው፤ እኔ የማየው ብቻም ነው ትክክል ብለንም የሌሎችን ሐሳብ አንግፋ። ለሕይወታችን ሊጠቅም የሚችለውን ወዳጅ እኔ እንደ ማየው አላየም ብለን አንግፋው። በጎ አንድነት እንዳይኖር የሚሻ ጠላት ልዩነትን ኾነ ብሎ እየፈጠረብንም እንደ ኾነ ልብ እንበል። የሚሻለን ኹሌም ቢኾን ራስን ዝቅ አድርጎ ለሕይወት ከሚጠቅመን ወዳጃችን ጋር በአንድነት መኖር ነው። እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን።
=> በሌላ በኩል ደግሞ አንድ ነገር በተለያየ መንገድ ለተለያዩ ሰዎች በማሳየት ሰይጣን ምን ያህል ፀብና ጥልን የሚፈጥር ክፉ ጠላት መኾኑን ልብ ማለት እንችላለን። ክፉው ጠላት ሰይጣን እኛን ለመጣል ያን ያህል የሚዋጋ ከኾን እኛስ እርሱን ለመግጠም ምን ያህል ሠልጥነን ይኾን? ይህን ኹላችንም ለየራሳችን እንጠይቅ። በክርስትና ሕይወት በጣም የዛልን፣ በእምነታችን ላይ ጥርጣሬ የመጣብን፣ በሃይማኖታዊ ጉዳይ ለዘብተኛ ወደ መኾን እየሄድን ያለን በሙሉ ለአንድ አፍታ ቆም ብለን እናስብ። ጠላት ምን ያህል የጥፋት ጉድጉድ እየቆፈረልን እንደ ኾነም ልብ በማለት ንቁ ተዋጋጊ እንኹን። ሊዋጋው እና ሊያጠፋው በብዙ ኃይል ታጥቆ የሚመጣን ጠላት እያየ ባዶ እጁን ቍጭ ብሎ የሚጠብቅ ተዋጋ ይኖራልን? ቢኖሩ እንኳን ለማሸነፍ ያሰበ ሳይኾን አስቀድሞ በስንፍናው ምክንያት የተሸነፈ ጠላትም ሲመጣ እጁን ሰጥቶ ባርያ ሊኾንለት ያቀደ ብቻ ነው ሊኾን የሚችለው። ወይም ሕይወቱን የጠላና ለበለጠ ሥቃይና መከራ ራሱን በፈቃዱ አሳልፎ ለመስጠት የፈቀደ ሞኝና ሰነፍ ነው ሊኾን የሚችለው። ይህ ደግሞ በራስ ላይ ራስን ጠላት እንደ ማድረግ ነው። ስለዚህ በጥንቃቄ እንኑር።
=> ሰይጣን በተለያየ መልክ እየተገለጠ ወደ ልዩነትና ፀብ የሚወስድ መኾኑን ልብ ከማለት ጋር እኔ የማየው ብቻ ነው ትክክል ከማለት በፊት ጸሎት ማድረግ ወደ እግዚአብሔር መጮህ ያስፈልጋል። ብዙ ጊዜ ልዩነት እየመሰሉን የምንጣላባቸው ነገሮች ልክ እንዲሁ ናቸው። ወደ ልዩነት፣ ፀብና ክርክር፣ አለፍ ሲልም ወደ ጭቅጭቅ እና ድብድብ ድረስ የሚያደርሰን ለነገሮች ያለን የተቃረነ አረዳድ ነው። ኹላችንም ማንኛውንም ነገር በጸሎትና እግዚአብሔርን በመጠየቅ ብናደርገው እጅጉን ጠቃሚ ነው። ተቃራኒ የሚመስለን ወደ ፀብ ሊያመራን የሚችል ነገር ኹሉ የጠላታችን የዲያብሎስ ወጥመድ መኾኑን ኹሌም ልብ እንበል። የእኔ ብቻ ትክክል ነው፣ ያንተ ትክክል አይደለም እያሉ የሌሎችን ሐሳብም ኾነ ንግግር ለማድመጥ ፈቃደኛ አለመኾን ወደ ጭቅጭቅና ከዚያም አልፎ ደም እስከ ማፋሰስ ድብድብ የሚያደርስ መኾኑን ልብ ይሏል። እንዲህ ዓይነት የልዩነትና የፀብ ፈተና በገዳም እንኳን የማይቀር መኾኑን ኹል ልብ እንበል። ስለዚህ አንዱ እሳት ሲኾን ሌላው ውኃ፣ አንዱ ቍጡ ሲኾን ሌላው በራድ፣ አንዱ ቸኳይ ሲኾን ሌላኛው ረጋ ያለ ትዕግሥተኛ መኾን አለበት። ዕለት ቀንና ሌሊት እንደሚኖረው ሕይወትም ብርሃንና ጨለማ ይኖረዋል። ጨለማ ብቻ ቢኾን ወይም ብርሃን ብቻ ቢኾን አኹን ባለን አኗኗር ጥሩ አይኾንም ነበር። እንቅልፍም ንቃትም ያስፈልጋሉና። አንዱ ሲተኛ አንዱ ካላነቃ፣ አንዱ ሲስት ሌላኛው ካላቀና እንዴትስ ሕይወት ሥምረት ሊኖራት ይችላል?
=> ኹለቱ መነኮሳት ለጊዜው ባይረዱትም ዃላ ወደየልቡናቸው ሲመለሱ ያጣላቸው ሰይጣን እንደ ኾነ ተረድተው፡ ይቅር ተባብለው፡ አንዴ አለያይቷቸው ደም ያፋሰሳቸውን ጠላት እስከ ሞታቸው ድረስ ተዋግተው ድል አድርገውት እነርሱ በፍቅር በአንድነት ምድራዊ ሕይወታቸውን አጠናቀዋል። እንግዲያውስ እኛም እንደነርሱ ወደየ ልቡናችን ተመልሰን የተጣላን ይቅር ብንባባልና ወደ ልዩነት እና ፀብ የመራን ሰይጣን መኾኑን ተረድተን በፍቅርና ክርስቲያናዊ በኾነ አንድነት ብንኖር አሸናፊ መኾናችን በዚያ ይታወቃል። እግዚአብሔር ለኹላችንም ንጹሕ ልቡና አድሎ በፍቅር በአንድነት የምንኖርበትን ኃይል ይስጠን፤ አሸነፍኩ ተሸነፍኩ ከሚያስብል ክፉ እልህና ግራ መጋባት ይሰውረን፤ በእርሱ ቃል ልቡናችን ተሸንፎ ራሳችንን ከኹሉ የምናንስ አድርገን ለመቍጠርም ያብቃን አሜን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
• ሄኖክ ሞትን እንዳያይ በእምነት ተወሰደ፣ ድንግል ግን በእምነቷ ሞትን የሚገድለውን ወለደች።
• ኖኅ ቤተሰቦቹን ለማዳን በእምነት መርከብን አዘጋጀ፣ ድንግል ማርያም ግን እግዚአብሔር ዓለሙን ያድን ዘንድ ራሷን መርከብ አድርጋ ሰጠች።
• ሣራ ዕድሜዋ ካለፈ በኋላ ዘርን ለመጽነስ ኃይልን በእምነት አገኘች፣ ድንግል ማርያም ግን ያለወንድ ዘር በድንግልና ለመጽነስ በእምነት ኃይልን አገኘች።
• አብርሃም ይስሐቅን እግዚአብሔር ከሙታን ያስነሣዋል ብሎ በእምነት አቀረበ፣ ድንግል ግን ልጅዋን እግዚአብሔርነቱ ከሞት ያስነሣዋል ብላ ሞቱን በዝምታ ዐይታለች።
• ሙሴ ከተወለደ በኋላ ወላጆቹ በእምነት ሦስት ወር ሸሸጉት፣ ንጉሥንም አልፈሩም። ድንግል ማርያም ግን ልጅዋን በእምነት ሦስት ዓመት ሸሸገችው፣ ሔሮድስንም አልፈራችም።
© የብርሃን እናት ገጽ 326
የእመቤታችን ረድኤት እና በረከት አይለየን። ጣዕሟን ከአንደበታችን ፍቅሯን ከልቡናችን አያጥፋብን። አሜን!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
በዚችም ዕለት የከበረ የሐዋርያው የጳውሎስ ደቀ መዝሙር የሆነ ቅዱስ አናሲሞስ በሰማዕትነት አረፈ።
ይህም ቅዱስ አስቀድሞ ፊልሞና ለሚባል ለሮሜ ሰው አገልጋይ ነበር። ሰይጣን የአናሲሞስን ልቡ ለወጠና የጌታውን ገንዘብ ሰርቆ ወደ ሮሜ ሔደ።
በእግዚአብሔርም ፈቃድ ወደከበረ ሐዋርያ ጳውሎስ ሔደ ትምህርቱንም ሰምቶ በክብርባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ ለቅዱስ ጳውሎስም ደቀ መዝሙሩ ሆነ። ነገር ግን የጌታውን ገንዘብ በመስረቁ በአናሲሞስ ልብ ጽኑ ሀዘን አደረ ለሐዋርያ ጳውሎስም የሠራውን ሁሉ ነገረው ሐዋርያ ጳውሎስም አትፍራ ልብህም አይዘን አለው የቀድሞ ጌታው በሰላም እንዲቀበለው ወደ ፊልሞናም መልእክትን ጻፈለት ይቺም ስለ አናሲሞስ የጻፋት ከመልእክቶቹ አንዲቱ ናት።
ይህ የከበረ አናሲሞስም ወደ ፊልሞና ወደ ጌታው በደረሰ ጊዜ በማመኑና በመጸጸቱ ደስ አለው ሐዋርያው እንዳዘዘውም ተቀበለው። ከዚህም በኋላ ሸኙትና ወደ ሮሜ አገር ተመለሰ በሰማዕትነት እስከ ሚሞትበት ጊዜ ሐዋርያ ጳውሎስን የሚያገለግልው ሆነ።
ከሐዋርያው ጳውሎስም የምስክርነት ሞት በኋላ የንጉሥ ጭፍራ ይህን ቅዱስ ይዞ ወደ አንዲት ደሴት ሰደደው በዚያም ያሉትን አስተምሮ አጠመቃቸው። ያ ጭፍራም ይህን በሰማ ግዜ በብዙ አሰቃይቶት በዚች ቀን ምስክርነቱንም ፈጸመ። የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ይኼንን ካህን መሳይ ደብተራ ጉድ ተመልከቱ!! የአባቶቻችን ትልቋ ድንቅ ጸሎት!! ካህን የሚመልስ እንጂ የሚያጠፋ አይደለም!! ለሴቶች የተላለፍ ጥብቅ መልእክት! https://youtu.be/Rm8pjyyo2Zc
ሰውን ሰው የሚያደርገው መንፈሳዊ መርሕ!! ከዓይነጥላ መንፈስ ጋር ትዳር የመሠረተው!! Daisy Tamrat ምን ነክቷት ነው?? ቅዱስ ቁርባንና አስተሳሰባችን! https://youtu.be/LdWMkxA4XF0
ጸሎት አለመጸለይ እንዲህ ያደርጋል!! ከአባት ወደ ልጅ የተሸጋገረ መንፈስና ጥፋቱ!! አለመጸለይ ኃጢአት እንደሆነ ስንቶቻችን እናውቃለን?? #ethiopia 😱😭 https://youtu.be/jWQgUJrK95k
ይኼንን ካዳረግን ዲያብሎስን እናሸንፋለን!! አገልጋዮች እያሾፍን ትውልዱን በመናፍስት አስበላነው! አለማዊነት በደማችን ገብቶ መከራ እናያለን! #ethiopia https://youtu.be/qhiikIVOX-k
የመምህር ግርማ የእስር ቤት ገጠመኝና የመናፍስቱ ሴራ!! ብዙዎቻችን በዚህ ሁኔታ ውስጥ ተወልደናል!! ቀያይ ልብስና ጥለቶችን የሚወዱ የዛር አጋንንቶች!! 😱💥😭 https://youtu.be/kKhI5vAOrtw
++ ከሰኞ ወዳሴ አምላክ ++
"የተባረኩ ደቀ መዛሙርትህን ዐይኖች እንደ ከፈትህ፣ የተቀደሱ መጻሕፍትንም እንዳወቁ፣ አምላካዊ የኾነ የቃሉን ትርጒምም እንደ ተረዱ ወደምታስደንቅና አምላካዊ ወደ ኾነ ዕውቀትም እንደ ተመለሱ። አቤቱ የተቀደሱ መጻሕፍትን ትርጓሜያቸውንም እረዳ ዘንድ፣ ትእዛዝህንና ፍቃድህን አደርግ ዘንድ የዕውሩን ዐይን እንዳበራህ ሥጋዊና መንፈሳዊ ብርሃንንም እንደ ሰጠኸው ለእኔም እንዲህ ዓይነት ጸጋን ስጠኝ፤ አቤቱ እውነተኛ ብርሃንን አይ ዘንድ የሚያስደስትህንም አደርግ ዘንድ የልቤን ዐይኖች ክፈትልኝ።" (ተስፋ ሚካኤል ታከለ (መ/ር ወተርጓሚ)፣ ውዳሴ አምላክ ዘሰኑይ ቍጥር 22)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
+2
የበረከት ሥራ ፡ ለሙዳይ የበጎ አድራጎት ማዕከል
ውድ ቤተሰቦቼ እንኳን ለዐብይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ። ዛሬ ለሁላችንም የሚጠቅም በረከት የምናገኝበት የበረከት ሥራ ይዠላችኋለሁ። አቅማችን በፈቀደው መንገድ እንሳተፍ ሁላችንም።
=> አንደኛ ቦታው ድረስ መሄድ የምትችሉ ቤተሰቦቼ ቦታ ድረስ በመሄድ በመጎብኘት ማገዝ በምትፈልጉት መንገድ ማገዝ ትችላላችሁ።
=> ሁለተኛው ደግሞ ካላችሁበት ሆናችሁ ባላችሁ ነገር እንደ አቅማቸሁ ይሄንን የበረከት ሥራ ማገዝ በገንዘብ፣ በሀሳብ በሌሎችም ነገር ማገዝ መልካም ነው። ከታች በመስቀምጠው ስልክ ደውላችሁ ማነጋገርና ማገዝ ትችላላችሁ።
=> ሦስተኛው ደግሞ እኔ እንዳደርስላችሁ የምትፈልጉና በዚህ የበረከት ሥራ ላይ አብራችሁን መሳተፍ የምትፈልጉ በዚህ ስልክ ደውላችሁ ልታናግሩን ትችላላችሁ 0939241162 ሌላው በአካውን በማስገባትም በዚህ የበረከት ሥራ መሳተፍ ትችላላችሁ። በቀጥታ ወደ አካውንት በማስገባትም እኛ እንድናደርስላችሁ ከፈለጋችሁ በመደወል ልታናግሩን ትችላላችሁ።
ውድ ቤተሰቦቼ ይሄንን የዐብይ ጾም በዚህ አይነት አገልግሎት በናሳልፍና የበረከቱ ተካፋይ ብንሆን መልካም ነው።
እግዚአብሔር ሁላችንንም ይርዳን ያግዘን። እንበርታ እንጠንክር።
ኪዳነ ምሕረት (16)
+++ በድንቅ ጥበቡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ያደነው እጅጉን መሐሪ ስለሆነ ነው፡፡ የቀደሙት የብሉይ ኪዳን ኪዳናት ሕዝቡን ከሲኦል መታደግ አልቻሉም ነበር፡፡ ፍጹም የሆነው ኪዳን የተደረገው በሰባተኛው ኪዳን ይህም ለሰው ዘር ምሕረትን ባስገኝች በንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ነው፡፡
+++ የምሕረት ቃል ኪዳን የተሰጠችውን እናታችንንም ‹‹ኪዳነ ምሕረት›› እያልን የምንማጸናት ለዚህ ነው፡፡ ለአዳም የተገባለት የምሕረት ቃል በእርሷ ተፈጽሟልና፡፡ እመቤታችን አምላክን በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ወልዳዋለችና፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራን ተቀብሎ እንዲሁም በመስቀል ተሰቅሎ ዓለምን ያዳነው ከእርሷ በነሣው ሥጋና ነፍስ ነውና፡፡
+++ በነገረ ማርያም ተጽፎ እንደምናገኘው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት በኋላ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ልጇ መቃብር ቦታ ጎልጎታ እየሄደች ትጸልይ ስለ ነበር በየካቲት ፲፮ ቀን በጸለየችው ጸሎት ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ ጸሎቷም እንዲህ የሚል ነበር፤ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ፥ ከሥጋዬ ሥጋ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በቻለችህ ማኅፀኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለ መሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡››
+++ ጌታችንም ምን ሊያደርግላት እንደምትሻ ሲጠይቃት በስሟ ለሚማጸኑ፣ መታሰቢያዋን ለሚያደርጉ፣ ለችግረኛ ለሚራሩ፣ በስሟ ቤተ ክርስቲያን ለሚያንጹ፣ ዕጣን፣ ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን ለሚሰጡ ምሕረትን እንዲያደርግላቸው ጨምራ ጠየቀችው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በየካቲት ፲፮ ዕለት የገባላትን ቃል ኪዳን እንዲህ በማለት በመሐላ አጽንቶታል፡፡ ‹‹መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበአቡየ ወበመንፈስ ቅዱስ ሕያው፤ በራሴ፣ በአባቴ እና በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ፡፡››
የምሕረት ቃል ኪዳን የተሰጠበት ይህ ዕለት ታላቅ ነውና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቅት ታከብረዋለች፡፡ ቀድሞ ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነውና፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡
+++ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ የሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና ችግረኛ መርዳት ይገባናል፡፡
+++ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎት፣ አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
የጠንቋይና የደብተራ ልጆችን ውጭ ሀገር ውስደው የሚያሰለጥኑ ፈረንጆች!! ገጠመኝ እያልክ ለምን ታሾፍብናለህ ይሉኛል!! የፈረንጆቹን ጉድና ሴራ ተመልከቱ!! https://youtu.be/65hctlj6fSo?si=U905jHV6xF5Pp9bM
+1
+++ ሰላም ሰላም እንዴት ናችሁ ሁሉ መልካም ነው። እንኳን ለኪዳነ ምህረት አመታዊ ክብረበዓል የዋዜማው ዕለት በሰላም አደረሳችሁ። ሰሞኑን በጣም ከገረሙኝ ነገሮች አንዱ፤ የእኛን ቻናሎች የማዘጋትና ቻናሉን የማስቆም ሥራዎችን በብዛት በስም የምናውቃቸው ብዙ ተከታይ ያላቸው ቻናሎች ያውም ደግሞ መንፈሳዊ ቻናሎች፤ የእኛ ቻናል ለየት ብሎ የዲያብሎስን ሴራ በማጋለጡ ቻናላችንን ለማዘጋት በሚገርም ሁኔታ ርፖርት እያደረጉ ይገኛሉ እና ይኼ ድርጊታቸው ከዚህ በፍትም እንዲሁ ክ37ሺህ በላይ ቤተሰብ የነበረኝን ቻናል ለማዘጋት እንዲሁ አድርገው ነበር ነገር ግን እነሱ የፈለጉትን መንገድ ይጓዙ እኛም ጠላታችንን ማዋረዳችንን እንቀጥላለን። አሁን ደግሞ ትላንት የወንድማችንን ፍቅረ ገብርኤልን @user-eneho-tube የዩቱብ ቻናል በአባ ገብረኪዳን ላይ በሰራው ቪዲዮ በሚገርም ሁኔታ ቻናሉን ለማዘጋት እንቅስዋሴ ላይ ናቸው። ይኼ በጣም የሚያሳዝን ነገር ነው በእውነት ሰልዚህ ውድ ቤተሰቦቼ ሁላችንም አሁንም በደንብ መንቃት ያለብን ጊዜ ነው። ስለዚህ ሁላችንም ወደ ቻናሎቻችን በመግባት ቤተሰብ ይሁን ለብዙ ሰዎች እንዲዳረስ ሸር እናድርግ። መልካም ቀን ይሁንልን።
የፍቅረ ገብርኤል የዩትብ ቻናል፡ @user-eneho-tube @estifo2239 @haileG2239
+++ የእግዚአብሔር ፍቅር በልብህ ውስጥ ጠልቆ ከገባ ድካምህ ይጠፋል። ከእግዚአብሔርና ከትዕዛዛቱ የበለጠ ኃጢአትን የምትወድ ከሆነ ደካማ ትሆናለህ። ነገር ግን ፍቅሩ ወደ ልብህ ከገባ በውስጥህ ያለውን የኃጢአት ፍቅር አውጥቶ ይጥለዋል። ስለሆነም ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ለመቃወም ብርቱ ትሆናለህ።
+++ ንስሐ ማለት ፍላጎትን በፍላጎት መቀየር ማለት ነው። ይህ ማለት የእግዚአብሔር ፍቅር የአለምን ፍቅር ይተካል ማለት ነው። ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር የሚመሩህን ማንኛውንም ዓይነት መንፈሳዊ መንገዶች ሁሉ ተከተል። ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔርን ከሚወዱት ጋር ሁለም ተባበር። እርሱን ስለ ወደዱት ሰዎች የተጻፈውንም አንብብ! በመጨረሻም ምሳሌያቸውን ተከተል።
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ጉዳችን! በተዋቡና ባማሩ ቤቶች ውስጥ እየኖሩ ውስጣቸው ግን ባዶ! በዲያቆን ሄኖክ የተነገረ አስገራሚ መልዕክት! ወንጌል የምንማረው ለጠቅላላ ዕውቀት አይደለም! https://youtu.be/Ap22EBJKY-A
=> የጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ረድኤት በረከት፣ ቃልኪዳናቸው ይደርብን በእውነት። የጻድቁ አባታችን አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁን። እግዚአብሔር አምላካችን ሆይ ስለ ጻድቁ አቡነ አረጋዊ ብለህ ማረን ይቅር በለን። ሀገራችንን ኢትዮጵያንም ሰላም አድርግልን። አሜን
+++ ብዙዎች በሰርጋቸው ቀን "የአገራችን ባሕል ነው" የዘፈን ድግስን ያዘጋጃሉ። ወይም ደግሞ "ቤተሰብ እሺ አይልም" በማለት እንደሚቸገሩ ይናገራሉ። ነገር ግን ይህን የቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ ቃል ማስታወስ ይገባል።
=> "አስተውሉ! ጋብቻ ዝሙትን የምናጠፋበት መድኃኒት ነው። ስለዚህ በዲያብሎስ ስራ (በዘፈን) ጋብቻን አናቃልል። ከዚህ ይልቅ አሁን የሚያገቡ ሰዎች በቃና ዘገሊላ እንደ ኾነው ያድርጉ። በመካከላቸው ጌታችን ክርስቶስ እንዲኖር ያድርጉ። "እንዴት ይህን ማድረግ ይችላሉ? ብሎ የሚጠይቅ ሰው ሊኖር ይችላል። ካህናትን በመጥራት! 'እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል' ይላልና (ማቴ 10:40)። ስለዚህ ዲያብሎስን አርቁት። የሴሰኝነት ዘፈኖችን፣ የርኵሰት ዜማዎችን፣ ሥርዓት የለሽ ጭፈራዎችን፣ የሚያሳፍሩ ቃሎችን፣ ዲያብሎሳዊ ትርኢቶችን፣ ሁከቶችን፣ቅጥ ያጡ ሳቆችን፣ ሌሎች እነዚህን የመሰሉ አግባብ ያይደሉ ነገሮችንም አስወግዱ። በእነዚህ ፈንታም የጌታችን ክርስቶስ ቅዱሳን አገልጋዮችን ጥሩ ፣ በእነርሱም በእውነት ያለ ሐሰት ከእናቱና ከወንድሞቹ ጋር በሰርጋችሁ ላይ ይገኛል። " በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ወንድሜ እኅቴም እናቴም ነው" ብሏልና (ማቴ 12:50)።
=> አንዳንድ ሰዎች እንደዚህ ያሉ ተግሣጻትን ስለምናገርና የጥንት ባሕሎችን ስለማስቀር አሰልቺና አስቸጋሪ እንደ ኾንኩ አድርገው እንደሚያስቡ ዐውቃለው። ነገር ግን እነርሱ ስለ ተቃወሙኝ በፍጹም አልጨነቅም። እኔ የምፈልገው በእናንተ ዘንድ ተቀባይነትን ማግኝት ሳይኾን የእናንተን ጥቅም ነውና። ከዚህ ጥበብ ጥቅምን እንድታገኙ እንጂ እንድታመሰግኑኝ አልፈልግምና። ስለዚህ "ይህ ባሕል ነው" ብሎ አንድ ሰውስ እንኳ አይንገረኝ። ኀጢአት በድፍረት የሚፈፀምበት እስከ ኾነ ድረስ ባሕሉን እርሱት። ክፉ ሣራ የሚሰራባቸው እስከ ኾኑ ድረስ ባህሎቹ የቱንም ያህል ጥንታውያን ቢሆኑ ከእናንተ አስወግዷቸው። ክፉ ስራ የማይሰራባቸው ከኾኑ ግን ያልተለመዱ እንኳን ቢሆኑ ተቀበሏቸው።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
“ላገቡት” የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር
=> ባልና ሚስት አንድ መኾናቸውን ብዙ ጊዜ ስለ ተማራችሁት እርሱን አልደግምላችሁም፡፡ ከዚህ ተነሥቼ ግን ጥያቄ ልጠይቃችሁ፦ ከሰውነታችሁ ውስጥ አንዱ ሕዋስ ቢታመም ቆርጣችሁ ትጥሉታላችሁን? ከሕመሙ ይፈወስ ዘንድ የምትጥሩ አይደላችሁምን? ለትዳር አጋራችሁም እንደዚህ መኾን አለባችሁ፡፡ እንደዉም'ኮ፥ ከሰውነታችሁ ሕዋስ ውስጥ ያለው በሽታ አንዳንዴ ላይድን ይችላል፡፡ የትዳር አጋራችሁ ግን፥ ምንም ክፉ ቢኾንም ሊለወጥ ይችላል፡፡ በሰውነታችን ላይ የሚኖረው አንዳንዱ ችግር ለምሳሌ ልምሾ እጅ ወይም እግር ሥራ መሥራትን ሊከለክለን፣ በሌላዉ የሰውነታችን ክፍል ላይ ጫና ሊያሳድርብን ይችላል፤ ነገር ግን ይበልጥ እንክብካቤ እናደርግለታለን እንጂ ቆርጠን አንጥለዉም፡፡ ታዲያ መዳን ለማይችለው ሰውነታችን ይህን ያህል እንብካቤ እያደረግንለት ሳለ፥ የመዳን (የመለወጥ) ዕድል ያለው አካላችንን (ባለ ትዳራችንን) መቁረጥ (መፍታት) እንደ አማራጭ ማስቀመጣችን እንዴት ብናብድ ነው? ታዲያ ሁላችንም ልናስብበት የሚገባ ወሳኝ ተግሳጽና ምክር ነው ቤተሰቦቼ!!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
የቤት አከራዮችና ተከራዮች የመናፍስት ፈተና!! የቤታዮ እህታችን አስገራሚው ጥያቄ!! ጸሎትና ስግደት ጀምሮ ማቆም ያለው ፈተና!! #ethiopia #ጸሎት #ንቁ https://youtu.be/OnYN7dmSvO0
