ar
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

الذهاب إلى القناة على Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

إظهار المزيد
2 280
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+117 أيام
+3830 أيام
أرشيف المشاركات
የመምህር ግርማ ገጠመኝና ፈተናዎቸ || ክፍል 1 መናፍስት ተንኮለን ከሰው ልጅ ሲማሩ || ዕድልና ራዕን የሚወጉ አጋንንቶች #ethiopia #ebstv 😱😭💥🔥🚩 https://youtu.be/TAxpwR6c--c

ሰይጣን ማንነታችንን የሚያጠቃው እንዴት ነው? የዲያብሎስ ማታለያዎች ሰይጣንን አስርቡት || የጥርጣሬ መንፈሶችና የእምነት ኃይል #ethiopia 😭😱🔥 https://youtu.be/ODLu8Z-l7Cg

ዲያቆኑ ከመናፍስቱ ጋር ያደረገው ግብግብ ይሄንን ማን ያምናል ድንቅ ምስክርነት! ጽንስ የሚያጨናግፉ፣ ትዳር የሚዘጉ አጋንንቶች #ethiopia 😱😭🔥💥 https://youtu.be/Vm85fixXbGM

የአንዳንድ አገልጋዮች ወጣ ያሉ ጠባዮችና ባሕሪዎች || ምዕመኑን በመተት የሚያስሩ ለፍቅረ-ንዋይና ለሥልጣን ያጎበደዱ || ራዕይ አልባ የሆነው አገልግሎት 😱😭 https://youtu.be/b9TVvTRqpeU

አወግዝሻለሁ አሉኝ! የወይራ ዘይት ባርኩልኝ ብላቸው! || የአመቺሳና የጬሌ ልጆች እንዲህ ናቸው! || ካልሰገድክልኝ እገድልሃለሁ ይለኛል መንፈሱ! #ebs 😭😱 https://youtu.be/Av39SLNg9UE

ንቁ! ሰይጣን በቅዱስ ጳውሎስ ሕይወት ውስጥ ሲያደፍጥ ቅዱስ ጳውሎስ አጋንንት ነበረበት ወይ? መምህር ግርማ ወንድማ ካስተማሩት #ethiopia 😱😭🔥 https://youtu.be/4TLuFlHb3d0

አጋንንት እኛ ብንረሳቸው እነሱ አይረሱንም! || የአንድ ቀን ሱባኤና ጥቅሙ ይሄ ነው! || ወንድማችን እሸቱ ምን ገጠመው? | የአቡነ ሐራ ድንቅ ተዓምር 😱😭💥 https://youtu.be/q0WRfKXT9ZI

የዕሼ ተዋህዶ #ቁጣ ና በአደባባይ አሳብድሀለሁ ብሎ የዛተው መጨረሻ https://youtu.be/mncmY1k0nHM

የዕለቱ የስንክሳር ምንባብ ጥቅምት 26 | ጻድቁ አቡነ ሐብተማሪያም | ቅዱስ ያዕቆብ | ቅዱስ አግናጥዮስ #ebstv #ethiopia #love #orthodox https://youtu.be/XciAQcVQXvc

መምህር ግርማ ሁለት ዓይነት ጸጋ አላቸው! | የደብተራው ሴራ ሲገለጥ መንጫጫት ጀመሩ | የምዕመናን የመናፍስት ውጊያ አረዳድ | ከመምህር ተስፋዬ የተወሰደ 😱😱 https://youtu.be/mDkZ2dZcZUI

በመምህር ተስፋዬ ትምህርት የአስማትና የጥንቆላ ልምምድን አቁምያለሁ ግለወሲብን በተደጋጋሚ እፈጽም ነበር በዲቁና ውስጥ የመናፍስቱ ሴራ #ebstv 😭😱 https://youtu.be/4Duo9gIFyD4

"እናንተስ ብትሆኑ ምን ታደርጋላችሁ?" => እህት ወንድሞቼ እኔ ደግሞ ዲቁና የተቀበልኩት በልጅነቴ ነው በርሱ መሀል የቅዳሴ ትምህርት በስርዓት ስላልተማርኩ ለተወሰነ ጊዜ ከቤተ ክርስቲያን ርቄ ነበር እና 8ኛ ክፍል ስደርስ ግብረ አውናን ማድረግ ጀመርኩ ከቀን ወደ ቀን ሱስ እየሆነብኝ መጣ ነገር ግን እሄን ያህል ሃጥያት አይመስለኝም ነበር። ከዛን የቅዳሴ መምህር ወደ ደብራችን ሲመጡ ቅዳሴ መማር ጀመርኩኝ ከዛም አልፌ ምስጢር አይቼ መቀደስ ጀመርኩ ለጊዜው የዚህ ነገር ሱስ ቀለል አለልኝ እና መልሼ ሱስ ውስጥ ገባሁ። => የሚገርመው በዚህ ላይ ደግሞ የአስማት ልምምድ ውስጥ ገባሁ ሰውን ለመጉዳት ምኞት ስላልነበረኝ ነጭ አስማት ነው ወይም ጥበብ ነው ሚባሉትን ለትምህርት ህልም ለማየት ለብር እደግም ነበር አንዳንድ በአስማቱ ውስጥ ያሉ ሰዎች እስኪገረሙብኝ ድረስ የሀገራችን ጥበብ ብዬ ለሁሉም ማብራርያ ሰጣለሁ እና አንድ ቀን የአስማት መፅሀፍ ስመለከት አንዲት የአስማት ቃል አየሁ እዚ ጋር ቃሉን መጥቀስ ባያስፈልግም መፅሀፉ ይሄንን ቃል ለ7 ቀን ብትደግም ቅዱስ ገብርኤል ወዳንተ ይመጣል ሮሃንያውያን ጭምር ይላል ይሄንን ሳይ ውስጤ ሽብር አለ ለራሴ እውነት ቅዱስ ገብርኤል ቅዱሳን ጨርቄን ማቄን ሳይሉ ቤት ንብረት ዘመድ ወገናቸውን ትተው እንደ አራዊት በበረሀ እየኖሩ ጥሬ እየቆረጠሙ አንተን ያያሉ እኔ ኃጥዑ በኃጥያት ተጨማልቄ ላይህ እችላለሁን? ብዬ ቃሉን ስወጣ ስገባ እደጋግመዋለሁ ገብርኤል ገብርኤል ይላል ውስጤ ከዛን እሱን ለማየት ስመኝ የሱ ፍቅር አደረብኝ እና በዕለተ ቀኑ ሌሊት 9 ሰዐት ተነስቼ ውዳሴ ማርያምን እና መልክአ ገብርኤልን ሻማ አብርቼ ፀልያለው የሚገርመው ከአለማወቄ የተነሳ ልተኛ ስል አስማቱን ደግሜ ውዳሴ ማርያምን አድርሼ ነው ምተኛው በጣም ብዙ ነገር አለ ብፅፈው የማያልቅ እናም እግዚአብሔር መልካም ፈቃዱ ሆኖ አስማት ልለቃቅም ዩቱብ ሳይ ከኔ ህይወት ጋር ትንሽ ሚመሳል የመምህር ተስፋዬን ገጠመኝ አየሁ ለጓደኛዬም አሳይቼ አስማቱን ለመተው እራሴን አሳመንኩ እና መንፈሱ ሌሊት ያስፈራራኝ ሁላ ነበር እውነት የምታመልጠኝ ይመስልሀል ይለኝ ነበር.. => እኔም ተስፋ ሳልቀርጥ ስግደት ፆም አበዛ ጀመር የሱሱ ነገር እንዳለ ነው። ከዛን አንድ ቀን የቅዱስ ገብርኤል ወራዊ በዓል ላይ እንደ ልማዴ ሌሊት 9 ሰዐት ሻማ አብርቼ ውዳሴ ማርያም ደግሜ መልክአ ገብርኤልን ልደግም ስል ሰውነቴ መቆም አቅቶት እጠማዘዝ ጀመር እንደምንም ሆኜ መልኩን አድርሼ ወደ አልጋዬ ሄጄ ተኛሁ እና በሕልሜ እዛው ቤቴ ቆሜ ድግምት ይሁን ፀሎት ቆሜ ስደግም ሰይጣን ከፊት ለፊቴ ጥቁር ተራራ መስሎ በኃል እየሮጠ ሲመጣብኝ ቅዱስ ገብርኤል በብርሃን ፍጥነት ከመሀላችን ገብቶ ብልጭ ሲል እራሴን ሳትኩ እና ስነቃ ቅድም ተኝቼ ነበር ግን ስነሳ እራሴን እንደሳትሁበተ አኳኋን እራሴን አገኘውት፤ በስመአብ ብዬ ደሞኮ ጨለማ ነው እስኪ ባትሪ ላብራ ብዬ ላበራ ስፈልግ ከኋላዬ ባትሪ ከፊት ለፊቴ ባለች ስዕለ ማርያም ላይ እየበራ ነበር እንዴ ባትሪ እየበራኮነው ብዬ ዞር ስል ሁለት ሰዎች ተደጋግፈው ቆመው አንደኛው ነው ባትሪውን አብርቶ ያለ እና ድጋሚ እራሴን ሳትሁ እና ከዛን በኋላ እየተጋሁ የአስማቱን ነገር ሙሉ ለሙሉ በእመቤቴ እና በቅዱስ ገብርኤል እርዳታ አቆምኩት። => ቅዱስ ገብርኤል አባቴም ብዙዎቹን ርኩሳን መናፍስት አሰረልኝ እናም ይሄ ሱስ ቀረ እሱን ለማቆም ማልኩ ተገዘትኩ እግዚአብሔር ሆይ ካሁን በኋላ ካደረኩ ይቅር አትበለኝ እስከማለት እንዲ እየበደልኩህ ከምኖር እራሴን ባጠፋስ እስከምል ድረስ እያለቀስኩ እንኳ ያን ነገር እፈፅም ነበር የእመቤቴን ስዕል ስለበደልኳት ቀና ብዬ አላይም ነበር ባያትም ስቅስቅ ብዬ አለቅሳለሁ እናም በዚህ ነገር አራት ዓመት ከተሰቃየሁ በኋላ አንድ ቀን እሄን ነገር እያደረኩ አይምሮዬ ውስጥ ከዚህ ነገር እና ከቅድስት ድንግል ማርያም ምረጥ የሚል ጥያቄ ሲመጣብኝ እመቤቴን ብዬ ደንግጬ አቆምኩት አቆምኩት ለማቆም ያላደረግኩት ነገር አልነበረም ንስሀም በተደጋጋሚ እገባ ነበር ግን ድጋሚ እወድቅ ነበር ከዚህ ጥያቄ በኋላ ግን እሄ ሱስ ላያዳግም ሄደ እመብርሃን ክብሯ ይስፋ አሁንም እመብርሃን እንደ በደሌ ሳይሆን እንደ ቸርነቷ ምንም ሳታጓድልብኝ እያኖረችኝ ነው። => እኔ ግን የጨነቀኝ ለንስሀ አባቴ ስናዘዝ ያለውን ነገር አብራርቼ ነገርኳቸው ስልጣኔን አፍርሼ እየቀደስኩ ያለሁ ነው ሚመስለኝ እንዲ እንዲ አድርጌ መቅደስ መቆሙ እራሱ ከብዶኛል ብዬ ነገርኳቸው እሳቸው ግን ቀኖና ሰጥተውኝ ቅዳሴ አልከለከሉኝም ግን እኔ ይጨንቀኛል በጣም እስከ ቅርብ ድረስ እንዲህ ያለ ከባድ ኃጥያት መሆኑን አላወኩም ነበር እና እግዚአብሔር እንዲምረኝ ምህረትን ለምኑልኝ እስኪ እመብርሃን እንድትመራኝ እና ለመሸሽ ላለመቀደስ እሞክራለሁ ግን ንስሀ ገብቼ እቀድሳለሁ አሁንም ግን በቃ የንስሀ አባቴ እንድቀድስ ስለፈቀዱልኝ አልፎ አልፎ እቀድሳለሁ ግን በቃ ውስጤ ይጨነቃል እና ከመቅደስ ውጪ ባለው አገልግሎት በቅኔ ማኅሌቱ በደንብ ተምሬ ባገለግልስ እላለሁ እሱንስ ማገልገል አይፈቀድልኝ ይሆን። => ዲያቆን ነኝ ለማለት አፍራለው ግን ያስተማሩኝ አባቴ በረከታቸው ይደርብንና መላእክት እስከማየት የደረሱ የበቁ አባት ነበሩ በጣም ተሰቃይተው ብዙ ግፍ እየተቀበሉ እንዳስተማሩኝ ሳስብ ዲያቆን ነኝ እላለሁ እናም አሁን ላይ ቅዳሴን ባልተውም ከስንት አንዴ ከቀደስኩ ነው ማኅሌት ግን በጣም ነው ምወደው በተቻለኝም አቅም ለማገልገል እሞክራልሁ እስኪ እህት ወንድሞቼ ለኔ ከኃጥያተኛም አልፌ ግፈኛ በደለኛ አረመኔ ለሆንኩት ወንድማችሁ ምን ትመክሩኛላችሁ? በኔ ቦታስ ብትሆኑ ምን ታደርጋላችሁ? #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

መምህር ግርማ ይናገራሉ እኔን ሉሲፈር ያደርጉኛል!! የውስጥ አይናቸው ያልተከፈቱ አገልጋዮች! የአባቶች በአዚም መንፈስ መጠቃት #ethiopia 😱😭🔥🚩 https://youtu.be/cDtZ5dqcEEY

«ሰው ለሰይጣን ጥብቅና የቆመበት ዘመን ላይ ደረስን» https://youtu.be/Os7EiG2ddrY

«ሁላችሁም አንብቡት!» ሰላም ወንድሜ እንዴት ነህ እኔ እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ነኝ። ጥያቄዬን ከመጠየቄ በፊት ሰለኔ አንዳንድ ነገሮች ልንገርህ። እኔ የተወለድኩት ቤተሰብ በከፍተኛ ሁኔታ በመናፍስት የሚፈተን ቤተሰብ ነው። እኔ ባልደርስበትም በአባቴ በኩል ያሉት አያቶቼ ጠቋር፣ አዳል ሞቲ እና ወሰን ገላ የተባሉ ዛሮችን ያመልኩ እንደነበር ሲወራ ሰምቻለሁ በተጨማሪም አባቴ ጥበብ ነው እያለ አውደ ነገስት ስራስር ምናምን በሚባሉ ነገሮች የሚያምን እና ከልጅነት ጀምሮ እኔና ወንድሞቼን ቅጠላ ቅጠል ስራስር እያበላን ነው ያሳደገን። እናቴ ደግሞ ደግ ሀይማኖተኛ እና ለእውነት የምትቆም ሴት ናት በቤታችን የቅዱስ ገብርኤልን ዝክር በየወሩ እስከ አሁን ይዘከራል። እና እንዲህ እንዲህ እያለ 13 አመት ሲሞላኝ ጉርምስና መጣና ፊልም ቤት እየሄድኩ የተለያዩ ፊልሞችን ለምሳሌ:- Spartacus የሚባል ዝሙት የበዛበት ፊልም አይ ነበር በዚያው porn ማየትም ለመድኩ። አንድ ቀን እንደዚህ porn አይቼ ለመጀመሪያ ጊዜ ግለ ወሲብ ፈፀምኩ እና ከዚያ በኋላ የማይለቅ ሱስ ሆኖብኝ ቀጠልኩ። እና ህይወት እንደዚህ እንደቀጠለ 15 አመት ሲሆነኝ በሰፈራችን አንድ ቤተክርስቲያን ነበር እዚያ የአብነት ትምህርት መማር ጀመርኩ በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን ግለ ወሲብ እፈፅም ኋጢአት እንደሆነም አላቅም ነበር። አንዳንዴ ግለወሲብ ፈፅሜ ለአብነት ትምህርት ቤተክርስቲያን የምሄድበት ጊዜ ነበር እና በዚያ መሀል በአብነት ትምህርቱ በጣም ጎበዝ ስለነበርኩ እና የሚያስፈልገውን ትምህርት ስለተማርኩ ዲቁና እንድቀበል የኔታ አዘዙኝ። ይሄን ለቤተሰብ ስነግር ተቃወሙኝ ሳስበው እግዚአብሔር በነሱ አድሮ እንዳልዳቆን እያስጠነቀቀኝ ነበር መሰለኝ ግን እኔ እምቢ ከማን አንሳለሁ ብዬ ዲቁና ተቀበልኩኝ። ከዚያ ቤተክርስቲያን ታቦቱ የሚቀመጥበት መቅደስ ውስጥ ገብቼ ባልቀድስም እና ምስጢር ባላይም በማህሌቱ ከካህናቱ ጋር በተማርኩት እውቀት መሰረት አገለግል ነበር። እና በዚህ መሀል እቤታችን wifi ወንድሜ አስገባልን እና youtube ስመለከት የመምህር ተስፋዬን ገጠመኝ የሚለውን program አገኘሁት እና ማዳመጥ ጀመርኩ። እና ስለ መተት ዛር አይነጥላ ምናምን ብዙ ታሪኮች ሰማሁ ብዙዎቹ የራሴ ታሪኮች ነበሩ። የሚገርምህ ገጠመኝ መስማት ከመጀመሬ በፊት አሰማት ድግምቱ ጥበብ ይመስለኝ እኔም እነዚህን ነገሮች ለመሰብሰብ እሞክር ነበር እና ገጠመኙን ስሰማ ደንግጬ የነበሩትን የአስማት ፅሁፎች ሁሉ አቃጠልኩኝ ስግደት ፀሎት ለማድረስ መታገል ጀመርኩ በዚያ መሀልም ስለ ግለወሲብም ስለሰማሁ በቤተክርስቲያን ከካህናት ጋር ማገልገሉን አቁሜ እንደ ምዕመናን በቅጥር ጊቢው ውስጥ ብቻ ማስቀደስ ጀመርኩ። ጓደኞቼም አንተ ልጅ ዲቁናህን አፈረስህ ወይ ለምንድን ነው የማታገለግለው ይሉኝ ነበር። እኔ ግን ለመናገር ስለሚያሳፍረኝ ዝም እል ነበር። እና አንዴ እየወደቅሁ አንዴ እየተነሳሁ አዚህ ደርሻለሁ አሁን የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነኝ በቻልኩት አቅም በአምልኮት ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር እየጣርኩ ነው። እግዚአብሔር ይመሰግን ፈጣሪም ደስ የሚል ሰላም ያለው ህይወት እንድኖር እያረገኝ ነው። ግን የኔ ጭንቀት በዙሪያዬ ያሉ ጓደኞቼ እና ቤተሰቦቼ ዲያቆን እንደሆንኩ ነው የሚያስቡት እንዳልነግራቸው ደግሞ ስራዬ ስለአሳፈረኝ ፈራሁ በዚያ ላይ እግዚአብሔርንስ እንዴት ልካሰው። ስለዚህ ጉዳይ እንድታማክረኝ ነበር ወንድሜ። ውድ ቤተሰቦቼ እስቲ የእናንተን አሳብ ጻፉልኝ በእውነት! አያችሁ የእኛ ትምህርት ዋናው አላማ ሰዎች ከዚህ ክፉ የመናፍስት ልምምድ እንድላቀቁ ማድረግ ነው። #እንንቃ_ወገን!! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ግለ ወሲብ ሱሰኛ ሆነዉ ትዳርን እስከ ማፍረስ ይደርሳሉ። ታዲያ እነዚህ ሰዎች ከጊዜ በኋላ ለራሳቸዉ የተሳሳተ አመለካከት ይኖራቸዋል ራሳቸዉን የሚጠሉ ከሰዉ ሁሉ ያነሱ አድርገዉ ስለሚያስቡ የግለ ወሲብ ሱሰኛ ከሆኑ በኋላ ለሥራቸዉ ለትዳራቸዉ ለሕይወታቸዉም ጭምር ግድ የማይሰጣቸዉ ይሆናሉ። ፮/ ግለ ወሲብን ለማቆም መቸገር፤ ግለ ወሲብ አንዴ ሱስ ከሆነ በኋላ በራስ ጥረት ማቆም ከባድ ይሆናል። ምክንያቱም መናፍስቶቹ አዕምሮ ዉስጥ የወሲብ ምስል ቀርጸዉ ስለሚያስቀምጡ በፈለጉበት ጊዜ ትዉስታዎችን በማምጣት ግለ ወሲብን ስለሚያስፈጽሙ ለእነዚህ ሰዎች ከዚህ ሕይወት መዉጣት ዳገት ይሆንባቸዋል። ፯/ ግለ ወሲብ ለኃጢአተ ሰዶም ይዳርጋል የሉሲፈር መንፈስ ኃጢአተ ሰዶምን ኢትዮጲያ ዉስጥ ማስፋፋት አጥብቆ የሚሻና በሰዉ ልጆች ዘንድም መመለክ የሚፈልግ ለትዉልድ አደገኛ የሆነ መንፈስ ነዉ። በነጮችና በትዉልደ ኢትዮጲያዊያን ዘንድም በደም ፊርማ ነፍሳቸዉን ሸጠዉለት እየተመለከ ያለ መንፈስ ነዉ። የሉሲፈር መንፈስ በግለ ወሲብ አሳኮ ሲቆራኝም በአንድ ቀን ዉስጥ ከ4:5 ጊዜ በላይ ግለ ወሲብን እያስፈጸመ አቅምን በማዳከም ግለ ወሲብን ለሰዶማዊነት ቅድመ ልምምድ ተጠቅሞ ከዚህ ሕይወት ዉስጥ መቼዉንም መዉጣት እንደማይችሉ እያረጋገጠላቸዉ እነዚህን ሰዎች በራሳቸዉ ላይ ተስፋ እንዲቆርጡና እግዚአብሔር እንደጠላቸዉ ጥቅም አልባ እንደሆኑ በመስበክ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ የተመሳሳይ ፆታ ፍላጎት አሳድሮባቸዉ ወደ ግብረ ሰዶም ሕይወት ይወስዳል፡፡ #እንንቃ_ወገን!! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«መናፍስት እኛን የግለወሲብ ጥገኛ ለማድረግ የሚጠቀሙት ስልቶች» ፩/ ግለ ወሲብ ኃጢአት እንዳልሆነ በማሳሰብ አይነጥላ ከማህፀን ሲቆራኝ ግለ ወሲብን ገና በለጋ እድሜ ያለማምዳል። መናፍስቶች ገና በማለዳዉ ሲቆራኙ ነገሮችን ከመልካምና ከክፋት አንፃር ለይተን እድናመዛዝን አይፈቅዱም፤ እዛዉ ክፋታቸዉ ዉስጥ ቆልፈዉ በማስቀመጥ ኃጢአትን መልካም እንደሆነ እየመከሩ የመዳኛ ጊዜ እስኪያልፍ ጥንቃቄ በተሞላ ስልታቸዉ ይስራሉ እንጂ። የአይነጥላ መንፈስም ግለ ወሲብ ሲያለማምድ ስለዚህ ተግባር ክፋቱንና አስከፊነቱን ምንም መረጃ እንዳይኖር በማሸሽ (መንገድ ይዘጋጋል) ግለ ወሲብ ኃጢአት እንዳልሆነ ኃጢአት የሚሆነዉ ከትዳር ዉጪ የሚደረግ ግንኙነት እንደሆነ ተቃራኒ ፆታ ብትቀርቡ በዚህ ኃጢአት ልትወድቁ እንደምትችሉ እያሳሰበ ትዳርም እንዳትይዙ የትዳር ጥላቻ እያሳደረ ራሱ ባለማመደዉ የኃጢአት አዘቅጥ ዉስጥ አስቀምጦ አዕምሮን አደንዝዞ በመያዝ ኃጢአት ይሁን አይሁን እስካልታወቀ ድረስ ከተቃራኒ ፆታ እያሸሸ የግለ ወሲብ ጥገኛ አድርጎ የሚያስቀምጥ ሴረኛ ነዉ። ስለዚሁም ነዉ! አንዳንድ ሰዎች በዚህ መንገድ ካለፉ በኋላ ይሄ ጸያፍ ተግባር ኃጢአት እንደሆነ ባለመረዳት ጥያቄ የሚያነሱት ይሄ ጥያቄያቸዉ የሚያሳየዉ መንፈሱ እነዚህ ሰዎች ምን ያህል አደንዝዞ እንደያዛቸዉና በራሱ የክፋት ዓለም ዉስጥ አስቀምጧቸዉ እንደነበረ የሚያመላክት ነገር ነዉ። ግለ ወሲብ ኃጢአት ከመሆኑም አልፎ በእግዚአብሔር ዘንድ የሚያስቀስፍ ኃጢአት ነዉ! እግዚአብሔር በአንድያ ልጁ በምህረት ኪዳን ባይጎበኘን ኖሮ ስንቶቻችን የሞት ቅስፈት በመጣብን ነበረ። ግብረ አዉናን እግዚአብሔር የማይወደዉና የሚጸየፈዉ ትልቅ ኃጢአት ነዉ! በዘፍጥረት ክታብ ላይ አዉናን ዘሩን በምድር ላይ በማፍሰሱ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀስፏል (ዘፍ፤38፤9:10) ዛሬም ዲያቢሎስ ይሄንን የሚያስቀስፈዉን ኃጢአት ነዉ እንግዲህ መልካም እንደሆነ በማሳየት ከመልካም መንገድ የሚያስፈነግጠዉ። ሌላዉ በተክሊል ለማግባት የሚያስቡም አሉ እርኩሱ መንፈስ ለእነዚህ ሰዎች ድንግልናቸዉ እንዳልተነካ ስለሚያሳስባቸዉ ጥያቄዉን ያነሳሉ። የጠላት ሴራ እንዲህ ነዉ፥ በኃጢአት ላይ ኃጢአት በማደራረብ ከእግዚአብሔር ጋር ማጋጨት የሥራ ድርሻዉ ነዉ። ግለ ወሲብ የፈጸመ ሰዉ የድንግልና ሕጉን በጠላት ምሪት ስለሚያፈርስ በተክሊል ማግባት አይችልም። ፪/ በተቃራኒ ፆታ ዘንድ እንዳትወደዱ በማድረግ መናፍስቶች ሰዉ ለማጥፋት ሲሆን እጅና ጓንት ሆነዉ በመረዳዳት ክፉ ስራቸዉን ይሰራሉ። ይሄ ሴረኛ ጠላት ተቃራኒ ፆታ እንዲቀርብ ስለማይፈልግ ግንባር ላይ ተቀምጦ ብቸኝነት እስኪሰማችሁ ድረስ ተቃራኒ ፆታን እያባረረ ከሰዉ እንድትርቁ ያደርጋል። ማንም እንደማይወዳችሁ፣ መልከ ጥፉ እንደሆናችሁ፣ ብትለብሱም ብታጌጡም የማታምሩ ፍጥረት እንደሆናችሁ፣ መስታወት ፊት አቁሞ በማሳየት ራሳችሁን እንድትጠሉና ከሰዉ ርቃችሁ የብቸኝነት ሕይወት እንድትመሩ ይመክራል። ከዚህ በኋላ ተስፋ ቆርጣችሁ በዚህ ጉዳይ ከማንም ጋር ላለማዉራት ወስናችሁ ሕይወታችሁን መምራት ስትጀምሩ የዝሙት መንፈሱ በተራዉ ይመጣና ሥራዉን ይጀምራል። ወደ ተቃራኒ ፆታ በዝሙት ዓይን እያስመለከተ በፍትወት እንድትቃጠሉ እያደረገ ያያችሁትን ሁሉ ለፍትወት እንድትመኙ ገፋፎቶ ወደዚህ ሕይወት ያሰማራል አንዴ በወጥመዱ ዉስጥ ከገባችሁ በኋላ በዚህ ጸያፍ ተግባር ተጠምዳችሁ እንድትኖሩ ያደርጋል። ፫/ በትዳር ሕይወታችሁ ደስተኛ እንደማትሆኑ በማሳሰብ መናፍስቶች ከኃጢአት አዘቅጥ ዉስጥ እንዳንወጣ ስለሚፈልጉ አሳማኝ በሆነ ምክንያት አስረዉ ያስቀምጣሉ። አይነጥላ ይሄንን ሀሳብ አዕምሮ ዉስጥ ለመቅረጽና ነገሩን በእርግጠኝነት አምናችሁ እንድትቀበሉ ከሌሎች መናፍስት ጋር መናብብ ይፈጥራል። መናብብ ማለት ቅዱሳን ሆኑ እርኩሳን መናፍስት በእኛ ገሐዳዊ ዓለም እርስ በእርስ የሚያደርጉት መግባባት ማለት ነዉ። እርኩሳን መናፍስት በማይገመት መልኩ አዕምሮን በክፉ ሀሳባቸዉ ይመርዛሉ። ይሄ ኩፉና ሴረኛ መንፈስ ከሌሎች መናፍስት ጋር በመናበብ ስለ ትዳር አስከፊነት ከልዩ ልዩ ባለትዳሮች እንድትሰሙና በተለይ በሩካቤ ጊዜ ያለዉን ችግር ግልጥ በሆነ መንገድ በተገኘዉ አጋጣሚ ሰዎች እንዲያወሩላችሁ እያደረገ በእናንተ ልብ ዉስጥ ፍርሀት ጨምሮ በአዕምሮ ዉስጥ የራሱን ምስል በመቅረጽ ገና ትዳርን ሳታዉቁት እንድትፈሩ ያደርጋል። በዚሁ በረከሰ ሕይወት ደስተኛ ሆናችሁ መኖር እንደምትችሉ በማሳሰብ የግለ ወሲብ ጥገኛ የሚያደርግ ሴረኛ የሆነ ጠላት ነዉ። ስለዚህም ነዉ በቤታችሁ ዉስጥ የጸሎት ቦታ አዘጋጅታችሁ የመንበርከኪያ ጊዜ ይኑራችሁ ጠላት ዲያቢሎስ ላይ ንቁ የሚባለዉ። ፬/ ዓይነ አፋር በማድረግ መናፍስቶች ሥራቸዉን የሚሰሩት በዕቅድና በዓላማ ነዉ። አይነጥላ ወንዱንም ሴቷንም ዓይናፋር በማድረግ ከሰዉ እያሸሻቸዉ የብቸኝነት ሕይወትን ያለማምዳቸዋል። አይነጥላ ዓይናፋር የሚያደርጋቸዉ ሰዎች ከሰዎች ጋር ሕብረት ማድረግ የማይችሉ ከቤተሰብ ጋር እንኳን ሳይቀር ለመግባባት የሚቸገሩ ዝምም ያሉ ፍጡሮች ስለሚሆኑ ተግባቦታቸዉና ግንኙነታቸዉ ከቴክኖሎጂ ጋር ብቻ ይሆናል። አብዛኛዉ ድህረገጾች የዲያቢሎስን ሴራ የሚስፋፋበት በመሆኑ መንፈሱ ለእነዚህ ሰዎች የኃጢአት መንገድ ለማሳየት አይቸገርም። በእርግጥ የቴክኖሎጂ መስፋፋት ጥቅም ቢያሰጠንም የብዙሃኑን ሕይወት እያቃወሰ በቁም እየገደለ ያለዉ የቴክኖሎጂ መስፋፋት ነዉ። መንፈሱ ሲታዩ ቀላል በሚመስሉ ሰዉነትን ሲዋሃዱ ግን ከመርዝ በላይ ገዳይ በሆነ ሴራዎቹ ሕይወት መጠልሸት ይጀምራል፤ በተንቀሳቃሽ ስልኮች በሚታዩ የወሲብ ፊልሞችና በልበ ወለድ መፅሐፍቶች ዉስጥ ለዝሙት የሚጋብዙ ቃላት፤ ሀገርኛ ፊልሞቻችን ላይ በሚታዩ አላስፈላጊ ተግባራት መሰረት በማድረግ [አጋጣሚዎችን በመጠቀም] እነዚህን ክፉ ምግባራት በማሳየትና በማስነበብ የሰዉ ልጆችን ሕይወት ማበላሸት ይጀምራል። የአይነጥላ መንፈስ የኃጢአት መንገዶችን ለማለማመድ አንድ ሰከንድ ከበቂዉ በላይ ነዉ። የወሲብ ስሜት ቀስቃሽ የሆነዉን ምስል ወይም ፅሑፍ አዕምሮ ዉስጥ በመቅረፅ በትዉስታ መልክ እያመጣ ግለ ወሲብ ያለማምዳል። ከዚህ በኋላ እራሱ አጥፊ እራሱ ወቃሽ ሆኖ ቁጭ ይልና ኃጢአተኛ ነህ እግዚአብሔር ጠልቶሃል፣ እንዴት እንዲህ ታደርጋለህ ወዘተረፈ… የሚሉ ወቀሳዎችን እያስከተለ የግለ ወሲብን ፍላጎት ከፍ በማድረግ ከበፊቱ በበለጠ መንገድ ሚስጥራዊና ባይተዋር እያደረገ ጥንቃቄ በተሞላ መልኩ የፖርኖ ግራፊ ፊልምና የግለ ወሲብ ጥገኛ ያደርጋል። ፭/ ለስንፈተ ወሲብ በመዳረግ የዲያቢሎስ ትልቅ ዓላማ ዓለምን በአንድ (globalization) ስር ጠቅልሎ መያዝ ስለሆነ በማንኛዉም መንገድ የኃጢአት መንገዶችን ያስፋፋል። አብዛኞቻችን በሕይወታችን ዉስጥ ለገጠመን ችግር መፍትሔ ፍለጋ ወደ ዓለም እንጂ ቅድሚያ ወደ እግዚአብሔር አናመለክትም። ሕክምናዉም የተሳካ የሚሆነዉ የእግዚአብሔር ፍቃድና እርዳታ ሲጨመርበት እንደሆነ ግንዛቤዉም የለንም ቢኖረንም አናደርገዉም። የእምነት ኃይላችን የተዳከመ ስለሆነ ይሄ ተግባራችን ለመናፍስቱ ሴራ አመቺ ሆኗል። ምክንያቱም ሐኪሙን እንደ መሳሪያ ተጠቅሞ ኃጢአትን ያለማምዳሉና። አይነጥላ፤ ዛር፤ የዝሙት መንፈስና ሌሎችም መናፍስቶች ጭምር የወንዶች ሀፍረተ ሥጋ ላይ በመቀመጥ ለስንፈተ ወሲብ ይዳርጋሉ መፍትሔ ፍለጋ ወደ ሐኪም በሚሄዱበት ጊዜም ወሲብ ቀስቃሽ የሆኑ ፅሑፎችን እንዲያነቡና ፖርኖግሪ ፊልሞችን እንዲመለከቱ ከባለሞያዉ ጥቆማ ስለሚያገኙ ወደዚህ ሕይወት በቀላሉ ይገባሉ። ከጊዜ በኋላ የ

መናፍስት እኛን የግለ ወሲብ ጥገኛ ለማድረግ የሚጠቀሙት ስልቶች ግለ ወሲብና በተክሊል ማግባት ግለ ወሲብ ወይም ሴጋ ምንድነው? #ethiopia 😱😭💥😱 https://youtu.be/5sPwT1Mij8M

photo content
+2

«ልብ ብለው ያንብቡት!» => ዛሬ የገድለ-ዲያብሎስ የዝና ታሪክ፣ የኃጢአትና የሞት ዜና መረጃ በበዛበት ዓለም ውስጥ እንገኛለን፡፡ ኃጢአት፤ ለዚህ ዘመን ሰው የመጀመሪያው ዕውቀትና የሥነ-ምግባሩ መግለጫ በመሆን፤ ጸሎት ጽድቅንና እውነትን የባርነት መንገድ አድርጎ እንዲያይ፤ የትውልዱ የውድቀት ጉዳይ ፈጻሚ የመሆን ዕጣ ድርሻውን ከዲያብሎስ ተምሯል፡፡ ‹‹በጎ እያደረጋችሁ፣ የማያውቁትን ሞኞች ዝም ታሰኙ ዘንድ እንዲህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነውና፤ አርነት ወጥታችሁ እንደ እግዚአብሔር ባሪያዎች ሁኑ እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ፡፡›› (1ጴጥ 2÷15-16) ክፉ መናፍስት፤ በሕይወታችንና በኑሯችን ውስጥ፤ ሥፍራና ቦታ አግኝተው፤ በውድቀት አዙሪት ውስጥ እንድንኖር ሊያደርጉ የቻሉበት አንዱና ዓብይ ምክንያት፤ ለአምላካችን የቅድስና አምልኮትና ለእግዚአብሔር ጸሎት ባለማድረሳችን ነው፡፡   => ከዲያብሎስ መሠረታዊ ሥልት አንዱ፤ በዓለማዊው መድረኮች ላይ ለመንፈሳዊ ሕይወት ቦታ እንዳይሰጥ፤ በተለይም ጸሎት ወደ እግዚአብሔር እንዳይደርግ ማዘናጋት ነው፡፡ ጸሎት አለማድረግ ደግሞ፤ ከእግዚአብሔር የሚያለያየን ዋንኛ መንገድ ነው፡፡ ዛሬ በዚህ ጎዳና ላይ እኛም እየተጓዝንበት እንገኛለን፡፡ ከአምላክህ ጋር ከተለያየህ ደግሞ፤ የምታዳብረው ጠባይ፤ ክፋትን፣ ተንኮልን፣ ፌዘኝነትና ደንታ ቢስነትን ወዘተ…ነው፡፡   => በዚህ መንገድ ከተጓዝን ደግሞ፤ ጸሎት የለም፡፡ ምናልባት የምንሰማውና የምናየው የአንድና የሁለት ደቂቃ የሕሊና ጸሎት የሚባለውን ነው፡፡ የሚገርመው ግን፤ ይህ የሕሊና ጸሎት ለማን እንደሆነ፣ ምን ተብሎ እንደተጸለየና ማን እንደሰማው አለመታወቁ ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነቱ ጸሎት፤ ዘመናዊው ሰው ምንጊዜም አቅጣጫውን ሲለውጥ፣ እምነቱን ሲጥል፣ የማንነት ጉዳዩን ከመናቅም በላይ፤ አዲስ ነገርና የፈጠራ ሃሳብ መሞከሪያ ሲሆን፤ እራሱን እያዘናጋ በሕይወት ተምሳሌቱና ከጊዜው እይታ ጋር ሲወዳደር፤ ለየግል ፍላጎቱ ከሥራ ጋር ሲባዝንና ሲሯሯጥ፤ በመሐል ሃይማኖቱንና እምነቱን በመዘንጋት፤ ለከባድ መቅሰፍት እንዲጋለጥ የሚያደርግ ነው፡፡   => ክርስቲያን ወገኖችም፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶችን ሁሉ በሚገባ በመከተል፤ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በአምልኮት በመንበርከክ፣ በቅዱስ ቁርባን፣ በንስሐ፣ በጸበል፣ ወዘተ… በመቀደስ፤ የእግዚአብሔር ሰው ለመሆን እስካልቻልን ድረስ፤ የዲያብሎስ  መጫወቻ ሆነን ብንቀር የሚያሳዝንና የሚያሰቆጭ አይሆንም፡፡ ብዙ ሰው ስለ ክፉው መንፈስ ያለው አመለካከትና  ግምት፤  በእኔ ላይ መተት አይሠራም፤ እግዚአብሔርን አምናለሁ፤ እንዳቅሜ ጸሎት አደርሳለሁ፤ እመጸውታለሁ፣ አንዳንዴ እጾማለሁ ሲመቸኝ ቤተክርስቲያን እሄዳለሁ፤ ሰንበቴና የጽዋ ማሕበር እጠጣለሁ፣ የቄስ ዘርና የቅዱሳን ዘር ነኝ፤ አያቴ ዳዊት ደጋሚና ቤተክርስቲያን ተካይ መነኮሴ ገዳማዊ ነበሩ፤ መናኝ ባሕታዊ ዘመድ ነበረኝ እያልን፤ ራሳችንን በትልቅነት ደረጃ ውስጥ አስገብተን እንመካለን፤ ብዙ እናወራለን፤ የሚገርመው ግን፤ ከእግዚአብሔር ልጆች የዲያብሎስ ልጆች የተንኮልና የግፍ አሠራሩ ላይ፤ ከማንም በላይ የሰለጠኑና የጥቃት ሥልታቸው የረቀቀ፤ ሂደቱን በእያንዳንዱ በኋላው ታሪክ በሚመጻደቅ ትውልድ ላይ ሁሉ፤ የመንፈሱ ጥቃት በምስጢራዊ ሁኔታ ተከናውኖ መገኘቱ ነው፡፡   => ሌላው ቀርቶ የዓይነ-ጥላ አብሮን የመወለዱን ጉዳይ እንኳን ገና በግልጽ አልተረዳንም፡፡ ይህም የቱን ያህል ከማለዳ የመያ’ዝ ጉዳይ ጋር የተወሳሰበ እንደሆነ ያስረዳናል:: በመንፈሳዊ የሕይወት ጅማሬ ውስጥ፤ ለዕውቀት ሲባል የሚወሰዱ ዕፅ-ፋርሶችና በሰውነት ውስጥ የሚቀበሩ ከመንፈሱ ጋር በዕፆች አማካኝነት የሚገቡና በሰውነት ውስጥ ተመሳስለውና ተዋህደው የሚኖሩ የመንፈሶች አደጋዎች፤ በስፋት ያጠቁት ወገን ብዙ ነው፡፡   => በዚህ ዓይነት መንፈስ ተጠምደው ቤተ እግዚአብሔርንና ለምዕመናን፤ ከአነጋገር እስከ ተግባር ድረስ  መሰናከል ሆኖ የሚኖረው የአገልጋዮች ችግር፤ ከዚህ የልማድ አምልኮት ጋር የተያያዘ እንደሆነ፤ ብዙ በቤቱ የሚመላለሱ ሰዎችና በርካታ ምዕመናን ገና አልገባቸውም፡፡ ነገር ግን በተግባር የሚታየው ሁሉ የክፉው መንፈስ የውክልና ሥራ በቃል ክፉ በመናገር በልብ በመመቅኘት፣ ተንኮል፣ ቅናትና አስማታዊ አሠራር መግለጫ ነው፡፡ በሰውነት ውስጥ ተዋህዶ በመኖሩ ምክንያት የአገልግሎት ዘመኑን ሁሉ ለዓለማዊ ጥቅም ብቻ እንዲሰለፍ፤ በጥቅሙ የሚመጣበትን ሁሉ በማንኛውም የክፋት መንገድ በመበቀል፤ የመዋጋቱ ጉዳይ፤ ለመንፈሳዊ እምነቱ ከሚሰጠው ቦታ በላይ፤ ተንኮሉ የበለጠ ነው፡፡   => ከእውቀቱ ዘርፍ፤ ክፉ መናፍስት ዕውቀትን ሰጭ አካል አድርጎ ከጀመረ መንፈሳዊ አገልግሎቱ ውስጥ፤ ብዙም መልካም ነገር ባይጠበቅ የሚገርም አይሆንም፡፡ ምክንያቱም፤ ክፉው ዲያብሎስ ሥልቱም ተፈጥሮውም ሃይማኖታዊ ጉዞን የሚያመጣውን ጸጋ፣ ሞገስና የእምነት ኃይሉን ተመሳስሎ ማዳከም ስለሆነ፤ ይሄው ግቡ ዛሬ ብዙ የተሳካለት መሆኑን  በየቤተክርስቲያን ያለው የመለያየት ችግር ማሳያ ነው፡፡   => በመንፈሳዊ ግንዛቤያቸው የተሻሉ ሰዎች ግን፤ ሕብረተሰቡ ውስጥ ያለውን የክፉ መንፈስ ውስብስብ ፈተና የኑሮ፣ የእምነትና የአእምሮ መቃወስ፣ የጤና ማጣት አደጋ ይገነዘባሉ፡፡ የዚያኑ ያህል በተቃራኒው፤ ሳይቀደሱ የሚባርኩ፣ ሳያመልኩ የሚያገለግሉና የሚገለገሉ፣ የያዙትን ወንበር የሚያመልኩ፣ ለሌላው ጥፋትና ክህደት ምሳሌ የሚሆኑ ለአሰተዳደራዊ በደል መፍትሔ የማይሰጡ፣ የተዘበራረቀ አመለካከት ያላቸው፣ በጥቅምና በባለጸጋ የሚታለሉ፣ ሃይማኖታዊ አደራቸውን የዘነጉና ለሕዝብ ደህንነት ራእይ የሌላቸው፣ ችግሩን የማያዩና የማይሰሙ፣ በምትሐተኞች እጅ የተያዙና በቤተ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ኃይል መኖር ያቃታቸው አገልጋዮች ጥቂቶች አይደሉም፡፡       => በአጠቃላይ በእግዚአብሔር ቤት የምንገኝ አገልጋዮች፣ ክርስቲያን ወንድሞችና እህቶች ሁሉ፤ የክፉ መናፈስቱን የውጊያ ሥልቶችና ጥበቦች፣ የመጠጊያ፣ የመግቢያና የማጥቂያ አቅጣጫዎቻቸውን፣ ረቂቅ ጠባያቸውንና ሥሌታቸውን በመገንዘብ፤ ከርኩሳን መናፍስት ተገዢነት ነጻ ወጥተን፤ እውነተኛውን የእግዚአብሔርን የጽድቅ መንገድ መከተል እንችል ዘንድ፤ ኃያሉና ልዑሉ አምላካችን እግዚአብሔር ማስተዋሉን ይስጠን፡፡ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239