ጣና ሚዲያ Tana Media
2 673
المشتركون
-1124 ساعات
-287 أيام
+8830 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
#አጫጭር ዜና
#በሰሜን ወሎ ወልዲያ ከተማ ፖሊስ ማዘዣ ላይ ጥቃት ተፈጸመ።
#በወልዲያ ከተማ ራስ ዓሊ ክ/ከተማ ጎንደር በር የሚገኘው 2ኛ ፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ላይ ሐምሌ 7/2016 ዓ.ም ሌሊቱን በተፈፀመ ጥቃት ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ደርሷል።
#በጥቃቱ ከአምስት በላይ የፖሊስ እና የዐድማ ብተና አባላት ሲሞቱ ሰባት ክፉኛ ቆስለዋል። ቁጥራቸው 6 የሚደርሱት በፋኖ ኃይሎች ተይዘው ተወስደዋል።
#የመሣሪያ ግምጃ ቤት ተሰብሮ ከ20 በላይ የነፍስ ወከፍና የቡድን መሣሪያዎች በፋኖ ኃይሎች እጅ ገብቷል።
#አንድ የሰው በላው_ወታደራዊ ተሽከርካሪ መሉ በሙሉ ወድሟል ሲሉ የመረጃ ምንጮች ገልፀዋል።
አስቸኳይ አስቸኳይ - ምስራቅ ጎጃም!
ወደ ደጀን ከተማ ለስብሰባ ሂደው የነበሩና "ስራ አጥ፣ ግንበኛ ወዘተ" የሚል መታወቂያ የያዙት የምስራቅ ጎጃም ዞን የወረዳ አመራሮች ለትናንት አስበውት የነበረውን ጉዞ በመሰረዝ ለዛሬ ሐምሌ 08/2016 ዓም ለጉዞ በመዘጋጀት ላይ መሆናቸው ታውቋል።
የአካባቢው ቀጠና ፋኖዎቻችን ዝግጁ!
መረጃው ይዛመት ይዳረስ!
#ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ!
#ከአማራ_ፋኖ_የደህንነት_ክፍል_የተገኘ_መረጃ
ያልታዎቁ ኃይሎች በአዲስ አበባ ያኃ
ሐምሌ 2/11/2016
አድስ አበባና ዙሪያውን ያለውን ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ ስለማሳወቅ
ከላይ በርዕሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው በአድስ አበባ ዙሪያ በፌዴራልና በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በመደገፍ በግልጽ ሲሰለጥን የቆየ በግልጽ አላማው የማይታወቅ ሚስጥራዊ ቡድን እንዳለ አይዘነግም ።
ይሄ ሚስጥራዊ ቡድን መጠሪያ ስሙ ወለጋ አካባቢ ልዩ መጠሪያ ስሙ ጋቸና ሲርና/Gaachenaa Sirna ሲሆን አድስ አበባ ዙሪያ ግን ኮሬ ነጌኛ/Koree Nageenyaa የሚል ተለዋጭ ስም ያለው መሆኑን የአማራ ፋኖ ያልታወቁ ኃይሎች/የደህንነት ክንፍ ሙሉ መረጃውን ደርሰውበታል።
ይሄ አደገኛ ሚስጥራዊ ቡድን የሚመራው በገዢው መንግስት ሲሆን ከሳምንት በፊት አዲስ አበባ ላይ በብዛት እየገባ መሆኑን የፋኖ ያልታወቁ ኃይሎች/የደህንነት ክንፍ ደርሰንበታል ነገሩን በተጨባጭ እየተከታተልን መሆኑን እናሳውቃለን::
በተጨማሪም ባለፉት ሁለት ቀናት ማለትም 28/10/2016 ቀን ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የአድስ አበባ ከተማ የመንግስት ሰራተኞች በግዜ ወደቤታቸው እንዲገቡ ከላይ የመጣ ትዛዝ ነው በሚል ስጋት ላይ መውደቃቸውን አረጋግጠናል::
በመሆኑም ይህ ሚስጥራዊ ሃይል ሰሞኑን አድስ አበባ ላይ ልዩ ልዩ እርምጃወችን ለመውሰድ ዝግጂቱን ጨርሷል።
ለመውሰድ ካቀዳቸው እርምጃወች ውስጥ
፩ ኛ የአማራ ባለሃብቶችን
፪ ኛ ህጻናት ተማሪዎችን
3 ኛ ለህዝብ የሚወግኑ የመንግስት ሰራተኞችን ፬ ኛ ታዋቂ ግለሰቦችንና የመሳሉትን በማገትና በመግደል ተልኮውን ከፈጸመ በኋላ የአማራ ፋኖን ለመወንጀል ትእዛዝ መቀበሉን ደርሰንበታል።
በመሆኑም የተከበርከው የአዲስ አበባ ሕዝብ ሆይ የተቀነባበረብህን መንግስታዊ ሽብር በመገንዘብ ከወድሁ ጥንቃቄ እንድታደርጉ ስንል መልዕክታችንን በአክብሮት እናስተላለፋለን
ከሰላምታ ጋር
የአማራ ፋኖ የደህንነት ክንፍ ያልታዎቁ ኃይሎች በአዲስ አበባ
አዲስ አበባ ኢትዮጲያ
#ድል_ለመላው አምሓራ_ፋኖ!
👍 3❤ 1
ቢታረሙ የምንላቸው ሁለት ጉዳዮች
1. በተለይ ቀንም ማታም ስለ ግለሰብ አመራር ብቻ የምትፅፉ አንዳንድ ሚዲያው ላይ ያላችሁ ወንድሞቻችን አካሄድ ግን መታረም አለበት። ይህ አካሄድ ግለሰቦቹንም አይጠቅምም፤ ትግላችንንም አይጠቅምም።
ዋና ትኩረታችን ትግሉ ላይ ሆኖ በሂደቱ ግለሰቦች ቢነሱ ችግር የለውም ነገር ግን ትዝብት ላይ በሚጥል መልኩ ግለሰብ ላይ ያተኮረ የሚመስል አክቲቪዝም ልክ አይደለምና ይታረም።
2. ከዚህ በተጻራሪ ደግሞ አንድን አመራር ወይም ቡድን ልክ እንደነሱ ዘለን እንድናወግዝ ግፊት የሚያደርጉም አሉ። ልክ እንደ ሞጣ ቀራንዮ ወይም ምናምን አኪላ እንደሚባለው ልጅ ማንንም እየዘለሉ መዘርጠጥ እኮ ቀላል ነው። ነገር ግን ይህ ለትግላችን ይጠቅማል ወይ ነው?
ችግሮች በእኛ ዝርጠጣ የሚፈቱ ቢሆን እኮ እኛም ዝርግ አፍ መሆን ይቻል ነበር -- ቁልፉ ነገር ችግሮች ሲኖሩ በአደባባይ ሳይሆን በቤት ውስጥ ተወያይቶ፣ ለሚመለከታቸው አካላት ጊዜ ሰጥቶ፣ ነገሮች በውይይት እንዲፈቱ መፍቀድ የተሻለ ነው። ችግሮችን ለመፍታት የሚዲያዎች የአደባባይ ዘገባ በአመዛኙ የማጋጋል ሚና እንጅ የአስታራቂነት ሚና ሊኖራቸው አይችልም። ለጠላትም በር ከፋች ነው!
የሚዲያ ሰዎች የአስታራቂነት ሚናን ሊወስዱ ቢችሉም የሚዲያ ዘገባና ማጋጋሎች፣ ጥራዝ ነጠቅ ትንተናና ዝርጠጣዎች ግን "ሽማግሌ ወይም ሽምግልና" ሊሆኑ አይችልም። የሚጠቅመውም በቀና ልብ መፍትሔ ማመላከት፣ በስሜት ሳይሆን በስክነትና በስሌት ለትግሉ በሚጠቅም መልኩ "መቼ ምን ማድረግ እንዳለብን መገንዘቡ" የተሻለ ነው።
اختر خطة مختلفة
تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.