ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 378 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 573 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 194 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 378 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 06 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 32، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -4، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 22.44‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.50‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 449 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 461 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 20.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 07 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 378
المشتركون
-424 ساعات
-257 أيام
+3230 أيام
أرشيف المشاركات
#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፯_ ** ለሰው በሚፈልገው ሰይጣናት ተመስለው በምትሐት እንደሚገለጹ፤ የሰይጣናት አሳሳች መሆናቸው ለጥቂት ደጋጎች እንጂ (በመጨረሻ በሥራቸው) እንጂ ለሁሉ እንደማይታወቁ፤ በገዳም የሚኖሩትን በምን እንደሚዋጋቸውና እንደሚያሸነፉት፤ ከሰው ልጆች የሚፈራቸውና የማይፈራቸውን/ ፠ አባ ጳውሊ፤ ለሰው በምትሐት የምትታዩት በስንት አምሳል ነው? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ለማሳት እኛ በምንፈልገው መልክ እርያ፥ እባብ፥ ሴት፥ ወንድ፥ ወጣት፥ ሽማግሌ፥ ቀበሮ፥ ጦጣ፥ ዝንጀሮ መስለን መታየት እንችላለን፡፡ ከእኛ እያንዳንዳችን በድንግል ማርያምና በልጇ አምሳል፤ በብርሃን መልአክና በቀደሙ ቅዱሳንና ቀድሞ በሞቱ ሰዎች አምሳልም ቢሆን ሰው በሚፈልገው ሁሉ እንታያለን አለው፡፡ (ሙት ሳቢ የሚባሉትን ልብ ይለዋል)፤ "ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና፡፡ እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤ ፍጻሜያቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል፡፡" /፪ቆሮ.፲፩፥፲፬/ ፠ አባ ጳውሊ፤ እናንተ አሳቾች እንደሆናችሁ ለሰው በምን ትታወቃላችሁ? መጨረሻችሁስ እንዴት ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ ለጥቂት ደጋጎች ነው እንጂ ለሁሉ አንታወቅም፡፡ በመጨረሻ ሥራችን ግን እንታወቃለን አለው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ ሥራህ ሁሉ ክፉ እንደሆነ ከአንተ ተረዳሁ አለው፡፡ ሰይጣን፤ እንደ አንተ ንጹሕ የሆነ ሁሉ በክፉ ሽታዬ ያውቀኛል፡፡ ኃጥአን ግን በሽታዬ ለይተው ሊያውቁኝ አይችሉም አለው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ #አንተ ከክብርህ የተዋረድክ #እንደ አንተ ንጹሕ የሆነ በማለት በውዳሴ ከንቱና በትምክሕት ወጥመድ ጠልፈህ ልትጥለኝ ትፈልጋለህን? እግዚአብሔር የተመኘኸውን አይስጥህ ያሰብኸውንም አይፈጽምልህ፡፡ እኔስ ኃጢአተኛ ነኝ እንጂ ንጹሕና ጻድቅ አይደለሁም፡፡ ዕለተ ሞቴን አስባለሁ፡፡ በፊቴ የእግዚአብሔር ፍርድ አለ አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ አንተ የተረገምክ! ዳግመኛም ስለምጠይቅህ ነገር ምንም ከእኔ እንዳትሰውረኝ በስሙ አምልሐለሁ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከአንተ የተነሳ ወዮልኝ፡፡ እነሆ ከዚህ በፊት ተሰምቶ በማይታወቅ መከራ ተፈተንኩ፡፡ አንተ ክፉ ሽማግሌ በእኔ ላይ ከወዴት እንደሠለጠንክ አላወቅሁም አለው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ እንዴት አድርገህ ነው በገዳም ከሚኖሩት ጋር የምትዋጋው አለው፡፡ ዲያብሎስም ከአንተ የተነሳ ወዮልኝ በጠላቶቼ መካከል ሰውን የማጠምድበትን ሥራዬን ትገልጥብኝ ዘንድ ትወዳለህን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ሥራህን ብቻ የምገልጥ አይደለሁም ለሰው ጥቅም የሌለው የጥበብህንም ፍጻሜ ነው እንጅ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አስቀድመን መነኰሳትን የምንዋጋቸው በገዳሙ ቆይታ ላላቸውና በእድሜ በማዕረግ ለሚበልጧቸው ለአበ ማኅበሩ እሺ በጀ ብለው እንዳይታዘዙ፥ ምክራቸውን፣ ተግሣጻቸውን እንዳይቀበሉና እንዳይሰሙ፤ እኔ የምነግራቸውና የማሳስባቸውን ለአበው እንዳይነግሩ በማድረግ ነው፡፡ ዳግመኛም ጥርጣሬንና መሸበርን የልብ ድንጋጤን በላያቸው እናመጣባቸዋለን፡፡ በሐሰተኛ ሕልም እናስታቸዋለን፡፡ በዚህ ባያምኑና ቢያቸንፉን ብዙ የምኞት ፈተናን እናመጣባቸዋለን፡፡ ወርቅና ብር መውደድን የላመ የጣመ መብላት መጠጣትን እናመጣባቸዋለን፡፡ የማይጠቅም ዙረትን እንዲያበዙ እናደርጋቸዋለን፡፡ ሰውን የሚያጣሉና ነገር አመላላሾች እንዲሆኑ የአበውን ምክር እንዳይሰሙ ልቡናቸውን እናደነድነዋለን፡፡ በዚህ አኗኗራቸው በአንድ ቦታ እንዳይጸኑ በየጊዜው ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ እንዲዛወሩና ሥራን እንዳይወዱ ፤ ሌላ የደከመበትን እንዲመገቡ በአፋቸው እኛ ዓለምን ንቀናል እንዲሉ፤ ዓለም ግን ከደስታዋና ከፍላጎቷ ሁሉ ጋር በእነርሱ ላይ በዝታ እንድትታይና መንፈሳዊ ዕውቀትን ትዕግሥትን መረጋጋትን እንዲያጡ እናደርጋቸዋለን፡፡ ሰይጣን፤ ከገዳማቸው በወጡ ጊዜ በነፍሳቸው ለገዳሙ አባት ሊገዙ ከገቡባት ከገዳማቸው ልቡናቸውን እናርቀዋለን፡፡ እኛ የዚህችን ዓለም ሥራ ስለምናሳምርላቸው በስም መነኮሳት ሲባሉ በገዳም መኖራቸውን ፈጽመው ይጠላሉ፡፡ በዚህ ፈትነናቸው ካቸነፉን ሌላ የሚፈተኑበት ምክንያት እናመጣባቸዋለን፡፡ ሌላው በሚሠራው ሥራ በመቅናትና በቂም አንዱ ለአንዱም መልካም ሥራ እንዳይሠራ እንቅፋት እንዲሆነው በማድረግ እንዋጋቸዋለን፡፡ በገዳሙ ውስጥ በሚሰሩት ሥራ ውዳሴ ከንቱን አብዝተው እንዲፈልጉና ራሳቸውን ከወንድሞቻቸው ከፍ እንዲያደርጉ፣ ከራሳቸው ሥራ በቀር የሌላውን እንዲነቅፉ እንዋጋቸዋለን፡፡ ኃላፊውን ዓለም መመኘትንና ሥጋዊ ትምክሕትን ዘወትር በልቡናቸው እናሳድርባቸዋለን፡፡ በዚህ ሁሉ የኃጢአት ወጥመድ ካቸነፉንም ተስፋ እንዲቆርጡ ክፉ ሐሳብን በእነርሱ ላይ ለማምጣት ዘወትር እንበረታለን፡፡ ከዚህ ሁሉ ጋር ዳግመኛ በላያቸው ላይ ጊንጡን እባቡን ቅማሉንና ቁንጫውን ትኋኑን የሚያሰቃዩአቸውን ሁሉ አራዊት እናስነሣባቸዋለን፡፡ ከምግባቸው ዘመሚቱን ትሉን ክፉውን ነገር ሁሉ እናስገባባቸዋለን፡፡ የእጅ ሥራ አዝመራቸውንና እንስሶቻቸውን በአራዊትና በአይጥ በአዕዋፍ በበሽታ በተቻለን ሁሉ እናጠፋባቸዋለን አለው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ በዚህ በምትዋጋቸው መከራ ምን ትጠቀማለህ? እነርሱስ በምን ያቸንፉሃል አለው፡፡ ዲያብሎስም ፈጣሪያቸውን እንዳያመሰግኑ ተስፋ እንዲቆርጡና የዘለዓለም ሕይወትንም እንድናሳጣቸው ነው እንጂ የምንጠቀመው ጥቅም የለንም፡፡ ዲያብሎስ፤ በምን ያቸንፉሃል ስለምትለኝም ፤ በፍቅር፥ በመታዘዝና በትዕግሥት፤ በጾምና በጸሎት፤ ከቂም በቀል ንጹሕ በሆነ ልቡና፤ ባለመለያየት ወንድሞቻቸውን ፈጽሞ በመውደድ፤ ከዚህ ሁሉ ጋር ትሕትና ከመንፈሳዊ ሥራቸው ሁሉ ትበልጣለችና በፍጹም ሃይማኖት ትሕትናን ቢይዙ ያቸንፉናል፡፡ በመጨረሻም የክርስቶስን ሥጋና ደም በመቀበላቸው ያርቁናል ፤ ያቸንፉናል፡፡ #የክርስቶስ ሥጋና ደም የእኛን መርዝ ያጠፋል፡፡ እሾሃችንንም ይነቅላል ፤ ያቃጥላልና አለው፡፡ ፠ አባ ጳውሊ፤ ከእናንተ የተነሳ ለሰው ወዮለት አለ፡፡ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጀመሪያ በራችሁን ይዝጋ ፤ ወጥመዳችሁን ያጥፋ ኃይላችሁም ያድክም አለው፡፡ ያን ጊዜ የተረገመ ዲያብሎስ አንተ ክፉ ሽማግሌ ከእንግዲህ ወዲህ ምንም ነገር አልነግርህም፡፡ ከአሁን በኋላ ከአንተ ዘንድ ወጥቼ እሄዳለሁ ብሎ ጮኸ፡፡ አባ ጳውሊ፤ ከዚህ የሚበዛ ብዙ የምጠይቅህ አለኝና አንተ ርኩስ የክፉ ሥራ ምሥጢርህን ጨርሰህ ሳትነግረኝ ከእኔ ትሔድ ዘንድ ሥልጣን የለህም፡፡ #ዲያብሎስ የሚፈራቸውና የማይፈራቸው ሰዎች፤ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን በምን እንደሚፈትናቸው… ክፍል ፰.… ይቀጥላል ከነገ ወዲያ ይጠብቁን/ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

ስለሚሰራው መስጊድ ቅሬታ አለን። (#እጅግ_በጣም_አስቸኳይ_ስለሆነ_አሁኑኑ #share #share ያድርጉ፡፡) ምዕመናኖቹ የተነሡት በልማት ሰበብ እንጂ ለመስጊድ መሥሪያ ተብለው እንዳልሆነ ሃገር ያወቀው፥ ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ በአፍሪካ ኅብረት ማስፋፊያ ልማት ተነሥቶ አሁን ባለበት ቦታ ሲቀመጥ ተገቢው ማካካሻ ቦታ ስላልተሰጠው ከዛሬ ነገ ይሰጠኛል ብሎ እየጠበቀ ባለበት ሁኔታ፤ በቦታው ላይ ቀድሞ ቦታ ለሌላው እምነት መስጠት በራሱ ውሳጣዊ ችግርና ደባ ለመሆኑ አመላካች ነው፡፡ በአካባቢው ለሚኖሩ ብዙ ሕዝበ ክርስቲያን በቂ መጠለያ እንኳን የሌለው ቅጽረ ቤተ ክርስቲያን እያለና በተደጋጋሚ ጥያቄ እየቀረበ ምላሽ ሳይሰጥ፤ ከአጠገቡ የ200 ሜትር እንኳን ርቀት በሌለው ያውም በቊጥር አነስተኛ ለሆኑ ሙስሊም ወንድሞቻችን መንግሥት 30ሺህ የሚጠጋ ካሬ ሜትር ለመስጠት መዘጋጀቱ፤ የተፈራ ዋልዋና የአሊ አብዶ ለእስልምና ያደላ ደባን እንድናስታውስ ያደርገናል፡፡ ++++++ በአ/ኅ/ደ/ም/ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ትይዩ በዛሬው ዕለት ለእስልምና እምነት ተከታዮች የአምልኮ ቦታ እንዲሆን 30,000 ካሬ የሚሆን ቦታ ተሰጥቶ በነገው ዕለት የመሠረት ድንጋይ ለመጣል እየተዘጋጁ ነው ሁላችሁም ፎቶውን እና መልዕክቱን በማንኛውም ማሕበራዊ ሚዲያ በማጋራት ሃይማኖታዊ ግዴታችንን እንወጣ !! በልማት ምክንያት ሃይማኖትን ማዳከም በግልጽ እየታየ ነው፡፡ በብዛት የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች የሚኖሩበትን ስፍራ በልማት ስም በማሰቃየት በ10 እና 15 ቀነ ገደብ አፍርሰው ለ5 እና 6 ዓመታት ያለምንም ልማት ኦና ሆኖ ተመልክተነዋል፡፡ ሆኖም አሁን በግልፅ ከላይ እንደጠቀስኩት ዓይነት ድርጊት ከመንግሥት አካላት የሃይማኖት ማዳከም ሥራ እየተካሄደ ነው፡፡ መስጊድ አይታነጽ ሳይሆን ከቤተክርስቲያን ይራቅ አንረባበሽ የሚለው ሀሳብ ቢያዝ የሰመረ ነው። በልማት ስም እምነትን የማስፉፉት ሴራ ከቀድሞውም የሹማምንት ግብር እንደሆነ ይታወቃል። አሁን ደግሞ በቀድሞ የሀገሪቱ አስተዳደር ለልማት በማለት የፈረሱ አካባቢዎችን እና ቦታዎችን ለእስልምና አማኞች መስጊድ እንዲሰሩባቸው በመስጠት በስልጣን ወንበር የተቀመጡ የእምነቱ ተከታዮች ጫና እያደረጉ ይመስላል። ከታች በምስሉ ምትመለከቱት ቦት በተለምዶ ቡልጋርያ አካባቢ ሀያ ቀበሌ ወይም ሳይቬርያ የሚባለው አካባቢ ሲሆን እዚህ አካባቢ ላይ አብዛኞቹ የክርስትና እምነት ተከታዮች የነበሩበት ነው። እንደተለመደው ልማት በሚባለው መንግስታዊ ቋንቋ ከተነሱ ከ4 ዓመት በላይ አስቆጥረዋል።ቦታውም ጫካ ሆኖ ዛፎች በቅለውበት መንግስታዊ ሳይሆን ተፈጥሯዊ ልማትን ይዟል። ታድያማ አሁን ያለው የአዲስ አበባ አስተዳደር የእስልምና ማዕከልና መስጊድ ይሰሩበት ዘንድ እዚያው ቦታ ላይ 30 ሺ ካሬ ለግሷቿል የሚል ተባራሪ ወሬ ሰማን። መጠርጠር ደግነቱ አስቀድሞ ለመጮህ የተመቸ ይሆናል። ይደንቃል ቤተክርስቲያን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ስትጠይቅ መከራ እንዳላየች ሁላ እንደቀልድ አንድ መንደርን ብድግ አደርጎ እንካቹ ማለት ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው። ታድያ ምን ችግር አለው የሚል ጥያቄ መጠየቁ የማይቀር ነው የነዋሪው እና የአካባቢው ቅሬታ ይህ መስጊድ እንዲሰራበት የተሰጠው ቦታ በጣም ቅርብ በሚባል ሁኔታ ከ27 ዓመት በላይ የቆየ የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አለ በተለመዶም ሙሉ ስሙ የአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ተብሎ ይጠራል። ብዙ የክርስትያን ነዋሪ በሚገኝበት ቦታ መሥራቱ ሳይከፉ ቤተክርስቲያን አጠገብ የመስጊድ ሥራን አምጥቶ መደቀኑ ይዋጣላቹ ይለይላቹ የሚል መልእክት ያለው ይመስላል። ካልጠፋ ቦታ አብያተ ክርስቲያናት በሚገኙበት ቅርብ ርቀት ላይ መስጊድ ስሩ ብሉ ይሁንታን መስጠት ምን የሚሉት ችሮታ ነው። ከዚህ በፊትም ለቱርክ ባለሃብቶች የተዘጋጀ ቦታ እየተባለ ለሃይማኖታዊ ግልጋሎት ሲውል ባናይም ሰምተን ግን አልፈናል። አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ አንድ ቀበሌ የሚያክል ቦታ መስጠት ወንበር ከመልቀቄ በፊት የሚል ሴራ የያዘ እንዲመስለን ሆኗል። ሌላው ትልቁ ችግር በብዙ ትእግስት ተቀመጦ የነበረውን ወጣት ማነሳሳቱ ነው። በአካባቢው ያሉ ይሆን ከሩቅ ያሉ ወጣቶች ይህን ሲሰሙ ከነፍስ ያለፍ ትርፍ ምን አለ በሚል ግብግብ ውስጥ ገብተው አላስፈላጊ የሆኑ ግጭቶችን አለመግባባቶችን ያስከትላል። ተቻችለን እንኑር ብሎ የሰከነውን ወጣት ያደገበት አጥቢያ ቤተክርስቲያን ላይ መጥቶ "አላሁ አክበር" የሚል ድምጽ ማሰማት ንቀት ስለሚመስል አሁንም ከቤተክርስቲያን ቅርብ ርቀት ለመስጊድ ተብለው የሚሰጡ ቦታዎች ቢታሰሰብባቸው ጥሩ ነው። ከ50 ሚልዮን በላይ ተከታይ ያላትን ቤተክርስቲያን መጥቀም ባንችልም መጉዳቱ ዋጋ የሚያስከፍል ስለሆን ዓመጽ ሳይበረታ ቡልጋርያ አካባቢ አፍሪካ ህብረትን ታኮ የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ካለበት ቅርብ ርቀት ላይ የተሰጠው የመስጊድ መስርያ 30.000ካሬ መሬት በተለዋጭ መሬት ቦታ ቢለወጥ መልካም ነው ይህ ሥራ የሀገር ባለውለታ ቤተክርስቲያንን መናቅ ነውና ክቡራን ሹማምንት በተለይ የመሰጊዱ አሰሪ መኳንንቶች አስቡበት። ወሬ ነጋሬ እንዳበጀው ነገ በ12 የመሠረት ድንጋይ በከንቲባው እና በሚኒስተር ሞፈሪያት የሚጣል ሲሆን የቤተክርስቲያናችን ሰበካ ጉባኤ እና አስተዳደር መስጊድ ይሰራበታል የተባለበትን ቦታ አይተዋል በቦታው የእምነቱ ተከታዮች ለነገው መሠረት ድንጋይ የሚጣልበትን ሲያጸዱ ተመልክተዋል። እኛ ጉዳያችን ከሙስሊም ወንድሞቻችን ጋር አይደለም ጥያቄያችን እዚህ ቦታ ላይ አጠገብ ለአጠገብ ሕገ መንግስቱ ላይ የተቀመጠውን እንኳን ባላከበረ መልኩ 200 ሜትር እንኳን በማይሞላ ርቀት እንዴት ይታሰባል። ትልቁ ችግር መስጊድ መሰራቱ ሳይሆን 1. በቦታው የነበረውን ሕዝበ ክርስቲያን ለልማት በሚል ሰበብ ከቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን አርቀው በግፍ መውሰዳቸው፤ 2. ከቦታው በቅርብ ርቀት የቄራ መስጊድ እያለ ሌላ መጨመር፤ 3. ከቦታው በቅርብ ርቀት ከሚገኘው ከቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ መሰራቱ ይህ የሚያስከትለው የድምፅ መረባበሽ ወዳልተፈለገ ግጭት ያመራል፤ 4. የቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ለረጅም ዓመታት ሲያነሳ የነበረው የቦታ ጥያቄ ምንም ምላሽ ሳያገኝ ይባስ ብሎ ቦታው ጠባብ ስለሆነ ከቅፅረ ቤተ-ክርስቲያኑ ውጪ ሆነው የሚያስቀድሱትን ምዕመናን በድምፅ የሚበክል ሌላ የዕምነት ተቋም ማቋቋም የማንታገሰው ድርጊት ነው። 5. ቦታውን መንግሥት የማይሠራበት ከሆነ ለተፈናቀሉት ምዕመናን ተመልሶ ቢሰጥ፡፡ (ምዕመናኖቹ የተነሡት በልማት ሰበብ እንጂ በመስጊድ ሰበብ እንዳልሆነ ሃገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው፡፡) 6. ከመቼ ጀምሮ ነው ቤተ ክርስቲያንና ሌሎች የእምነት ድርጅቶች ማምለኪያ ቦታቸውን ሲሠሩ መሠረት ድንጋይ ለማስቀመጥ ከንቲባውና የሰላም ሚኒስተር ተገኝተው የሚያውቁት፤ ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አግኝተው ይሆንን!!! *** ስለዚህ ይህንን ተግባር መንግሥት በአስቸኳይ እንዲያቆም በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፤ ካልሆነ ግን ወደ አላስፈላጊ ግጭት ያመራናል። ** መሠረት ለመጣል የሚገኙት ከንቲባውና የሰላም ሚኒስተር ሞፈሪያትም ሌላው የእምነት ተቋም ላይ ለመሠረት ድንጋይ ተገኝተው የማያውቁትን እዚህ ልገኝ ብለው ያሰቡትን ልብ ብለው ቢያስቡበት መልካም ነው፡፡ ''ይትባረክ አምላከ አበዊነ'' (ዘገባው የአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስያን ሰ/ት/ቤት ነው፡፡)

ትልቁ ችግር መስጊድ መሰራቱ ሳይሆን 1. በቦታው የነበረውን ሕዝበ ክርስቲያን ለልማት በሚል ሰበብ ከቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን አርቀው በግፍ መውሰዳቸው፤ 2. ከቦታው በቅርብ ርቀት የቄራ መስጊድ እያለ ሌላ መጨመር፤ 3. ከቦታው በቅርብ ርቀት ከሚገኘው ከቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ መሰራቱ ይህ የሚያስከትለው የድምፅ መረባበሽ ወዳልተፈለገ ግጭት ያመራል፤ 4. የቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ለረጅም ዓመታት ሲያነሳ የነበረው የቦታ ጥያቄ ምንም ምላሽ ሳያገኝ ይባስ ብሎ ቦታው ጠባብ ስለሆነ ከቅፅረ ቤተ-ክርስቲያኑ ውጪ ሆነው የሚያስቀድሱትን ምዕመናን በድምፅ የሚበክል ሌላ የዕምነት ተቋም ማቋቋም የማንታገሰው ድርጊት ነው። 5. ቦታውን መንግሥት የማይሠራበት ከሆነ ለተፈናቀሉት ምዕመናን ተመልሶ ቢሰጥ፡፡ (ምዕመናኖቹ የተነሡት በልማት ሰበብ እንጂ በመስጊድ ሰበብ እንዳልሆነ ሃገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው፡፡) 6. ከመቼ ጀምሮ ነው ቤተ ክርስቲያንና ሌሎች የእምነት ድርጅቶች ማምለኪያ ቦታቸውን ሲሠሩ መሠረት ድንጋይ ለማስቀመጥ ከንቲባውና የሰላም ሚኒስተር ተገኝተው የሚያውቁት፤ ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አግኝተው ይሆንን!!! (በአካባቢው ለሚኖረው ብዙ ሕዝበ ክርስቲያን በቂ መጠለያ እንኳን የሌለው ቅጽረ ቤተ ክርስቲያን እያለው፤ ከአጠገቡ የ200 ሜትር እንኳን ርቀት በሌለው ያውም በቊጥር አነስተኛ ለሆኑ ሙስሊም ወንድሞቻችን 30ሺህ የሚጠጋ ካሬ ሜትር ለመስጠት መዘጋጀቱ፤ የተፈራ ዋልዋና የአሊ አብዶ ለእስልምና የተሠራ ደባና እንድናስታውስ ያደርገናል፡፡) *** ስለዚህ ይህንን ተግባር መንግሥት በአስቸኳይ እንዲያቆም በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን፤ ካልሆነ ግን ወደ አላስፈላጊ ግጭት ያመራናል። ** መሠረት ለመጣል የሚገኙት ከንቲባውና የሰላም ሚኒስተር ሞፈሪያትም ሌላው የእምነት ተቋም ላይ ለመሠረት ድንጋይ ተገኝተው የማያውቁትን እዚህ ልገኝ ብለው ያሰቡትን ልብ ብለው ቢያስቡበት መልካም ነው፡፡ ''ይትባረክ አምላከ አበዊነ'' (ዘገባው የአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስያን ሰ/ት/ቤት ነው፡፡)

ስለሚሰራው መስጊድ ቅሬታ አለን። አሁኑኑ (#እጅግ_በጣም_አስቸኳይ_ #share #share ማድረግዎን አይዘንጉ፡፡) ምዕመናኖቹ የተነሡት በልማት ሰበብ እንጂ ለመስጊድ መሥሪያ ተብለው እንዳልሆነ ሃገር ያወቀው፥ ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ በአፍሪካ ኅብረት ማስፋፊያ ልማት ተነሥቶ አሁን ባለበት ቦታ ሲቀመጥ ተገቢው ማካካሻ ቦታ ስላልተሰጠው ከዛሬ ነገ ይሰጠኛል ብሎ እየጠበቀ ባለበት ሁኔታ፤ በቦታው ላይ ቀድሞ ቦታ ለሌላው እምነት መስጠት በራሱ ውሳጣዊ ችግርና ደባ ለመሆኑ አመላካች ነው፡፡ በአካባቢው ለሚኖሩ ብዙ ሕዝበ ክርስቲያን በቂ መጠለያ እንኳን የሌለው ቅጽረ ቤተ ክርስቲያን እያለና በተደጋጋሚ ጥያቄ እየቀረበ ምላሽ ሳይሰጥ፤ ከአጠገቡ የ200 ሜትር እንኳን ርቀት በሌለው ያውም በቊጥር አነስተኛ ለሆኑ ሙስሊም ወንድሞቻችን መንግሥት 30ሺህ የሚጠጋ ካሬ ሜትር ለመስጠት መዘጋጀቱ፤ የተፈራ ዋልዋና የአሊ አብዶ ለእስልምና ያደላ ደባን እንድናስታውስ ያደርገናል፡፡ ++++++ በአ/ኅ/ደ/ም/ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ትይዩ በዛሬው ዕለት ለእስልምና እምነት ተከታዮች የአምልኮ ቦታ እንዲሆን 30,000 ካሬ የሚሆን ቦታ ተሰጥቶ በነገው ዕለት የመሠረት ድንጋይ ለመጣል እየተዘጋጁ ነው ሁላችሁም ፎቶውን እና መልዕክቱን በማንኛውም ማሕበራዊ ሚዲያ በማጋራት ሃይማኖታዊ ግዴታችንን እንወጣ !! በልማት ምክንያት ሃይማኖትን ማዳከም በግልጽ እየታየ ነው፡፡ በብዛት የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች የሚኖሩበትን ስፍራ በልማት ስም በማሰቃየት በ10 እና 15 ቀነ ገደብ አፍርሰው ለ5 እና 6 ዓመታት ያለምንም ልማት ኦና ሆኖ ተመልክተነዋል፡፡ ሆኖም አሁን በግልፅ ከላይ እንደጠቀስኩት ዓይነት ድርጊት ከመንግሥት አካላት የሃይማኖት ማዳከም ሥራ እየተካሄደ ነው፡፡ መስጊድ አይታነጽ ሳይሆን ከቤተክርስቲያን ይራቅ አንረባበሽ የሚለው ሀሳብ ቢያዝ የሰመረ ነው። በልማት ስም እምነትን የማስፉፉት ሴራ ከቀድሞውም የሹማምንት ግብር እንደሆነ ይታወቃል። አሁን ደግሞ በቀድሞ የሀገሪቱ አስተዳደር ለልማት በማለት የፈረሱ አካባቢዎችን እና ቦታዎችን ለእስልምና አማኞች መስጊድ እንዲሰሩባቸው በመስጠት በስልጣን ወንበር የተቀመጡ የእምነቱ ተከታዮች ጫና እያደረጉ ይመስላል። ከታች በምስሉ ምትመለከቱት ቦት በተለምዶ ቡልጋርያ አካባቢ ሀያ ቀበሌ ወይም ሳይቬርያ የሚባለው አካባቢ ሲሆን እዚህ አካባቢ ላይ አብዛኞቹ የክርስትና እምነት ተከታዮች የነበሩበት ነው። እንደተለመደው ልማት በሚባለው መንግስታዊ ቋንቋ ከተነሱ ከ4 ዓመት በላይ አስቆጥረዋል።ቦታውም ጫካ ሆኖ ዛፎች በቅለውበት መንግስታዊ ሳይሆን ተፈጥሯዊ ልማትን ይዟል። ታድያማ አሁን ያለው የአዲስ አበባ አስተዳደር የእስልምና ማዕከልና መስጊድ ይሰሩበት ዘንድ እዚያው ቦታ ላይ 30 ሺ ካሬ ለግሷቿል የሚል ተባራሪ ወሬ ሰማን። መጠርጠር ደግነቱ አስቀድሞ ለመጮህ የተመቸ ይሆናል። ይደንቃል ቤተክርስቲያን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ስትጠይቅ መከራ እንዳላየች ሁላ እንደቀልድ አንድ መንደርን ብድግ አደርጎ እንካቹ ማለት ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው። ታድያ ምን ችግር አለው የሚል ጥያቄ መጠየቁ የማይቀር ነው የነዋሪው እና የአካባቢው ቅሬታ ይህ መስጊድ እንዲሰራበት የተሰጠው ቦታ በጣም ቅርብ በሚባል ሁኔታ ከ27 ዓመት በላይ የቆየ የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አለ በተለመዶም ሙሉ ስሙ የአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ተብሎ ይጠራል። ብዙ የክርስትያን ነዋሪ በሚገኝበት ቦታ መሥራቱ ሳይከፉ ቤተክርስቲያን አጠገብ የመስጊድ ሥራን አምጥቶ መደቀኑ ይዋጣላቹ ይለይላቹ የሚል መልእክት ያለው ይመስላል። ካልጠፋ ቦታ አብያተ ክርስቲያናት በሚገኙበት ቅርብ ርቀት ላይ መስጊድ ስሩ ብሉ ይሁንታን መስጠት ምን የሚሉት ችሮታ ነው። ከዚህ በፊትም ለቱርክ ባለሃብቶች የተዘጋጀ ቦታ እየተባለ ለሃይማኖታዊ ግልጋሎት ሲውል ባናይም ሰምተን ግን አልፈናል። አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ አንድ ቀበሌ የሚያክል ቦታ መስጠት ወንበር ከመልቀቄ በፊት የሚል ሴራ የያዘ እንዲመስለን ሆኗል። ሌላው ትልቁ ችግር በብዙ ትእግስት ተቀመጦ የነበረውን ወጣት ማነሳሳቱ ነው። በአካባቢው ያሉ ይሆን ከሩቅ ያሉ ወጣቶች ይህን ሲሰሙ ከነፍስ ያለፍ ትርፍ ምን አለ በሚል ግብግብ ውስጥ ገብተው አላስፈላጊ የሆኑ ግጭቶችን አለመግባባቶችን ያስከትላል። ተቻችለን እንኑር ብሎ የሰከነውን ወጣት ያደገበት አጥቢያ ቤተክርስቲያን ላይ መጥቶ "አላሁ አክበር" የሚል ድምጽ ማሰማት ንቀት ስለሚመስል አሁንም ከቤተክርስቲያን ቅርብ ርቀት ለመስጊድ ተብለው የሚሰጡ ቦታዎች ቢታሰሰብባቸው ጥሩ ነው። ከ50 ሚልዮን በላይ ተከታይ ያላትን ቤተክርስቲያን መጥቀም ባንችልም መጉዳቱ ዋጋ የሚያስከፍል ስለሆን ዓመጽ ሳይበረታ ቡልጋርያ አካባቢ አፍሪካ ህብረትን ታኮ የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ካለበት ቅርብ ርቀት ላይ የተሰጠው የመስጊድ መስርያ 30.000ካሬ መሬት በተለዋጭ መሬት ቦታ ቢለወጥ መልካም ነው ይህ ሥራ የሀገር ባለውለታ ቤተክርስቲያንን መናቅ ነውና ክቡራን ሹማምንት በተለይ የመሰጊዱ አሰሪ መኳንንቶች አስቡበት። ወሬ ነጋሬ እንዳበጀው ነገ በ12 የመሠረት ድንጋይ በከንቲባው እና በሚኒስተር ሞፈሪያት የሚጣል ሲሆን የቤተክርስቲያናችን ሰበካ ጉባኤ እና አስተዳደር መስጊድ ይሰራበታል የተባለበትን ቦታ አይተዋል በቦታው የእምነቱ ተከታዮች ለነገው መሠረት ድንጋይ የሚጣልበትን ሲያጸዱ ተመልክተዋል። እኛ ጉዳያችን ከሙስሊም ወንድሞቻችን ጋር አይደለም ጥያቄያችን እዚህ ቦታ ላይ አጠገብ ለአጠገብ ሕገ መንግስቱ ላይ የተቀመጠውን እንኳን ባላከበረ መልኩ 200 ሜትር እንኳን በማይሞላ ርቀት እንዴት ይታሰባል።

፠ ‹‹አባቴ ተክለ ሃይማኖት የሚለኝ ሁሉ፤ በፍልሰቴ ቀን በገዳሜ ይገኝ እኔም ልጄ እለዋለው ከቅዱስ ሚካኤልና ከልጄ ፊልጶስ ጋር እባርከዋለው።›› /ገድለ ተክለ ሃይማኖት/ ፠ አባታችን ባረፉ በ54ኛ ዓመታቸው በ1354 ዓ.ም በአፄ ሰይፈ አርዕድ ዘመን ለ4ኛው እጨጌ ሕዝቅያስ ተገልጸው አጽማቸው ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል፡፡ ፠ ግንቦት 12 በደብረ ሊባኖስ ትልቁ በዓል ነው፡፡ ጥንተ መሠረቱም፤ 12ቱ እጨጌዎች ከያሉበት ቦታ እየመጡ 1ድ 1ድ ወር ሙሉ በፈረቃ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ቅዱስ አጽም ተራ ገብተው ያጥኑ ነበር፡፡ ግንቦት 12 ግን ሁሉም ከያሉበት ተሰባስበው በአንድነት ያከብራሉ፡፡ #የጻድቁ_ዋና_ዋና_የታሪክ_ሂደቶች፤ ፠ከአባታቸው ከቅዱስ ጸጋ ዘአብና ከቅድስት እግዚዕ ኀረያ፤ መጋቢት 24 ቀን ተጸንሰው፤ በታኅሣሥ 24 ቀን በ1190 ዓ.ም. በእቲሣ ተወለዱ፡፡ ፠በተወለዱ በ3ኛው ቀን አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብለው ፈጣሪያቸውን አመሠገኑ፡፡ ፠በተወለዱ በ40ኛው በደብረ አጋዓዚት ማርያም ፍስሐ ጽዮን “የጽዮን ደስታ” ተበለው ተጠሩ፡፡ ፠እስከ 7 ዓመታቸው ድረስ ከአባታቸው ከጸጋዘአብ ዘንድ እየተማሩ ፠በ15 ዓመታቸው ዲቁናን ከጌርሎስ ዘንድ ተቀበሉ፡፡ ፠በ22 ዓመታቸው ከአቡነ ጌርሎስ ዘንድ ቅስናን ተቀበሉ፡፡ ፠በከተታ አውራጃ 3 ዓመት ወንጌልን እያስተማሩ ብዙ ድንቅ ነገርን አደረጉ፡፡ ፠በኅዳር 24 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ወደ ላይ ነጠቃቸው ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ካህን ሆነው የሥላሴን መንበርን አጠኑ ፠በሐይቅ እስጢፋኖስ 10 ዓመት፥ በደብረዳሞ 12 ዓመት ኖረዋል፡፡ ፠በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች እየተዘዋወቱ አስተምረዋል፤ በአኵሱም ጽዮን፣ በዋልድባና በዙሪያቸው ባሉ ገዳማት እየዞሩ ተሳልመዋል፡፡ ወደ ኢየሩሳሌም በመውረድም ተሳልመው ተመልሰዋል፤ ሲመለሱም ብዙ ቅዱሳን አብረዋቸው ተመልሰዋል፡፡ /እነ እጨ ዮሐንስ ዘጎንድ (ዘጠገሮን) ልብ ይሏል፡፡ ፠በ1267 ዓ.ም ደብረ ሊባኖስን በአት አድርገው ኖሩ፡፡ ለ22 ዓመት ቆመው በመጸለይ የአንድ እግራቸው አገዳ ተሠበረ ደቀ መዝሙሮቻቸው በጨርቅ ጠቅልለው ቀበሩት፡፡ በአንድ እግራቸው ለ7 ዓመት በጸሎት ቆሙ በጠቅላላው ለ29 ዓመት በጸሎት ከቆሙ በኋላ በ99 ዓመት ከ10 ወር ከ10 ቀን ነሐሴ 24 ቀን 1290 ዓ.ም አረፉ፡፡ ፠፠፠አባታችን ባረፉ በ54ኛ ዓመታቸው በ1354 ዓ.ም በአፄ ሰይፈ አርዕድ ዘመን ለ4ኛው እጨጌ ሕዝቅያስ ተገልጸው አጽማቸው ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል፡፡ ፠የደብረ ሊባኖስንም ቦታ የሰጠው ሐኖ (ተክለ ሃይማኖት) /የግራርያ ሰው/፤ ሲሆን ዓፄ ልብነ ድንግል በነገሠ በ8ኛው ዓመት ‹መርሕ› ከምትባል ስፋራ ታቦቱ ከነዋየ ቅድሳቱ ጋር ‹ከምድኃሬ› ተዛውሯል፡፡ ይህንንም ያደረገው እጨጌው አባ ጴጥሮስ ነበር፡፡ #የጻድቁ_ክብረ_በዓላቶቻቸውም፤ #ኅዳር 24፤ ከካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን መንበር ያጠኑበት #ታኅሣሥ 24፤ የአባታችን ልደት #ጥር 24፤ የአባታችን ስባረ አጽም #መጋቢት 24፤ የአባታችን ጽንሠት #ግንቦት 12፤ የአባታችን ፍልሰተ አጽም #ነሐሴ 24፤ የአባታችን በዓለ እረፍት ናቸው፡፡ ፠ ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ፤ እስመ በውስቴታ ተገብረ ፍልሰተ ሥጋሁ ወአጽሙ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ዝክረ ቅዱስ ያሬድ ማክሰኞ ግንቦት 11/2012 ዓ.ም. ከታች በተዘረዘሩት በ3ቱ ቀጥታ ይተላለፋል፡፡ ፠ በEOTC Daily Prayer Sermon https://www.youtube.com/watch?v=B
+2
ዝክረ ቅዱስ ያሬድ ማክሰኞ ግንቦት 11/2012 ዓ.ም. ከታች በተዘረዘሩት በ3ቱ ቀጥታ ይተላለፋል፡፡ ፠ በEOTC Daily Prayer Sermon https://www.youtube.com/watch?v=BylxRxzTg4Q ፠ በዳላስ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል (Dallas Debre Meheret Saint Michael EOTC) https://www.facebook.com/DallasMichaeleotc/?__tn__=kCH-R&eid=ARB4uklsHUef5OsLZl9Vj0Fwg2N88Qbq6kNQXK8H8ls3gLTXceTY_o0L-kiLay36CQlA0uOBNFrPXEkQ&hc_ref=ARRpkBWvHBrPY1UVssHFP2NR5yb8yW8whdCedp6vuGmYUI7r3Mj2Gkq4hd6pJ9v6nBQ&fref=nf ፠ በአትላንታ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሰንበት ትምህርት ቤት ከ6 - 8 PM (መግቢያ፤ 4708692200 ኮድ፤ *7365791672)

በቅዱስ ያሬድ ወንበር ተተክተው ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ የቅዱስ ያሬድን ዜማውን ከነይትበሃሉ፥ ምልክቱን ከነድምፁ (ድጓውን፣ ጾመ ድጓውን፣ መዋስዕት፣ ዝማሬንና ምዕራፍን) ለመምህርነት ደረጃ እ
+1
በቅዱስ ያሬድ ወንበር ተተክተው ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ የቅዱስ ያሬድን ዜማውን ከነይትበሃሉ፥ ምልክቱን ከነድምፁ (ድጓውን፣ ጾመ ድጓውን፣ መዋስዕት፣ ዝማሬንና ምዕራፍን) ለመምህርነት ደረጃ እያስተማሩ ያሉ ሦስት ዐበይት የምስክር ጕባኤ መምህራን እነዚህ ናቸው፡፡ ጕባኤዎቻቸውም ዐዘቅተ ጥበብ (የጥበብ መፍለቂያ በመባል ይታወቃሉ፡፡) እነዚህም ቤተ ልሔም፣ ዙር አባ አቡነ አረጋዊ ናቸው፡፡ አምላከ ቅዱስ ያሬድ በረድኤት፥ በበረከት፥ በጤና፥ በመግቦት ይጠብቅልን፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#የቅዱስ_ያሬድ_የዜማው_ይዘት_፤ #የዜማው_ጠባያት_፤ #ከሌሎች_ዓለማዊ_ዜማዎች_የሚለይበት_ጠባይና_ #የዜማው_ጥቅም #ሀ_የቅዱስ_ያሬድ_የዜማው_ይዘት ፠ቅዱስ ያሬድ ዜማውን ያዘጋጀው ከብሉያት፣ ከሐዲሳት፣ ከሊቃውንት መጻሕፍት እየመረጠ ለምስጋናና ለጸሎት እንዲኾኑ አድርጎ ነው፡፡ ፠ዜማው ምስጢሩ የማይጠገብ፥ቃሉ የሚያረካ፥ አነጋገሩ የተሳካ፥ ጣዕመ ቃሉና ኀይለ ቃሉ ደስ የሚያሰኝ፥ ልብን የሚነካ ነው፡፡ ፠በይዘቱም የሥነ ፍጥረት ውበትን በማድነቅና የሥነ ፍጥረት አስገኝ የኾነውን እግዚአብሔርን በማመስገን ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ፠በአጠቃላይ የቅዱስ ያሬድ ድርሰት ጌታ ለሰው ልጆች ሲል በዚህ ዓለም የፈጸመውን የማዳን ሥራ ሁሉ ገልጦ የሚያስረዳ ነው፤ የቅድስት ድንግል ማርያምን፣ የቅዱሳን መላእክትን፣ የነቢያትን፣ የሐዋርያትን፣ የጻድቃንና የሰማዕታትን ክብርና ቅድስና በማውሳት በስማቸው መማፀንና መጸለይ የሚያስገኘውን ጥቅም የሚያስረዳ ታላቅ ዜማዊ ሀብት ነው፡፡ ፠ከእርሱ በፊት የነበሩና በእርሱ ዘመን የተጻፉ የቅዱሳን ገድላትና ድርሳናትን እንዲሁም የበዓላትን ጥንታዊ አመሠራረት ውስጠ ምሥጢር በማስረዳት በዜማ ድርሰቱ አካቷል፡፡ ፠ምስጋናውንም ለአራቱ ክፍላተ ዘመን ለክረምት፣ ለመፀው (ለጥቢ)፣ ለሐጋይ (ለበጋ)፣ ለጸደይ (ለበልግ) እንዲኾን አዘጋጅቶታል፡፡ #ለ_የዜማው_ጠባያት ፨የቅዱስ ያሬድ ዜማ ሰማያዊ በመኾኑ ኅሊናን የመመሠጥ፣ ሥጋዊ ደስታንና ኀጢአትን ከማሰብ የመጠበቅ፣ ሰማያዊውን ድንቅ የምስጋና ምስጢር የማሳወቅ ኀይል አለው፡፡ ፨ከእግዚአብሔር የተገኘ ስጦታም በመኾኑ ብልየት (እርጅና)፣ ውላጤ (መለወጥ) የማይታይበት ዘወትር ሕያው የኾነ ብቸኛ ዜማ ነው፡፡ ፨የመንፈስ ቅዱስ ስጦታም በመኾኑ ዘወትር አዲስና የማያልቅ ጥልቅ ምንጭ ያለው ሕይወትን የሚያለመልም ነው፡፡ ፨ዜማውም ሰማያዊና መንፈሳዊ፣ ከእግዚአብሔር የተገኘ ለመኾኑ ማስረጃ የሚኾነን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ውጪ ያሉ ሰዎች ዜማውን ለተለያየ ዐላማ ይመኙታል፤ ነገር ግን ለመያዝም ኾነ ለመወሰን አይችሉም፡፡ ምክንያቱም በምድራዊ ጥበብና ፍልስፍና የሚያዝ የሚወሰን ሳይኾን ታላቅ መሥዋዕትነትን የሚጠይቅ፣ ሌት ተቀን ልቡናን ለሥላሴ ሰጥተው ከእግዚአብሔር የሚያገኙት በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የሚያጸኑት፣ የሚማሩትና የሚያዜሙት እንጂ በገንዘብ የማይገዛ ታላቅ ጸጋ መኾኑ ነው፡፡ #ሐ.#የቅዱስ_ያሬድ_ዜማ_ከሌሎች _ዓለማዊ_ዜማዎች_የሚለይበት_ጠባይ፤  ዜማው አሳብን የሚገዛ፣ ከሥጋ ይልቅ በመንፈስ መመላለስን የሚያስተምር በመኾኑ፤  በአቀራረቡም የተወሰነ የዜማ ስልትና ቀመር ያለው በመኾኑ፤  ዜማው በአዝማናት ተለይቶ በወቅት ተከፋፍሎ የሚዜም መኾኑ፤  ማንኛውም ሰው ከተወሰነ የዜማ ስልትና ቀመር ውጪ በራሱ ፍላጎት የድምፅ ቅላጼውን ለማሳመር ስለፈለገ የሚያሻሽለው ወይም የሚለውጠው አለመኾኑ፤  ዜማው በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ምሥጢር የተሞላ መኾኑና  የዜማው ምልክቶችና ዐይነቶች ጥልቅ ምሳሌና ምስጢር ያላቸው መኾናቸው ነው፡፡ #መ_የቅዱስ_ያሬድ_ዜማ_ጥቅም ሀ. የቤተ ክርስቲያንን አንድነት በመጠበቅ፤ በየትኛውም አካባቢ የምትኖር የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አንድ ዓይነት መዝሙር፣ አንድ ዓይነት ቅዳሴ፣ አንድ ዓይነት ማኅሌት፣ አንድ ዐይነት ሥርዐት በአንድ ዓይነት ጊዜ በአንድ ቀን ማቅረብና መፈጸም እንድትችል አስችሏታል፡፡ ለ. በነገረ መለኮት ትምህርት፤ ሊቁ የትርጓሜ መምህር ስለሆነ ከብዙ መጻሕፍት ስለሚጠቅስና የሃይማኖት ትምህርቱትንም በዜማ አቀነባብሮ መድረሱ በጣም ተወዳጅ ትምህርት እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ሐ. በሥርዓተ ጸሎት፤ ከዓመት እስከ ዓመት ለሚከናወኑ (የዘመናትና የሳምንታትን ጨምሮ) ማንኛውም ሥርዐተ ጸሎት ዋና መሪው የቅዱስ ያሬድ ድርሰት ነው፡፡ ማኅሌቱ፣ ቅዳሴው፣ ፍትሐቱ፣ ጥምቀተ ክርስትናው ሁሉ በዜማው መሪነት የሚከናወኑ አገልግሎቶች ናቸው፡፡ መ. ለቱሪዝም ሀብት (መስህብነት)፤ ክርስቲያናችን በየወሩና በየዓመቱ ከምታከብራቸው በዓላት ላይ ከሚቀርቡት ዝግጅቶች አብዛኛውን ክፍል የሚይዘው በቅዱስ ያሬድ ዜማ የሚቀርበው የዝማሬና የቅዳሴ አገልግሎት ነው፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

የቅኔ ጀማሪም ነው፡፡ ‹‹ሕንፄሃ …›› የሚለውን ቤት መምቻ ያለውን ቅኔ ልብ ይሏል፤ አንድ ባለቅኔ ግን ይህን ሳይረዳ ‹‹ተትሕተ ያሬድ …›› የሚል ቅኔን ተቀኝቷል፡፡ #የቅዱስ_ያሬድ_አስደናቂ_ነገሮች ፠#ከጌዴዎን ዘንድ ትምህርቱን አቋርጦ ሄደ ስንል፤ በአንድ ሾላ ዛፍ ላይ በትል አማካይነት ትዕግስትንና ማስተዋልን ቀስሞ፤ ወደ አጎቱ ተመልሶ ተምሮና ትምህርትን አምላክ ገልጾለት መምህረ መምህራን ሁኖ እንገኘዋለን፤ /እግዚአብሔር አምላክ ለቅዱስ ያሬድ ያንን ኹሉ ጥበብ ቶሎ ያልገለጸለት በቀላሉ ቢያገኘው ኋላ እንዳይታበይ ብሎ ነው፤ የሐዊራ ብስድር እስክንድራን ታሪክ ልብ ይሏል) ፠#መምህር ነው ስንል፤ መናኝ ባሕታዊ ኾኖ እናገኘዋለን፤ /በደብረ ሐዊ ለ22ዓመታት መመኑን ልብ ይሏል/ ፠#መናኝ ነው ስንል የተለያዩ የሃገራችንን ክፍሎች ገዳማትና አድባራት ሲጎበኝ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ሲጓዝ እንገኘዋለን፤ /ጣና ቂርቆስ፤ ዙር አባ አቡነ አረጋዊ፣ …. ሌላውንም ልብ ይሏል) ፠#ወደ ገዳማትና አድባራት ይጓዛል ስንል፤ ወደ ደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ በደመና ተጭኖ ሂዶ ምሽቱን ወደ በዓቱ ሲመለስ እንገኘዋለን፡፡ ፠#በሃገራችን በዋና ከተማ አኵሱም ተወልዶ ያደገ ነው ስንል፤ ሰው ሊኖርበት በማይችለው፥ በረድ በሚፈላበት፥ የነፋስ እሩምታ በሚያይልበት፥ ቅዝቃዜው አጥንት በሚሰነጥቅበት፥ ውርጩ እጅጉን በሚቀዘቅዝበት፥ ደመና በሚፈስስበት በራስ ደጀን ተራራ አጠገብ በደብረ ሐዊ መንኖ እናገኘዋለን፡፡ ፠#ከሰዎች ጋር አብሮ ኑሯል ስንል፤ ከሰው የማይቀርቡና በዐለማችን ላይ ብርቅዬ ኾነው በሃገራችን የሚገኙ ከሃገራችን ኢትዮጵያም በሰሜን ተራሮች በአብዛኛው ከሚገኙት ዋልያ ጋር አብሮ ሲኖር፤ ዋልያዎችንም እንደ መጓጓዣና እንደ መጫኛ ሲያገለግሉት እንገኛለን፡፡ ፠#በሙራደ ቃል የመላእክት ዜማ ተገልጾለት ተማረ ስንል፤ የግእዝ ቋንቋ ምሁርና ጠበብት ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ (ለተሰዓቱ ቅዱሳን መምህር መሆኑን ልብ ይሏል) ፠#የዜማ ጀማሪ አባት ነው ስንል ባለቅኔ ኾኖ እንገኘዋለን (ሕንፄሃ ወሡራሬሃ …. የሚለው ቅኔውን ልብ ይሏል)፤ ፠#ባለቅኔ ነው ስንል መተርጕም ኾኖ እንገኘዋለን፤ (ድጓው የብሉይና የሐዲስ ትርጓሜ መሆኑን ልብ ይሏል) ፠#መተርጕም ነው ስንል ባለታሪክ፥ የታሪክ ምሁር ኹኖ እናገኘዋለን፤ ፠#የታሪክ ምሁር ነው ስንል፤ የመርሐ አዝማን ሊቅ ኹኖ እናገኘዋለን፤ (ዓመቱን በሚገርም ሁኔታ ከወቅታቱ ጋራ አገናዝቦ መሠየሙን ልብ ይሏል) ፠#የመርሐ አዝማን ሊቅ ነው ስንል ቅዱስ ኾኖ እንገኘዋለን፤ የቅዱሳንም ጓደኛ ኹኖ እንገኘዋለን፡፡ /የአቡነ አረጋዊ፣ የአጼ ገብረ መስቀልን ታሪክ ልብ ይሏል፡፡/ ፠#ነቢይ ነው ሰንል ሐዋርያ ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ (ስለ ዳግም ምጽአት፣ ስለ መንግሥተ ሰማያትና …. ሌሎችንም ልብ ይሏል) ፠#ሐዋርያ ነው ስንል ሰማዕት ኹኖ እናገኘዋለን፡፡ (እግሩን በጦር መወጋቱን ልብ ይሏል)፤ ሌላም ሌላም …. ፠#በአጠቃላይ ምድራዊ ነው ስንል ሰማያዊ፤ ሰማያዊ ነው ስንል ምድራዊ (ብእሲ ሰማያዊ ወመልአክ ምድራዊ) ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ #ዜማውን በግዕዝ ዕዝል አራራይ የዜማ ስልት የደረሰ፤ #በዓለም ደረጃ የዜማ ምልክቶች ባልታወቁበት ጊዜ ዜማዎቹን በምልክት የቀመረ፤ #የዜማ ሥርዓትን በመንደፍ የዓመቱን ቀለም ያዘጋጀ፤ #ዜማውን በ4ት ዘመናት ከፋፍሎ፤ ዘመናቱን በንዑሳን ዘመናት ከፋፍሎ ለወራቱና ለሰሙኑ ለእለቱ የሚገባውን ቀምሮ የደረሰ፤ #እንኳን በእርሱ ዘመን ዛሬ እንኳን ብዙ ነገሮች ተሰባስበዋል በተባለበት ዘመን ሊሠራ አይደለም ሊታሠብ በማይችሉ መልኩ መጽሕፍትን እንደ ንብ እየቀሰመ፤ እንደ ወይን እየጨመቀ፤ እንደ አረቂ እያጣራ፤ እየተረጐመ ላሰበው ድርሠት ያዋለ፤ … ስለ ቅዱሱ ምኑን ተናግረን እንጨርሰዋለን፡፡ … ##.. ይኼማ ኢትዮጵያዊ ሊኾን አይችልም ብለው ብዙ የውጭ ሃገራት ወደ ራሳቸው ለመውሰድ የሚዳዳቸው፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

#ማሕሌቱን_ለማሕሌት_አባት_እናቅርብለት:: #የቅዱስ_ያሬድ_ሌሎች_መጠሪያ_ስሞች #ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘግንቦት_፲፩ #የቅዱስ_ያሬድ_ልደትና_የስሙ_ትርጓሜ #የቅዱስ_ያሬድ_ድርሰቶች፤ #የቅዱስ_ያሬድ_አስደናቂ_ነገሮች #የቅዱስ_ያሬድ_የዜማው_ይዘት_፤ #የዜማው_ጠባያት_፤ #ከሌሎች_ዓለማዊ_ዜማዎች_የሚለይበት_ጠባይና_ #የዜማው_ጥቅም #የቅዱስ_ያሬድ_ሌሎች_መጠሪያ_ስሞች ፠ ጥዑመ ልሳን፤ ፠ የሱራፌል አምሳያ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤ ፠ መዓርዒረ ዜማ፤ ፠ ካህን (ካህነ ስብሐት) ፠ ማኅሌታይ፤ ፠ መዘምር ዘበድርሳን፤ ፠ ሊቅ (ርእሰ ሊቃውንት) ፠ ዓርከ ሊቃውንት፤ ፠ ደራሲ፤ ፠ የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ) ፠ ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤ ፠ የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ ፠ ልዑለ ስብከት፤ ፠ ሰማዕት፤ ፠ ባሕታዊ፤ ፠ መናኝ ፠ የዜማ አባት፤ ፠ የኢትዮጵያ ብርሃን፡፡ ፠ አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም) የኾነ:: ፠ እግሮቹ በመልካም መንገድ የሚጓዙና ወደ መልካም መንገድ የሚያስጕዙ ፠ ልቡናው የቅድስና ማኅደር የኾነ:: ፠ ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ የኾነ:: ፠ አእምሮው የመጠቀ፤ ፠ ድርሰቱ የተራቀቀ፤ ፠ እስከ አርያም ተነጥቆ ዕፁብ ድንቅ ምሥጢራትን የተመገበ ማን እንደርሱ:: …... #ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘግንቦት_፲፩ /ማኅሌቱን በአ.አ ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ የምትቆሙ በደብረ ይባቤ የሚለውንና በሰማየዊ ቀለም የተቀባውን እየመረጣችሁ መጠቀም ስትችሉ፤ በሌሎች አድባራት ግን ሰማያዊ ቀለም የሌለበትን (በቢጫና እንዲሁ ያለቀለም የተቀመጠውን) እየመረጣችሁ መጠቀም ትችላላችሁ፡፡/ ፨*፨(ሥርዐተ ማኅሌቱን ስናዘጋጅ የደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያንን ይትበሃል በመንገር ለተባበራችሁን ለሊቀ ጠበብት አባ ኤርምያስና አርድዕቶቻቸው በተለይም ለዲ.ን አውራሪስ አምላከ ቅዱስ ያሬድ መድኀኔ ዓለም ይስጥልን፡፡) #የቅዱስ_ያሬድ_ልደትና_የስሙ_ትርጓሜ ꔰ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች ልደቱን 493 ዓ.ም. ነው ይላሉ፤ እንዲሁም አባቱ ኖኅ ነው ይሉና መሪጌታ ይስሐቅ የቀለም አባቱ /መምህሩ/ ነው ይላሉ፡፡) ꔰ የስሙም ትርጓሜም ያሬድ ማለት እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው ፡፡ እነዚህ መሣሪያዎች በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ የያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥቱ ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክትን፥ ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና፡፡ አንድም ያሬድ ርደት፣ ወሪድ፤ መውረድ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጵያ አውርዷልና፡፡ * አንድም ያሬድ ማለት ንብ ማለት ነው፤ ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከመጻሕፍት የማይጠቅሰው የማይቀሰመው የለም፤ አንድም ያሬድ ማለት ረአዬ ምሥጢር፥ ነጻሬ ኅቡአት ማለት ነው፤ የመላእክት ምሥጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፣ ነጻሬ ኅቡአት አለ፥ ኅቡእ (ስውር) የሆነ የጻድቃን፣ የሰማዕታት የነቢያት የሐዋርያትን ገድል አምልቶ አስፍቶም ይናገራልና፡፡ * አፄ ካሌብ ቤተ እስራኤል፣ ገብረክርስቶስና ገብረ መስቀል የሚባሉ ልጆች ነበሩት፤ ቅዱስ ያሬድ የተነሳው ከእነዚህ ውስጥ በአፄ ገብረመስቀል ዘመን ነው፡፡ #የቅዱስ_ያሬድ_ድርሰቶች፤ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ፤ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ፤ በከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ፡፡ #፩ኛ) #ምዕራፍ (ውዳሴ ማርያም በዜማን፣ መስተጋብዕ፣ አርባዕት፣ አርያም፣ ሠለስት፣ ክስተተ አርያምን) ያጠቃልላል፡፡ ፠ #የውዳሴ_ማርያም_ዜማ ቅዱስ ኤፍሬም ሦርያዊ የደረሰውን ለቅዱስ ያሬድ እየነገረው ልብን የሚመስጥ ዜማ ደርሶለታል፡፡ ፠ #መስተጋብዕ፤ ስብስብ ማለት ሲኾን፡፡ ከዳዊት መዝሙር (ከ180ው የመስተጋብእ ድርሰት 1ድ ድርሰት በስተቀር) ለጸሎትና ለዝማሬ ተስማሚ የኾነው እየተውጣጣ ለመዝሙር ተስማሚ የኾነው የተቀመረ ነው፡፡ መስተጋብዕ ሲጀምር ‹‹ወለቡ ጽራኅየ (ጩኸቴን ልብ አድርግ›› ብሎ ነው፡፡ በዐቢይ ጾም ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ጠዋት ጠዋት ይዘመራል፤ የቀድሞ መምህራን በፍልሠታም ይዘምሩት ነበር፤ ዜማው በዋነኛነት በግዕዝና በዕዝል ሲኾን በአራራይ ከሐሙስ ‹‹አንተሰ እግዚኦ ለዓለም›› የሚለውና ከቅማዴ ‹‹መንግሠትከሰ መንግሥት›› የሚለው ይገኙበታል፡፡ በየእለቱ እንዲደርስ (ከእሑድ በስተቀር) አድርጎ የደረሰው ነው፤ ፠ #አርባዕት፤ አራት አራተኛ ማለት ሲን በዳዊት መዝሙር በአራተኛው መሥመር ውስጥ እየገባ የሚዘመር ነው፤ ‹‹ቃልየ አጽምእ እግዚኦ ወለቡ ጽራኅየ፤ ወአጽምአኒ ቃለ ስእለትየ፤ ንጉሥየኒ ወአምላኪየኒ፡፡ ከፈጸመ በኋላ አርባዕት ይገባል፡፡ አርባዕት ሲጀመር ‹‹ቃልየ፤ ከመ ያፈቅርለ ጐሥዓ፤ ዐቢይ፤ ተሣሃለኒ›› ብሎ ነው (በዳዊት መዝሙር ጀምሮ ቀጥሎ በቅዱስ ያሬድ ድርሠት በኾነው በአርባዕት ያጠናቅቃል፡፡አብዛኛው በግጥም መልክ የተቀመረ ሲኾን አልፎ አልፎም በስድ ንባብ መልክ ይገኛል፡፡ ግእዝ ዕዝልና አራራይ ዜማ አለው፡፡ ፠ #አርያም፤ አርያም ልዑል፥ ከፍተኛ ማለት ሲኾን፤ ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ሰምቶ ‹‹ቀዳሚ ዜማ፤ አንድም ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ›› ስላመጣው ነው፡፡ ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብሎ የግጥም መል ባለው አእያም በተባለው ይጀምራል፡፡ በግጥም መልክና በስድ ንባብ ሲገኝ የግጠም አገጣጠሙ ከፍ ያለ የግጥም አገጣጠምን የተከተለነው፡፡ የሚባልበት ጊዜ በጾም ጊዜ በጾመ ድጓው እየገባ፣ በተለይ ደግሞ በክብረ በዓል ክሥተተ አርያም ሲደርስ ይዘመራል፡፡ #ሠለስት፤ ስምዐኒ ብሎ የሚጀምር ባለ ብዙ ሃሌታ ያለው፤ በዳዊት መዝሙር በሦስተኛው መሥመር እየገባ የሚዘመር፤ አንድም 3 መዝሙሮች ብቻ የሚዘመሩለት ብዙውን ጊዜ በግጥም የሚቀርብ ሲኾን፤ ይኽ ዜማ የሚደርሰው በክብረ በዓላት ዋይዜማ፤ በስብሐተ ነግህ፣ በአርያም፣ በጾመ ድጓ ውሎ፣ በአርያም፣ በሰንበት፣ በፍትሐት ጊዜ ነው፡፡ #ክስተተ_አርያም፤ የሰማይ መከፈት ማለት ሲኾን በታላላቅ በዓል ቀን እንዲሁም ታላላቅ? ሰዎች ሲሞቱ የሚዘመር ነው፤ ክስተትን ቅዱስ ያሬድ ያዘጋጀው ከዳዊት መዝሙራት፥ ከጸሎተ ነቢያትና ከራሱም ጭምር ኀይለ ቃል ያላቸውን ባለሁለት መስመሮች ሐረግ በመውሰድ ሲኾን ዜማው እጅጉን ነፍስና ሥጋን፥ ልብንና ኅሊናን የሚመስጥ ነው፡፡ ፪ኛ) #ጾመ_ድጓ፤ በዐቢይ ጾም የሚባል ነው፡፡ ፫ኛ) #ድጓ፤ በ4ት ክፍላተ ዘመናት የተቀመረና ጾመ ድጓን በውስጡ የሚያካትት ነው፡፡ ፬ኛ) #ዝማሬ፤ ቅዱስ ቊርባን ድርገት ሲወርድ ለቅዱስ ቊርባን ክብር የሚዘመር ነው፡፡ ፭ኛ) #መዋሥዕት፤ ሰው ሥጋው ከነፍ ስትለይ ፍትሐት የሚደረግበት ጸሎት ነው፡፡ ፮ኛ) #የ፲፬ቱ ቅዳሴያት ዜማ፤ 14ቱን ቅዳሴያት 14ት አባቶች የደረሷቸው ቢሆንም ዜማ የደረሰላቸው ግን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ፯ኛ) #አንቀጸ ብርሃንን፤ ድርሰቱ ነው፡፡ /ይቀጥላል……/ በተጨማሪም ደግሞ፤ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ዐይነቶች ግእዝ፣ ዕዝልና ዓራራይ በመባል ይታወቃል፡፡እነዚህ የዜማ ዐይነቶች የአንዱ ድምፅ ከሌላኛው ድምፅ ያልተደባለቀ፣ ወጥ የሆነ ድምፅ አላቸው፡፡ በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ትርጉም ያላቸው በሆኑ የዜማ ምልክቶች (ድፋት፤ ሂደት፤ ቅናት፤ ይዘት፤ ቁርጥ፤ ጭረት፤ ርክርክና ደረት) ደርሷል፡፡

#የቅዱስ_ያሬድ_ድርሰቶች፤#የዜማው_ይዘት_የዜማው_ጠባያት_ከሌሎች_ዓለማዊ_ዜማዎች_የሚለይበት_ጠባይና_የዜማው_ጥቅም #ሀ_የቅዱስ_ያሬድ_የዜማው_ይዘት ፠ቅዱስ ያሬድ ዜማውን ያዘጋጀው ከብሉያት፣ ከሐዲሳት፣ ከሊቃውንት መጻሕፍት እየመረጠ ለምስጋናና ለጸሎት እንዲኾኑ አድርጎ ነው፡፡ ፠ዜማው ምስጢሩ የማይጠገብ፥ቃሉ የሚያረካ፥ አነጋገሩ የተሳካ፥ ጣዕመ ቃሉና ኀይለ ቃሉ ደስ የሚያሰኝ፥ ልብን የሚነካ ነው፡፡ ፠በይዘቱም የሥነ ፍጥረት ውበትን በማድነቅና የሥነ ፍጥረት አስገኝ የኾነውን እግዚአብሔርን በማመስገን ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ፠በአጠቃላይ የቅዱስ ያሬድ ድርሰት ጌታ ለሰው ልጆች ሲል በዚህ ዓለም የፈጸመውን የማዳን ሥራ ሁሉ ገልጦ የሚያስረዳ ነው፤ የቅድስት ድንግል ማርያምን፣ የቅዱሳን መላእክትን፣ የነቢያትን፣ የሐዋርያትን፣ የጻድቃንና የሰማዕታትን ክብርና ቅድስና በማውሳት በስማቸው መማፀንና መጸለይ የሚያስገኘውን ጥቅም የሚያስረዳ ታላቅ ዜማዊ ሀብት ነው፡፡ ፠ከእርሱ በፊት የነበሩና በእርሱ ዘመን የተጻፉ የቅዱሳን ገድላትና ድርሳናትን እንዲሁም የበዓላትን ጥንታዊ አመሠራረት ውስጠ ምሥጢር በማስረዳት በዜማ ድርሰቱ አካቷል፡፡ ፠ምስጋናውንም ለአራቱ ክፍላተ ዘመን ለክረምት፣ ለመፀው (ለጥቢ)፣ ለሐጋይ (ለበጋ)፣ ለጸደይ (ለበልግ) እንዲኾን አዘጋጅቶታል፡፡ #ለ_የዜማው_ጠባያት ፨የቅዱስ ያሬድ ዜማ ሰማያዊ በመኾኑ ኅሊናን የመመሠጥ፣ ሥጋዊ ደስታንና ኀጢአትን ከማሰብ የመጠበቅ፣ ሰማያዊውን ድንቅ የምስጋና ምስጢር የማሳወቅ ኀይል አለው፡፡ ፨ከእግዚአብሔር የተገኘ ስጦታም በመኾኑ ብልየት (እርጅና)፣ ውላጤ (መለወጥ) የማይታይበት ዘወትር ሕያው የኾነ ብቸኛ ዜማ ነው፡፡ ፨የመንፈስ ቅዱስ ስጦታም በመኾኑ ዘወትር አዲስና የማያልቅ ጥልቅ ምንጭ ያለው ሕይወትን የሚያለመልም ነው፡፡ ፨ዜማውም ሰማያዊና መንፈሳዊ፣ ከእግዚአብሔር የተገኘ ለመኾኑ ማስረጃ የሚኾነን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ውጪ ያሉ ሰዎች ዜማውን ለተለያየ ዐላማ ይመኙታል፤ ነገር ግን ለመያዝም ኾነ ለመወሰን አይችሉም፡፡ ምክንያቱም በምድራዊ ጥበብና ፍልስፍና የሚያዝ የሚወሰን ሳይኾን ታላቅ መሥዋዕትነትን የሚጠይቅ፣ ሌት ተቀን ልቡናን ለሥላሴ ሰጥተው ከእግዚአብሔር የሚያገኙት በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የሚያጸኑት፣ የሚማሩትና የሚያዜሙት እንጂ በገንዘብ የማይገዛ ታላቅ ጸጋ መኾኑ ነው፡፡ #ሐ.#የቅዱስ_ያሬድ_ዜማ_ከሌሎች _ዓለማዊ_ዜማዎች_የሚለይበት_ጠባይ፤  ዜማው አሳብን የሚገዛ፣ ከሥጋ ይልቅ በመንፈስ መመላለስን የሚያስተምር በመኾኑ፤  በአቀራረቡም የተወሰነ የዜማ ስልትና ቀመር ያለው በመኾኑ፤  ዜማው በአዝማናት ተለይቶ በወቅት ተከፋፍሎ የሚዜም መኾኑ፤  ማንኛውም ሰው ከተወሰነ የዜማ ስልትና ቀመር ውጪ በራሱ ፍላጎት የድምፅ ቅላጼውን ለማሳመር ስለፈለገ የሚያሻሽለው ወይም የሚለውጠው አለመኾኑ፤  ዜማው በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ምሥጢር የተሞላ መኾኑና  የዜማው ምልክቶችና ዐይነቶች ጥልቅ ምሳሌና ምስጢር ያላቸው መኾናቸው ነው፡፡ #መ_የቅዱስ_ያሬድ_ዜማ_ጥቅም ሀ. የቤተ ክርስቲያንን አንድነት በመጠበቅ፤ በየትኛውም አካባቢ የምትኖር የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አንድ ዓይነት መዝሙር፣ አንድ ዓይነት ቅዳሴ፣ አንድ ዓይነት ማኅሌት፣ አንድ ዐይነት ሥርዐት በአንድ ዓይነት ጊዜ በአንድ ቀን ማቅረብና መፈጸም እንድትችል አስችሏታል፡፡ ለ. በነገረ መለኮት ትምህርት፤ ሊቁ የትርጓሜ መምህር ስለሆነ ከብዙ መጻሕፍት ስለሚጠቅስና የሃይማኖት ትምህርቱትንም በዜማ አቀነባብሮ መድረሱ በጣም ተወዳጅ ትምህርት እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ሐ. በሥርዓተ ጸሎት፤ ከዓመት እስከ ዓመት ለሚከናወኑ (የዘመናትና የሳምንታትን ጨምሮ) ማንኛውም ሥርዐተ ጸሎት ዋና መሪው የቅዱስ ያሬድ ድርሰት ነው፡፡ ማኅሌቱ፣ ቅዳሴው፣ ፍትሐቱ፣ ጥምቀተ ክርስትናው ሁሉ በዜማው መሪነት የሚከናወኑ አገልግሎቶች ናቸው፡፡ መ. ለቱሪዝም ሀብት (መስህብነት)፤ ክርስቲያናችን በየወሩና በየዓመቱ ከምታከብራቸው በዓላት ላይ ከሚቀርቡት ዝግጅቶች አብዛኛውን ክፍል የሚይዘው በቅዱስ ያሬድ ዜማ የሚቀርበው የዝማሬና የቅዳሴ አገልግሎት ነው፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#የቅዱስ_ያሬድ_አስደናቂ_ነገሮች ፠#ከጌዴዎን ዘንድ ትምህርቱን አቋርጦ ሄደ ስንል፤ በአንድ ሾላ ዛፍ ላይ በትል አማካይነት ትዕግስትንና ማስተዋልን ቀስሞ፤ ወደ አጎቱ ተመልሶ ተምሮና ትምህርትን አምላክ ገልጾለት መምህረ መምህራን ሁኖ እንገኘዋለን፤ /እግዚአብሔር አምላክ ለቅዱስ ያሬድ ያንን ኹሉ ጥበብ ቶሎ ያልገለጸለት በቀላሉ ቢያገኘው ኋላ እንዳይታበይ ብሎ ነው፤ የሐዊራ ብስድር እስክንድራን ታሪክ ልብ ይሏል) ፠#መምህር ነው ስንል፤ መናኝ ባሕታዊ ኾኖ እናገኘዋለን፤ /በደብረ ሐዊ ለ22ዓመታት መመኑን ልብ ይሏል/ ፠#መናኝ ነው ስንል የተለያዩ የሃገራችንን ክፍሎች ገዳማትና አድባራት ሲጎበኝ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ሲጓዝ እንገኘዋለን፤ /ጣና ቂርቆስ፤ ዙር አባ አቡነ አረጋዊ፣ …. ሌላውንም ልብ ይሏል) ፠#ወደ ገዳማትና አድባራት ይጓዛል ስንል፤ ወደ ደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ በደመና ተጭኖ ሂዶ ምሽቱን ወደ በዓቱ ሲመለስ እንገኘዋለን፡፡ ፠#በሃገራችን በዋና ከተማ አኵሱም ተወልዶ ያደገ ነው ስንል፤ ሰው ሊኖርበት በማይችለው፥ በረድ በሚፈላበት፥ የነፋስ እሩምታ በሚያይልበት፥ ቅዝቃዜው አጥንት በሚሰነጥቅበት፥ ውርጩ እጅጉን በሚቀዘቅዝበት፥ ደመና በሚፈስስበት በራስ ደጀን ተራራ አጠገብ በደብረ ሐዊ መንኖ እናገኘዋለን፡፡ ፠#ከሰዎች ጋር አብሮ ኑሯል ስንል፤ ከሰው የማይቀርቡና በዐለማችን ላይ ብርቅዬ ኾነው በሃገራችን የሚገኙ ከሃገራችን ኢትዮጵያም በሰሜን ተራሮች በአብዛኛው ከሚገኙት ዋልያ ጋር አብሮ ሲኖር፤ ዋልያዎችንም እንደ መጓጓዣና እንደ መጫኛ ሲያገለግሉት እንገኛለን፡፡ ፠#በሙራደ ቃል የመላእክት ዜማ ተገልጾለት ተማረ ስንል፤ የግእዝ ቋንቋ ምሁርና ጠበብት ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ (ለተሰዓቱ ቅዱሳን መምህር መሆኑን ልብ ይሏል) ፠#የዜማ ጀማሪ አባት ነው ስንል ባለቅኔ ኾኖ እንገኘዋለን (ሕንፄሃ ወሡራሬሃ …. የሚለው ቅኔውን ልብ ይሏል)፤ ፠#ባለቅኔ ነው ስንል መተርጕም ኾኖ እንገኘዋለን፤ (ድጓው የብሉይና የሐዲስ ትርጓሜ መሆኑን ልብ ይሏል) ፠#መተርጕም ነው ስንል ባለታሪክ፥ የታሪክ ምሁር ኹኖ እናገኘዋለን፤ ፠#የታሪክ ምሁር ነው ስንል፤ የመርሐ አዝማን ሊቅ ኹኖ እናገኘዋለን፤ (ዓመቱን በሚገርም ሁኔታ ከወቅታቱ ጋራ አገናዝቦ መሠየሙን ልብ ይሏል) ፠#የመርሐ አዝማን ሊቅ ነው ስንል ቅዱስ ኾኖ እንገኘዋለን፤ የቅዱሳንም ጓደኛ ኹኖ እንገኘዋለን፡፡ /የአቡነ አረጋዊ፣ የአጼ ገብረ መስቀልን ታሪክ ልብ ይሏል፡፡/ ፠#ነቢይ ነው ሰንል ሐዋርያ ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ (ስለ ዳግም ምጽአት፣ ስለ መንግሥተ ሰማያትና …. ሌሎችንም ልብ ይሏል) ፠#ሐዋርያ ነው ስንል ሰማዕት ኹኖ እናገኘዋለን፡፡ (እግሩን በጦር መወጋቱን ልብ ይሏል)፤ ሌላም ሌላም …. ፠#በአጠቃላይ ምድራዊ ነው ስንል ሰማያዊ፤ ሰማያዊ ነው ስንል ምድራዊ (ብእሲ ሰማያዊ ወመልአክ ምድራዊ) ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ #ዜማውን በግዕዝ ዕዝል አራራይ የዜማ ስልት የደረሰ፤ #በዓለም ደረጃ የዜማ ምልክቶች ባልታወቁበት ጊዜ ዜማዎቹን በምልክት የቀመረ፤ #የዜማ ሥርዓትን በመንደፍ የዓመቱን ቀለም ያዘጋጀ፤ #ዜማውን በ4ት ዘመናት ከፋፍሎ፤ ዘመናቱን በንዑሳን ዘመናት ከፋፍሎ ለወራቱና ለሰሙኑ ለእለቱ የሚገባውን ቀምሮ የደረሰ፤ #እንኳን በእርሱ ዘመን ዛሬ እንኳን ብዙ ነገሮች ተሰባስበዋል በተባለበት ዘመን ሊሠራ አይደለም ሊታሠብ በማይችሉ መልኩ መጽሕፍትን እንደ ንብ እየቀሰመ፤ እንደ ወይን እየጨመቀ፤ እንደ አረቂ እያጣራ፤ እየተረጐመ ላሰበው ድርሠት ያዋለ፤ … ስለ ቅዱሱ ምኑን ተናግረን እንጨርሰዋለን፡፡ … ##.. ይኼማ ኢትዮጵያዊ ሊኾን አይችልም ብለው ብዙ የውጭ ሃገራት ወደ ራሳቸው ለመውሰድ የሚዳዳቸው፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

#ማሕሌቱን_ለማሕሌት_አባት_እናቅርብለት:: #ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘግንቦት_፲፩ #፫) የቅዱስ_ያሬድ_ሌሎች_መጠሪያ_ስሞች ፠ ጥዑመ ልሳን፤ ፠ የሱራፌል አምሳያ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤ ፠ መዓርዒረ ዜማ፤ ፠ ካህን (ካህነ ስብሐት) ፠ ማኅሌታይ፤ ፠ መዘምር ዘበድርሳን፤ ፠ ሊቅ (ርእሰ ሊቃውንት) ፠ ዓርከ ሊቃውንት፤ ፠ ደራሲ፤ ፠ የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ) ፠ ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤ ፠ የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ ፠ ልዑለ ስብከት፤ ፠ ሰማዕት፤ ፠ ባሕታዊ፤ ፠ መናኝ ፠ የዜማ አባት፤ ፠ የኢትዮጵያ ብርሃን፡፡ ፠ አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም) የኾነ:: ፠ እግሮቹ በመልካም መንገድ የሚጓዙና ወደ መልካም መንገድ የሚያስጕዙ ፠ ልቡናው የቅድስና ማኅደር የኾነ:: ፠ ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ የኾነ:: ፠ አእምሮው የመጠቀ፤ ፠ ድርሰቱ የተራቀቀ፤ ፠ እስከ አርያም ተነጥቆ ዕፁብ ድንቅ ምሥጢራትን የተመገበ ማን እንደርሱ:: …... /ማኅሌቱን በአ.አ ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ የምትቆሙ በደብረ ይባቤ የሚለውንና በሰማየዊ ቀለም የተቀባውን እየመረጣችሁ መጠቀም ስትችሉ፤ በሌሎች አድባራት ግን ሰማያዊ ቀለም የሌለበትን (በቢጫና እንዲሁ ያለቀለም የተቀመጠውን) እየመረጣችሁ መጠቀም ትችላላችሁ፡፡/ ፨*፨(ሥርዐተ ማኅሌቱን ስናዘጋጅ የደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያንን ይትበሃል በመንገር ለተባበራችሁን ለሊቀ ጠበብት አባ ኤርምያስና አርድዕቶቻቸው በተለይም ለዲ.ን አውራሪስ አምላከ ቅዱስ ያሬድ መድኀኔ ዓለም ይስጥልን፡፡) #የቅዱስ_ያሬድ_ልደትና_የስሙ_ትርጓሜ ꔰ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች ልደቱን 493 ዓ.ም. ነው ይላሉ፤ እንዲሁም አባቱ ኖኅ ነው ይሉና መሪጌታ ይስሐቅ የቀለም አባቱ /መምህሩ/ ነው ይላሉ፡፡) ꔰ የስሙም ትርጓሜም ያሬድ ማለት እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው ፡፡ እነዚህ መሣሪያዎች በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ የያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥቱ ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክትን፥ ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና፡፡ አንድም ያሬድ ርደት፣ ወሪድ፤ መውረድ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጵያ አውርዷልና፡፡ * አንድም ያሬድ ማለት ንብ ማለት ነው፤ ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከመጻሕፍት የማይጠቅሰው የማይቀሰመው የለም፤ ** አንድም ያሬድ ማለት ረአዬ ምሥጢር፥ ነጻሬ ኅቡአት ማለት ነው፤ የመላእክት ምሥጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፣ ነጻሬ ኅቡአት አለ፥ ኅቡእ (ስውር) የሆነ የጻድቃን፣ የሰማዕታት የነቢያት የሐዋርያትን ገድል አምልቶ አስፍቶም ይናገራልና፡፡ *** አፄ ካሌብ ቤተ እስራኤል፣ ገብረክርስቶስና ገብረ መስቀል የሚባሉ ልጆች ነበሩት፤ ቅዱስ ያሬድ የተነሳው ከእነዚህ ውስጥ በአፄ ገብረመስቀል ዘመን ነው፡፡ #የቅዱስ_ያሬድ_ድርሰቶች፤ #፩ኛ) #ምዕራፍ (ውዳሴ ማርያም በዜማን፣ መስተጋብዕ፣ አርባዕት፣ አርያም፣ ሠለስት፣ ክስተተ አርያምን) ያጠቃልላል፡፡ ፠ #የውዳሴ_ማርያም_ዜማ ቅዱስ ኤፍሬም ሦርያዊ የደረሰውን ለቅዱስ ያሬድ እየነገረው ልብን የሚመስጥ ዜማ ደርሶለታል፡፡ ፠ #መስተጋብዕ፤ ስብስብ ማለት ሲኾን፡፡ ከዳዊት መዝሙር (ከ180ው የመስተጋብእ ድርሰት 1ድ ድርሰት በስተቀር) ለጸሎትና ለዝማሬ ተስማሚ የኾነው እየተውጣጣ ለመዝሙር ተስማሚ የኾነው የተቀመረ ነው፡፡ መስተጋብዕ ሲጀምር ‹‹ወለቡ ጽራኅየ (ጩኸቴን ልብ አድርግ›› ብሎ ነው፡፡ በዐቢይ ጾም ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ጠዋት ጠዋት ይዘመራል፤ የቀድሞ መምህራን በፍልሠታም ይዘምሩት ነበር፤ ዜማው በዋነኛነት በግዕዝና በዕዝል ሲኾን በአራራይ ከሐሙስ ‹‹አንተሰ እግዚኦ ለዓለም›› የሚለውና ከቅማዴ ‹‹መንግሠትከሰ መንግሥት›› የሚለው ይገኙበታል፡፡ በየእለቱ እንዲደርስ (ከእሑድ በስተቀር) አድርጎ የደረሰው ነው፤ ፠ #አርባዕት፤ አራት አራተኛ ማለት ሲን በዳዊት መዝሙር በአራተኛው መሥመር ውስጥ እየገባ የሚዘመር ነው፤ ‹‹ቃልየ አጽምእ እግዚኦ ወለቡ ጽራኅየ፤ ወአጽምአኒ ቃለ ስእለትየ፤ ንጉሥየኒ ወአምላኪየኒ፡፡ ከፈጸመ በኋላ አርባዕት ይገባል፡፡ አርባዕት ሲጀመር ‹‹ቃልየ፤ ከመ ያፈቅርለ ጐሥዓ፤ ዐቢይ፤ ተሣሃለኒ›› ብሎ ነው (በዳዊት መዝሙር ጀምሮ ቀጥሎ በቅዱስ ያሬድ ድርሠት በኾነው በአርባዕት ያጠናቅቃል፡፡አብዛኛው በግጥም መልክ የተቀመረ ሲኾን አልፎ አልፎም በስድ ንባብ መልክ ይገኛል፡፡ ግእዝ ዕዝልና አራራይ ዜማ አለው፡፡ ፠ #አርያም፤ አርያም ልዑል፥ ከፍተኛ ማለት ሲኾን፤ ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ሰምቶ ‹‹ቀዳሚ ዜማ፤ አንድም ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ›› ስላመጣው ነው፡፡ ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብሎ የግጥም መል ባለው አእያም በተባለው ይጀምራል፡፡ በግጥም መልክና በስድ ንባብ ሲገኝ የግጠም አገጣጠሙ ከፍ ያለ የግጥም አገጣጠምን የተከተለነው፡፡ የሚባልበት ጊዜ በጾም ጊዜ በጾመ ድጓው እየገባ፣ በተለይ ደግሞ በክብረ በዓል ክሥተተ አርያም ሲደርስ ይዘመራል፡፡ ሠለስት፤ ስምዐኒ ብሎ የሚጀምር ባለ ብዙ ሃሌታ ያለው፤ በዳዊት መዝሙር በሦስተኛው መሥመር እየገባ የሚዘመር፤ አንድም 3 መዝሙሮች ብቻ የሚዘመሩለት ብዙውን ጊዜ በግጥም የሚቀርብ ሲኾን፤ ይኽ ዜማ የሚደርሰው በክብረ በዓላት ዋይዜማ፤ በስብሐተ ነግህ፣ በአርያም፣ በጾመ ድጓ ውሎ፣ በአርያም፣ በሰንበት፣ በፍትሐት ጊዜ ነው፡፡ ክስተተ አርያም፤ የሰማይ መከፈት ማለት ሲኾን በታላላቅ በዓል ቀን እንዲሁም ታላላቅ? ሰዎች ሲሞቱ የሚዘመር ነው፤ ክስተትን ቅዱስ ያሬድ ያዘጋጀው ከዳዊት መዝሙራት፥ ከጸሎተ ነቢያትና ከራሱም ጭምር ኀይለ ቃል ያላቸውን ባለሁለት መስመሮች ሐረግ በመውሰድ ሲኾን ዜማው እጅጉን ነፍስና ሥጋን፥ ልብንና ኅሊናን የሚመስጥ ነው፡፡ ፪ኛ) #ጾመ_ድጓ፤ በዐቢይ ጾም የሚባል ነው፡፡ ፫ኛ) #ድጓ፤ በ4ት ክፍላተ ዘመናት የተቀመረና ጾመ ድጓን በውስጡ የሚያካትት ነው፡፡ ፬ኛ) #ዝማሬ፤ ቅዱስ ቊርባን ድርገት ሲወርድ ለቅዱስ ቊርባን ክብር የሚዘመር ነው፡፡ ፭ኛ) #መዋሥዕት፤ ሰው ሥጋው ከነፍ ስትለይ ፍትሐት የሚደረግበት ጸሎት ነው፡፡ ፮ኛ) #የ፲፬ቱ ቅዳሴያት ዜማ፤ 14ቱን ቅዳሴያት 14ት አባቶች የደረሷቸው ቢሆንም ዜማ የደረሰላቸው ግን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ፯ኛ) #አንቀጸ ብርሃንን፤ ድርሰቱ ነው፡፡ /ይቀጥላል……/ በተጨማሪም ደግሞ፤ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ዐይነቶች ግእዝ፣ ዕዝልና ዓራራይ በመባል ይታወቃል፡፡እነዚህ የዜማ ዐይነቶች የአንዱ ድምፅ ከሌላኛው ድምፅ ያልተደባለቀ፣ ወጥ የሆነ ድምፅ አላቸው፡፡ በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ትርጉም ያላቸው በሆኑ የዜማ ምልክቶች (ድፋት፤ ሂደት፤ ቅናት፤ ይዘት፤ ቁርጥ፤ ጭረት፤ ርክርክና ደረት) ደርሷል፡፡ የቅኔ ጀማሪም ነው፡፡ ‹‹ሕንፄሃ …›› የሚለውን ቤት መምቻ ያለውን ቅኔ ልብ ይሏል፤ አንድ ባለቅኔ ግን ይህን ሳይረዳ ‹‹ተትሕተ ያሬድ …›› የሚል ቅኔን ተቀኝቷል፡፡

እንኳን ለቅዱስ ያሬድ በዓለ ስዋሬ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡ #18ቱ_የቅዱስ_ያሬድ_ገዳማትና_አድባራት፡፡ እሑድ ግንቦት 11 ከዋይዜማው ጀምሮ ቀጠሯችሁን የት ለማድረግ አስባችኋል???፤ በአቅራቢያችሁ በሚገኙ የቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ታደርጉ ዘንድ 15ቱን የቅዱስ ያሬድ ገዳማትና አድባራት እናስተዋውቃችሁ፡፡ ፠ (#ቅዱስ_ያሬድን_ያልዘከረ_ኢትዮጵያዊ_ምኑን_ኢትዮጵያዊ_ኾነ!?) ፠ (#ቅዱስ_ያሬድን_ያልዘከረ_ካህን_ምኑን_ካህን_ኾነ!?) ፠ (#ቅዱስ_ያሬድን_ያልዘከረ_ሰንበት_ተማሪ_ምኑን_ሰንበት_ተማሪ_ኾነ!?) ፩ኛ). #ደብረ_ሐዊ_ቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ (ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት በበየዳ ወረዳ ቤተ ክህነት ከራስ ደጀን ተራራ አጠገብ የሚገኝ)፡፡ እመቤታችን በስደቷ ወቅት ያረፈችበት፤ ጃንደረባው ባኮስ የተሠወረበት፤ ቅዱስ ያሬድ ለ22 ዓመታት የመነነበት፥ ያስተማረበትና የተሠወረበት፤ በሀገራችን ትልቁ የሱባዔ መግቢያ ቅዱስ መካን፤ በዓለም ላይ በሃገራችን ብቻ፤ ከሀገራችንም በአብዛኛው በሰሜን ተራሮች ላይ ብርቅዬ ኾነው የሚገኙት ዋልያና ጭላዳ በአብዛኛው የሚገኙበት ቦታም ነው፡፡ በዚህ ቦታ ቅዱስ ያሬድ ያስተማረበትና የተማሪዎቹ ወንበር ጕባኤ ቦታና የደንጊያ ወንበር፤ ጽዮንን ከሩቅ እያየ ያለቀሰበት ቦታ ላይ የፈለቀ ጠበልና በዘንጉ ያፈለቀው ፈዋሽ ጠበል፤ የተሠወረበት የዋሻ ቤተ ክርስቲያን፣ እንዲሁም አበውና እማት የሚኖሩበት ገዳም ይገኛል፡፡) ፪ኛ). #በየዳ_ደብረ_ገነት_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ከርስቲያን፤ በደብረ ሐዊ ተራራ በስተጀርባ የሚገኝ ሲኾን፤ ቅዱስ ያሬድ በደብረ ሐዊ በምናኔ እንደመኖሩ መጠን በተራራው ጀርባ በገጠሩ መንደር የሚገኙ ምዕመናን እኛም ቅዱስ ያሬድን ልንዘክረው ይገባል፤ የቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ደብረ ሐዊ ላይ ብቻ ሳይኾን በኹሉም ቦታ መኖር ይገበዋል በሚል መንፈሳዊ ቅንዓት ተነሣሥተው የሠሩት ነው፡፡) ፫ኛ). #ጣና_ቂርቆስና_ቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ (ከፎገራ ከመንገዱ የ3 ሰዓት መንገድ እንደተጓዙ፤ በመርከብ ደግሞ ከባሕር ዳር፣ ከጎርጎራ፣ ከደልጊ፣ ከቁንዝላ ተሣፍረው ከጣና ክርስቶስ ሠምራ አጠገብ የሚያገኙት ታላቅ ገዳም ነው፤ መስዋዕተ ኦሪት ይሰዋበት የነበረ፤ ታቦተ ጽዮን ለበርካታ ዓመታት ያረፈችበት፤ ቅዱስ ያሬድ ምልክት ያለውን ድጓ የጻፈበት ቦታ ነው) ፬ኛ). #ወገራ_ደልደሊት_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን፤ (በሰሜን ጎንደር ወገራ አውራጃ አምባ ጊዮርጊስ ወረዳ የሚገኝ ሲኾን፤ በቅዱስ ያሬድ ዜማ ከብቶች ኹሉ ተመስጠው ሳያርሱ በመቆማቸው ምክንያት ቅዱስ ያሬድ የተገረፈበት ቦታ ነው) ፭ኛ). #አኵሱም_ደብረ_ዝማሬ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን፤ (ከአኵሱም ዩኒቨርሲቲ አጠገብ የሚገኝ ሲኾን፤ የአኵሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዴት ቅዱስ ያሬድ ተወልዶ ባደገባት፥ ተምሮ ባስተማረባት፤ ሰማያዊ ምሥጢራትና በተገለጡለት፤ የተሰዓቱ ቅዱሳንን የበርካታ ቅዱሳን መናኸሪያ በኾነችው፤ የገዳማትና የአድባራት ራስ፤ የምዕመናን ሁሉ አምባ መጠጊያ በኾነችው ከተማ እንዴት መታሰቢያ ቤተ ከርስቲያን ሳይሠራለት እስካሁን ቀረ ብለው በመንፈሳዊ መነሣሣት በአጭር ጊዜ ውስጥ ያሠሩት ቤተ ክርስቲያን ነው) ፮ኛ). #አኵሱም_ማይኪራህ_ደብረ_መድኀኒት_ወፈለገ_ጥበብ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን፤ (ከአኵሱም ከተማ በ4 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በቅዱስ ያሬድ የትውልድ ቦታ አጠገብ በዋናው መንገድ ዳር የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ነው፤ ቅዱስ ያሬድ ከትሏ መውደቅና መነሳት በመመልከት ማስተዋልን የተማረባት ቦታ ስትኾን ሾላዋ እስካሁንም ድረስ እየተካች ትገኛለች፤ ከሾላው ሠር የሚፈልቅ ፈዋሽ ጠበልም አለ፡፡ ይህ ቤተ ክርስቲያን የተሠራው የአኵሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የደብረ ዝማሬን ቤተ ክርስቲያን ሲሰሩ የሃገሬው ሰው ተመልክቶ እንዴት የትውልድ ቦታው ላይ እኛ ቤተ ክርስቲያን ሳንሠራ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቀድመውን ሠሩ በሚል መንፈሳዊ ቅንዓት ተነሣሥጠው በተፋጠነ ሁኔታ ያነጹት ነው፡፡) ፯ኛ). #አዲስ_አበባ_ደብረ_ይባቤ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን (አዲስ አበባ ጎተራ ማሰለጫ መንገድ አጠገብ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ሲኾን፤ የቅዱስ ያሬድ ፍቅር በልባቸው ባደረባቸው እናት ወ/ሮ ደስታ ሞላ በ1948 የተሠራ ሲሆን ኋላ ላይ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት የፓትርያርክነት ዘመን በምዕመናን አሁን ያለው ሕንፃ ቤ/ክ ተሠርቷል፤ የቅዱስ ያሬድ ትምህርቶች እየተሰጡበት የሚገኝና ወደፊትም በኮሌጅ ደረጃ አስፋፍቶ በርካታ ደቀመዛሙርትን ለማስተማር እቅዱ አለ፤ በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ፈዋሽ ጠበልም ይገኛል፡፡) ፰ኛ). #ጎንደር_ደብረ_ሣህል_ቅዱስ_ሩፋኤል_ወአቡነ_ሐራ_ድንግል_ቤተ_ክርስቲያን፤ (ይህ ቤተ ክርስቲያን በጎንደር ከተማ የሚገኝ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ ሲኾን፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ቅዱስ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፱ኛ). #ጎንደር_ጎሐ_ተራራ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን ፲ኛ). #ደብረ_ብርሃን_አንሳስ_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን (በደብረ ብርሃን ከተማ የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ስትኾን ፈዋሽ ጠበል ያለባትና፤ የአቋቋሙ ሊቅ፣ የቅዳሴና የሌሎች ዜማ ትምህርቶች መምህር የኾኑት የመምህር ለምኔ ማስተማሪያ ደብር ነች፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ቅዱስ ያሬድ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፲፩ኛ). #ጀርመን_ክሮምበርግ_ቅዱስ_ዑራኤልና_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን (በጀርመን ሃገር በክሮምበርግ ከተማ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያናችን ነው፡፡) ፲፪ኛ). #ዋሽንግተን_ዲሲ_ኆኅተ_ምሥራቅ_ኪዳነ_ምሕረት_ቤተ_ክርስቲያን፤ (በአሜሪካ ሃገር ዋሽንግተን ዲሲ የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ስትኾን፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፲፫ኛ). #ርዕሰ_አድባራት_ዱባይ_ሻርጃ_አጅማን_ሰአሊተ_ምሕረት_ቅድስት_ማርያም_ቤ/ክ (በዱባይ ሃገር ሻርጃ አጅማን የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ናት፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ቅዱስ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፲፬ኛ). #ባሕር_ዳር_ፈለገ_ጥበብ_ቅዱስ_ማርቆስና_ቅዱስ_ያሬድ ቤ/ክ፤ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ይባብ ካምፓስ አጠገብ የሚገኝ፡፡ ፲፭ኛ). #ደቡብ_አፍሪካ_የቅድስት_ሥላሴና_የቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ በደቡብ አፍሪካ የሚገኝ፡፡ ፲፮ኛ). #ድሬደዋ_ደብረ_ሰላም_መድኀኔ_ዓለም፤ (በዚህ ደብር ታቦተ ቅዱስ ያሬድ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፲፯ኛ). ደረስጌ ወረዳ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ፲፰ኛ). #ዳንግል_ደብረ_ሣህል_ቅዱስ_ሚካኤል_ቤ/ክ፤ በጎጃም ክፍለ ሃገር በአዊ ሃገረ ስብከት የሚገኝ ሲሆን በዚህ ደብር ታቦተ ቅዱስ ያሬድ ከ8/10/2008 ዓ.ም. ጀምሮ በድርብነት ይከበራል)፡፡ ከላይ በተጠቀሱት በአቅራቢያችን ባሉ ገዳማትና አድባራት እንድንገናኝ መድኀኔ ዓለም ይፍቀድልን፡፡ /አስተጋባኢ፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡/ ሌሎች ያላካተትናቸው ካሉና በፎቶ ያልዘገብናቸውን ጨምሩበት፡፡