ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 335 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 641 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 191 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 335 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 14 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -76، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 22.40‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.40‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 435 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 595 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 25.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 15 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 335
المشتركون
-124 ساعات
-67 أيام
-7630 أيام
أرشيف المشاركات
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለትና ቡልጋ፥ አይዞሽ አሞራ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → አይዞሽ አሞራ (ወደ ደብረ ሲና እየተጓዙ ሳለ በመገንጠል) → በለስ ዋሻ ኢየሱስ፡፡ ወይም ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → በኩክ የለሽ መንገድ → ዘንባባ ኢየሱስ → በለስ ዋሻ ኢሱስ (በእግር የ2 ሰዓት መንገድ) ፬. አማኑኤል ኢየሱስ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ምሥራቅ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ደንበጫ፥ አማኑኤል ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በባሕር ዳር መስመር (ከደብረ ማርቆስ 27 ኪ.ሜ) (በደጀንና በደንበጫ መሃል ላይ)፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ በውስጥ አሳውቁን) /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ጥር ፮፤ #በዓለ_ግዝረቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ፡፡ #በዓለ_ዕርገቱ_ለኤልያስ_ነቢይ፡፡ #በዓለ_ዕረፍቱ_ለኖኅ_አቡነ፡፡ #ግዝረተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ፠ ጌታችን በተወለደ በ8ኛ ቀኑ ዕጉለ ማዕነቅ ይዞ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ፠ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› /ሮሜ.፲፭፥፰/፡፡ ፠ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ በስምንተኛው ቀን እንደ ኦሪቱ ሥርዓት ግዝረት ይፈጸምለት ዘንድ ሕፃኑ ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ሲገረዝ የሊቀ ካህን ልጅ ነው ብለው ሊገርዙት ወደ እርሱ መጡ፡፡ ጌታችን ግን ወደ ምድር የመጣው ለትሕትና ነው እንጂ ለልዕልና አይደለምና ወሰዱት አለ /ትርጓሜ ወንጌለ ሉቃስ/፡፡ ፠ የእመቤታችን ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደመውጣቱ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ፡፡ እንዲሁ በተዘጋ ቤት መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እነዲሁ እንደፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ፡፡ #ቅዱስ_ኤልያስ_በእሳት_ሰረገላ_ወደ_ብሔረ_ሕያዋን_ያረገበት_ዕለት_ነው፡፡ **በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነቢያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነቢይ ነው፡፡ ✤  የሰማርያው ነቢይ ቴስቢያዊው ኤልያስ ከቅዱሳን አበው ነቢያት አንዱ ሲኾን አባቱ ኢያሴዩ እናቱ ደግሞ ቶናህ(ቶና) ሲባሉ ሲወለድ መላእክት በእሳት ሰፋድል (መጠቅለያ መጐናጸፊያ) ጠቅልለውት ነው፡፡ የስሙ ትርጉምም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ነው›› ማለት ነው፡፡ ** ኤልያስ ብዙ ነገር ስለሚያስተምር የቀና እምነቱን ውጤት ጥቂት መመልከት እኔ ማነኝ? ለሚሉት እጅ ይዞ ይመራል፡፡ ✤ 1. ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ ሰማይ ዝናም ለዘር፥ ጠል ለመከር ከመስጠት እንዲከለከል ምድርም የተከሉባትን ✤  2. አመጸኞች አክአብንና ኤልዛቤልን ምንነታቸውን ካሳወቀ በኋላ የዘጋውን ለመክፈት ወደ ፈጣሪው በመጸለይ ዝናም አዝንሟል፡፡ ✤ 3. በተፈጥሮ የማይመስላቸው በቋንቋም የማይግባባቸው እንኳን ለሰው ሥጋ ሊያመጡ ከሰው ሥጋ የሚነጥቁ አሞራዎች እንጀራና ሥጋ ለምግብ እንዲያመላልሱለት አደረገ 1ኛ ነገሥ. 17፥6-7፡፡ እነዚህ አሞራዎች ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ በጋ ከክረምት የለምንም እረፍት ኤልያስን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ እምነት ካለ ተአምር መሥራት አይገድም ይህንም ከኤልያስ ይማሯል፡፡ ✤ 4. ለአንዲት መበለት ዱቄትና ዘይት አበረከተ፤ ኤልያስ ቁራሽ እየለመነ ያደረገውን ተአምር ልብ ይሏል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 17፥16-24፡፡ ✤ 5. ዱቄትና ዘይት ያበረከተላት የሰራፕታዋ ሴት ልጇ /ኋላ ዮናስ ነቢይ የሆነው/ ቢሞት ከሞት አስነሳው 1ኛ ነገሥ. 17፥20-23 ✤ 6. ለብዙ ጊዜ በቤተ መንግሥት ተሰግስገው አክአብና ኤልዛቤልን በሐሰት ሲደልሉ፥ ግብዝ ሕብረተሰቡን ሲያታልሉ፥ ለፍቶ ያገኘው ገንዘቡን ሲሸልጉ፥ በኀጢአት ሊያስወጉ የነበሩ ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖትን በሕብረተሰቡ ፊት እስከ መምህራቸው ሰይጣን በቅሌት አከናንቦ ሲያስቅባቸው ውሏል፤ ሐሰቶች የነበሩትን 850 የሚጠጉ የጣዖት ካህናትንም ወደ ቂሶን ወንዝ አውርዶ ፈጅቷቸዋል፡፡ 1ኛ ነገሥ. 18 20 -29 ✤ 7. ወደ ፈጣሪው በጸሎት በማመልከት ያቀረበው ንጹሕ መሥዋዕቱን ከሰማይ እሳት ወርዶ በሰው ፊት በላለት (ተቀበለለት) 1ኛ ነገሥ. 18፥30-40፡፡ በዚህም ማንነቱን በሰይጣንና በሰይጣን አቀንቃኞች ፊት አስመስክሯል፡፡ ✤ 8. እሳት ከሰማይ በማዝነም ሊጣሉት የመጡትን መምለኪያነ ጣኦት፥ ምሉአነ ኀጢአት፤ የሰይጣን ሠራዊት በሰው ደም የሰከሩ፥ በዲያብሎስ የሚመሩ ጠላቶቹን አጋይቷል 2ኛ ነገሥ 1 9-13 ✤ 9. ምግብና መጠጥ መልአክ ከሰማይ አመጣለት ያንን ተመግቦ ለአርባ ቀን ያለምንም ምግብና መጠጥ እስከ እግዚአብሔር ተራራ እስከ ኮሬብ ድረስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ተጉዟል 1ኛ ነገሥ. 19፥5-7፡፡ ✤ 10. በመጎናጸፊያው የዮርዳኖስን ባሕር ከፍሎ ከነ ደቀመዝሙሩ በደረቅ ተሻግሯል 2ኛ ነገሥ. 2፥11፡፡ ለደቀመዝሙሩም ሀብተ መንገፈስ ቅዱስን አድሎታል፡፡ ✤ 11. በትህትናው ‹‹ይበቃኛል፤ አሁንም አቤቱ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ›› ብሎ እንዲሞት ለመነ፡፡ እግዚአብሔር ግን ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ918 ዓመተ ዓለም ሳይሞት በሕይወቱ መራራውን ሞት ዕያየው በብርሃን ሠረገላ ወደሰማይ አሳርጎታል፡፡ 2ኛ ነገሥ. 2፥6-9 ✤ 12. እንደ አስፈላጊነቱ ከፈጣሪው ጋር ለብዙ ጊዜ ተነጋግሯል፡፡ ✤✤#ከአንድ እስከ አስራ አንድ ያደረጋቸውን ተአምራት የፈጸመለት ታማኝ ፈጣሪው ሰው በሆነበት ወራት በተራራ ከጓደኞቹ ጋር ብርሃነ መለኮቱን ገለጠለት ማቴ 17፥3፡፡ ዳግመኛም ዛሬ የአባታችን ኖኅ መታሰቢው ነው፡፡ ኖኅ ግን በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን አገኘ …ኖኅም በትውልዱ ጻድቅ፥ ፍጹምም ሰው ነበር፡፡ ኖኅ አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡ /ዘፍ. 6፥7/ #ዳግመኛም በዚህች ዕለት በበረሃ ስልሳ ዘመናት የኖረ የቅዱሳንን ልቡና ከማየቱ የተነሣ ያደነቀ፤ ፊቱም ተለውጦ እንደእሳት ፍሕም ሆነ አባ ሙሴ በዓለ ዕረፍቱ ነው፡፡ #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የጌታችን_በዓለ_ግዝረት_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው #፮ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ #በአዲስ_አበባ_የጌታችን_በዓለ_ግዝረት_የሚከበርባቸው_ #፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ገነተ ኢየሱስና ገነተ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ፤ ታክሲ፤ ከአራዳ ጊዮርጊስ ሞቢሉ ጋር (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ/ኢየሱስ/፤ ፪. ገዳመ ኢየሱስ ቤ/ክ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከመርካቶ → ኮልፌ፡፡ ወይም ከጦር ኃይሎች ዊንጌት/አስኮ/ → (በሚል ታክሲ) (በቀለበት መንገድ) #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የጌታችን_በዓለ_ግዝረት_የሚከበርባቸው_ #፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ምዕራፈ ቅዱሳን በልበሊት ኢየሱስ ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ እንሳሮ ወረዳ፥ ጀማ በረሃ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መራካቶ አውቶቡስ ተራ → መርሃ ቤቴ /አለም ከተማ/ መንገድ → ጀማ በረሃ → በልበሊት ኢየሱስ፡፡ ወይም፤ ከደቡብ ወሎ (ደሴ ወይም ወግዲ) → አለም ከተማ ጀማ በረሃ → በልበሊት ኢየሱስ፡፡ ፪. ለብቃ ኢየሱስ፤ (ተአምረኛ የኾነ ፍልውሃ ጠበል የሚፈልቅበት፤ በቆዳ በሽታ በአካል፥ ደዌ የፈራረሰን ሰውነት ሳይቀር የሚጠግን)፡፡ ከገናናነቱ ተነሣ የሚከተለው ግጥሞች ተገጥሞለታል፡፡ ፨ የለብቃው ኢየሱስ፥ የለብቃው፤ የፈረሰ ገላ ትጠቅማለህ አሉ፡፡ እየተባለ የሚዘመርለት፡፡ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መርሐ ቤቴ፥ ሚዳና ወረሞ ወረዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መራካቶ አውቶቡስ ተራ → መርሃ ቤቴ /አለም ከተማ/ → ሚዳ ወረሞ ወረዳ → ለብቃ ኢየሱስ፡፡ ወይም፤ ከደቡብ ወሎ (ደሴ ወይም ወግዲ) → መርሃ ቤቴ /አለም ከተማ/ → ለብቃ ኢየሱስ፡፡ ፫. በለስ ዋሻ ኢየሱስ ገዳም፤ (ጥንታዊና የቅዱሳን መናኸሪያ፤ በተጕለት ከሚገኙ ከ5ቱ የቅዱሳን መናኸሪያ ገዳም አንዱ፡፡)

#ጥር_4_ተዝካረ_ፍልሰቱ (በዓለ ስዋሬው ) #ለቅዱስ_ዮሐንስ_ሐዋርያ ፤ ዮሐንስ ወንጌላዊ ፤ ፍቁረ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ በተለያዩ ቅጽል ስሞች የሚጠራ፤ ጌታቸችንን ሥነ ስቅለት የሳለ፡፡ ከ81ዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች 5ቱንና ሌሎች መጻሕፍትን (ነገረ ማርያምን ..) የደረሰ፤ #ብዙ ደቀ መዛሙርትን ያስተማረ፤ ጌታ እናቱንም እነሆ ልጅሽ ያላት እርሱን ደቀ መዝሙሩንም እነኋት እናትህ ያለው ነው፡፡ ✤ዮሐንስ ንጹሕ በአምሳለ ትጉሃን፤ (#ዮሐንስ_እንደ_መላእክት_ንጹሕ_ነው፤) ✤ዮሐንስ ድንግል ምክሐ ቅዱሳን፤ (#ዮሐንስ_ድንግል_የቅዱሳን_መመኪያ_ነው፤) ✤ዮሐንስ ስርግው በቀጸላ ሥን በሜላተ ብርሃን፤ (#ዮሐንስ_በብርሃን_መጐናጸፊያና_ሻሽ_የተጌጠ_ነው፤) ✤ዮሐንስ አርጋኖነ ዘቤተ ክርስቲያን፤ (#ዮሐንስ_የቤተ_ክርስቲያን_በገና_ነው፤) ✤ወበቃለ ቀርን ዘይኬልህ በኤፌሶን፥ ይስአል ለነ ስርየተ ለኀጥኣን፡፡ (#በኤፌሶን_ዐዋጅ_የሚናገር_ዮሐንስ_ኀጥኣን_ለምንሆን_ለኛ_ይቅርታን_ይለምንልን፡፡ /መጽሐፈ ሰዐታት/ ፨#100_አካባቢ_ከሚጠጉ_ስሞቹ_ጥቂቶቹን_21ዱን_ስሞች_እነኾ፤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ዮሐንስ፤ ዮሐንስ #ፍቁረ እግዚእ፥ (የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ለጌታ በጣም ቀራቢ ከነበሩት ሦስት የምሥጢር ሐዋርያት (ጴጥሮስ ፣ ናያዕቆብ ) ዮሐንስ ቀዳሚዉ ነዉ፡፡ ጌታችን ምሥጢረ ተአምራትን በኢያኢሮስ ቤት ፣ ምሥጢረ መንግስትን (መለኮትን) በደብረ ታቦር፣ ምሥጢረ ምጽአትን በደብረ ዘይት ፣ ምሥጢረ ጸሎትን በጌቴ ሴማኒ ሲገልጽና ሲያሳይ አብሮ የተመለከተ በመሆኑና ለጌታ በጣም ቀራቢ በመሆኑና በወንጌልም ‹‹ጌታ ይወደዉ የነበረ ደቀ መዝሙር ››ተብሎ ስለ ተጠቀሰ የጌታ ወዳጅ ፍቁረ እግዚእ ይባላል፡፡ዮሐ 13፡ 23 ፡፡ ወልደ #ዘብድዮስ ፥ ዮሐንስ #ነባቤ መለኮት ፥ ዮሐንስ #ቦኦርኔጌስ ፥ ዮሐንስ #አብቀለምሲስ ፥ (ፍጥሞ በምትባል ደሴት ላይም ወደ ፊት የሚሆነዉን ነገር በራእይ ስለተገለጸለት በግሪክ ቋንቋ አቡቀለምሲስ ተብሏል፡፡ትጉሙም የራዕይ አባት ማለት ነዉ፡፡) ዮሐንስ #ወንጌላዊ ፥ ዮሐንስ #ድንግል ዮሐንስ #ታዎሎጎስ ቅዱስ ዮሐንስ ምሥጢረ ሥላሴንና ምሥጢረ ሥጋዌን አስፍቶ በመጻፉ (ታዎሎጎስ) ተብሏል፡፡ትርጉሙም ነባቤ መለኮት (የመለኮትን ነገር የሚናገር)ማለት ነዉ፡፡ 1. #ዮሐንስ_ብፁዕ (ብፁዕ ዮሐንስ) ፣ 2. ዮሐንስ ድንግል ፣3. #ዮሐንስ_ፍንው፣4. #ዮሐንስ_ካህን ፣ 5. #ዮሐንስ_ኅሩይ ፣ 6. ዮሐንስ ሥርግው፣7. #ዮሐንስ_ምዑዝ8. ዮሐንስ ቅኑይ ፣ 9. #ዮሐንስ_ማኅቶት ፣ 10. ዮሐንስ ቤዛ ሰማይ ፣ 11. #ዮሐንስ_ክቡር12. ዮሐንስ ጻድቅ ፣ 13. #ዮሐንስ_ረድእ፣ 14. ዮሐንስ ማኅቶት፣ 15. #ዮሐንስ_ድንግል፣ 16. ዮሐንስ ንጹሕ ፣ 17. #ዮሐንስ_ለባዊ ፣18. ዮሐንስ መረግድ፣ 19. #ዮሐንስ_ዕንቈ ፣ 20. ዮሐንስ መልአክ ፣21. #ዮሐንስ_ኪሩብ ፣22. #ቁጽረ ገጽ #ስዋሬው፤ ቅዱስ ዮሐንስ እስከ መስቀል ድረስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለዉን መከራ በማየቱ ከዚያ ዕለት ጀምሮ 70 ዘመን ሙሉ ፊቱ በኅዘን የተቋጠረ በመሆኑ (ቁጽረ ገጽ) ሆኖ ኖሯል፡ ቅዱስ ዮሐንስ ብዙ ተጋድሎን አርገጐ ዓለምን ሁሉ ዞሮ ካስተማረ ቦኃላ በመጨረሻም ደቀ መዝሙሩ አብሮኮስን ከወንድሞችም ሌሎች ሁለትን መርጦ መቆፈሪያ ይዘው ይከተሉት ዘንድ አዘዘ ፡፡ ጕድጓድም እንዲቆፍሩ አዘዘ ከዚያም ወረዶ ቆመ ልብሱንም አስወገደ የበፍታ ቀሚስ በቀር ሌላ አላረገም ነበር ፡፡ እየጸለየ ወደ ከተማም አሰናበታቸው፡፡ በክርስቶስ ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለሕዝብ ይነግሩአቸው ዘንድ አዘዘ ሁሉም እንደየ ስራቸው ጌታ እንደሚከፍላቸው ነገራቸው ፡፡ካዛም እንዲህ አለ እኔ ከሁላችሁም ደም ንፁሕ ነኝ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ ሳልነግራቹ የተውኩት ምንም ምን የለምና እናንተም ከእንግዲህ ከቶ ፊቴን አታዩም አላቸው ፡፡ እነርሱም እጅና እግሮቹን ስመውት ትተውት ሄዱ ሲመለሱም ልብስና ጫማ እንጂ ምንም አላገኙም እግዚአብሔርንም አመሰገኑት፡፡ ወልደ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ዘጠና ዓመትም ኖረ፤ እንደባላሟሎቹ ሐዋርያት በመሰየፍ ሞትን አለቀመሰም፡፡ ‹‹ያ ደቀ መዝሙር አይሞትን እንዲል ›› ዮሐ 21 ስለ ድንግልናውና ስለንጽሕናው ይህ ሁሉ ሆነ፡፡ በዚህ በከበረ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን አሜን /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

በኋላ ግን የቤተክህነቱ ባለሥልጣናት ታቦቱን ከአስገባን ዘንድ ንግሥትን ጠርተን ማሳየት ግዴታችን ነው፤ ከአዩት ደግሞ በቤቱ አነስተኛነት መቆጣታቸው አይቀርምና ከዚህ ከፍ ያለ ቤት ብንፈልግ ይሻለናል በማለት በፀበሉ ቦታ ላይ በዘመኑ የተሻለ ነው ተብሎ የሚገመተውን የነጋድራስ ሠርፀ ወልድ ፎቅ ቤትን በማስለቀቅ ጥቅምት 4 ቀን 1914 ዓ.ም. ግርማዊት ንግሥተ ነግሥታት ዘውዲቱ በተገኙበት ለ፪ኛ ጊዜ ታቦተ ቅዱስ ዮሐንስ ከመጀመሪያ የሳር ክዳን ጎጆ ቤት ወደ ሁለተኛው ፎቅ ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ የመጀመሪያው ሕንፃ ክብ ቤ/ን (ዛሬ የእመቤታችን ቤ/ን ያለበት) የመሠረት ድንጋይ በፊታውራሪ አባ ይሬ ቦታ ላይ በ1924 ተጣለ፤ ከ2ት ዓመታት በኋላም በ1926 ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አልቆ ንግሥት ባሉበት ተመርቋል፤ ንግሥቲቱም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አንሶ በመሠራቱ ቅር ተሰኝተዋል፤ በእግዚአብሔር ፈቃድ ታላቅ ቤ/ንን እሠራለታለሁ እስከዚያው ድረስ ከመቃኞው ወደ አዲሱ ክቡ ቤ/ን ይግባ ብለው ገብቷል፡፡ ንግሥቲቱም ያሰቡትን ቤ.ን ሳይሠሩ በ1922 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ዐርፈዋል፡፡ ✧ #የአዲሱ_ሕንፃ_ቤተ_ክርስቲያን_መሠራት፡፡ የዐፄ ኀይለ ሥላሴ ልጅ የሐረሩ መስፍን ልዑል መኮንን የተወለደው በዮሐንስ እለት ሲሆን የክርስትና ስሙም አርአያ ዮሐንስ ነው፡፡ አርአያ ዮሐንስም ቅዱስ ዮሐንስን በስሙ የተሰየመበት በመኾኑ ከብላታ ተሰማ ደባልቄ ጋራ በመሆን አባቱ አፄ ኀይለ ሥላሴን የደብረ ነጐድጓድ ቅ/ዮሐንስ ቤ/ንን በአዲስ መልክ አሻሽለው እንዲሠሩለት ይጠይቃቸዋል፡፡ ነገር ግን አባቱ እኛ እንሠራዋለን የሚል መልስ ሰጡት፤ ለጉዳዩ ብዙም ትኩረት ሳይሰጡት፥ ሕንፃውም ሳያሠራ ቆየ፡፡ ብዙም ሳይቆይ መስፍኑ ልጃቸው በቅዱስ ዮሐንስ እለት በግንቦት 4/1949ዓ.ም. አረፈ፡፡ ንጉሡም የልጃቸውን ምኞት ባለመፈጸማቸው ተጸጽተው፤ ልጃቸው ባረፈ በ12ኛው ቀን ወደ ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ን በመምጣት የቤተ ክርስቲያኑን ጥንተ ታሪኩን ጠይቀውና ተረድተው፥ ቤተ ክርስቲያኑን ተሳለመውና አፀዱንና ቅጥሩን ተመልክተው የልጃቸውን ራዕይ ለማሳካት በዘመናዊ አሠራር አዲስ ቤ/ን እንደሚያንፁ ቃል ገቡ፡፡ በቃላቸው መሠረትም አፄ ኀይለ ሥላሴ ራሳቸው ተገኝተው በ1960 የመጀመሪያ መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ባለበት ቦታ ላይ የመሠረት ደንጊያ ተጣለ፡፡ የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አርቴክት ኢጣሊያዊ ነው፡፡ በዐፄ ኀይለ ሥላሴ የገንዘብ ሥጦታም ከ3 ዓመታት በኋላ በ1963 ሕንፃው አልቆ ተመረቀ፤ የሕንፃ ሥራው የተጓተተበት ምክንያትም በ1960 በጄኔራል መንግሠቱ ንዋይና በወንድሙ ግርማሜ ንዋይ መሪነት በተካሄደው መፈንቅለ መንግሥት የሕንፃው ሥራ እየተቋረጠ እንደገና ሲጀምር ጊዜ በመውሰዱ ነው፡፡ ታቦተ ዮሐንስ ከመጀመሪያው ክብ ቤተ ክርስቲያን ወጥቶ በልዩና ባመረ ኹኔታ፥ በመስቀልኛ ቅርጽ፥ በዘመናዊ አሠራር (በአዲስ አበባ በአሠራሩ አምሳያ በሌለው) ወደተሠራው ሕንፃ ቤ/ን ገባ፡፡ በመጀመሪያ በተሠራው የክብ ቤተ ክርስቲያን ውስጥም ከታቦተ ዮሐንስ ጋር ታቦተ ማርያም አብራ በድርብነት ትኖር ነበርና፤ #በ1963 ታቦተ ዮሐንስ አዲስ ወደታነጸው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ሲገባ ታቦተ ማርያም ደግሞ በዚሁ በቀድሞው ክብ ቤ/ን ቆየች፤ ስያሜዋም መካነ ጎልጎታ ማርያም ኾነ፤ በዚህም ምክንያት የደብሩ ሙሉ መጠሪያ ስያሜ ደብረ ነጐድጓድ ዮሐንስ ብቻ በመባል ፈንታ #ደብረ_ነጐድጓድ_ዮሐንስ_ወመካነ_ጎልጎታ_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን ሆነ። ✧ #የቤተ_ክርስቲያኑ_አስተዳደር ከ1922 እስከ 1960 ድረስም የተዳደረው በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን ሥር ሲኾን የሚያስተዳድሩት አለቃውም ኾነ ገበዙ የገነተ ጽጌ አለቃና ገበዝ ነበሩ፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ በተመሠረተበት ወቅት የሚያገለግሉት በ2ት ምድብ የተመደቡ ሰሞንኛ 10 አገልጋይ ካህናት ብቻ ነበሩ፡፡ ርስት ጉልት ስላልተጎለተለት አገልጋዮቹ የሚተዳደሩትም በደመወዝ ነበር፡፡ ደመወዛቸውም የቀሳውስት በወር 10ብር፥ የዲያቆናት በወር 5 ብር ሲኾን ገንዘቡ የሚከፈለውም ከቤተ ክህነት ለቤተ ክርስቲያኑ ከተበጀተ ገንዘብ ነበር፡፡ ✧ #ጠበል_ቤት_ በጠበል ቤቱ ግቢ ውስጥ 9ኝ ጠበሎች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም፤ 1ኛ) የሥላሴ ጠበል፤ 2ኛ) የእግዚአብሔር አብ ጠበል፤ 3ኛ) የመድኀኔ ዓለም ጠበል፤ 4ኛ) የእመቤታችን የማርያም ጠበል፤ 5ኛ) የኪዳነ ምሕረት ጠበል፤ 6ኛ) የቅዱስ ሚካኤል ጠበል፤ 7ኛ) የቅዱስ ገብርኤል ጠበል፤ 8ኛ) የቅዱስ ጊዮርጊስ ጠበል፤ 9ኛ) የአቡነ ተክለሃይማኖት ጠበል ናቸው፡፡ #በደብሩ_የሚከበሩ_ክብረ_በዓላት፤ ✧ ጥር 4፤ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በዓለ ሥዋሬው፤ ✧ መስከረም 21፣ ኅዳር 21፣ ጥር 21፣ ግንቦት 21፤ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓል፤ ኅዳር 12፣ ሰኔ 12፤ የቅዱስ ሚካኤል በዓል፡፡ ✧ #ታቦተ_ሕጉ_ወጥቶ_ባይከበርም #የሊቁ_የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ_ታቦትም_ይገኛል፡፡ አምላካችን ደብሩን ይጠብቅልን፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

✧ #የአዲስ_አበባ_ደብረ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስና #መካነ_ጐልጎታ_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን። ✧ ጠባቂዬ የዮሐንስ ወንጌላዊ ታቦት በደቡብ ጎንደር ስላለ እርሱ ሳይመጣ እኔ አልነግሥም፡፡ /ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ/ ✧ ንግሥት ዘውዲቱ የነገሠችው በምትወደውና ታቦተ ሕጉ አብሯት በማይለየው በቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ እለት የካቲት 4 ቀን 1909ዓ.ም. ነው፡፡ ✧ ደብረ ነጐድጓድ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያንም አሁን ባለበት ቦታ ላይ የተመሠረተው ጥቅምት 4ና ጥቅምት 25 ቀን 1914 ዓ.ም. ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ አሁን ባለበት ቦታ የተከሉት ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ /1909-1922ዓ.ም./ ሲሆኑ የተመሠረተበትም፤ በዕለተ ዐርብ ጥቅምት 25 ቀን በ1914 ዓ.ም. ነው፡፡ ጽላቱ የመጣው ዐፄ ዮሐንስ 4ኛ /1864-1881ዓ.ም./ ወደ ኢየሩሳሌም በላኳቸው አንድ መነኵሴ አማካይነት ሲሆን፤ መነኵሴው ቅዱስ ዮሐንስን እጅግ ይወዱ ስለነበርና በተለይም የዮሐንስ ወንጌል 1፡14 ቃል ሥጋ ኾነ የሚለው ቃል ምሥጢርን ያደንቁ ነበርና በኢየሩሳሌም ለ፮ ዓመታት ቆይተው ወደ ሃገራቸው ሲመለሱ የቅዱስ ዮሐንስ ስም የተቀረጸበትን ታቦተ ዮሐንስ ወንጌላዊን ይዘው መጥተዋል፡፡ ታቦተ ሕጉ በንጉሡ ዐፄ ዮሐንስ ቤተ መንግሥት /መቀሌ/ ግቢ ከቆየ በኋላ ንጉሡ ለልጃቸው ለአርአያ ሥላሴ /ኋላ ራስ/ ሰጥተውታል፡፡ አርአያ ሥላሴም ጥቅምት 13/1875ዓ.ም. ከንጉሥ ምኒልክ /ኋላ አጼ/ ልጅ ወ/ሮ ዘውዲቱ /ኋላ ንግሥተ ነገሥታት/ ጋር ተጋብተዋል፤ ለባለቤታቸው ወ/ሮ ዘወዲቱ ታቦተ ዮሐንስን ‹‹ብትጠብቂው ይጠብቅሻል›› ብለው አደራ ሰጥተዋቸዋል፡፡ ራስ አርአያ ሥላሴ ዮሐንስም በየካቲት 1880ዓ.ም. ሲያርፉ፤ ዐፄ ምኒልክ ልጃቸው ዘውዲቱን ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ እንዲያመጡ ሊጋባ ገብርኤልንና ደጃች አባተን ላኩ፤ ነገር ግን በጕዞው ላይ ኃይለኛ ዝናብ በመዝነቡ ምክንያት ወንዞች ስለሞሉና ወደ አዲስ አበባ መመለስ ባለመቻሉ ወ/ሮ ዘውዲቱ ለአንድ ዓመት በደብረ ታቦር ተቀመጡ፥ ታቦተ ዮሐንስም በማኅደረ ማርያም ተቀመጠ፡፡ ኋላ ወ/ሮ ዘውዲቱ ደጃዝማች ጉግሣ ወሌን /ኋላ ራስ/ በቊርባን አግብተው ወደ በጌምድር ደብረ ታቦር በሄዱ ጊዜ ታቦተ ዮሐንስን አስመጥተው በደብረ ታቦር ቤተ መንግሥት ግቢ ውስጥ አነስተኛ ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለ12 ዓመታት ሲኖሩ ታቦተ ዮሐንስም በዚሁ ቤተ መንግሥት ግቢ አብሯቸው ኖረ፡፡ ባላቸው ራስ ጉግሣ ወሌ በ1902 ዓ.ም. ታሠሩ እስከ 1906ዓ.ም ወደ አፍቀራ ኮረብታ በግዞት ተወሰዱ፡፡ ወ/ሮ ዘውዲቱም ራስ ጉግሣ ወሌ የቊርባን ባላቸው ስለኾኑ ማንንም ሳያገቡ በአዲስ አበባ ቤተ መንግሥት ቆዩ፡፡ ቀጥሎም ወ/ሮ ዘውዲቱ ወደ ፋሌ በርስታቸው ቦታቸው ላይ ከባላቸው ከራስ ጉግሣ ወሌ ጋር ኖሩ፡፡ በመስከረም 19/1909ዓ.ም. ልጅ ኢያሱ ከሥልጣን ሲሻሩ፤ ወይዘሮ ዘውዲቱ አልጋውን እንዲይዙ አጃቢዎች ተልከው መስከረም 22 ቀን 1909ዓ.ም. አዲስ አበባ ገቡ፤ የዘውድ በዓላቸው በኅዳር 12 ቀን 1909 ዓ.ም. እንዲኾን ሲጠየቁ፤ ጠባቂዬ ታቦተ ዮሐንስ በደብረ ታቦር ስላለ እርሱ ካልመጣ አልነግሥም ስላሉ የዘውድ በዓሉ ተላልፎ፤ ታቦተ ዮሐንስ በጥር 29 ቀን 1909 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ መጥቶ በዐፄ ምኒልክ ጸሎት ቤት (ሥዕል ቤት) ተቀመጠ፡፡ የንግሥት ዘውዲቱ የዘውድ በዓልም በምትወደውና ታቦተ ሕጉ አብሯት በማይለየው በቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ እለት የካቲት 4 ቀን 1909ዓ.ም. በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን ግርማዊት ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ ተብለው በዓሉ ተደረገ፤ በእለቱም ታቦተ ዮሐንስ ከስዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት ወደ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሂዶ ተቀድሶበት ዋለ፤ በዐውደ ምሕረቱም ንግሥቲቱ ከታቦተ ሕጉ ጋር አብረው ዑደት አድርገው የዘውድ በዓሉ ተደረገ፡፡ (በሌላ ታሪክ ዐፄ ዮሐንስ ለወሎው ገዢ ራስ ሚካኤል ታቦተ ዮሐንስን ሰጥተዋቸው ኋላ ላይ በተደረገው የሰገሌ ጦርነት ታቦተ ዮሐንስ ወደ አ.አ. መጥቷል የሚሉም አሉ፡፡) #ንግሥተ_ነገሥታት_ዘውዲቱ_ምኒልክ_ለከተማችን_ብቸኛ_የኾነውን_የቅዱስ#ዮሐንስ_ወንጌላዊ #ቤ/ን #እንድትሠራ_ያደረጓት #፫ት #ምክንያቶች፤ 1ኛ) ከመጀመሪያ ባሏ ከአርአያ ሥላሴ ዮሐንስ የተሰጣት በመኾኑና በችግሯም ኾነ በደስታ ኹሉ አብሯት የነበረ ታቦት በመኾኑ፤ 2ኛ) የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ን መካነ መቃብር በመሙላቱ ከቤተ ክህነት ጋር በመመካከር ሌላ የቀብር ቦታ እንደሚያስፈልግ በመታመኑ 2033lm2 ያህል ቦታ እንዲኖረው ተደርጎተከልሏል፡፡ 3ኛ) በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውና በከተማችን Nov. 1918 ብዙ ሰዎችን የጨረሰው የኢንፍሉዌንዛ (የኅዳር በሽታ) በፈዋሴ ሕመም የሚታወቀው ሐዋርያና ወንጌላዊው ዮሐንስ ከከተማችንና ከሃገራችን ይህንን የወረርሽኝ በሽታ ነቅሎ እንዲያጠፋው ነው፡፡ ከዘውድ በዓሉ 1909 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ 1914 ዓ.ም. (ለ5ት ዓመታት) በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቆየ (እስከ 1915 በሥዕል ቤትቆየ የሚሉም አሉ)፡፡ የንግሥት ዘውዲቱ መንፈሳዊ ምኞታቸው ለቅዱስ ዮሐንስ ታቦት ትልቅ ቤ/ን ማሠራት ሲሆን፤ ለጊዜው አሁን ቤተ ክርስቲያኑ ያለበትን ቦታ ጠቁመው መቃኞ እንዲሰራለት በሰጡት ትዕዛዝ መሠረት፤ #በእለተ_ዐርብ_ጥቅምት #25 ቀን #በ1914 ዓ.ም. አሁን የደብረ ነጐድጓድ ዮሐንስ ሕንፃ ቤ/ን የተሠራበት ቦታ ላይ ታቦቱ ከመምጣቱ በፊት መስቀል ዞሮ ቦታው ተከለለ፡፡ የቦታው ባለቤቶች የንጉሣውያን ቤተሰብ የኾኑት ፊታውራሪ አባ ይሬ፣ ደጃዝማች ይገዙ በሀብቴና ነጋድራስ ሠርፀ ወልድ ናቸው፡፡ ይዞታቸውም፤ * መጀመሪያ የታቦተ ዮሐንስ መቃኞ ቤት የነበረበት (አሁን አዲሱ የዮሐንስ ቤ/ን የተሠራበት)ና የመቃብሩ ሥፍራ የደጃዝማች ይገዙ በሀብቴ፤ * ቀድሞ የዮሐንስ ቤ/ን (አሁን የእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን) ያለበት ሥፍራ ደግሞ በተለይ የፊታውራሪ አባ ይሬ ቦታ ነው፤ * የጠበሉ ቦታ የነጋድራስ ሠርፀ ወልድ ቦታ ነው፡፡ ከዚያም በቀሳውስት፣ በዲያቆናት በመዘምራን ስበሐተ እግዚአብሔር እየቀረበ፤ ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ዲያቆናት በመካከል ሁነው፤ በጥንቱ አራዳ ዘበኞች በሚባሉ ወታደሮች ታጅቦ፥ እምቢልታና መለከት እየተነፋ ከገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ አሁን ቤተ ክርስቲያኑ ወዳለበት ቦታ መጥቶ አንድ የሣር ክዳን ቤተ ንጉሥ የኾነ የደጃዝማች ይገዙ በሀብቴ ቤት ተባርኮ ታቦቱ በመቃኞነት (በመቃረቢያነት) ቆየ፡፡ በእለቱም ታቦተ ሕጉን አጅበው ከመጡት ታዋቂ ሰዎች መካከል ነጋድራስ ወንድማገኘሁ፣ አቶ ይታጠቁ፣ አቶ ዱባለ፣ አቶ ደምሴ በልልኝ፣ አቶ ድልነሣሁ፣ አቶ ተክለማርያም ደምሴና ሌሎችም ነበሩ፡፡ እነዚህ ታዋቂ ሰዎችም ብዙ ርስት ያላቸው ስለበሩ ለቅዱስ ዮሐንስ ባላቸው ጽኑ ፍቀር የተነሣ ታቦቱ በገባበት እለት እህል ውኃ አቅርበው ከዛሬ ጀምሮ እዚህ ቤተ ክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ #ማኅበረ_ሰንበቴ አቋቁመናልና ይዘከርልን በማለት ሰንበቴ ቤቱ ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብሮ ተመሠረተ፡፡ እስካሁንም ድረስ በየሳምንቱ እየተዘከረ ይገኛል፡፡

ወይም ከደሴ → ወልድያ → ደብረ ታቦር → ወረታ → ፎገራ፤ ፲፰. ሐዋሳ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ሐዋሳ ሃገረ ስብከት ፥ ሐዋሳ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ሐዋሳ፡፡ ፲፱. ሆሳዕና ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሃገረ ስብከት፥ ሆሳዕና፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ሆሳዕና፡፡ ፳. ማፌድ ጓረባ ጠብረሪ ደብረ ዕንቊ ቅድስት ልደታ ወዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሃገረ ስብከት፥ ማፌድ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ሆሳዕና → ማፌድ፡፡ ፳፩. እዣ ስራይ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሃገረ ስብከት፥ እዣ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ሆሳዕና → እዣ፡፡ ፳፪. ደብረ ዘይት ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፤ አድራሻ፤ ምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አድአ ወረዳ → ደብረ ዘይት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ዘይት፡፡ ፳፫. አለም ገና ቤ/ን (ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ በድርብነት ይከብራል)፤ አድራሻ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ አለም ገና፤ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ → ጀሞ → አለም ገና፡፡ አቅጣጫ ምንጭ ገዳማት ገጽ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ጥር ፬፤ #በዓለ_ስዋሬሁ_ለዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ_፡፡ #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የቅዱስ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ_በዓለ_ስዋሬ_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው #ገዳማትና_አድባራት፡፡ #በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፫ #ገዳማትና_አድባራት_፡፡ ፩. ደብረ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ማርያም ቤ.ክ. ታቦተ ሕጉ ከኢየሩሳሌም የመጣ፥ ከዐፄ ዮሐንስ ጋር በመቀለ፤ ከራስ ጉግሳ ወሌ ጋር በደብረ ታቦር፤ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ከደብረ ታቦር ወደ አዲስ አበባ መናገሻ ገተ ጽጌ ያመጣችው፤ አፄ ኀይለ ሥላሴ ደግሞ አሁን ያለውን ሕንፃ ያሠሩት፤ በአዲስ አበባ በወልደ ነጐጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ስም በመሰየም ብቸኛው ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ አራዳ ክፍለ ከተማ፥ ሰባራ ባቡር፥ አባ ኮራን፥ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ታክሲ፤ ከፒያሳ ጴጥሮስ ዐደባባይ → ዊንጌት አስኮ በሚለው ታክሲ ተሳፍረው ቤተ ክርስቲያኑን ያገኛሉ፡፡ ወይም ከመርካቶ ጎጃም በረንዳ → አዲሱ ገበያ (ቀጨኔ) በሚሉ ታክሲዎች ተሳፍረው ቤተ ክርስቲያኑን ያገኛሉ፡፡ ፪. ብሔረ ጽጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያምና መድኀኔዓለም ቤ/ክ (የሐዋርያው ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ታቦት ቤተ ክርስቲያኑ ከተመሠረተበት ከ፲፱፻፹፮ ዓ.ም ጀምሮ በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ፥ ብሔረ ጽጌ፤ ከብሔረ ጽጌ መናፈሻ 100 ሜትር ያህል ገባ እንዳሉ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሰታዲየም)(መርካቶ)(መገናኛ)→ አደይ አበባ/ሳሪስ/ → ብሔረ ጽጌ፡፡ ፫. ምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም (ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ባይከብርም፥ ከቀድሞ ጀምሮ በኪዳንና በሰዐታት፤ በውዳሴ፥ በቅዳሴ ይከበራል፡፡) አድራሻው፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ 6 ኪሎ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሽሮሜዳ በሚለው ታክሲ (ምስካየ ኅዙናን ጋር) ወይም ከመርካቶ ራጕኤል (ከጊዮርጊስ)→ ሽሮሜዳ በሚለው → መነን (የካቲት 12 ት/ቤት) ተወርዶ → ምስካየ ኅዙናን፡፡ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፳፫ #ገዳማትና_አድባራት_፡፡ ፩. መአቁዲ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ (ጥንታዊው ደብር፤ ለአንድ ቀን ብቻ ጠበል የፈለቀበት)፤ አድራሻ፤ ትግራይ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ወልድያ → መአቁዲ፡፡ ፪. ደቡብ ወሎ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ (ጥንታዊው ደብር፤ ከመካነ ሥላሴ አጠገብ የሚገኝ)፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → መካነ ሥላሴ፡፡ ፫. ሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ሐይቅ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደሴ → በወልድያ መስመር (ሐይቅ ከተማ) ፬. ደብረ በንኰል ገዳም አጠገብ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ አድራሻ፤ ትግራይ፥ ሰለኽላኻ፥ ከታላቁ ገዳም ደብረ በንኰል አጠገብ ትራንስፖርት፤ ከመቀለ(አኵሱም) → ሽሬ → ሰልኽላኻ → ደብረ በንኰል መስመር የቅ/ዮሐንስን ደብር ያገኙታል፡፡ ወይም ከጎንደር በሊማሊሞ ሽሬ (ዳንሻ፤ ሁመራ፤ ሽሬ) መስመር → ሰልኽላኻ → ደብረ በንኰል መስመር የቅ/ዮሐንስን ደብር ያገኙታል፡፡ ፭. አደቁዋረክ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ አኵስም (ማዕከላዊ ትግራይ) ሃገረ ስብከት፥ ማኅበረ ዴጎ አጠገብ/፤፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → በደሴ → ወልድያ → መቀለ → አኵስም → ማኅበረ ዴጎ → አደቁዋረክ፤ ወይም ከአ.አ. (በአውሮፕላን ) → አኵስም → ማኅበረ ዴጎ → አደቁዋረክ፤ ወይም ወይም ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በቡሬ/በሞጣ/ ባህርዳር → ጎንደር → ከጎንደር በሊማሊሞ ሽሬ (ዳንሻ፤ ሁመራ፤ ሽሬ) መስመር → ሽሬ → አኵስም → ማኅበረ ዴጎ → አደቁዋረክ፤ ፮. ገደፈና_ዮሐንስ /ማይጨው አጠገብ/፤ አድራሻ፤ ትግራይ፥ ማይጨው ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → በደሴ → ወልድያ → ማይጨው → ገደፈና፤ ፯. መንዝ ማማ ሞላሌ ደዋ ዮሐንስ (900 ዓመታት በላይ ያስቈጠረ) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፥ ሞላሌ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ሞላሌ → ደዋ፤ ፰. ዣት ደብረ ፀሐይ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ጅሩ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → በደብረ ብርሃን በኩል → ጅሩ ፥ እነዋሪ → ዣት፤ ወይም ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በሙከጡሪ (መርሐ ቤቴ መስመር) → ለሚ → ጅሩ ፥ እነዋሪ፤ ፱. ዘንስር ደብረ ተድላ ዮሐንስ ማዕከላ ለጐንደር፤ /ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱና ዋነኛው፤ በጎንደር ከተማ የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ወደ ግምጃ ቤት ማርያም ከመዛወሩ በፊት በብቸኝነት የጎንደርና የመላው ኢትዮጵያ ሊቃውንት የማኅሌተ ጽጌን ቁመት ለመቆም የሚተሙት ታላቅ ደብር/፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በቡሬ /በሞጣ/ መስመር → ባህር ዳር →  ወረታ → ጎንደር ከተማ፡፡ ወይም ከመቀለ /አኵሱም/ → ሽሬ → በሊማሊሞ (በሁመራ ዳንሻ) → ጎንደር ከተማ፤ ወይም ከደሴ → ወልድያ → ደብረ ታቦር → ወረታ → ጎንደር ከተማ፤ ፲. ሞያሌ ደጋ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ሞያሌ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. → ሞያሌ፤ ፲፩. ደምበጫ አጠገብ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ ደምበጫ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → /በባህር ዳር መስመር/ ደምበጫ፤ ፲፪. ቦኮሙራ ወልደ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.ን፤ አድራሻ፤ ሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት፥ ሚሻ ወረዳ፥ ቦኮሙራ ቀበሌ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → ስልጤ → በኮሙራ፤ ፲፫. ናዝሬት(አዳማ) ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ምሥራቅ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ናዝሬት(አዳማ)፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → በደብረ ዘይት (በፈጣን መንገድ) → ናዝሬት (አዳማ) ከተማ፤ ፲፬. ደሴ ዩኒቨርሲቲ ደብረ ነጎድጓድ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ደሴ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ደሴ ከተማ፤ ፲፭. መቱ ደብረ ሳሌም ወነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤ (በ1915 ዓ.ም. የተመሠረተ) አድራሻ፤ ም.ወለጋ ሃገረ ስብከት፥ መቱ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወለጋ/መቱ፤ ፲፮. ጨንቻ ዶርዜ አይራ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ጋሞ ጎፋ ሃገረ ስብከት ፥ ጨንቻ ወረዳ፥ ዶርዜ አይራ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወለጋ/መቱ፤ ፲፯. ፎገራ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤ አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት ፥ ፎገራ ወረዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በቡሬ /በሞጣ/ መስመር → ባህር ዳር →  ወረታ → ፎገራ፡፡ ወይም ከመቀለ /አኵሱም/ → ሽሬ → በሊማሊሞ (በሁመራ ዳንሻ) → ፎገራ፤

#ጥር ፫፤ የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው እና የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን_ጸበል_ያፈለቁ የታላቁ አባት አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ በዓለ ዕረፍት ነው ። #በአ.አ. #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት ቀድሞ በቅዳሴና በውዳሴ ታቦተ ሕጋቸው ሲከበር የቆየው የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ታቦተ ሕጋቸው #ቅዳሜ_ጥር 3/2017 ዓ.ም. ሰባተኛ ጊዜ_ታቦተ_ሕጋቸው_ወጥቶ_ይከብራል፡፡ (ሁላችሁም እንድትገኙ ገዳሟ ጥሪዋን አስተላልፋላች)፡፡ አባ ሊባኖስ #የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው፤ ፠ ቅዱስ ላሊበላ ከ11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱን በስማቸው ያነፀላቸው፡፡ ፠ #ከደረቅ_ዐለት_ላይ_ውሃ_እያፈለቁ_ድውያንን_የሚፈውሱ_ተአምረኛ_አባት ፠ በኤርትራ አካለ ጉዛይ ገዳመ መጣዕ፣ በአኵሱም ከተማ አጠገብ፣ በላስታ ላሊበላ፣ ደብረ ወርቅ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፣ እንዲሁም ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ በአ.አ. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ገዳም ክብረ በዓል የሚከበርላቸው። ፠ አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ሊድሯቸው ሲሉ መመነን በመፈለጋቸው መልአክ በሌሊት መጥቶ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡ ፠ አባ ጳኩሚስም ሥርዐተ ገዳምን፥ አስኬማ መላእክትን፥ ቅናተ ዮሐንስን አስተማሯቸው፤ አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡ ፠ ቀድሞ የመራቸው መልአክ ከአባ ጳኩሚስ ‹‹ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድሎህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአኵሱም ተቀመጡ፡፡ ፠ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው (ቀድሞ የዋልድባን ገዳም ባስፋፉ አባቶች የተመሠረተችውን #የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን እስፋፍተው፡፡) ተመልሰው ወደ አኵሱም ሄዱ፡፡ ፠ በአኵሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ፥ ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአኵሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል ‹‹ተራ ውሃ ነው›› ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ ‹‹አምላከ አባ ሊባኖስ›› ብሎ አመሰገነ፡፡ (ስዕላቸው የሚገልጸው ይህንን ተአምር ነው፡፡) ፠ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው ‹‹ምትሃት ነው የሚያሳየው›› ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡ ፠ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአኵሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ፤ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው ‹‹አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን›› ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡ ፠ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ (የአሁኗ ደብረ ሊባኖስ) መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው ‹‹ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኮሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል›› አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡ ፠ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አኵሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም ‹‹ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ›› አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ ‹‹ሊባኖስ ዘመጣዕ›› የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ በወቅቱ የነበረው አፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡ ፠ ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ አፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡ ፠+፠ በመጨረሻም ጥቅምት 2 ቀን ተፀንሰው ፤ ፠+፠ ሐምሌ 3 ቀን ተወለደው፤ ፠+፠ በ140 ዓመታቸው ጥር 3 ቀን በክብር ዐርፈዋል፡፡ ፠+፠ ቅዳሴ ቤታቸው ደግሞ ሐምሌ 3 ነው፡፡ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡ * እኛም ለክብረ በዓሉ የሚሆነውን ከዋይዜማው ጀምሮ ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት እነሆ ብለናል፡፡ #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም ፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡ ፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው ጠበሏን አፍልቀው ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡ ፠ በ197 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለአቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡ ፠ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ይመስገን፨ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ጥር ፫፤ #የአቡነ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ_በዓለ_ዕረፍት_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፲፩ ገዳማትና አድባራት፡፡ (አባ ሊባኖስ በሃገራችን ላይ 80 ገዳማትን መሥተዋል) በ79 ገዳማትና አድባራት ላይ ሲከበሩ ዐበይቶቹ የሚከተሉት ናቸው፤ #በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ እንጦጦ፤ ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ ጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (ከመርካቶ) → ሽሮ ሜዳ → እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት፡፡ #ለቅምሻ_በአጭሩ፤ #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም ፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ደግሞ ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡ ፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው፥ ጠበሏን አፍልቀው፥ ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡ ፠ በ1967 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡ ፠ ባለውለታዋን ዘንግታ የቆየችው እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳምም ከ በኋላ በዕለተ እሑድ ጥር 3/2012 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ ታቦተ ሕጉን አውጥታ አክብራለች፨ ፪. አያት ጣፎ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን፡፡ (በድርብነት ይከበራል) አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አያት 2 ኮንዶሚንየም ትራንስፖርት፤ ከመገናኛ → አያት(በሲኤምሲ) አደባባይ ወደ ጣፎ በሚወስደው መንገድ ወይም ከመገናኛ በኮተቤ ጣፎ /አባ ኪሮስ ጋር ወርደው/ በባጃጅ (በታክሲ) ያገኙታል፡፡ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ደብረ ወርቅ ገዳመ መጣዕ አቡነ ሊባኖስ፤ (በ523 ዓ.ም. በጻድቁ በአቡነ ሊባኖስ የተገደመና በአፄ ገብረ መስቀል የታነጸ፥ ገደል ወገብ ላይ የታነፀና የሚያስደንቅ፡፡) (የጻድቁ የከበረ አጽም የሚገኝበት፥ ሙት ያስነሳበት፥ ዕውር ያበራበት ገዳም ነው) አድራሻ፤ ደቡብ ኤርትራ፥ አካለ ጉዛይ አውራጃ፥ ሃም ታርካ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ (በአውሮፕላን) → ኤርትራ → አካለ ጉዛይ → ሃም ታርካ፡፡ ፪. አኵሱም አጠገብ የሚገኝ አባ ሊባኖስ፤ (ጻድቁ የዋሻ በዓት ሠርተው የጸለየበት፥ 7ት ዓይነት ጠበል ያፈለቀበት፤ አንዲት እናት ውኃ ነው ብላ ብትዳፈር ልጇ ሞቶባት እንደ ኤልያስ ያስነሳበት፥ የአከባቢው ካህናት ቢያድሙበት እንደ ኤልያስ በዚህ አካባቢ ላይ ለ3ት ዓመት ዝናብ እንዳይዘንብ የከለከለበት ኋላ ደግሞ በይቅርታ ቢጠይቁት ዝናብ ያዘነበበት ነው) (ልጅ ያጡ የሚወልዱበት መታሻ ደንጊያ ያለበት፥ ከዐለት ላይ የሚፈልቅ ተአምረኛ ጠበል ያለበት) (ገዳሙ ዋሻና ለእኅቶች ደግሞ ክብ ሕንፃ ቤ/ን አለ) አድራሻ፤ አኵስም ሃገረ ስብከት ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ በጎንደር/በሽሬ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ) ወይም ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/ወልድያ/መቀለ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ) ፫. ተንቤን አምበራ አቡነ ሊባኖስ (በአፄ ገብረ መስቀል የታነፀ) አድራሻ፤ ትግራይ ትራንስፖርት፤ ከአኵሱም → ተንቤን ፬. ላስታ ላሊበላ ቤተ አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ፥ በላስታ ከሚገኙት 11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ አንዱ የኾነና ከ11ዱ ሙሉ ለሙሉ ከተራራ ላይ ተፈልፍሎ ባለመውጣቱ በአሠራሩ ልዩ የኾነ) አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ፥ ላሊበላ ከተማ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/በጋሸና/ → ላሊበላ ወይም ከአ.አ. (በአውሮፕላን) → ላሊበላ ወይም ከጎንደር (ባህር ዳር) /በወረታ/ /ደብረ ታቦር/ /ጋሸና/ → ላሊበላ ወይም ከመቀለ በወልድያ መስመር/ጋሸና/ → ላሊበላ ፭. ዛራ ሐሙሲት አካባቢ የሚገኘው አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ) አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት ትራንስፖርት፤ ከባህር ዳር /በጎንደር መስመር/ → ሐሙሲት ፮. ጎንደር ግራርጌ (ቆላ ድባ) ፈለገ ሕይወት አቡነ ሊባኖስ፤ (በአፄ ገብረ መስቀል እንደተመሠረተ የሚነገርለት፥ አጸዱ እጅግ በጣም የሚማርክ /ዕድሜ ጠገብና አርስ በእርሱ የገጠመ 4 ትላልቅ ወርካና 4 ጽድ የሚገኝበት፤ ወርካውን ፈልፍለው መነኰስ ይኖሩበት የነበረው ለምስክር ቆሞ የሚገኝበት፥ 1ዱ ጽድ በ1880 አካባቢ ወድቆ እስካሁን ዝናብና ፀሐይ እየፈራረቀበት ሳይበሰብስ የሚገኝበት)፤ ውሎ ቅዳሴ የሚቀደስበት፤ የአከባቢው ገበሬ እህሉን ወደ ጎታው ከቅዳሴ በኋላ የሚያስገባበት የበረከት ቃል ኪዳን የተሰጠው ምድር፡፡ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደንቢያ ወረዳ፥ ቆላ ድባ ከተማ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከጎንደር (አዘዞ) → ወደ ጎርጎራ መስመር (በደረስጌና በቆላ ድባ መሃል ላይ ያገኙታል) (በ25 ኪ.ሜ አስፓልቱ ዳር) ፯. በመንዝ ቀያ ሀገረ ገራዴ አባ ሊባኖስ አፅመ ቅዱሳን ዋሻ (ፈዋሽ ጠበልና አስገራሚ ዋሻ ያለበት)፡፡ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ፥ ዘመሮ ከተማ፥ በንዲ ቀበሌ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘመሮ → 9 ኪ.ሜ ያህል እንደተጓዙ በንዲ ቀበሌ (ከአዲስ አበባ 328 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ይገኛል) ፰. መንዝ ላሎ አንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፥ ዘብር፥ ላሎ፥ አንጀትላ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘብር(247 ኪ.ሜ.) → የ2ት ሰዐት የእግር መንገድ → የአንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፡፡ ፱. *** ነገር ግን የመሠረቱት፥ ለ40 ዓመታት በዓት ሠርተው የኖሩበትና፥ በስማቸው የሚጠራው ታላቁ ገዳም ደብረ ሊባኖስ ግን ባለፉት 10ር ዓመታት ውስጥ ገድላቸውን በግእዝና በአማርኛ ከማሳተም የዘለለ የሚጠበቅበትን ሥራ አልሠራም፡፡ (ያልጠቀስናቸው ካሉ በውስጥ አሳውቁን) / #ክብረ_በዓላት #Feasts / / #ገዳማትና_አድባራት #Monasteries_and_Churches / /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w