ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 394 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 590 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 197 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 394 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 21، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 21.61‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.23‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 327 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 576 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 17.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 01 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 394
المشتركون
+124 ساعات
+307 أيام
+2130 أيام
أرشيف المشاركات
#አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ #በአ.አ. #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት ቀድሞ በቅዳሴና በውዳሴ ታቦተ ሕጋቸው ሲከበር የቆየው የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ታቦተ ሕጋቸው #ሰኞ_ጥር 3/2013 ዓ.ም. ለሁለተኛ ጊዜ_ታቦተ_ሕጋቸው_ወጥቶ_ይከብራል፡፡ (ሁላችሁም እንድትገኙ ገዳሟ ጥሪዋን አስተላልፋላች)፡፡ #ጥር_3 #አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ_ዕረፍታቸው_ነው_፡፡ ፠ #የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው፤ ፠ ቅዱስ ላሊበላ ከ11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱን በስማቸው ያነፀላቸው፡፡ ፠ #ከደረቅ_ዐለት_ላይ_ውኃ_እያፈለቁ_ድውያንን_የሚፈውሱ_ተአምረኛ_አባት ፠ በኤርትራ አካለ ጉዛይ ገዳመ መጣዕ፣ በአኵሱም ከተማ አጠገብ፣ በላስታ ላሊበላ፣ ደብረ ወርቅ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፣ እንዲሁም ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ በአ.አ. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ገዳም ክብረ በዓል የሚከበርላቸው፡፡ (ሌሎቹን የምታውቋቸውን ከነፎቷቸው ላኩልን) ፠ አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ሊድሯቸው ሲሉ መመነን በመፈለጋቸው መልአክ በሌሊት መጥቶ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡ ፠ አባ ጳኩሚስም ሥርዐተ ገዳምን፥ አስኬማ መላእክትን፥ ቅናተ ዮሐንስን አስተማሯቸው፤ አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡ ፠ ቀድሞ የመራቸው መልአክ ከአባ ጳኩሚስ ‹‹ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድሎህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአኵሱም ተቀመጡ፡፡ ፠ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው (ቀድሞ የዋልድባን ገዳም ባስፋፉ አባቶች የተመሠረተችውን #የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን እስፋፍተው፡፡) ተመልሰው ወደ አኵሱም ሄዱ፡፡ ፠ በአኵሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ፥ ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአኵሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል ‹‹ተራ ውሃ ነው›› ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ ‹‹አምላከ አባ ሊባኖስ›› ብሎ አመሰገነ፡፡ (ስዕላቸው የሚገልጸው ይህንን ተአምር ነው፡፡) ፠ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው ‹‹ምትሃት ነው የሚያሳየው›› ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡ ፠ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአኵሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ፤ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው ‹‹አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን›› ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡ ፠ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ (የአሁኗ ደብረ ሊባኖስ) መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው ‹‹ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኮሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል›› አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡ ፠ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አኵሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም ‹‹ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ›› አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ ‹‹ሊባኖስ ዘመጣዕ›› የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ በወቅቱ የነበረው አፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡ ፠ ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ አፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡ ፠+፠ በመጨረሻም ጥቅምት 2 ቀን ተፀንሰው ፤ ፠+፠ ሐምሌ 3 ቀን ተወለደው፤ ፠+፠ በ140 ዓመታቸው ጥር 3 ቀን በክብር ዐርፈዋል፡፡ ፠+፠ ቅዳሴ ቤታቸው ደግሞ ሐምሌ 3 ነው፡፡ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡ ***** እኛም ለክብረ በዓሉ የሚሆነውን ከዋይዜማው ጀምሮ ሙሉውን ሥርዐተ ማኅሌት እነሆ ብለናል፡፡ (ምንጭ፤ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ፣ 5ኛ መጽሐፍ የቅዱሳን ታሪክ) #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም #ለ1512 #ዓመታት_ባለውለታዋን_ዘንግታ_የቆየችው_እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም_ጥር_3/2012 ዓ.ም. #ባለውለታዋን_አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕን_ፎቶ_ላይ_በምታዩት_ሁኔታ_ዘክራለች_፡፡ አሁን ደግሞ ለሁለተኛ ጌዜ በድምቀት ተዘክራለች ፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡ ፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው ጠበሏን አፍልቀው ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡ ፠ በ197 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለአቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡ ፠ የአባቶቻችን አምላክ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ይመስገን፨ #ሰኞ_ጥር 3/2013 ዓ.ም. በገዳሙ እንገናኝ::

/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ክብረ_በዓላት #feasts #ቅዱሳን_ሐዋርያት #Apostles

ጥር 4 ተዝካረ ፍልሰቱ(በዓለ ስዋሬው ) ለቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ ፤ ዮሐንስ ወንጌላዊ ፤ ፍቁረ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ በተለያዩ ቅጽል ስሞች የሚጠራ፤ ችንን ስነ ስቅለት የሳለ፡፡ ከ81ዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች 5ቱንና ሌሎች መጻሕፍትን (ነገረ ማርያምን ..) የደረሰ፤ #ብዙ ደቀ መዛሙርትን ያስተማረ፤ #share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ ጌታ እናቱንም እነሆ ልጅሽ ያላት እርሱን ደቀ መዝሙሩንም እነኋት እናትህ ያለው ነው፡፡ ✤ዮሐንስ ንጹሕ በአምሳለ ትጉሃን፤ (#ዮሐንስ_እንደ_መላእክት_ንጹሕ_ነው፤) ✤ዮሐንስ ድንግል ምክሐ ቅዱሳን፤ (#ዮሐንስ_ድንግል_የቅዱሳን_መመኪያ_ነው፤) ✤ዮሐንስ ስርግው በቀጸላ ሥን በሜላተ ብርሃን፤ (#ዮሐንስ_በብርሃን_መጐናጸፊያና_ሻሽ_የተጌጠ_ነው፤) ✤ዮሐንስ አርጋኖነ ዘቤተ ክርስቲያን፤ (#ዮሐንስ_የቤተ_ክርስቲያን_በገና_ነው፤) ✤ወበቃለ ቀርን ዘይኬልህ በኤፌሶን፥ ይስአል ለነ ስርየተ ለኀጥኣን፡፡ (#በኤፌሶን_ዐዋጅ_የሚናገር_ዮሐንስ_ኀጥኣን_ለምንሆን_ለኛ_ይቅርታን_ይለምንልን፡፡ /እመጽሐፈ ሰዐታት/ ፨#100_አካባቢ_ከሚጠጉ_ስሞቹ_ጥቂቶቹን_21ዱን_ስሞች_እነኾ፤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ዮሐንስ፤ ዮሐንስ #ፍቁረ እግዚእ፥ (የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ለጌታ በጣም ቀራቢ ከነበሩት ሦስት የምሥጢር ሐዋርያት (ጴጥሮስ ፣ ናያዕቆብ ) ዮሐንስ ቀዳሚዉ ነዉ፡፡ ጌታችን ምሥጢረ ተአምራትን በኢያኢሮስ ቤት ፣ ምሥጢረ መንግስትን (መለኮትን) በደብረ ታቦር፣ ምሥጢረ ምጽአትን በደብረ ዘይት ፣ ምሥጢረ ጸሎትን በጌቴ ሴማኒ ሲገልጽና ሲያሳይ አብሮ የተመለከተ በመሆኑና ለጌታ በጣም ቀራቢ በመሆኑና በወንጌልም ‹‹ጌታ ይወደዉ የነበረ ደቀ መዝሙር ››ተብሎ ስለ ተጠቀሰ የጌታ ወዳጅ ፍቁረ እግዚእ ይባላል፡፡ዮሐ 13፡ 23 ፡፡ ወልደ #ዘብድዮስ ፥ ዮሐንስ #ነባቤ መለኮት ፥ ዮሐንስ #ቦኦርኔጌስ ፥ ዮሐንስ #አብቀለምሲስ ፥ (ፍጥሞ በምትባል ደሴት ላይም ወደ ፊት የሚሆነዉን ነገር በራእይ ስለተገለጸለት በግሪክ ቋንቋ አቡቀለምሲስ ተብሏል፡፡ትጉሙም የራዕይ አባት ማለት ነዉ፡፡) ዮሐንስ #ወንጌላዊ ፥ ዮሐንስ #ድንግል ዮሐንስ #ታዎሎጎስ ቅዱስ ዮሐንስ ምሥጢረ ሥላሴንና ምሥጢረ ሥጋዌን አስፍቶ በመጻፉ (ታዎሎጎስ) ተብሏል፡፡ትርጉሙም ነባቤ መለኮት (የመለኮትን ነገር የሚናገር)ማለት ነዉ፡፡ 1. #ዮሐንስ_ብፁዕ (ብፁዕ ዮሐንስ) ፣ 2. ዮሐንስ ድንግል ፣3. #ዮሐንስ_ፍንው፣4. #ዮሐንስ_ካህን ፣ 5. #ዮሐንስ_ኅሩይ ፣ 6. ዮሐንስ ሥርግው፣7. #ዮሐንስ_ምዑዝ8. ዮሐንስ ቅኑይ ፣ 9. #ዮሐንስ_ማኅቶት ፣ 10. ዮሐንስ ቤዛ ሰማይ ፣ 11. #ዮሐንስ_ክቡር12. ዮሐንስ ጻድቅ ፣ 13. #ዮሐንስ_ረድእ፣ 14. ዮሐንስ ማኅቶት፣ 15. #ዮሐንስ_ድንግል፣ 16. ዮሐንስ ንጹሕ ፣ 17. #ዮሐንስ_ለባዊ ፣18. ዮሐንስ መረግድ፣ 19. #ዮሐንስ_ዕንቈ ፣ 20. ዮሐንስ መልአክ ፣21. #ዮሐንስ_ኪሩብ ፣22. #ቁጽረ ገጽ #ስዋሬው፤ ቅዱስ ዮሐንስ እስከ መስቀል ድረስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለዉን መከራ በማየቱ ከዚያ ዕለት ጀምሮ 70 ዘመን ሙሉ ፊቱ በኅዘን የተቋጠረ በመሆኑ (ቁጽረ ገጽ) ሆኖ ኖሯል፡ ቅዱስ ዮሐንስ ብዙ ተጋድሎን አርገጐ ዓለምን ሁሉ ዞሮ ካስተማረ ቦኃላ በመጨረሻም ደቀ መዝሙሩ አብሮኮስን ከወንድሞችም ሌሎች ሁለትን መርጦ መቆፈሪያ ይዘው ይከተሉት ዘንድ አዘዘ ፡፡ ጕድጓድም እንዲቆፍሩ አዘዘ ከዚያም ወረዶ ቆመ ልብሱንም አስወገደ የበፍታ ቀሚስ በቀር ሌላ አላረገም ነበር ፡፡ እየጸለየ ወደ ከተማም አሰናበታቸው፡፡ በክርስቶስ ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለሕዝብ ይነግሩአቸው ዘንድ አዘዘ ሁሉም እንደየ ስራቸው ጌታ እንደሚከፍላቸው ነገራቸው ፡፡ካዛም እንዲህ አለ እኔ ከሁላችሁም ደም ንፁሕ ነኝ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ ሳልነግራቹ የተውኩት ምንም ምን የለምና እናንተም ከእንግዲህ ከቶ ፊቴን አታዩም አላቸው ፡፡ እነርሱም እጅና እግሮቹን ስመውት ትተውት ሄዱ ሲመለሱም ልብስና ጫማ እንጂ ምንም አላገኙም እግዚአብሔርንም አመሰገኑት፡፡ ወልደ ነጐድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ዘጠና ዓመትም ኖረ፤ እንደባላሟሎቹ ሐዋርያት በመሰየፍ ሞትን አለቀመሰም፡፡ ‹‹ያ ደቀ መዝሙር አይሞትን እንዲል ›› ዮሐ 21 ስለ ድንግልናውና ስለንጽሕናው ይህ ሁሉ ሆነ፡፡ በዚህ በከበረ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን አሜን #share እና #Like ማድረግ እንዳይረሱ በሃገራችን በኢትዮጵያ ጥር 4 የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዓመታዊ ክብረ በዓል የሚከበርባቸውን አድባራትና ገዳማት ------------------------- በኢዲስ አበባ ማክበር ለምትፈልጉ #ደብረ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስና_መካነ_ጎልጎታ_ማርያም_ቤ_ክ_ማዕከላ_ለአዲስ_አበባ /መሐል አዲስ አበባ ከራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ የሚገኝ፤መቶኛ አመት የምሥረታ በዓልን በማክበር ላይ የሚገኝ ፣ ታቦተ ሕጉ ከኢየሩሳሌም የመጣና በአዲስ አበባ ብቸኛው የወልደ ነጐጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ.(እስከ ቅርብ ጊዜ )፡፡/፤ (አዲስ አ) ----------------------- 1ኛ) #ደቡብ_ወሎ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /ጥንታዊው ደብር፤ ከመካነ ሥላሴ አጠገብ የሚገኝ/፤ (መላው ወሎ በዚሁ ደብር እንገናኝ/ 2ኛ) #ሐይቅ_ደብረ_ነጎድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስ_ (የሐይቅና የደሴ ነዋሪ በዚህ ታላቅ ደብር እንገናኝ) 3ኛ) #ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /#ከታላቁ_ደብር_ከደብረ_በንኰል_ገዳም_አጠገብ/ (ሰለኽላኻ ሽሬና አካባቢዋ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 4ኛ) #አደቁዋረክ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /ማኅበረ ዴጎ አጠገብ/፤ (አኵስምና በአካባቢው ያላችሁ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 5ኛ) #ገደፈና_ዮሐንስ /ማይጨው አጠገብ/፤ (ማይጨው ራያና መቀለ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 6ኛ) #ዣት_ደብረ_ፀሐይ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /ሰሜን ሸዋ፥ ጅሩ/ (ሙሉ ሸዋ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 7ኛ) #ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ /ደምበጫ አጠገብ/፤ (ጎጃም በሙሉ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 8ኛ) #ዘንስር_ደብረ_ተድላ_ዮሐንስ_ማዕከላ_ለጐንደር፤ /ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱና ዋነኛው፤ በጎንደር ከተማ የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ወደ ግምጃ ቤት ማርያም ከመዛወሩ በፊት በብቸኝነት የጎንደርና የመላው ኢትዮጵያ ሊቃውንት የማኅሌተ ጽጌን ቁመት ለመቆም የሚተሙት ታላቅ ደብር/፤ (ጎንደርና አካባቢዋ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንገናኝ) 9.1ኛ) #ደብረ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስና_መካነ_ጎልጎታ_ማርያም_ቤ_ክ_ማዕከላ_ለአዲስ_አበባ /መሐል አዲስ አበባ ከራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ የሚገኝ፤ ታቦተ ሕጉ ከኢየሩሳሌም የመጣና በአዲስ አበባ ብቸኛው የወልደ ነጐጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ.ክ./፤ (አዲስ አበባና በአካባቢዋ ያላችሁ በዚሁ ደብር እንድንገናኝ ይሁን) 9.2ኛ) #ምስካየ_ኅዙናን_መድኀኔ_ዓለም_ገዳም (ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ባይከብርም ከጥንት ጀምሮ በውዳሴ በቅዳሴ ይከበራል፡፡) 10ኛ) #ቦኮሙራ_ወልደ_ነጐድጓድ_ቅዱስ_ዮሐንስ_ ቤ.ክን /ሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ሚሻ ወረዳ ቦኮሙራ ቀበሌ/፤ (በሀድያ፣ በስልጤ፣ በጉራጌና በደቡብ የምትገኙ ሁሉ በዚሁ ደብር እንድንገናኝ ይሁን፡፡) 11) #ናዝሬት_ደብረ_ፍስሐ_ቅዱስ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጎድጓድ_ቤ/ክ 12) #ደሴ_ዩኒቨርሲቲ_ደብረ_ነጎድጓድ_ቤ/ክ 13) #መቱ_ደብረ_ሳሌም_ሐይቅ_ደብረ_ነጎድጓድ_ (ያልጠቀስነው ካለ ኮሜንት ላይ ይጻፉ)

፲፩. አሸዋ ሜዳ ቤሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ላሊበላ ቤተክርስቲያን፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ ወልመራ ወረዳ፥ (አዲስ ዓለም አካባቢ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → አምቦ (አዲስ ዓለም) ፲፪. ቂልጠፋት በዓለ ወልድ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እንደጋይ ወረዳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ ፲፫. ጉንችሬ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እነሞር ወረዳ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ ፲፬. ደብረ ገሊላ ቅዱስ በዓለ ወልድ ወሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን፤ አድራሻ፤ አሜሪካ ሃገረ ስብክት፥ ሲያትል ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን)→ አሜሪካን (ሲያትል) ፲፭. ሆሳዕና ደብረ ምሕረት ቅዱስ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ሆሳዕና ፲፮. ቡኢ ደብረ ሰላም በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሃገረ ስብከት፥ ቡኢ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ቡኢ ፲፯. ባሕር ዳር በዓለ ወልድ (በዐለ እግዚአብሔር) ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ባሕር ዳር ሃገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡ ፲፰. ወለንጪቲ ጨመሪ በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ወለንጪቲ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወለጪቲ፡፡ ፲፱. ወንዶ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሳዲማ ሃገረ ስብከት፥ ወንዶ ገነት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወንዶ ገነት፡፡ ፳. ደብረ ምሕረት ዱና በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ዱና፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ዱና፡፡ ፳፩. ደብረ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሃገረ ስብከት፥ ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ደብረ ገነት፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ጾም #አጽዋማት #fasting's #ክብረ_በዓላት #Feast_of_the_lord #በዓለ_እግዚእነ

**ዳዊትም በመዝሙሩ ‹‹እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ፣ ዛሬም በተዋሕዶ ወለድኩህ አለኝ፡፡ ለምነኝ አሕዛብን ርስት አድርጌ እሰጥሃለሁ፣ ግዛትህም በመላው ዓለም ነው፡፡›› ዳግመኛም አብ አለ ‹‹ቀዳማዊ ወልድ በኃይል ቀን ካንተ ጋራ ሳለሁ ከአጥቢያ ኮከብ በፊት ከሆድ ወለድኩህ፣ እንደ መልከ ጸዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለሙ አገልጋይ ካህን ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ፣ ከማለም አይፀፀትም፡፡›› ዕንባቆምም ‹‹አቤቱ ድምፅህን ሰምቼ ፈራሁ ሥራህንም አይቼ አደነቅሁ፤ በሁለት እንስሳ መካከል አየሁህ›› (ዕን ፫፥፪) **ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም ‹‹በበረት ውስጥ የዓለም ገዢ መተኛት እጅግ ድንቅ ነው፤ በበረት ከጽርሐ አርያም ይልቅ ረዘመ፤ ከምድር ዳርቻም ሰፋ፤ ሕዝቅኤል ካየው ሠረገላ ዳንኤልም ካየው ኪሩባዊ ዙፋን በረት በለጠ (ሕዝ 1፡18-23፣ ዳን 7፡9) ብለው ተናገሩላት፡፡ #ኢትዮጵያና ግብፅ የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርሰቶስ ልደት በዓልን ታኅሣሥ 29 (በ4ት ዓመት 1ዴ ታኅሣሥ 28) ቀን ያከብራሉ፤ ለምን የሚለውን ከባሕረ ሓሰብ ሊቃውንትና ከመጻሕፍት እንድታነቡ እየጋበዝን ይህን ሁኔታ በጥልቀት ካጠኑት ዐበይት ሊቃውንት መካከል ዋናዎቹ #ማሪ ኤፍሬም ሶርያዊ፤ #ሰዒድ ወልደ በጥሪቅ፤ #መበንጋዊ/ማኅቡብ/፤ #ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ/አልአሚድ/፤ #ወልደ መነኰስ፤ #ሐዋርያት በዲድስቅልያ አንቀጽ 29 ገጽ 37፤ ሊቃውንት ወመምህራን ዘኢትዮጵያ ወግብፅ /ለአብነትም ከኢትዮጵያውን ደብረ ቢዘንና የጕንዳጒንዶ ሊቃውንት፣ አለቃ አሥራስ የኔሰው፣ አለቃ ሰዐት ከብቴ … እንዲሁም ቅዱስ ድሜጥሮስና ዮሐንስ አቤልሄሬም(ዮሐንስ አቡሻኽር) ከግብፅ ሊቃውንት/ ይጠቀሳሉ፡፡ #ታኅሣሥ 29 ልደታቸው ከጌታችን ልደት ጋር የተባበረላቸው ቅዱሳን፤ #አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፤ #ቅዱስ ላሊበላ፤ #ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ፤ #አቡነ አብሳዲ ዘደብረ መጕና #ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ፤ #ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃ፤ #አቡነ አካለ ክርስቶስ፤ #አቡነ መዝራእተ ክርስቶስ፤ #መስፍኑ ኢያሱ፤ #የገርአልታው አቡነ ዳንኤል፤ #ዳግማዊ ቂርቆስ ዘቡልጋና ሌሎችም ቅዱሳን አሉ፤ ነገር ግን ከቅዱሳን በዓል በላይ የጌታ በዓል መከበር ስለሚገባው የቅዱሳኑ ዋና በዓላቸው በሌላ ቀናት /በዕረፍታቸው…../ ቀን ይታሳባል፡፡ "#ታኅሣሥ ፳፱፤ #ልደተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ_፡፡ #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_ #የጌታችን_ልደት_የበዓለ_ወልድ_የገና_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፳፱ ገዳማትና አድባራት፡፡ ክብረ በዓሉ የሚከበርበት ምክንያት፤ የጌታችንና የአምላካችን የመድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፤ ልዩ ማስታወሻ፤ ከቅዱሳንም ሆነ ከእመቤታችን በላይ የጌታችን በዓል ከዋለ የጌታችን በዓል በዋነኛነት ስለሚከበር፤ ጾምም ከሆነ ጾሙ ቀርቶ በዓል ስለሚደረግ፤ በዓላቸው በዚህ ቀን የኾኑ ቅዱሳን በዓላቸው በሌላ ቀን ቅያሬ ሲከበር ነገር ግን በቦታቸው ላይ የጌታችን ልደት በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ ነገር ግን የጌታችን ልደት፤ ከ9ኙ ዐበይት የጌታችን በዓላት አንዱ በመኾኑ፤ በሁሉም ገዳማትና አድባራት ዋይዜማ ተዚሞ፥ ማኅሌት ተቁሞ፥ ሰዐታት ተቁሞ፥ ኪዳን ተደርሶ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ ይከበራል፡፡ #በመዲናችን_በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. አዲስ አበባ መካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ (አዲስ አበባ ላይ በ1883 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ነገር ግን ታቦቱ ቀድሞ የነበረና ከ600 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው) አድራሻ፤ አራዳ ከተማ ክፍለ ከተማ፤ 4ኪሎ ታክሲ፤ ከፒያሳ → አራት ኪሎ ፪. ለቡ ደብረ ታቦር በዓለ ወልድና አበ ብዙኃን አብርሃም ገዳም አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ለቡ ፫. ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤ/ክ አድራሻው፤ ሐና፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሐና፡፡ ፬. አንቀፀ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (የቅዱስ ላሊበላ ታቦት በድርብነት ይወጣል) አድራሻ፤ የካ_ክፍለ_ከተማ፥ ራስ ካሣ ታክሲ፤ ከ4 ኪሎ → ፈረንሳይ → አንቀጸ ምሕረት (ራሳ ካሣ ሚካአል) ፭. ፊሊዶሮ መድኀኔዓለም ቅዱስ ላሊበላ፡፡ አድራሻው፤ ፊሊዶሮ፡፡ ታክሲ፤ ከመርካቶ → ኮልፌ(ፊሊዶሮ)፡፡ ፮. አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ፯. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻው፤ መካኒሳ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መካኒሳ ፰. ኮልፌ ቀራንዮ (ታቦት ማደርያ) ደብረ ተአምራት ዳግማዊ ጻድቃኔ ማርያም፡፡ (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ዘነበወርቅ ታቦት ማደሪያ ጀርባ፤ ከዘነበወርቅ ወደ ታቦት ማደሪያ በሚወስደው መንገድ ላይ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃይሎች → ዘነበ ወርቅ፡፡ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፳፩ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ቤተልሔም፥ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም (ጌተችን የተወለደባት) አድራሻ፤ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን) → እስራኤል ፪. ማኅበረ ሥላሴ ገዳም (የሺዎች ገዳም)፤ (ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታ በተወለደባት ዕለት የጌታችን መወለድ በኢትዮጵያ የተበሠረባት) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ቋራና (መተማ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጎንደር → ሸዲ/መተማ/ ፫. ደብረ ሮሐ ላስታ ቅዱስ ላሊበላ (ዳግማዊት /አምሳለ/ ኢየሩሳሌም) አድራሻው፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ ፬. መንበረ ልዑል ደብረ መጕና አቡነ አብሳዲ ወቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወማኅበረ በኵር ገዳም፡፡ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከጎንደር ከተማ → ዳንሻ መስመር ላይ → በበው የምትባል መንደር ላይ ተወርዶ → የእግር ጕዞ ፭. ዞዝ አንባ አቡነ አብሳዲ (ቅዱስ ላሊበላ ከፈለፈላቸው አንዱ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ በለሳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ማክሰኚት → በለሳ (ዞዝ አንባ) ፮. ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አድራሻ፤ ጉራጌ ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ምደረ ከብድ ፯. ርዕሰ አድባራት አደባባይ ኢየሱስ ቤ.ክ.፤ /ጽላቱ ከደበቡ ኢትዮጵያ የሄደ፥ እጅግ ጥንታዊ ታሪክ ያለው፥ ኋላ ላይ ቊጥሩ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ የሆነ/ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፥ ጃንተከል ወርካ ጋር ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቱቡስ ተራ → ጎንደር ፰. ደብረ ስብሐት ቀሃ ኢየሱስ፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ፤ የጎንደር ላይ ቤት አቋቋም ትምህርት ቤት ማስመስከርያ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ ጥምቀተ ባሕሩ አጠገብ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቱቡስ ተራ → ጎንደር ፱. አለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል)፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ አለም ገና ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → አለም ገና፡፡ ፲. ገፈርሳ(ታጠቅ) በዓለ ወልድ ወአቡነ ሳሙኤል ወአቡነ ኪሮስ፤ አድራሻው፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ገፈርሳ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ታጠቅ ወይም መናገሻ የሚል ትራንስፖርት ይዘው ገፈርሳ ድልድዩ ጋር በዓለ ወልድን ያገኛሉ፡፡

#ጌና_እና_ልደት ጌና እና ልደት ዋዜማና ክብረ በዓል /የተለያዩ ቀናት/ ቢኾኑም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን ጌና ልደትን እየተካ እንጠቀምበታለን፤ ነገር ግን ይህ ሊስተካከል ይገባዋል፡፡ ልዩነት ስላለውም የኢትዮጵያ ብርሃን የተባለው አፈ ጳዝዮን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለጌናና ለልደት ለ2ቱም በዓላት ለየብቻቸው በመጽሐፈ ምሥጢር ድርሰት ደርሶላቸዋል፡፡ #ጌና፤ የልደት በዓል ዋዜማ ቀን ሲኾን በዚህ ቀን ‹‹በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ›› የተባለለትን ‹‹የገና ጨዋታ›› እንጫወታለን፤ የምንጫወትበት የኳሱ ስያሜ ‹‹ሩር›› ሲባል ስያሜውን ያገኘው፤ ሰብዓ ሰገል እልፍ እልፍ ሠራዊት አስከትለው የተወለደውን አይሁድ ንጉሥ ፍለጋ ወደ ንጉሡ ሔሮድስ ደርሰው ነበርና፤ ሔሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ፈልጎና በውስጡ ሸሽጎ ለሰብዓ ሰገል ሂዱ ሕፃኑን ፈልጉ ስታገኙትም ንገሩኝ ብሎ ሰድዷቸዋል፤ ነገር ግን በዚያው ሳይነግሩኝ እንዳይሄዱ በማለት እነርሱ ሳያውቁ ‹‹ሩር›› የተባለ ሰላይ በመሃላቸው አስገብቶ ነበርና ሰብዓ ሰገልን ይመራቸው የነበረው ኰከብ ተሠውሮባቸዋል፤ ሰብዓ ሰገል ሠራዊታቸውን ቢያጣሩ ከመሃከላቸው የተቀላቀለ ሩር የተባለ የሔሮድስን ሰላይ አገኙ ይህንንም ሰላይ የሰብዓ ሰገል ሠራዊት አንገቱን በሰይፍ ቀልተውታልና ያን ለማስታወስ ዛሬ በገና ጨዋታ ላይ ሩር የተባለው ኳስ የሔሮድስ ሰላይን ‹‹ሩር›› እንዲያስታውስ አባቶች ሥርዐትን ሠሩ፡፡ #ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #‹‹#ቤዛ_ኩሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ::›› /#ቅዱስ_ያሬድ/ ጌታችን ለሰው ልጆች ብሎ፤ የሰው ልጆች ፍቅር አገብሮት ንጽሕትና ቅድስት ከኾነች ከእመቤታችን ያለ ወንድ ዘር በመጋቢት 29 ተጸንሶ ታኅሣሥ 29 በ1ዓ.ም. (ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ በ5,500 ዓመት) በበረት ተወልደ፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው፤ ወሰነውም በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ እረኞች ነበሩ፡፡ መልአኩ መጥቶ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹እነሆ! ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና፡፡ ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ›› አላቸው፡፡ ሉቃ2፡10-12፡፡ ከመለአኩም ጋራ ሠራዊተ መላእክት መጥተው ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዕጓለ እመሕያው /ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ/›› አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ እረኞቹ እርስ በርሳቸው ‹‹እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ፣ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ›› ተባባሉና ፈጥነው መጡ፡፡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ፡፡ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ፤ የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሯቸው ነገር አደነቁ፤ የብርሃን እናቱ እመ አምላክ ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር፡፡ ሉቃ 2፡13-19፡፡ መላእክትም ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆኑለት አምላክ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በጎል ተኝቶ በጨርቅ ተጠቅልሎ አይተውት ደስ ብሏቸው ወደ ሰማይ ቢያርጉ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዕሪና ከመንበሩ አይተውት ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት›› ብለው አመስግነውት በጣዕም ላይ ጣዕም፤ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨምሮላቸው ደስ ብሏቸዋል፡፡ ልደቱን ይሹታልና፤ መላእክትም ብቻ አይደሉም እንስሳትም አራዊትም ደስ ብሏቸዋል፡፡ #ይህም_ሊታወቅ_አንድ_ባሕታዊ_በቋራ_/_ኋላ_ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም/_ቋርፍ_ሲምስ_ቶራ_ሚዳቋ_ዮም_ተወልደ_ መድኀኔ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ከሣቴ_ብርሃን፡፡ እያለች ስትዘል አይቷል። በጌታችን በልደቱ የባሕር ውኃ ወተትና ማር ተራሮች እንጀራ እንጨቶችም የበረከት ፍሬ ሆነዋል፡፡ ልደቱንም በኮከብ ተረድተው ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች) ስማቸውም ማንቱሲማር፣ ሜልኩ በዲዳስፋ የተባሉ የፋርስ ነገሥታት ከገነት የተገኘ ወርቅ፣ ዕጣን ከርቤ አምጥተው ገብረውለታል፡፡ /ዘኅ 20፡17፡፡ ‹‹ሰው ሆይ! ፈጽመህ ደስ ይበልህ፣ እግዚአብሔር ዓለሙን ወዶታልና አንድ ልጁንም የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም ፈጽሞ ይድን ዘንድ አሳልፎ ሰጥቷልና ልዑል ክንዱን ሰደደልን፡፡›› ‹‹በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፤ ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፤ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፡፡ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ፡፡›› ‹‹ከቅድስት ሥለሴ አንዱ ወልድ መዋረዳችንን አይቶ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ባሕርዩን ዝቅ አደረገና መጥቶ በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደ እኛ ሰው ሆነ፡፡ ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩለት በቤተልሔም ተወለደ፤ ፈጽሞ አዳነን፣ ወገኖቹም አደረገን፡፡›› ይህችም ዕለት፤ ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ብሎ ትንቢት የተናገረላት ናት፡- ‹‹እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅ ትወልዳለች፣ ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች፣ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ /ት.ኢሳ. 7፥14/ **ነቢይ ሕዝቅኤል ‹‹እግዚአብሔርም አለኝ ‹ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች፣ አትከፈትም፣ የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር››› አለ፡፡ **ነቢዩ ዳንኤልም ‹‹ሌሊት በራእይ አየሁ ‹እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ፤ ዘመኑን ወደሚያስረጅ ደረሰ፣ ከፊቱም አቀረቡት፣ የዘላለም አገዛዝ፣ ጌትነት፣ መንግሥት ተሰጠው፡፡ ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል፤ አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው፤ መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው››› አለ፡፡ **ዳግመኛም ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጠልኝ›› አለ፡፡ አሁንም ደግሞ ‹‹አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ›› አለ፡፡ ሁለተኛም ‹‹በእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፣ ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል›› አለ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው፣ ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ይባላል›› አለ፡፡ **ነቢዩ ኤርምያስም ስለ እግዚአብሔር ‹‹በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ፣ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል፣ እግዚአብሔርም ያመኑትን ያድናቸዋል›› አለ፡፡ **ኤልሳም ‹‹እግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል፣ በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል፡፡ ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል›› አለ፡፡ **ናሆምም ‹‹እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል፣ ልብሱም እንደልብሴ ነው›› አለ፡፡ **ኢዩኤልም ‹‹የእግዚአብሔር ዙፋን የሆነች ብላቴና ድንግልን አየሁ፣ እርሷም እንደ እሳት ያልባት ነበር፡፡ ስለእርሷ ‹ይህች ማናት/› ብዬ ኪሩብን ጠየቅሁት፡፡ እርሱም ‹ከአዳም ልጆች የተመረጠች የእግዚአብሔር ዙፋን ይህች ድንግል ናት፣ በእርሷም የተጎሳቆሉ አሕዛብ ይድናሉ፤ ለአመነባትም ረድኤትና መጠጊያ ናት› ብሎ ነገረው፡፡››

#ጾመ_ገሃድ/ጋድ የገሃድ ጾም ከ7ቱ የአዋጅ አጽዋማት አንዱ ነው ፡፡“ገሃድ የቃሉ ትርጉም መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው ” ጥምቀት ረቡዕ፣ አርብ ሲውል በዚያ ለውጥ ማክሰኞ፣ ሐሙስ ይጾማልና ለዚህም ጋድ አለው እንላለን ፡፡ ፍትሐ ነገሥቱ ጾሙን “ጾመ ድራረ ጥምቀት/ ጾመ ድራረ ልደት” በሎ ይጠቅሰዋል፡ ፡ #የልደት_በዓል_እንደ_ጥምቀት_ገሃድ_አለው፡፡ ለዚህም “…ወእምኔሆሙ ዘይከውን በአምሳለ ጾም ዐባይ በተጠናቅቆ፡፡ ወይእቲ ሰሙነ ሕርቃል ዘትከውን እምቅድመ ጾም ዐቢይ ወጾመ ሰብአ ነነዌ ፫ቱ ዕለታት፡፡ወጾመ ድራረ ልደት ወጾመ ድራረ ጥምቀት፡፡ ……ከእነርሱም እንደ ዐቢይ ጾም በመጠንቀቅ የሚሆን አለ፡፡ ይህችውም ከዐቢይ ጾም አስቀድማ የምትሆን የሕርቃል ጾም ናት፡፡ የነነዌ ሰዎች ጾም 3 ቀን፤ የልደትና የጥምቀት ዋዜማ ጾም፤ (ገሀድ)፡፡”›› የሚለው የፍትሐ ነገሥታ ቃል ገላጭ ነው ነው፡፡‹‹ አንቀጽ 15 ላይ ሌሎች አዋጆችንም ይንግረናል ፡፡ #እንዴት_በጾመ_ነቢያት_ላይ_ደምረን_ገሃድን_እንጾማለን ? ጾመ ነቢያት/ የገና ጾም ከኅዳር 15 ጀምሮ እስከ ታኅሳስ 28 ቀን ለ44 ቀናት ይጾማል፡፡ ከእነዚህም መካከል 40ው ቀን ጾመ ነቢያት፣ 3ቱ ጾመ አብርሃም ሶርያዊ ሲሆኑ የቀረው 1 ቀን ደግሞ የገሃድ ጾም ነው፡፡ በልደት የሚጾመው የገሃድ ጾም በጾመ ነቢያት ውስጥ ተካቶ ይጾማል ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት በዐቢይ ጾም ውስጥ ጾመ ሕርቃልና ሰሙነ ሕማማት ተካትተው እንደሚጾሙ ማለት ነው፡፡ (ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15 ቁጥር 565፣ 567)፡፡ በዘመነ ዮሐንስ በዓለ ልደት በታኅሳስ 28 ነውና የገና ጾም የሚጾመው ለ43 ቀናት ነውና የዘመነ ዮሐንስ ገና ገሃድ የለውምን? የሚል ጥያቄም ከተነሣ መልሱ ልደት በዘመነ ዮሐንስም ገሃድ አለው የሚል ነው፡፡ ይልቁንም በዐቢይ ጾም፣ በጾመ ሐዋርያት፣ በጾመ ፍልሰታ፣ በጾመ ነቢያትና በጾመ ነነዌ ጾመ ድኅነትን (የረቡዕና ዓርብ ጾምን) ደርበን እንደምንጾም እንዲሁ ገሃድን በጾመ ነቢያት ውስጥ ደርበን እንጾማለን፡፡ ዐቢይ ጾምን ሳይጾሙ ሰሙነ ሕማማትንና ጾመ ሕርቃልን እንደማይጾሙት ጾመ ነቢያትን ከኅዳር 15 ጀምሮ ሳይጾሙ ለልደት የገሃድ ጾምን ልጹም ማለት ትልቅ ድፍረት እና ኃጢያት ነው ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #ጾም #አጽዋማት #fasting's #ክብረ_በዓላት #Feasts