ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 456 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 521 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 194 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 456 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 31 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 69، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -9، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.29‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 8.00‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 065 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 237 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 22.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 02 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 456
المشتركون
-924 ساعات
+787 أيام
+6930 أيام
أرشيف المشاركات
ለ64 ዓመታት ታላቁን ደብር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምን በጸሎት ያገለገሉት ጸሎተኛው አባት አባ ወልደ አረጋዊ ዐረፉ፡፡ ፨ ‹‹ወኢትጸመም ሞቶ ለዘተልአከከ (ያገለገለህን ሰው ሞት ቸል አትበል)፡፡›› ሲራ. 38÷16 ሁልጊዜም ጠዋት ጠዋት ከደወል ቤት ፊት ለፊት ቁጭ ብለው ጸሎት ማድረስ የዘወትር ተግባራቸው በመሆኑ በሁሉም ዘንድ ይታወቃሉ! አባ ወልደ አረጋዊ፡፡ አባ ወልደ አረጋዊ አብርሃ ጎሹ መካነ ትውልዳቸው ትግራይ ገርዓልታ ማይ ደዓሮ ሲሆን፡፡ በተወለዱበት አካባቢ በሚገኘው፤ በቦታው አቀማመጥ በሀገራችን እና በዓለማችን ዕፁብ ድንቅ በተባለለት በታላቁ ገዳም በገርዓልታ ማይቁዲ ዮሐንስ (በገመድ የሚወጣ ገዳም ነው) የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ተምረዋል፡፡ በዚሁ ገዳምም በወጣትነት ዘመናቸው በዲቁና እያገለገሉ ቤተሰቦቻቸውንም ደግሞ በግብርና ሥራ እያገለገሉ አድገዋል፡፡ በዚሁ አገልግሎት እያሉ ሕመም ስላጋጠማቸው ለሕክምና ወደ ራያ ወደሚገኝ ሐኪም ቤት፤ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ አቅንተዋል፡፡ ወደ አዲስ አበባ እንደመጡም መጀመሪያ ወደ ዘነበ ወርቅ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በማቅናት ለጥቂት ጊዜ ቆይተዋል፤ ነገር ግን ሕመማቸው የአንድ እግራቸውን አሳጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ ታላቁ ደብር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም በደጅ ጸኚነት መጡ፡፡ ደብራችንም ከመላው ኢትዮጵያ የሚመጡ አገልጋዮች ማረፊያ (ወደ አዲስ አበባ የመጣ ካህንን ቀጨኔ ፈልጉት) እስከሚባል ድረስ የደረሰ የእንግዳ ተቀባይነት ታሪክ ስላለው፤ በዚሁ መሠረት በወቅቱ የነበሩት የደብራችን አባቶችም ለአባ ወልደ አረጋዊ መኖሪያ ቤት ሰጥተው፣ የሚያስፈልገውን ነገርም አሟልተው በጸሎት እያገለገሉ እንዲቀመጡ አደረጓቸው፡፡ እርሳቸውም በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም የ64 ዓመታት የአገልግሎት ቆይታቸውም፤ 1ኛ) ለ64 ዓመታት ሁልጊዜም በጸሎት ይተጉ ነበረ፤ የጾም ሰዐታቸውም ሁልጊዜም ዘነፍ አትልም ነበረ፡፡ 2ኛ) በጸሎት አስቡኝ የሚላቸውንም ማንኛውንም ምዕመን ያለምንም ክፍያ በጸሎት ያስቡ ነበረ፡፡ 3ኛ) ጥንታዊ የሆነውን የገርዓልታ ድጉም አቡነ ስምዖን ገዳም ሕንፃ ቤ/ክ ለብቻቸው አሣንጸዋል፡፡ 4ኛ) ለ131 አብያተ ክርስቲያናት መቀደሻ አልባሳት፣ ንዋያተ ቅድሳት፣ ለመሥዋዕት መገበሪያ፣ …… አበርክተዋል፡፡ 5ኛ) በተለያዩ ቦታዎች ላሉ ረጂ ለሌላቸው፤ እናት አባት ለሞተባቸውም ሕፃናት ከ3መቶ ሺሕ ብር በላይ እየላኩ ረድተዋል፡፡ ፨ ዕድሜ ዘመናቸውን በዚህ ዓይነት አገልግሎት ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ የዕረፍት ጊዜያቸውን ቀድመው በማወቃቸው ይረዷቸው እና ይላላኳቸው ወደነበረው ወደ አቶ ተክሌ ቤት ሄደው ለ10 ቀናት ከቆዩ በኋላ እመቤቴ እየመጣች ነው ጸሎት ላድርስ ብለው ጸሎታቸውን እንደጨረሱ ለአቶ ተክሌ አንድ ቃል ብቻ ነግረዋቸው በብዙኃን ማርያም ቀን መስከረም 21 ቀን በ92 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፈዋል፡፡ ሥርዐተ ግብዓተ መሬታቸውም በኑዛዜያቸው መሠረት መስከረም 22/2018 ዓ.ም. ባሣነጹት ትግራይ ገርዓልታ ድጉም አቡነ ስምዖን ገዳም ተፈጽሟል፡፡ ‹‹…በጺሐኪ ድንግል ጊዜ ዕረፍትየ፤ ጽጌ ዕፀ ገነት ገሪ ላዕሌየ፤ በመዐዛሁ ትትመሠጥ ነፍስየ፡፡ (ድንግል በዕረፍቴ ጊዜ ደርሰሽ የገነት የዛፍ አበባን በእኔ ላይ ጣዪ፥ ዕጠኚ፤ በመዐዛው ነፍሴ ከሥጋዬ ትለይ ዘንድ፡፡) /ማኅሌተ ጽጌ ቊ.፻፲፮/

በቀጨኔ መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን ለሰባት ዓመታት አስተዳዳሪ የነበሩት መልአከ ገነት ምናሴ ዘለቀ የሕይወት ታሪካቸው በመጽሐፍ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን መስከረም 25, 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓ
በቀጨኔ መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን ለሰባት ዓመታት አስተዳዳሪ የነበሩት መልአከ ገነት ምናሴ ዘለቀ የሕይወት ታሪካቸው በመጽሐፍ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን መስከረም 25, 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ በቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ አዳራሽ ይመረቃል።

✤እንኳን ለመስከረም 21፤ብዙኃን_ማርያም #ብዙኃን_ሊቃውንት_ለተሰበሰቡበት_ብዙኃን_ማርያም_፤ #ክቡር_መስቀሉና_ሌሎችም_ንዋያተ_ቅድሳት-በግሸን_ደብረ_ከርቤ_አምባ_ላይ_በክብር_ላረፉበት_ዕለት፤ #ለቅዱስ_ቆጵርያኖስ_(ኃይለኛ ሥራየኛ ጠንቋይ የነበረውና በኋላም አምኖ ለክርስቶስ ምስክር ሆኖ አንገቱን የተሰየፈው )ና ፡ ቆጵርያኖስን ያሳመነችውና ስሟ በተጠራበት ቦታ ሰይጣናት እንደ ትቢያ ሆነው የጠፉት ታላቋ ቅድስት ድንግሊቱ ዮስቴና በሰማዕትነት ላረፉበት ዕለት፤ #ሃይማኖታቸው_ለቀና_ለ318ቱ_አበው_ሊቃውንት  (#በ325 ዓ.ም #አርዮስን_አስተምረው_ለመመለስ_#በኒቅያ_የተሰበሰቡባት_ዕለት )፣ /የጉባኤውም ፍጻሜ ኅዳር ዘጠኝ ነው/ እንዲሁም #ከ72ቱ_አርድእት_አንዱ_ለሆነው_ለሐዋርያው_ቅዱስ_ጢባርዮስ_ዕረፍት በሰላምና በጤና አምላከ አበው መድኀኔዓለም አደረሳችሁ አደረሰን፡፡ ✤✤✤✤ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓሏ መስከረም ፳፩ ቀን መከበሩ ስለ  ሁለት ነገር ነው፡፡ ፠1ኛ) መስከረም ፳፩ የምናከብርበት አንደኛው ምክንያት  መስቀልን አስመልክቶ ነው፡፡ መስቀሉ በመስቀልኛ ቦታ በግሸን ደብረ ከርቤ በክብር ያረፈበት ዕለት ነው፡፡    #ግሸን_ደብረ_ከርቤ ደብረ #ንገሥት  ፣ ደብረ #ነጐድጓድ ፣ ደብረ #እግዚአብሔር በሚባሉ ስም ትጠራ ነበር ፡፡ በመጀመርያም የተመሠረትቸው በአፄ ካሌብ  ዘመን ነበር ፡፡ሁለት ጽላቶች ከናግርን (አጼ ካሌብ ድል አድርጎ ከተመለሰ በኃላ ) በአባ ፈቃደ ክርስቶስ አማካኝንት (መነኰስ) አምጥተዋል ፤ ከዛም ሲመጡ  ወደ ጊሸን ተራራ ሊወጡ ሲሉ በዚያ ንብ ሰፎ ማር ሲንጠባጠብ በማየታቸወው በግእዝና አረብኛ ቋንቋ   #አምባ አሰል ብለው ጠሩት ትሩጉሙም የማር አማባ ማት ነው እስካሁንም አካባቢው አምባሰል እየተባለ ይጠራል፡፡ የመጡትንም ጽላቶች በማስገባት የመጀመሪያውን ቤ.ክ ሠረተው ደብሩን መስርተዋል፡፡   በሺህ አንድ መቶ ሃያ ሰባት ዓመት ሰማዕታት ሃይማኖታቸው የቀና የዳግማዊ ዳዊት ልጅ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ከአፄ ይኩኖ አምላክ ከተረፈው የመንግሥት ቅብዓት ተቀብተው ነገሡ፡ ስመ መንግሥታቸውም #ቆስጠንቲኖስ ተባለ፡ በተወለዱም በሃምሣ ዓመት ‹‹ መስቀሌን በመስቀል ላይ አስቀምጥ የሚል ራዕይ አይተው ›› ጠይቀው ሲረዱ አባታቸው የተረከበው መስቀል በመካ መዲናው አሕዛብ ሹም እንዳለ ተረዱ ክተት ሰራዊት ብለው አደሊዋ ድረስ ዘመቱ በዚህ ጊዜ የምስሩ ንጉሥ የአባትህ ገንዘብ እኔጋ  ስላለ እባክህ ከእኔ ጋር አተዋጋ መስቀሉን ፣ ሥዕላቱን እና ንዋያተ ቅዱሳቱን እስጥካለሁ አላቸው ( ማብራርያ መስከረም 17 የለጠፋነውን ጽሑፍ ተመልከቱ ) ይህንን ተቀብለው ተመልሰው ለ3 ዓመታት መስቀለኛ ቦታ ፈለጋ በኢትዮጵያ ተራሮች ዞሩ  ቅዱስ ዑራኤልም ይራዳቸው ነበር ፡፡ ከሥስት ዓመት ቦኃላም አምባሰል ደርሰው ቦታዋ  በመስቀል አምሳል የተቀረጸች መሆኗን አዩ፡፡ መግቢያው ቦታ እጅግ አስቸጋሪ ስለነበር አረፈው በነበሩበት ጊዜ ቅዱስ ዑራኤል ተገልፆ ይህች ደብረ ከዛሬ ጀምሮ ደብረ ከርቤ ትባላለች ፡፡ደብረ ነጐድጓድ ትባለ የነበረውም የካህናትና የነገሥታት መኖርያ ስለሆነች ነው ፡፡ሥላሴን የሚክዱ ሊኖሩባት አይችሉም ፡፡ ወደ ውስጥ ስትገባ ሁለት አብያተ ቤ.ክ ታገኛለህ አንዲቱ #በእግዚአብሔር አብ ስም  የተሠራች ናት፡፡ አንዲቱ ደግሞ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም የታነጸች ናት፡፡     እመቤታቸንም ተገልጻለት #በኢትዮጵያ በተሰደድኩበት ጊዜ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ ርስት ትሁንሽ ብሎ ስምሽ እስከ ዕለተ ምጽአት ሲመሰገን ይኑርባት ብሎ ሰጥቶኛል እና ሄድ  ብላ ቦታዋን #ጠቆመችው፡፡     በ1446 ዓ.ም መስከረም 21 ወደ ተራረው ገብተው አይተው ተደሰቱ በታዘዙትም መሠረት ቅዱስ መስቀሉን በእግዚአብሔር ስም በተሰራው መቅድስ #አስቀመጠው፡፡   መስከረም 21 ቀንም መስቀሉ የተቀመጠበት የእግዚአብሔር አብ ቤ.ክ ቅዳሴ ቤቱ ሆነ ፡፡ ጌታችን በዘባነ ኪሩቤል ላይ ሆኖ አእላፍ መላእክትን አስከትሎ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር መጣ ፡፡ እጅግም ብዙ ቃል ኪዳን ገባለት፡፡ ለቦታዋም ታላቅ ክብርን ሰጣት ደብረ ታቦርም ትሁንልህ አለው ፡፡ ፠፠፠ #ብዙኃን_ማርያም፤ ፠2ኛ) ደግሞ ጉባኤ ኒቅያን ይመለከታል፤ ለ፲፰ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ለተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ ካሉት ደቀ መዛሙርት መካከል አርዮስ፣ አኪላስና እለእስክንድሮስ የሚባሉት ዋነኞቹ ነበሩ፡፡ አርዮስ እውቀቱ  በመምህሩ የተመሠከረለት ሊቅ ነበር፡፡ ነገር ግን “እጅግ ጥበብ ያደርሳል ከሞት” እንዳለ ሰሎሞን የተጻፈውን ትቶ ባልተጻፈው ላይ ፍልስፍና ጀመረ፡፡ በምሳ. ፰÷፳፪ ላይ ያለውን ቃል በተሳሳተ መንገድ ፈታው፤ ነገር ግን ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ ጠርቶ ቢመክረው ቢገስጸው እንቢ በማለት የክህደት ትምህርቱን ቢቀጥልበት ከሹመቱ አውርዶ አወገዘው፡፡ ተፈጻሜተ ሰማዕት ከደቀመዛሙርቱ መካከል አኪላስን ተክቶ ኅዳር ፲፱ ቀን በሰማዕትነት አረፈ፡፡ አኪላስም የጓደኝነት ፍቅር አድልቶበት አርዮስን ከውግዘት ቢፈታው በመቅሠፍት ሞት ሞተ፡፡ በመንበሩም እለእስክንድሮስ ተተካ፡፡ በዚህ ጊዜ የአርዮስ የክህደት ትምህርት በሀገሪቱ ሞላ፡፡ ይህ ነገርም እየተባባሰ በመሔዱ በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘንድ ተሰማ፡፡ ንጉስ ቈስጠንጢኖስም ይህን ሲሰማ ለአርዮስ ጥያቄ መልስ ይሠጥበት ዘንድ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጕባኤ እንዲደረግ ሰኔ ፳፩ ቀን አዋጅ አስነገረ፡፡ ይህንን አዋጅ የሰሙት ሊቃውንት ሁሉ መስከረም ፳፩ ቀን የእመቤታችን እለት ተሰባሰቡ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ “ለምን ቈስጠንጢኖስ መልዕክት ከላከበት ጊዜ በኋላ ወዲያውኑ ለምን አልመጡም? ለምን ዘገዩ?” የሚለው ጥያቄ ይነሳል፡፡ ምክንያቱም፤ #አንደኛ መጓጓዣ ችግር ስለነበር፤ #ሁለተኛ ሁሉም ሊቃውንት አስተማሪዎች በመሆናቸው ለምዕመናኑ (ለተማሪዎቻው) ሌላ መምህር ማዘጋጀት ስለነበረባቸው፤ #ሦስተኛ ደግሞ በእድሜ የገፉ ስለነበሩ አንድም ሊቃውንቱ ሲያስተምሩ በአላውያን ነገሥታት ባላመኑ ሰዎች ግፍ ይድርስባቸው ስለነበር ነው፡፡ ለምሳሌ ቶማስ ዘመርዓስ በእነዚህ ሰዎች በግፍ እግሩና እጁ ተቆርጦ ስለነበር ለማስተማር በቅርጫት ይዘውት ነበር የሚጓዘው፡፡ ወደ ጕባኤውም ሲመጣ ደቀ መዛውርቱ ያመጡት #በቅርጫት ይዘውት ነበር ( ማብራርያ የጥቅምት 14 የለጠፍነውን እይ ) ፡፡ ከዚህ በኋላ 2,340 ሊቃውንት መስከረም ፳፩  ቀን ተሠባሰቡ፡፡ ከእነዚህ መካከል ግን 318ቱ ሊቃውንት ‹‹ዘእሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ ›› በማለት  በሃይማኖታቸው የጸኑ ነበሩ፡፡  ጉባኤውን ከመጀመራቸው በፊት አርባ (፵) ቀን ሱባኤ እስከ ኅዳር ዘጠኝ (፱) ቀን ይዘውና ጕባኤውን አድርገው በአንዲት ቀን ያንን ታላቅ መናፍቅ አርዮስን ድል ነሥተውታል፡፡ ከዚህ ጋር አያይዘውም የኃይማኖታችን መሠረት የሆነውን ጸሎተ ሃይማኖትን  አዘጋጅተዋል፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/     #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

የ2018 ዓ.ም የመስቀል በዓለ ንግሥ። /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958