ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 395 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 567 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 182 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 395 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 5، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 20، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 21.05‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.41‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 240 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 602 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 17.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 395
المشتركون
+2024 ساعات
+257 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
የባለትዳሮች ጉባኤ እና የእኅቶች ጉባኤ እሁድ ሐምሌ 3 / 2014 ዓ.ም ተከናወነ፡፡
+1
የባለትዳሮች ጉባኤ እና የእኅቶች ጉባኤ እሁድ ሐምሌ 3 / 2014 ዓ.ም ተከናወነ፡፡

#አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ ሐምሌ 3 ልደታቸው ነው፡፡ በድጋሚም ሐምሌ 3 ቅዳሴ ቤታቸው ነው ፥ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡ #በአ.አ#እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት ቀድሞ በቅዳሴና በውዳሴ ታቦተ ሕጋቸው ሲከበር የቆየው የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ታቦተ ሕጋቸው #እሁድ_ሐምሌ 3/2014 ዓ.ም. ታቦተ_ሕጋቸው_ወጥቶ_ይከብራል፡፡ (ሁላችሁም እንድትገኙ ገዳሟ ጥሪዋን አስተላልፋላች)፡፡ #የደብረ_ሊባኖስ_ገዳምን_የመሠረቱና_በስማቸው_የተሠየመላቸው፤ ፠ ቅዱስ ላሊበላ ከ11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱን በስማቸው ያነፀላቸው፡፡ ፠ #ከደረቅ_ዐለት_ላይ_ውኃ_እያፈለቁ_ድውያንን_የሚፈውሱ_ተአምረኛ_አባት ፠ በኤርትራ አካለ ጉዛይ ገዳመ መጣዕ፣ በአኵሱም ከተማ አጠገብ፣ በላስታ ላሊበላ፣ ደብረ ወርቅ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፣ እንዲሁም ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ በአ.አ. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ገዳም ክብረ በዓል የሚከበርላቸው፡፡ ፠ አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ሊድሯቸው ሲሉ መመነን በመፈለጋቸው መልአክ በሌሊት መጥቶ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡ ፠ አባ ጳኩሚስም ሥርዐተ ገዳምን፥ አስኬማ መላእክትን፥ ቅናተ ዮሐንስን አስተማሯቸው፤ አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡ ፠ ቀድሞ የመራቸው መልአክ ከአባ ጳኩሚስ ‹‹ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድሎህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአኵሱም ተቀመጡ፡፡ ፠ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው (ቀድሞ የዋልድባን ገዳም ባስፋፉ አባቶች የተመሠረተችውን #የእንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳምን እስፋፍተው፡፡) ተመልሰው ወደ አኵሱም ሄዱ፡፡ ፠ በአኵሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ፥ ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአኵሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል ‹‹ተራ ውሃ ነው›› ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ ‹‹አምላከ አባ ሊባኖስ›› ብሎ አመሰገነ፡፡ (ስዕላቸው የሚገልጸው ይህንን ተአምር ነው፡፡) ፠ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው ‹‹ምትሃት ነው የሚያሳየው›› ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡ ፠ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአኵሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ፤ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው ‹‹አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን›› ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡ ፠ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ (የአሁኗ ደብረ ሊባኖስ) መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው ‹‹ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ (አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኮሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል›› አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡ ፠ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አኵሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም ‹‹ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ›› አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ ‹‹ሊባኖስ ዘመጣዕ›› የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ በወቅቱ የነበረው አፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡ ፠ ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ አፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡ ፠+፠ በመጨረሻም ጥቅምት 2 ቀን ተፀንሰው ፤ ፠+፠ ሐምሌ 3 ቀን ተወለደው፤ ፠+፠ በ140 ዓመታቸው ጥር 3 ቀን በክብር ዐርፈዋል፡፡ ፠+፠ ቅዳሴ ቤታቸው ደግሞ ሐምሌ 3 ነው፡፡ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡ #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም ፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡ ፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው ጠበሏን አፍልቀው ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡ ፠ በ197 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለአቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡

፰. ፀዶበር ዮሐንስ መጥምቅ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መንዝ ፥ ቀያ ገብርኤል፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መንዝ → ቀያ ገብርኤል፡፡ ፱. አርባ ምንጭ ገረሴ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ (ፈዋሴ ድውያን የሆነ ፈዋሽ ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ አርባ ምንጭ ሀገረ ስብከት፥ ገረሴ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. አለም ባንክ አውቶቡስ ተራ → አርባ ምንጭ → ገረሴ (ከአርባ ምንጭ 55 ኪ.ሜ.)፡፡ ፲. ወንጪ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ወንጪ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ ውቶቡስ ተራ → ወንጪ፡፡ ፲፩. ደብረ ዘይት (ቢሾፍቱ) ዳግማዊ ሸንኮራ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ (ፈዋሴ ድውያን ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ አድአ ወረዳ ቤተ ክህነት ፥ ከታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ዘይት → ከታ፡፡ ፲፪. ተንታ ደብረ ብርሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ (ንጉሥ ሚካኤል በሚያስደንቅ ሁኔታ ያሠሩት) አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል፥ ተንታ ወረዳ፥ ጠዓት ቀበሌ፥ እሜገኝ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ፡፡ ፲፫. ሰበታ ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ሰበታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ሰበታ፡፡ ፲፬. ሰበታ ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ሰሜን አሜሪካ ሀገረ ስብከት፥ ቨርጂኒያ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር መንገድ → አሜሪካ /ቨርጂኒያ/፡፡ አቅጣጫ ምንጭ ዋሊ..

#ሰኔ #፴ ፤ #በዓለ_ልደቱ_ለቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_፡፡ #በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፴፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ #በአዲስ_አበባ_የቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_በዓለ_ልደት_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ #፳፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ ጨምሩበት፡፡) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ፩. ቦሌ ደብረ ሳሌም ዮሐንስ መጥምቅ (ኋላ መድኀኔ ዓለም ወዮሐንስ መጥምቅ) ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቦሌ መድኀኔ ዓለም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቦሌ፤ ፪. ፉሪ ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ዮሐንስና ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ 3፥ መስታወት ፋብሪካ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሜክሲኮ → ጀሞ፡፡ ፫. ደብረ ሰሊሆም መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ በርታ ሰፈረ ሰላም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4ኪሎ) → ቃሊቲ፡፡ ፬. ቱሉ አቦ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ዑራኤልና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቱሉ አቦ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ቱሉ አቦ፡፡ ፭. ጎፋ መብራት ኀይል ደብረ መዊዕ ቅዱስ መርቆሬዎስና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ጎፋ፥ መብራት ኀይል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጎፋ መብራት ኀይል፡፡ ፮. ላፍቶ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለም (ለብቻው የቅዱስ ዮሐንስ ሕንፃ ቤ/ክ አለ)፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ቀርሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሜክሲኮ → ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለም፡፡ ፯. ቦሌ ቡልቡላ ፍኖተ ሕይወት ማርያምና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፤ አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቡልቡላ ኮንዶሚንየም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሳሪስ → ቡልቡላ፤ ፰. ቤተል ጌቴሴማኒ ቅድስት ማርያም ወዮሐንስ ፤ አድራሻው፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤቴል፥ መኪና መለማመጃ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → መኪና መለማመጃ፤ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #እንዲሁም_በድርብነት_፤ ፱. ጉለሌ ሸጎሌ ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ አዲሱ ገበያ ፥ ቶታል፥ ወደ ዊንጌት በቀለበት መንገገዱ ትንሽ ሄደው፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (አስኮ) → አዲስ ገበያ፡፡ ፲. አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አንቆርጫ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → አንቆርጫ፡፡ ፲፩. ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ፈረንሳይ ፥ ብረት ድልድይ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → ብረት ድልድይ፡፡ ፲፪. ቦሌ ሰሚት መካነ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሰሚት፥ ወጂ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሰሚት፡፡ ፲፫. ገዳመ ኢየሱስ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ሆላንድ ኤምባሲ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ኮልፌ አጣና ተራ፡፡ ፲፬. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም ቤ/ከ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አውግስታ፥ ሸሚዝ ፋብሪካ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃይሎች → አውግስታ፡፡ ፲፭. አስኮ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለምና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ፥ አዲስ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከአራዳ (ፒያሳ) → አስኮ አዲስ ሰፈር፡፡ ፲፮. መዝገበ ምሕረት ቅዱስ ፋኑኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ፋኑኤል ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ) → ካራቆሬ፡፡ ፲፯. ምዕራፈ ቅዱሳን ፈለገ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና አቡነ አረጋዊ ገዳም፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሳሪስ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሳሪስ ፲፰. ሳሪስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሳሪስ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ሳሪስ ፲፱. ቀርሳ ፈለገ ብርሃን ቅድስት ልደታ ለማርያምና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ገላን ኮንዶሚኒየም፥ ቀርሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ቀርሳ፡፡ ፳. ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፥ ጠሮ አራት መንታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → ዊንጌት፡፡ ፳፩. ካራ አሎ ደብር ቅዱስ ደብረ ቀርሜሎስ መደኀኔ ዓለምና አቡነ ገሪማ ገዳም፤ አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ፥ ካራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሾላ መገናኛ → ኮተቤ ካራ፤ ፳፪. ምሥራቀ ፀሐይ ገብርኤል፤ አርሴማና አቡነ አዳም ቤ/ክ ፤ አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፥ ጀርመን ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ /ጀርመን ዐደባባይ/፤ ፳፫. ሰርጢ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰርጢ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ/አቃቂ → ሰርጢ፤ ፳፬. አቃቂ ፈንታ ደብረ ጽጌ ሩፋኤልና አርሴማ፤ አድራሻው፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ፈንታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ/አቃቂ → ፈንታ፤ #እንዲሁም_ ፈዋሴ ድውያን ወገባሬ ተአምራት የሆኑ #ጠበሎቹ፤ መካነ ሰማዕት ደብረ ፍስሓ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ (ለገሃር ምድር ባቡር ጣቢያ ጀርባ)፤ ፈዋሽ የፍልውኃ ጠበል በላፍቶ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ አለ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ጥንታውያን #፲፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ደብረ ቢዘን ዘንባባ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገዳም፤ (የቅዱሳን መናኸሪያ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለት፤ ትራንስፖርት፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → በኩክ የለሽ መስመር የ1 ሰዐት የእግር ጕዞ፤ ወይም፤ ከጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን → ይዞሽ አሞራ → የ1 ሰዐት እግር ጕዞ፡፡ ፪. ጎንደር ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፫. ሸንኮራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ዮሐንስ ፤ (ዮሐንስ ጌታን ሲያጠምቀው በሚስል ሁኔታ ከደረቅ አለት መሃል በተሰቈረ ቀዳዳ የሚፈልቅ አስደናቂ ጠብል ያለበት) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ምንጃር፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ሞጆ → ሸንኮራ፤ ፬. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤ/ክ፤ (በሸንኮራ ዮሐንስ መስመር መንገድ ዳር ላየይ የሚገኝ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ምንጃር፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ሞጆ → ሸንኮራ (ሳማ ሰንበት) መንገድ አጠገብ የሚገኝ፤ ፭. ደብረ አናጕግ ቅዱስ ሚካኤል ወዮሐንስ መጥምቅ ፤ አድራሻው፤ አኵሱም (ማዕከላዊ ትግራይ) ሀገረ ስብከት፥ አኵስም አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → አኵስም → አናጕግ፡፡ ፮. መርሐ ቤቴ አሮጋንዳ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ መርሐ ቤቴ → ዓለም ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → መርሐቤቴ /አሮጋንዳ/፤ ፯. አዲስጌ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ፤ አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ እንሳሮ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ለሚ → እንሳሮ፡፡

የተለያዩ የግብይይት ሥርዓቶች ተጽእኖ በመንፈሳዊ ሕይወት ክፍል 3 ((ሶስተኛ ሳምንት)) ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ ---› https://cutt.ly/lLqXnQg