ar
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

تُعد قناة Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 369 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 633 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 187 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 369 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -46، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 37، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 22.37‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 7.87‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 438 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 210 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 22.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

15 369
المشتركون
+3724 ساعات
+367 أيام
-4630 أيام
أرشيف المشاركات
#ቡሄ ማለት ምን ማለት ነው ? #ችቦ ለምን እና መቼ ይበራል?  #ሙልሙል ልምን ይታደላል?  በቡሄ ወቅት #ጭራፍ ለምን ይጮሃል  ? #ቡሄ ቡሄ ማለት ብራ፣ ብርሃን፣ ደማቅ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት በዓል የሚዘከርበት እና ለበዓሉም ችቦ ስለሚበራ የብርሃን በዓል በማለት የቡሄ በዓል እንላለን፡፡ ወቅቱ የክረምት ፤ጨለማ አልፎ የብርሃን የሚወጣበት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት የመሸጋገሪያ ወቅት ነው፡፡ “ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት” እንዲሉ፡፡ በሌላ በኩልም “ቡኮ/ሊጥ” ተቦክቶ ዳቦ የሚጋገርበት “#ሙልሙል” የሚታደልበት በዓል በመሆኑ ቡሄ ተብሏል፡፡  ፨፨፨ #ጅራፍ   በደብረ ታቦር በዓል በትውፊታዊ መልኩ የሚታየው ምስጢር፤ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው የጌታችን ምስጢራዊ ሞቱ ነው፡፡ ጅራፍ መገመድ(መጥለፍ) እና ጅራፍ ማጮኽ ሁለት ዓይነት ምስጢር የያዘ ትውፊታዊ ተግባር ነው፡፡ የመጀመሪያው ግርፋቱንና ሞቱን እናስብበታለን፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ፤ድምፁን ስንሰማ የባሕርይ አባቱን የአብን ምስክርነት ቃል፤ እንደ ነጎድጓድ ድምፅ ያስታውሰናል፡፡ የጅራፍ ትውፊታዊነት /ውርስ/፣ መጽሐፋዊ ትምህርትና ምስጢር ጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ጨዋታውን በተራራማ አካባቢ፣ ከመኖሪያ ቤት ርቆና፣ በሜዳ ማድረጉ ጠቃሚ ነው፡፡ ጅራፍን #በርችት መቀየር የሚያመጣውን የምስጢር ተፋልሶ ብቻ መመልከት ከማኅበራዊ ጎጂ ገጽታው በላይ እንድናስወግደው ያስገድደናል፡፡ ፨፨፨         #ችቦ      ችቦ የጌታችንን ብርሃነ መለኮት መገለጥ የሚያመለክት ነው፡፡ በመሆኑም ችቦ ለኩሰን በዓሉን እናከብራለን፡፡ የዚህ ትውፊታዊ አመጣጥ በብርሃኑ ድምቀት የቀኑን መምሸት ያልተረዱ እረኞች በሜዳ ቀርተዋልና ወላጆች ከመንደር ችቦ ለኩሰው ልጆቻቸውን ፍለጋ ሔደዋልና ታሪኩን እያዘከርን በዓሉት እናከብራለን፡፡ የችቦው መንደድም ሌላ ትርጉም አለው፡፡ አንድ ምእመን ለሌላው ምእመን መካሪ አስተማሪ መሆኑን፣ መከራ እየተቀበለም አርአያ፣ ምሳሌ፣ ብርሃን መሆኑን ያሳያል፡፡ በሃይማኖትም አርአያ ምሳሌ ይሆንላቸዋል፡፡ ከዚህ ጋርም ተያይዘዞ ችቦ #በ13 ምሽት ይበራል ፣ብርሃኑ የተገለጠው በዚችው ዕለት ነውና ፡፡ ፨፨፨     #ሙልሙል በችቦ ብርሃን ልጆቻቸውን ፍለጋ የወጡ ወላጆች ዳቦ ጋግረው ይዘውላቸው ወጥተዋል፡፡ ስጦታው ቤተሰባዊነትን፣ ፍቅርንና መተሳሰብን መግለጫ ነው፡፡ ወደ ቤታችን “ ቡሄ ” እያሉ ለሚመጡ አዳጊዎችም፤ ዘምረው እንዳበቁ የሚሰጥ “ሙልሙል” ዳቦ አለ፡፡ ሕፃናቱም ሊዘምሩ ሲመጡ ዳቦ መስጠት ልማዳዊ ብቻ አይደለም፡፡ ሕፃናቱ የደቀመዛሙርት ምሳሌ ናቸው፡፡ መዝሙራቸው ደግሞ ሐዋርያት “የምሥራች” ይዘው የመምጣታቸው ምሳሌ ነው፡፡ ሐዋርያት በገቡበት አገር አስተምረው አጥምቀው የጸጋ ልጅነትን አሰጥተው በረከት አድለው እንደሚሔዱም፣ ልጆችም ዘምረው፣ አመስግነው፣ መርቀው “ውለዱ ክበዱ፣ ሀብት አግኙ፣ የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች ያድርጋችሁ ….” ይላሉ፡፡ በአጠቃላይ በዓለ ደብረ ታቦር ከእነዚህ ምስክር ካላቸው ትምህርቶቹ፣ ምሥጢር ከሚራቀቅባቸው ትርጓሜያቱና ከትውልድ ትውልድ በቅብብል በተላለፈው ቅዱስ ትውፊት ጋር ሃይማኖታዊ ባሕል ሆኖ ሊቀጥል ይገባዋል፡፡ ይህን ማድረግ የሚቻለው ግን አዳጊዎች ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ይዘው እንዲያድጉ ጥቆማ በመስጠት፣ ግጥም በመግጠምና ምሥጢሩን በማብራራት የመጀመሪያዎቹ ባለድርሻዎች ወላጆች ናቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ የሚሰሙ ግጥሞች ስድብ፣ ፌዝና ሥላቅ የተቀላቀለባቸው ይሆናሉ፡፡ ሕፃናቱም ዝማሬውን ሲጀምሩ “ከሰጡን እንነሣ ከነሱን እናርዳ” ብለው ይጀምሩታል፡፡ ከሰጡን እንመርቃለን ካልሰጡን እንራገማለን በማለት፡፡ አሳሳቢው ነገር ደግሞ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ወደ ገንዘብ ማግኛነት የቀየሩ ሁኔታዎች መታየታቸው ነው፡፡ ዳቦ /ሙልሙል/ ትምህርቱንም፣ ምስጢሩንም፣ ትውፊቱንም በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል ከዚም ጋር ተያይዞ ሰንበት ት/ት ቤታችን ለበረካታ ዓመታት ሰወረድ የመጣውን የዝማሬ ሥርዓት ለአጥብያው ምእምን በየቤቱ በመሄድ የብሄን ዝማሬ ከነሥርዓቱ በመዘመር አገልግሎት ይሰጣል ፤የደብር ታቦርን በዓል በተመለከትም የወረቀት ጽሑፎችን ይበትናል በዝማሬ መኃል ያድላል  ፡፡ ቤተክርስቲያን የምሥጢር ግምጃ ቤት ናት፤ የምታከናውነውን ሁሉ ከበቂ መረጃ ጋር ነው ተግባራዊ የምታደርገው፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ ፠፠፠     #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

#ከተራራው ግርጌ ከቅዱሱ ተራራ ግርጌ ዘጠኙ ደቀ መዛሙርት ተቀምጠዋል፡፡ ነቢዩ “አቤቱ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰውስ ተራራህ ማን ይኖራል” / መዝ.14፥1/ በማለት ጠይቆ ወደ ተቀደሰው ተራራ የሚወጡ ሰዎች ምን ዓይነት ሕይወት ያላቸው ሊሆን እንደሚገባ ሲገልጥ “… በአንደበቱ የማይሸነግል፤ በባልንጀራው ላይ ክፉትን የማያደርግ … በንፁሑ ላይ መማለጃን የማይቀበል ….” በማለት የጠቀሳቸው ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ /መዝ. 14፥1-5/ ወደ ቅድስናው ስፍራ ወጥቶ ምስጢር ለማየት ብቃት ያልነበረው ይሁዳን ለመለየት አምላክ ባወቀ ዘጠኙን ከተራራው ግርጌ አቆይቷቸዋል፡፡ “የኃጥእ ዳፋ ጻድቁን ያዳፋ” የሚል ብሂል አለ፡፡ ይህ አባባል ግን ከተራራዉ ግርጌ ለቀሩት ደቀ መዛሙርት አይሆንም፡፡ ይሁዳን በጥበብ ከምስጢር ለየው እንጂ ጌታ ስምንቱ ደቀ መዛሙርቱን የምስጢሩ ተካፋይ አድርጓቸዋል፡፡ ለጥፋቱ ምክንያት እንዳያገኝ ከምስጢሩ ቢለየኝ ከሞቱ ገባሁበት እንዳይል በጥበብ ይህን አደረገ፡፡ ስምንቱ ደቀ መዛሙርት ግን በንጹሕ ልቡና ከተራራው ግርጌ ተቀምጠውም ምስጢር አልተከለከላቸውም፡፡ ምክንያቱም “ልበ ንጹሐን ብፁዓን ናቸው እግዚአብሔርን ያዩታልና” /ማቴ.5/፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ እግዚአብሔርን ለማየት ለሚወዱ “ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ ያለ እርሱ ጌታን ሊያይ የሚቻለው የለምና” እንዲል፡፡ /ዕብ.11/፡፡ #ሙሴና ኤልያስ ለምን ተመረጡ? ሙሴንና ኤልያስን ወደ ደብረ ታቦር እንዲመጡ ያደረገበት ምክንያት የባሕርይ አምላክ መሆኑን እንዲመሰክሩ ነው፡፡ ሙሴን ከመቃብር ተነሥቶ ስለጌታችን እንዲህ የሚል ምስክርነት ሰጥቷል፡- “እኔ ባሕር ብከፍልም፤ ጠላት ብገድልም፤ ደመና ብጋርድም፤ መና ባወርድም እስራኤልን ከክፋታቸው መልሼ ማዳን ያልተቻለኝ ደካማ ነኝ፤ የእኔን ፈጣሪ እንዴት ሙሴ ይሉሃል? የሙሴ ፈጣሪ እግዚአብሔር ይበሉህ እንጂ!” ኤልያስም ደግሞ ከብሔረ ሕያዋን መጥቶ “እኔ ሰማይ ዝናብ እንዳይሰጥ ብለጉም፣ እሳት ባዘንብም፣ እስራኤልን ከክፋታቸው ማዳን የማይቻለን ነኝ እንዴት የእኔን ፈጣሪ ኤልያስ ነህ ይሉሃል? የኤልያስ ፈጣሪ እግዚአብሔር ይበሉህ እንጂ!” ብለው የባሕርይ አምላክነቱን በደብረ ታቦር ላይ መስክረዋል፡፡ በማቴ.16፡14 ላይ “አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት።” ይላልና፡፡ ሙሴና ኤልያስ የተመረጡበት ሌላው ምክንያት ሙሴ “ጀርባዬንም ታያለህ፤ ፊቴ ግን አይታይም” ተብሎ ስለተነገረለት /ዘጸ.33፡23/ ኤልያስ “በኋለኛው ዘመን ምስክሬ ትሆናለህ” ስለተባለ ያንን ለመፈጸም ነው፤ ካገቡት ሙሴን ከደናግል ኤልያስ ያመጣቸው መንግሥተ ሰማያት በሕግ የተጋቡ ሕጋውያንና ሥርዐት ጠብቀው የሚኖሩ ደናግላን እንደሚወርሷት ለማስተማር ሁለቱን መርጧቸዋል፡፡

#ደብረ_ታቦር ደብረ ታቦር ከገሊላ ባሕር በምዕራባዊ በኩል 10 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ተራራ ሲሆን፤ ከፍታው ከባሕር ወለል በላይ 572 ሜትር ይሆናል፡፡ በዚህ ተራራ ላይ ጌታችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን እንደሚገልጽ ምሳሌና ትንቢት ተነግሯል፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ “#ታቦርና #አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል” ብሎ የተናገረው ትንቢት እንዲፈጸም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተአምራቱን በዚህ ተራራ ላይ ገልጧል /መዝ. 88፥12/፡፡ በዘመነ መሳፍንት ባርቅ ሲሣራን ከነሠራዊቱ ድል ያደረገው በደብረ ታቦር ተራራ ላይ ነው፡፡ ምሳሌነቱም ባርቅ የጌታችን ሲሣራ ደግሞ የአጋንንት ነው፡፡ ጌታችን በደብረ ታቦር ክብሩን በመግለጥ በአይሁድ እያደረ አምላክነቱን እንዲጠራጠሩ ያደረጋቸውን አጋንንት ድል የማድረጉ ምሳሌ ነው /መሳ. 4፥6/፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን በቂሳርያ “የሰውን ልጅ ማን ይሉታል?” ብሎ ከጠየቃቸው ከስድስት ቀን በኋላ #አዕማድ ተብለው የሚጠሩ ሦስቱን ሐዋርያት ይዞ ወደ ረጅም ታቦር ተራራ ወጣ፡፡ በፊታቸውም ተለወጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ፡፡ እነሆም #ሙሴና #ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው፡፡ ቅዱስ #ጴጥሮስ መልሶ ጌታችን ኢየሱስን ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፡፡ ብትወድስ በዚህ ሦስት ዳስ እንስራ አንዱን ለአንተ አንዱን ለሙሴ አንዱን ለኤልያስ አለ፡፡ በዚህ ጊዜ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፡፡ ከደመናውም በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል ድምፅም ተሰማ፡፡ ሐዋርያት ይህንን ሰምተው የጌታችንን መለኮታዊ ክብር አይተው በፊታቸው ወደቁ እጅግ ፈርተው ነበር፡፡ ጌታችንንም ተነሡ አትፍሩም አላቸው፡፡ በዚህ መልኩ አምላክነቱን ገለጠላቸው /ማቴ. 17፥1-10/፡፡ ፠፠፠ #አዕማደ_ሐዋርያት_ለምን_ተመረጡ "አዕማደ ሐዋርያት ተብለው የተጠሩት #ጴጥሮስ፣ #ያዕቆብና #ዮሐንስ ናቸው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ጴጥሮስ፣ ዮሐንስና ያዕቆብን “አዕማድ ሐዋርያት” እያለ ጠርቷቸዋል /ገላ. 2፥9/፡፡ ስያሜውን ያገኙበት ዋናው ምክንያት የኢየሩሳሌምን ቤተ ክርስቲያን በሓላፊነት ያስተባብሩ ስለነበረ ነው፡፡ ከዚህን በተጨማሪ ጌታችን በኢያኢሮስ ቤት ልጁን ሲፈውስ፣ በጌቴ ሴማኒ ሲጸልይና በደብረ ታቦር ምስጢረ መለኮቱን ሲገልጥ ከእሱ ስላልተለዩና ይዟቸው ስለሔደ ነው /ማር.5፥37-43/፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሦስቱ ደቀ መዛሙርት የተመረጡበትን ምክንያት ሲያትቱ እንዲህ ብለዋል፡፡ ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ሹመት፣ ሽልማትና ክብር ፈላጊዎች ነበሩ፡፡ ከዚህ ሃሳብ እንዲወጡ ከብልየታቸው እንዲታደሱ ለይቶ አውጥቷቸዋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለድኅነተ ዓለም የመጣው በሕማማቱ በሞቱ ቤዛ የሚሆነን አምላክ “ልሰቀል ነው” ባላቸው ጊዜ “አይሁንብህ” ብሎት ነበር፡፡ እንዲህ ያለው ሃሳብ የጠላት እንጂ የሰው ልጆች ሊሆን አይችልም ከሞቱ በቀር ድኀነት ሊያስገኝልን የሚችል የለምና፡፡ ደቀ መዝሙሩ ግን ከሞተ ክብሬ ምንድን ነው ብሏልና “አይሁንብህ” አለ፡፡ /ማቴ. 16/ በሌላም ስፍራ እንዲሁ “ሁሉን ትተን ተከተልንህ እንግዲያስ ምን እናገኝ ይሆን?” በማለት ይጠይቃል፡፡ /ማቴ.19/፡፡ ጌታ ግን ዋጋችሁ #ሰማያዊ #ክብራችሁ ዘላለማዊ ነው ሲል እስከ ፍጹማን መዓርግ /ነጽሮተ #ሥሉስ ቅዱስ/ አድርሶ ብርሃነ መለኮትን ገልጦ ተስፋውን ነገራቸው፡፡ ሁለቱ ወንድማማች ደቀ መዛሙርትም እናታቸውን ልከው ሹመት ሽልማት መዓርግ ለምነዋል፡፡ ስለዚህም ጌታችን በደብረ ታቦር “በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ነገር” ስለሞቱ እንዲነጋገሩ አደረገ፡፡ ሞቱ እርግጥ ሆነ ማለት ነው፡፡ አባቱም “ኦሆ በልዎ ለክርስቶስ”፤ እሺ በሉት እርሱን ስሙት ሲል፡፡ ሞቱ እርግጥ በመሆኑ ከልባቸው እንዲጠፋ መርጦ ወደ ቅዱስ ተራራ ይዟቸው ወጥቷል፡፡ “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም” እንዲል /ሚል 3፥6/ በእርሱ ዘንድ ወረት የለም፡፡ አስቀድሞ ከተዓምራቱ ከምሥጢሩ አይለያቸውም ነበርና ብርሃነ መለኮትን ለማየት አበቃቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ለማወቅ፣ ለመማር፣ ለመጠየቅ ያሳዩት ትጋት ምስጢር ተገልጦላቸዋል፡፡ ይህ ምስጢር ለሦስቱ ደቀ መዛሙርት ተገልጦ የሚቀር አይደለም፡፡ እስከ ዓለም ፍፃሜ እግዚአብሔር ለመረጣቸው ሲገለጥ፣ በመረጣቸውም ሲነገር የሚኖር ነው፡፡ደቀ መዝሙሩ ጴጥሮስ “አልክድህም አልተውህም” የሚለው /ማቴ. 26፥35/ ቢወድደው አይደለምን? ፍቅሩን መግለጡ ለክብር አብቅቶታል፡፡ ሁለቱ ደቀ መዛሙርትም “ጽዋዬን ልትጠጡ አትችሉም” ቢላቸውም /ማቴ. 20፥22/ አንዳችን በቀኝ ሌላችን በግራ ሆነን አብረንህ እንሞታለን ሲሉ በምስጢር ለምነዋል፡፡ ሞታቸውን ከሞቱ ጋር መደመራቸው ፍቅራቸውን መግለጣቸው ነው፡፡ ፠፠፠ #Share #like #The_feast_of_the_transfiguration_of_our_lord_on_mount_tabor #Nehhasee 13

#የየኔታ_ወልደሚካኤል_አጭር_የሕይወት_ታሪክ #የኔታ_ወልደሚካኤል_ተወልደ_ብርሃን  ልዩ ስሙ ፅልማ ስራዬ አዲለጎ በ1920ዓ.ም ሚያዝያ 29 ተወለዱ  በአያታቸው ቤትም  መምህር ትርፉ ክፍሉ ከተባሉት  ፊደል ንባብ መልክዐ ማርያም መልክዐ ኢየሱስ ሰዓታት እና ግብረዲቁና  ተማሩ በ1939 መጋቢት ወር ወደ ላስታ ገለሶት ሃዋ ሚካኤል ቄስ ተስፋዬ ከሚባሉ ጋር አባ ኪሮስ ወደ ሚባሉ የድጓ መምህር በመምጣት የቃል ትምህርት አጠናቀዋል  በ1940 ዓ.ም  መስከረም 21 ከአራት  ጓደኞቻቸው ጋር ሆነው ወደ #ግሸን_ማርያም በመሄድ  የአቋቋም የድጓ  የዝማሬ እና የቅዳሴ መምህር ወደ ሆኑት  የኔታ መንግስቱ የሚባሉ ስመጥር መምህር  ጋር የሄዱ ሲሆን ክብረ በዓሉን አክብረው የኔታ መንግስቱ  ወደ ደሴ የኔታ አፈወርቅ ወደ ሚባሉ 150አካባቢ ተማሪ  ወደነበራቸው የቅኔ መምህር ደሴ መድኃኔዓለም ላኳቸው። ደሴ መድኃኔዓለም ቅኔ መማር የጀመሩ ሲሆን  በ10ወር ቅኔ ተቀኝተው ወደ ግሸን ማርያም በመመለስ  ምርቃት በመቀበል ተመልሰው ደሴ መድኃኔዓለም ቅኔውን ማስፋፋት ያዙ። በ1941 ዓ.ም መምህሩ ወደ ደብረ ሊባኖስ  ሲሄዱ  እዛው ደሴ የኔታ ኤልያስ እና  የኔታ ወልደማርያም ከሚባሉ  መምህራን እየተማሩ ቆዩ ታህሳስ 22 በ1941 ዓ.ም ከሁለት ተማሪዎች ጋር ሆነው ወደ  ደብረሊባኖስ  በመሄድ የኔታ አፈወርቅ ጋር  ገብተው  የቅኔ  ትምህርታቸውም ማስፋፋት ቀጠሉ በመሃል  የኔታ አፈወርቅ ወደ አዲስዓለም ማርያም ሲሄዱ  የኔታ ወልደሚካኤል ደብረፅጌ የኔታ ይትባረክ  (የሩፋኤል አስተዳዳሪ የነበሩት ጋር) አንድ ወር ከግማሽ  አሁን የቅኔ ትምህርታቸውን ሲያስፋፉ የቆዩ ሲሆን  ሰኔ 21,1941 ዓ.ም ወደ ቀድሞ መምህራቸው የኔታ አፈወርቅ ዘንድ   ወደ አዲስ ዓለም ማርያም በመሄድ የቅኔ ትምህርታቸውን እያስፋፉ ተማሪዎችንም ያስቀፅሉ ነበር። የኔታ ወልደ ሚካኤል በትምህርት ቤት በነበሩበት ጊዜያት ሁሉ  ከስራቸው ያሉ ተማሪዎችን በማስቀፀል ይታወቃሉ በ1944 ዓ.ም  በርዕሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ማርያም ከመምራቸው የኔታ አፈወርቅ  በቅኔ መምህርነት ተመርቀው እዚሁ ደብር  በቅኔ መምህርነት እንዲያስተምሩ የተቀጠሩ ሲሆን #ማስተማር_እንጂ_ደመወዝ_አልወስድም በማለት አንድ ዓመት ቅኔ አስተምረዋል። ተስፋሚካኤል የሚባለው ወንድማቸው በ1946 ዓ.ም መጥቶ ከአዲስ አለም ወደ አስመራ የወሰዳቸው ሲሆን እዛም የተለያዩ አድባራት እያገለገሉ  ቆይተው በ1947 ዓ.ም  ወደ መቀሌ በመምጣት መቀሌ ኪዳነምህረት  እና  መድኃኔዓለም የኔታ ኃይለሥላሴ ከሚባሉት እውቅ መምህር በድጋሚ ፀዋትወ  ዜማ እየቀፀሉ ቅኔ ማስተማር ጀመሩ በወቅቱም የዜማ መምህራቸው የኔታ ኃይለሥላሴም  የኔታ ወልደ ሚካኤል ዘንድ ቅኔ ይማሩ ነበር  መስከረም 1950 ዓ.ም የቅኔ መምህራን ተመርጠው ለፈተና  ቅድስት ሥላሴ ተፈትነው የኔታ ወልደሚካኤል ፈተናውን አልፈው   አንድ ዓመት  የመምህርነት ስልጠና በመውሰድ በዕጣ ጋሞጎፋ ተመድበው ግብረ ገብ እና አማረኛ መምህር ሆነው 3 ዓመት አስተምረዋል። በ1944 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ በመዛወር አምሃደስታ ት/ቤት ተመድበው  እስከ 1959 ዓ.ም  ለስድስት ዓመታት አምሃ ደስታ  ትምህርት ቤት ሲያስተምሩ ቆይተው  በ1960 ዓ.ም ቀለመ ወርቅ ት/ቤት ተመድበው የመጡ ሲሆን   ከ1960 ዓ.ም ጀምሮ #ቀጨኔ_ደብረሰላም_መድኃኔዓለም_እና_ደብረ_ትጉሃን_ቅዱስ_ገብርኤል_ቤ/ክ በማህሌት በመቆም እና ቅኔ በመቀኘት አገልግሎት የጀመሩ ሲሆን በ1966 ዓ.ም ድጋሚ ወደ አምሃ ደስታ ት/ቤት በመመለስ እስከ 1981 ዓ.ም በማስተማር በዛን ጊዜ በነበረው ሕግ መሠረት በ55ዓመታቸው ጡረታቸውን አስከብረዋል። በ1987 ዓ.ም ከጡረታ በኋላ በሚያውቋቸው መምህራን ጠቋሚነት ምስካየ ኅዙናን ገዳም  ዘመናዊ ት/ቤቱ ውስጥ ለአንድ ዓመት ከሰባት ወር ግዕዝ አስተምረዋል በተያያዥም ቀን ቀን በገዳሙ የተመደቡ የቅኔ መምህር ስለነበሩ #በበጎ_ፈቃደኝነት ማታ ማታ ደግሞ የኔታ ወልደሚካኤል መነኮሳቱን ግስ ያስተምሩ ነበር። በ1989 ዓ.ም  ዘመናዊ ትምህርት ማስተማሩን በማቆም  #ቀጨኔ_ደብረሰላም_መድኃኔዓለም_እና_ደብረ_ትጉሃን_ቅዱስ_ገብርኤል_ቤ/ክ ልክ እንደ አንድ መደበኛ ሠራተኛ #በእለተ_ሰንበት #በወርሃዊ_በዓላት እና #በዓበይት_በዓላት #በገረገራው_ውስጥ_በማደር  በሕመም ቤት እስከዋሉበት ጊዜ ድረስ መድኃኔዓለምን በቅንነት ያገለገሉ አባት ነበሩ ። የአገልግሎት ዋጋቸውን የሚከፍለው ያገለገሉት አምላክ ቢሆንም #በፍኖተ_ሕይወት_ሰንበት_ት/ቤት እና #ማኅበረ_አሃው የአጥቢያው ማኅበር በሚዘጋጀው "#ዝክረ_አበው" በተሰኘው አባቶች በሕይወተ ሥጋ ባሉበት ወቅት ፀሎታቸው እና ምርቃታቸውን እንዲሁም በአገልግሎት አርአያ በመሆናቸው ለመታሰቢያ በሚዘጋጀው መርሐ ግብር #የሙካሽ_ካባ ተበርክቶላቸዋል የኔታ ወልደሚካኤል በአገልግሎት በቆዩባቸው ዘመናት #ምንም_ድካም_የማይታይባቸው_ብርቱ_አባት_ነበሩ የኔታ ወልደሚካኤል ባለትዳር እና የ3ሴት ልጆች አባት ነበሩ ነፍሳቸውን ከደጋግ አባቶች ዘንድ ያሳርፍልን ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመድም መፅናናትን ያድልልን ለቤተክርስቲያንም እንዲህ ያሉ መምህራንን መድኃኔዓለም ይተካልን። Facebook  https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube    https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/Finotehiwott www.Finotehiwotsundayschool.com

#_የየኔታ_ወልደ_ሚካኤል_አጭር_ የህይወት_ታሪክ የኔታ ወልደ ሚካኤል ተወልደ ብርሃን ልዩ ስሙ ፅልማ ስራዬ አዲለጎ በ1920ዓ/ም ሚያዝያ 29 ተወለዱ በአያታቸው ቤትም መምህር ትርፉ ክፍሉ ከተባሉት ፊደል ንባብ መልክዐ ማርያም መልክዐ ኢየሱስ ሰዓታት እና ግብረዲቁና ተማሩ በ1939 መጋቢት ወር ወደ ላስታ ገለሶት ሃዋ ሚካኤል ቄስ ተስፋዬ ከሚባሉ ጋር አባ ኪሮስ ወደ ሚባሉ የድጓ መምህር በመምጣት የቃል ትምህርት አጠናቀዋል። በ1940ዓ/ም መስከረም 21 ከአራት ጓደኞቻቸው ጋር ሆነው ወደ ግሸን ማርያም በመሄድ የአቋቋም የድጓ የዝማሬ እና የቅዳሴ መምህር ወደ ሆኑት የኔታ መንግስቱ የሚባሉ ስመጥር መምህር ጋር የሄዱ ሲሆን ክብረበዓሉን አክብረው የኔታ መንግስቱ ወደ ደሴ የኔታ አፈወርቅ ወደ ሚባሉ 150አካባቢ ተማሪ ወደነበራቸው የቅኔ መምህር ደሴ መድኃኔዓለም ላኳቸው እዚሁ ቅኔ መማር የጀመሩ ሲሆን በ10ወር ቅኔ ተቀኝተው ወደ ግሸን ማርያም በመመለስ ምርቃት በመቀበል ተመልሰው ደሴ መድኃኔዓለም ቅኔውን ማስፋፋት ያዙ በ1941መምህሩ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሲሄዱ እዛው ደሴ የኔታ ኤልያስ እና የኔታ ወልደማርያም ከሚባሉ መምህራን እየተማሩ ቆዩ ታህሳስ 22 በ1941ዓ/ም ከሁለት ተማሪዎች ጋር ሆነው ወደ ደብረሊባኖስ በመሄድ የኔታ አፈወርቅ ጋር ገብተው የቅኔ ትምህርታቸውም ማስፋፋት ቀጠሉ በመሃል የኔታ አፈወርቅ ወደ አዲስዓለም ማርያም ሲሄዱ የኔታ ወልደሚካኤል ደብረፅጌ የኔታ ይትባረክ (የሩፋኤል አስተዳዳሪ የነበሩት ጋር) አንድ ወር ከግማሽ አሁን የቅኔ ትምህርታቸውን ሲያስፋፉ የቆዩ ሲሆን ሰኔ 21/1941 ዓ/ም ወደ ቀድሞ መምህራቸው የኔታ አፈወርቅ ዘንድ ወደ አዲስ ዓለም ማርያም በመሄድ የቅኔ ትምህርታቸውን እያስፋፉ ተማሪዎችንም ያስቀፅሉ ነበር የኔታ ወልደ ሚካኤል በትምህርት ቤት በነበሩበት ጊዜያት ሁሉ ከስራቸው ያሉ ተማሪዎችን በማስቀፀል ይታወቃሉ በ1944ዓ/ም በርዕሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ማርያም ከመምራቸው የኔታ አፈወርቅ በቅኔ መምህርነት ተመርቀው እዚሁ ደብር በቅኔ መምህርነት እንዲያስተምሩ የተቀጠሩ ሲሆን ማስተማር እንጂ ደመወዝ አልወስድም በማለት አንድ ዓመት ቅኔ አስተምረዋል በ1946ዓ/ም ተስፋሚካኤል የሚባለው ወንድማቸው መጥቶ ከአዲስ አለም ወደ አስመራ የወሰዳቸው ሲሆን እዛም የተለያዩ አድባራት እያገለገሉ ቆይተው በ1947ዓ/ም ወደ መቀሌ በመምጣት መቀሌ ኪዳነምህረት እና መድኃኔዓለም የኔታ ሃይለስላሴ ከሚባሉት እውቅ መምህር በድጋሚ ፀዋትወ ዜማ እየቀፀሉ ቅኔ ማስተማር ጀመሩ በወቅቱም የዜማ መምህራቸው የኔታ ኃይለስላሴም የኔታ ወልደ ሚካኤል ዘንድ ቅኔ ይማሩ ነበር መስከረም 1950ዓ/ም የቅኔ መምህራን ተመርጠው ለፈተና ቅድስት ሥላሴ ተፈትነው የኔታ ወልደሚካኤል ፈተናውን አልፈው አንድ ዓመት የመምህርነት ስልጠና በመውሰድ በዕጣ ጋሞጎፋ ተመድበው ግብረ ገብ እና አማረኛ መምህር ሆነው 3ዓመት አስተምረዋል በ1944ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ በመዛወር አምሃደስታ ት/ቤት ተመድበው እስከ 1959ዓ/ም ለስድስት ዐማታት አምሃ ደስታ ትምህርት ቤት ሲያስተምሩ ቆይተው በ1960ዓ/ም ቀለመወርቅ ት/ቤት ተመድበው የመጡ ሲሆን ከ1960ዓ/ም ጀምሮ ቀጨኔ ደብረሰላም መድኃኔዓለም እና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ያን በማህሌት በመቆም እና ቅኔ በመቀኘት አገልግሎት የጀመሩ ሲሆን በ1966ድጋሚ ወደ አምሃ ደስታ ት/ቤት በመመለስ እስከ 1981ዓ/ም በማስተማር በዛን ጊዜ በነበረው ህግ መሰረት በ55ዓመታቸው ጡረታቸውን አስከብረዋል በ1987/ዓ/ምህረትከጡረታ በኋላ በሚያውቋቸው መምህራን ጠቋሚነት ምስካየህዙናን ገዳም ዘመናዊ ት/ቤቱ ውስጥ ለአንድ ዓመት ከሰባት ወር ግዕዝ አስተምረዋል በተያያዥም ቀን ቀን በገዳሙ የተመደቡ የቅኔ መምህር ስለነበሩ በበጎ ፈቃደኝነት ማታ ማታ ደግሞ የኔታ ወልደሚካኤል መነኮሳቱን ግስ ያስተምሩ ነበር ከ1989ዓ/ም ዘመናዊ ትምህርት ማስተማሩን በማቆም ቀጨኔ ደብረሰላም መድኃኔዓለም እና ደብረትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክን ልክ እንደ አንድ መደበኛ ሰራተኛ በእለተ ሰንበት በወርሃዊ በዓላት እና በዓበይት በዓላት በገረገራው ውስጥ በማደር በህመም ቤት እስከዋሉበት ጊዜ ድረስ መድኃኔዓለምን በቅንነት ያገለገሉ አባት ነበሩ የአገልግሎት ዋጋቸውን የሚከፍለው ያገለገሉት አምላክ ቢሆንም በፍኖተ ህይወት ሰንበት ት/ቤት እና ማህበረ አሃው የአጥቢያው ማህበር በሚዘጋጀው "ዝክረ አበው" በተሰኘው አባቶች በህይወተ ስጋ ባሉበት ወቅት ፀሎታቸው እና ምርቃታቸውን እንዲሁም በአገልግሎት አርአያ በመሆናቸው ለመታሰቢያ በሚዘጋጀው መርሐ ግብር የሙካሽ ካባ ተበርክቶላቸዋል የኔታ ወልደሚካኤል በአገልግሎት በቆዩባቸው ዘመናት ምንም ድካም የማይታይባቸው ብርቱ አባት ነበሩ የኔታ ወልደሚካኤል ባለትዳር እና የ3ሴት ልጆች አባት ነበሩ ነፍሳቸውን ከደጋግ አባቶች ዘንድ ያሳርፍልን ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመድም መፅናናትን ያድልልን ለቤተክርስቲያንም እንዲህ ያሉ መምህራንን መድኃኔዓለም ይተካልን።

#ዜና_እረፍት በደብራችን ቀጨኔ ደብረሰላም መድኃኔዓለምቤተ ክርስቲያን ሲያገለግሉ የነበሩት መምህር ወልደሚካኤል በዛሬው እለት ነሐሴ 08/2016 ዓ.ም አርፈዋል። "እግዚኦ አዕርፍ ነፍሰ መምህርነ ወል
#ዜና_እረፍት በደብራችን ቀጨኔ ደብረሰላም መድኃኔዓለምቤተ ክርስቲያን ሲያገለግሉ የነበሩት መምህር ወልደሚካኤል በዛሬው እለት ነሐሴ 08/2016 ዓ.ም አርፈዋል።     "እግዚኦ አዕርፍ ነፍሰ መምህርነ ወልደሚካኤል"

ለአባ ሕርያቆስ ፤ለቅዱስ ኤፍሬም ፤ለቅዱስ ያሬድ ፤ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ ጾሙን ጾመ ሥርየት ፤ጾመ መድኃኒት ያድርግልን አሜን ፡፡/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: ꔰ #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/Finotehiwott http://tiktok.com/@finotehiwot .YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w www.finotehiwotsundayschool.com ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት . Telegram (https://t.me/finotehiwot1927)

#ነሐሴ ሰባት ጽንሰታ #ለማርያም_ድንግል #ጴጥርቃ እና #ቴክታ የሚባሉ ሰዎች በኢየሩሳሌም በአንድነት ተጋብተው ይኖሩ ነበር፡፡ እነዚህም በእግዚአብሔር የሚያምኑ የተወደዱ ጻድቃን ደግ ሰዎች ነበሩ፡፡ እነዚህም ሰዎች በእግዚአብሔርም በሰውም ዘንድ የተመሰከረለላቸው ባለጸጎች ነበሩ:: ነገር ግን የሚወርሳቸው ልጅ አልነበራቸውምና መካን ነበሩ፡፡ ✣ ✣ አንድ ቀን ጴጥርቃም ቴክታን እህቴ ሆይ ይህን ሁሉ የሰበሰብነውን ገንዘባችንን ምን እናደርገዋለን ልጅ የለን የሚወርሰን ፤ አንቺም መካን ነሽ እኔም ካንቺ በቀር ሌላ ሴት አላውቅም አላት፡፡ እርሷም ወንድሜ ሆይ አምላከ እስራኤል ለእኔ ልጅ ቢነሳኝ አንተም እንደኔው ሆነህ ትቀራለህን? ከሌላ ደርሰህ ውለድ እንጂ ብላ ብታሰናብተው እንደዚህ ያለ ነገር እንኳንስ ላደርገው በልቦናዬ እንዳላስበው አምላከ እስራኤል ያውቅብኛል አላት እሷም አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም ትላንትና ማታ በህልሜ #ነጭ ጥጃ ከማህጸኔ ስትወጣ ያችም ነጭ ጥጃ ሌላ #ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲሁ እስከ #7ት ትውልድ ሲዋለድ ሰባተኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ #ጨረቃዋም #ፀሐይን ስትወልድ አየሁ አለችው:: ✣ ✣ ✣ እርሱም በጠዋት ከህልም ፈቺ ዘንድ ሂዶ የነገረችውን ሁሉ ነገረው፡፡ ያም ህልም ፈቺ እግዚአብሔር በምህረቱ አይቷችኋል በሳህሉ መግቧችኋል 7 አንስት ጥጆች መውለዳቹ 7 ሴቶች ልጆች እና የልጅ ልጆች ትወልዳላቹ ከቤታቹ ሰባተኛይቱ #ጨረቃ መውለዷ ከሰው የበለጠች ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁ #የፀሐይ ነገር ግን አልታወቀኝም አለው፡፡ እርሱም የነገረውን ሁሉ ሄዶ ነገራት እርሷም እንጃ አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን ማን ያውቃል ብላ ዝም አለች:፡ ✣ ✣ ✣ ከዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች፡፡ ስሟንም ሄሜን ብለው አወጡላት፤ ሄሜንም አድጋ ለአካለ መጠን ስደርስ አጋብተዋት ሴት ልጅ ወለደች በስምንተኛ ቀኗም ዴርዲ ብለው ስም አወጡላት ፤ #ዴርዲም አድጋ እንዲሁ ሴት ወለደች እና #ቶና አለቻት፤ቶናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሲካር አለቻት #ሲካርም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሴትና አለቻት፤ #ሴትናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ# ሄርሜላ አለቻት ፤ ሄርሜላም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ንጽህት ቅድስት ክብርት የምትሆን እመቤታችንን የምትወልደችውን #ሃናን ወለደች:: ከጴጥርቃና ከቴክታ የተወለዱ 67 ወንዶች ልጆች አሉ የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ትውልድ ለመቁጠር ትንቢት አልተነገረላቸውም ሱባኤ አልተቆጠረላቸውምና አልተፃፈም፡፡ ይህቺም ሃና በስርዓት በቅጣት አደገች፡፡ ለአእምሮ ስትበቃ አካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ መንግስት ወገን ከነቅዱስ #ዳዊት ወገን ከሆነው ከቅዱስ #እያቄም ጋር አጋቧት:: ✣ ✣ ✣ እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄም እና ሃና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ፤ ከእለታት አንድ ቀን ወደ ቤተ እግዚአብሔር ሂደው ሲፀልዩ ሲያዝኑ ዋሉ፡፡ ሃዘናቸው እንዴትስ ነው ቢሉ ፡- ኢያቄም:-"አቤቱ ጌታዬ ያባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ አትጣለኝ አትናቀኝ ፀሎቴን ስማኝ ፈቃዴን ፈጽምልኝ፤ ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የሚሆን የተባረከ ወንድ ልጅ ስጠኝ" ብሎ ሲለምን ዋለ:፡ ሃናም በበኩሏ "አቤቱ ጌታዬ የአባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ፤ ስማኝ ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የምትሆነኝ የተባረከች ሴት ልጅ የማህፀኔን ፍሬ ስጠኝ" ብላ ስትለምን ዋለች፡፡ እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት አይታ አቤቱ ጌታዬ ለዚች ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ ብላ ምርር ብላ አለቀሰች፡፡ እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲፀልዩ ውለው ከዘካርያስ ከሊቀ ካህናቱ ሄደው አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ማይ(ውሃ) ቀድታ መሶብ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን ብለው ስዕለት ገቡ:: ዘካርያስም እግዚአብሔር ጸሎታችሁን ይስማችሁ ስእለታችሁን ይቀበልላችሁ ጻህቀ ልቦናችሁን ይፈጽምላችሁ ብሎ አሳረገላቸው። ✣ ✣ ✣ ከዚያም በኋላ ቅድስት ሃና እና ቅዱስ እያቄም ዕለቱን ራእይ አይተው ነገር አግኝተው አደሩ፡፡ ራእዩም እንዴት ነው ቢሉ ኢያቄም 7ቱሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ አላት ፤ ወፍ የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባህሪው ነው ፤ ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ ማለቱ ፤ የኢያቄምን ( የሰውን) ባህርይ ባህርይ እንዳደረገው እወቅ ሲል ነው ፤ 7ቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ልዩ ባህርይው፤ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩና መንግስቱ ናቸው፡፡ ✣ ✣ ✣ ሃናም እኔም አየሁ አለችው፤ ምን አየሽ ቢላት፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማሕጸኔ ስትተኛ አየሁ አለችው:: ርግብ የተባለች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት:ነጭነቱ ንጽህናዋ : ቅድስናዋ ድንግልናዋ ነው፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማህጸኔ ስትተኛ አየሁ ማለቷ ብስራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን መጽነሷን ነው፡፡ ይህንኑም ራእይ ያዩት ሐምሌ 30 ዕለት ነው:: ✣ ✣ ✣ እነሱም እንዲ ያለ ራዕይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም፤ ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን ብለው አዳምንና ሄዋንን ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሏት ብሎ ያበሰረ አምላክ ለኛስ ይልክልን የለምን? ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ 7ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ፡፡ ነሐሴ ሰባት በሰባተኛው ቀን ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላቹህ ብሎ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ለሃና ነገራት በፈቃደ እግዚአብሔር በብስራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እሁድ ዕለት #ነሐሴ_7 ቀን ተፀነሰች፡: ✣ ✣ ✣ እመቤታችን ከተፀነሰች በኋላ አይሁድ ቀንተው ተነሱባቸው ቅናቱ እንዴት ነው ቢሉ፡፡ ሳሚናስ የሚባል የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ካጎቱ ቤት ሄዶ ሞተ እነርሱም እንቀብራለን ብለው ባልጋ ይዘው ሲሄዱ ከመንገድ አሳረፉት ፤ የሃናም የአጎቷ ልጅ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ ቆዩአት ፤ እርሷም አብራ እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብድግ ብሎ ተነስቶ ስብሃት ለኪ ማርያም እሙ ለፀሃየ ጽድቅ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላዲቱ ለመንፈስ ቅዱስ ጽርሃ ቤቱ ተፈስሂ ደስ ይበልሽ ብሎ ሰገደላት፤አይሁድ ከዛ ነበሩና ምነው ሳሚናስ ምን አየህ? ምን ትላለህ? ቢሉት ከዚች ከሃና ማህፀን የምትወለደው ሕፃን ሰማይ ምድርን እመቅ አየርን የፈጠረ አምላክን ትወልዳለች እያሉ መላእክት ሁሉ ሲያመሰግኑአት ሰማኋቸው እኔንም ያነሳችኝ የፈወሰችኝ ያዳነችኝ እርሷ ናት አላቸው ፤ በል ተወው ሰማንህ ብለው ቅናት ጀመሩ:: እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም በተፀነሰች በ9 ወር ከአምስት ቀን የግንቦት መባቻ ዕለት ግንቦት 1 ተወለደች::

በአጠቃላይ #የእመቤታችን ለሐዋርያት በተለያዩ ጊዜያት መታየት፣ የሥጋዋና የነፍሷ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ፍልሰት ሲባል ከዚህ የተነሣ #የነሐሴ ጾም በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐት መሠረት ሐዋርያት ያገኙትን በረከት ለማግኘት ጾመ ፍልሰታን እንጾማለን። /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: ꔰ #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot .YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w www.finotehiwotsundayschool.com ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት . Telegram (https://t.me/finotehiwot1927)