ar
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

الذهاب إلى القناة على Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የጥበብ ማዕድ

تُعد قناة የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 16 230 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 245 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 081 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 16 230 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 06 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 625، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -24، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 2.69‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 2.08‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 437 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 337 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 11.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 07 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

16 230
المشتركون
-2424 ساعات
+2177 أيام
+62530 أيام
أرشيف المشاركات
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሰራት ቅዱስ መላዕክ ማን ይባላል?

መስቀል ማለት ምን ማለት ነው ?

ስጠው አንድ ምክንያት፡ ስተህ ከበጎነት ፡ እጅህ ካ'ጥፊ ውሎ፣ ወዳጄ ነው ያልከው፣ የዘመናት ተክል፡ ዳግም ሕይወት አይሰጥ ፡ ከስሩ ተነቅሎ። የዘመናት መልካምነት የአንድ ቀን ስህተትን ለመግዛት ለምን አቅም አጣ?! አቡ(አላዛር ቴዎድሮስ)

አንዳንዴ ለሔደ ሰው ፡ ሰው እንተካለን ፡ እንጂ ፤ የሔደውን ሰው አንተካውም!!!

ማስተዋልን ያጣህለት መውደቂያህን ታፋጥናለህ ልክ ወጥመድ ውስጥ እንደምትገባ አይጥ!!!

ካንተ የሆነው መልካም ነው! ተመስገን! 🙏 🥰🥰

💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕 [┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ [┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ 🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇 🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧

መስቀል ማለት ምን ማለት ነው ?

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሰራት ቅዱስ መላዕክ ማን ይባላል?

መስቀል ማለት ምን ማለት ነው ?

መስቀል ማለት ምን ማለት ነው ?

💁 " ፍልሰታ " ማለት ምን ማለት ነው ❓

ራሱን ያስከበረ ሰው ከፊቱ ማንም አይደፍርም ፤ ከጀርባው ያሙታል እንጂ!!!

ደስታ የት ነው ያለችው? ደስተኛ ሕይወት መኖር የብዙ ሰው ፍላጎት ነው ሰው ከሁሉም ነገር በላይ ለደስታ ሲል እውቀቱን ጉልበቱን ገንዘቡን ያወጣል በዚሕ መልኩ ደስታውን ሲፈልግ ብዙ ሰው አያገኘውም የደስታ መገኛ ወዴት ነው?  ደስታን ሰው በተለያየ ቦታ እየዞረ ይፈልጋታል አንዳንዱ መንፈሳዊ ቦታዎች በመሔድ ይፈልጋታል አንዳንዱ በእውቀት መገኛ ቦታ በትምሕርት ቤት ይፈልጋታል አንዳንዱ በሥራ ቦታ በሥራ ውስጥ ይፈልጋታል አንዳንዱ ደግሞ በመዝናኛ ቦታዎች ዘና እያለ ይፈልጋታል አንዳንዱ ደግሞ በመጠጥ ቤት እየጠጣ መጠጥ ውስጥ ይፈልጋታል አንዳንዱ በስፖርት ቤት በስፖርት ውስጥ አንዳንዱ በማሕበራዊ ግንኙነቶች ውስጥ አንዳንዱ በእንቅልፍ አንዳንዱ በሀብትና ንብረት ውስጥ ይፈልጋታል ግን በሁሉም ውስጥ ደስታ አትገኝም ደስታ ለአንተ ታስፈልግሀለች እንጂ አንተ ለእርሷ አታስፈልጋትም ደስተኛ መሆን የሁሉም ፍላጎት ነው ሰው ለረጅም ዘመን ያካበተውን ሀብት ለደስታ ለማውጣት አይግደረደርም ምክንያቱም ሁሉም ለደስታ ነውና ታዲያ እቺ በሰው የምትወደድ የምትፈለግ ደስታ መገኛዎ ወዴት ነው?  መገኛዎማ ራስሕ ውስጥ ነው አንተ በውጪ ትፈልጋታለሕ እንጂ ደስታ ያለቺው ውስጥሕ ነው ዎጋዎም ርካሽ ነው ደሀውም ሀብታሙም እኩል ገንዘብ ሊያደርጓት ይችላሉ ። ደስታ ውስጥሕም ብትሆን የአንተ አያያዝና አጠቃቀምሕ ነው ሕይወት የሚዘራባት ካለበለዚያ በውስጥሕም ብትኖር ትገድላታለሕ ደስታን የምትፈልጋት ከሆኔ እኔ ልጠቁምሕ በሕሊናሕ ውስጥ ወዳለው እውነት ግባ በዛም ውስጥ ደስታሕን ታገኘዎለሕ እውነትን ተቀበል በእውነት ኑር እውነተኛ እርዳታ አድርግ በእውነት የኑሮ ደረጃሕን አምነሕ ተቀበል ገንዘብ ስትሰበስብ ሳይሆን ገንዘብን ስትሰጥ ነው ደስታ ምታገኘው  በእውነት ፍረድ በእውነት ምከር በእውነት ሥራ በእውነት አግባ በእውነት ጸልይ በእውነት አግኝ በእውነት ተማር ለእውነት ተጠቀምበት በእውነት አስተዳድር በእውነት ተመራ በእውነት ውደድ በእውነት ተወደድ በእውነት ዝቅ ዝቅ በል በእውነት ድከም በእውነት አግኝ ለእውነት ኑር ለእውነት ሙት እዛ ውስጥ ነው ደስታ የምትገኘው ።         🥰🥰መልካም ቀን ይሁንላችሁ🥰🥰

+ ወደ ኖኅ መርከብ ለመጨረሻ ጊዜ የገባችው እንስሳ + የኖኅ መርከብ ጉዳይ በጣም አስገራሚ ከሚሆኑብኝ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች አንዱ ነው:: በዓለማችን አሁን ያሉ እንስሳት ሁሉ "ከነ ባለቤትዎ" እንዲገኙልን እንደሚባልበት ሰርግ ጥንድ ጥንድ ሆነው የገቡባት ትልቅ መርከብ ታሪክ : ዳግም ለሰው ልጆች ወላጆች ለመሆን የተመረጡ አራት ወንዶችና አራት ሴቶች ብቻ የተሳፈሩባት ትልቅ መርከብ ሁኔታ ትኩር ብሎ ላየው አስገራሚ እውነቶችን ያዘለ ነው:: ከሁሉም በላይ ግን መርከቢቱ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ መሆንዋ ብዙ ነገር እንድናስብ ያግዘናል:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ወደ ኖኅ መርከብ ተኩላ ገብቶ ሲወጣም ተኩላ ሆኖ ይወጣል:: ወደ ቤተክርስቲያን ግን ተኩላ ሆነው ገብተው በግ ሆነው የወጡ ብዙዎች ናቸው" ብሎአል:: እውነትም ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን መለወጥ የምትችል መርከብ ናት:: ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደ ጅብ ሆዳም ሆነው ገብተው ጾመኞች ሆነው የወጡ አሉ:: እንደ የሌሊት ወፍ በቀን መኖር አቅቶአቸው ሌሊቱን የልባቸው ዓይን ታውሮ በኃጢአት ጨለማ ሲደናበሩ የኖሩ ሰዎች ወደ መርከቢቱ ገብተው እንደ ንስር አርቀው አጥርተው ቀኑን የሚያዩ ሆነዋል:: ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን የምትለውጥ መርከብ ናት:: ውኃ ወደ እርስዋ ሲገባ ጠበል ይሆናል:: አፈር ወደ እርስዋ ሲገባ እምነት (እመት) ይሆናል:: ዘይት ወደ እርስዋ ሲገባ ቅዱስ ቅባት ይሆናል:: ኅብስትና ወይን ወደ እርስዋ ሲገባ ወደ ቅዱስ ቁርባን ይለወጣል:: ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ያልተለወጠ ሰው ግን ሲገባም ጅብ ሲወጣም ጅብ ሆኖአል:: ኖኅ ከመርከብ መልእክት ልኮት የቀረው የቁራ ነገርስ? ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው ስንቶች በዚያው ቀርተዋል? ለዓለም ጨው እንዲሆኑ ተልከው በዚያው ሟሙተው የቀሩ ስንት አሉ:: ርግብ ግን ማረፊያ ስታጣ ተመልሳ ነበር:: ከመርከቢቱ የራቅን ሁላችን "ልባችን በእግዚአብሔር እስካላረፈ ድረስ ዕረፍት የለውም" እንዳለ ሊቁ ወደ መርከቢቱ ፈጥነን መመለስ አለብን:: ሰሞኑን ደግሞ አንድ ጥያቄ በአእምሮዬ ተመላለሰብኝ:: "ወደ ኖኅ መርከብ ለመጨረሻ ጊዜ የገባው እንስሳ ማን ሊሆን ይችላል?" የሚል:: ይህን ጥያቄ በግልም በጉባኤ ላይም ሰዎችን ጠይቄ ነበር:: መቼም ለዚህ ጥቅስ አያስፈልገውም:: ኖኅ ቆሞ እንስሳቱ እስኪገቡ ድረስ እንደጠበቀና ማንንም እንስሳ ጥሎ እንዳልገባ የታወቀ ነው:: በዚህ ምክንያት እንስሳቱ ወደ መርከቢቱ የሚገቡት እንደደረሱበት ቅደም ተከተል ነው:: ክንፍ ያላቸው በርረው ቀድመው ይገባሉ:: እንደ ጥንቸል እንደ ካንጋሮ እንደ ሚዳቁዋ ያሉትም እየዘለሉ ፈጥነው ይገባሉ:: ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነፍሳቸውን ለማዳን ፈጥነው በርረው የገቡ እንደ ሚዳቋ ዘልለው የደረሱ ብርቱዎች አሉ:: እንደ ፒኮክ ያሉ ባለ ውብ ክንፎች : እንደ ቀጭኔ ያሉ ባለ ረዥም አንገቶች እንደ ጃርት ያሉ ሌላው ላይ የሚሰኩት እሾኽ የለበሱ እንስሳት ወደ መርከብዋ ገብተዋል:: በቤተክርስቲያን እንደ ፒኮክ አምሮ መታየት መዘባነን የሚወዱ ለታይታ የሚገዙ ብዙዎች ገብተዋል:: እንደ ቀጭኔ አንገታቸውን ከፍ አድርገው ሰውን ቁልቁል የሚመለከቱና "አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የዕብራውያን ሴቶች" ዓይነት ሕይወት ያላቸውም ገብተዋል:: እንደ ጃርት በክፉ ንግግር የሰው ልብ ላይ የሚሰኩት ጥላቻ የተላበሱ ሰዎችም ገብተዋል:: የኖኅ መርከብ ያልያዘችው እንስሳ እንደሌለ ቤተ ክርስቲያንም ያልተሸከመችው ዓይነት ሰው የለም:: ወደ ጥያቄው ስመለስ በእኔ ግምት ወደ መርከቡ በጣም ዘግይታ የገባችው ኤሊ ነበረች:: በላይዋ ድንጋይ የተጫናት እጅግ ቀርፋፋዋ ኤሊን የማይቀድም እንስሳ መቼም አይኖርም:: ምንም ብትዘገይም ኖኅ እስከመጨረሻው ጠብቆ አስገብቶ ለዘር አትርፎአታል::  የኤሊ ዘሮችም "ኖኅ ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ዳይኖሰር በጠፋን ነበር" ብለው ኖኅን ማመስገናቸው አይቀርም:: እግዚአብሔር ምንም ብትዘገይ ኤሊ ሳትገባ መርከቡን አልዘጋውም:: የኤሊ በመርከቡ መትረፍ በቤተ ክርስቲያን ልንተርፍ ተስፋ ለምናደርግ ለእኛ ትልቅ መጽናኛችን ነው:: ወዳጄ ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመምጣት እንደ ወፍ ትበርራለህ? እንደ ሚዳቋ ትዘልላለህ? ወይንስ እንደ ኤሊ ትጎተታለህ?  እግሮችህ ለመንፈሳዊ ነገር ሲሆን አቅም እያጡ አልተቸገርህም? ልብህ ቢፈልግም እንደ ኤሊዋ የተጫነህ የኃጢአት ድንጋይ አላንቀሳቅስ ብሎህ አልዘገየህም? እንዲህ ከሆነ አትጨነቅ መርከብዋ ቤተ ክርስቲያን አንተን ሳትይዝ ጥላህ ወዴትም አትሔድም:: ጉዞህን እስካላቆምህ ድረስ ትጠብቅሃለች:: እየተጎተትህም እየተሳብህም ቢሆን አንተ ብቻ ወደ ደጁ ገስግስ:: አንተ ብቻ መንገድ ጀምር እንጂ ፈጣሪ በሩን የሚዘጋው አንተ እስክትገባ ጠብቆ ነው:: ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር እንዲህ ብለህ ለምነው :- "ብበድልህም እንኳን አሁንም በርህን እያንኳኳሁ ነው:: እየተጎተትሁም ቢሆን አሁንም የምጉዋዘው ወደ አንተ ለመምጣት ነው" ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ! በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

አንተ ሰው! ቊጥር የሌላቸው ክፋቶች ቢኖሩብህም እንኳ በጎ ምግባር በልጅህ ይኖር ዘንድ በማድረግ አካክሰው፡፡ ለክርስቶስ የሚኾን ተሽቀዳዳሚ (ሯጭ) አሳድግ! ወዳጄ ሆይ! እንደዚህ ብዬ ስነግርህ አትፍራ፤ አትሸበርም፡፡ ልጅህ እንዳያገባ አድርገው አላልኩህም፡፡ ወደ ገዳም ወስደህ እንድታመነኩሰው ወይም የብሕትውና ሕይወትን እንዲመራ አድርገው አላልኩህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ይህን አይደለም፡፡ ልጅህ ቢመነኩስ እወድ ነበር፡፡ ብዙዎች ወደዚህ ሕይወት እንዲገቡ የዘወትር ጸሎቴ ነውና፡፡ ነገር ግን የምንኵስና ሕይወት [ሳይጠሩ ከገቡበት] ከባድ ሸክም ስለ ኾነ ሰዎች መነኰሳት ካልኾኑ ብዬ ግድ አልልም፡፡ ለአንተም እንደዚህ በግድ አመንኩሰው አልልህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ለክርስቶስ የሚኾን ተሸቀዳዳሚ አሳድግ ነው፡፡ በዚህ ዓለም አግብቶ፣ ልጆችንም ወልዶ የሚኖር ቢኾንም እንኳን ገና ከሕፃንነቱ አንሥቶ ሰውን የሚያከብር እንዲኾን አድርገህ አሳድገው ነው፡፡ ገና ጨቅላ እያለ በጎ በጎ ትእዛዛት በሕሊናው ጓዳ በልቡናው ሰሌዳ ላይ ከተቀረጸ፥ በሰም እንደ ታተመ ጸንቶ ይኖራል እንጂ ሲያድግ እነዚህን ትእዛዛት ሊያጠፋበትና ሊፍቅበት የሚችል ማንም አይኖርምና፡፡ ልጅህ አሁን ያለበት ዕድሜ ደግሞ በሚያየውና በሚነገረው በሌላም ነገር ኹሉ የሚንቀጠቀጥበት፣ የሚፈራበትና የሚደነግጥበት ዕድሜ ነው፡፡ ስለዚህ ልክ እንዳልደረቀ ሰም እንደምትፈልገው አድርገህ ቅረጸው፡፡ እንደዚህ አድርገህ ስታበቃ፥ መልካም ልጅ ቢኖርህ የመጀመሪያው ተጠቃሚ የምትኾነው አንተው ራስህ ነህ፡፡ እግዚአብሔር የሚጠቀመው ከአንተ በኋላ ነው፡፡ ስለዚህ የምትደክመው ለሌላ አካል ሳይኾን ለራስህ ነው፡፡ "ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው" መጽሐፍ በ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ ገፅ 86