HUHCSF ✞
الذهاب إلى القناة على Telegram
Haramaya University, Harar Health Campus Christian Students Fellowship Worship Center: @ Me'erab Harar MKC Meet Leaders: @Gutewr
إظهار المزيد291
المشتركون
+124 ساعات
+17 أيام
+130 أيام
أرشيف المشاركات
291
🧎♀➡️🧎➡️የፀሎት ጊዜ
👉እግዚአብሔር አምላክ ና አባታችን በምህረትህ ደግፈህ ለዛሬ ስላደረስከን እናመሰግናለን፤ስምህ የተባረከ ይሁን።🙏🙏
“በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል። እግዚአብሔርን፦ አንተ መታመኛዬ ነህ እለዋለሁ፤ አምላኬና መሸሸጊያዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ።”
መዝሙር 91፥2
እግዚአብሔር አንተ መጠጊያችን መታመኛችን ነህ ክብር ለአንተ ይሁን፤ ተመስገን። ከብዙ ነገር አምልጠን የተሸሸግንብህ መሸሸጊያ ማረፋያችን ነህ ተመስገን።🙏🙏
¹ አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ፤ እንደ ምሕረትህም ብዛት መተላለፌን ደምስስ።
² ከበደሌ ፈጽሞ እጠበኝ፥ ከኃጢአቴም አንጻኝ፤
³ እኔ መተላለፌን አውቃለሁና፥ ኃጢአቴም ሁልጊዜ በፊቴ ነውና።
⁴ አንተን ብቻ በደልሁ፥ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ፥ በነገርህም ትጸድቅ ዘንድ በፍርድህም ንጹሕ ትሆን ዘንድ።…
⁷ በሂሶጵ እርጨኝ፥ እነጻማለሁ፤ እጠበኝ፥ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።
መዝሙር 51
ጌታ እግዚአብሔር በማወቅ ሆነ ባለማወቅ የበደልንህን ኃጢያት በደላችንን ይቅር በለን፤ ዛሬም ከኃጢአት ሁሉ በሚያነፃዉ በልጅ ደም አጥበህ አንፃን። እኛም የበደሉንን ይቅር እንድንል እርዳን።🙏🙏
¹⁵ እንዲህም አላቸው፦ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።
¹⁶ ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።
ማርቆስ 16
የዘላለም አምላክ እግዚአብሔር በቀረው ዘመናችን ወንጌል የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን ለአለም መናገር እንድንችል እርዳን፤ እኛ የቀመስነውን ፍቅር እኛ ነፃ የወጣንበትን ይህን እውነት ለሌሎች ማካፈል እንድንችል ፀጋህን አብዛልን፤
ይህ የእረፋት ጊዜ ጌታ ሆይ በእኛ በኩል አንዲት ነፋስ የምትድንበት ይሁንልን፤
ላላመኑት የሚራራ ልብ ፍጠርልን፤ በዚህ ማደግ ይሁንልን። 🙏🙏
ስለ ሁሉ ተመስገን እንወድሃለን። 🙏🙏
291
የቀደሙ አባቶች ላንተ የጨከኑ
መከራ ስደትን ሁሉ የተቀበሉ
ለስምህ መሞትን እንደ ክብር ቆጥረው
ህይወታቸው አለፈ ፍቅራቸውን ገልጠው
አዝ:-ምን ያህል እወድህ ይሆን ጌታዬ
ከአፌ ባለፈ በህይወት ተግባሬ
እንዴት ይሆን ክርስትናዬ
አንተን ምወድበት መጠኑ የፍቅሬ
ከአንበሳ ከነብር ፊትለፊት ተፋጠው
መች ስምህን ካዱ አናውቀውም ብለው
አንገታቸውን ሰጥተው ጥቂት ሳይበገሩ
በመከራ ስቃይ እስከሞት ታገሉ
ስለስምህ ትተው የናሩትን ሁሉ
የሰማዩን አክሊል ክብር እያሰቡ
ዘመናቸው ሳያልፍ ምድርን እያዩ
የናፈቁት ሰማይ ሀገራቸው ገቡ
አዝ:-ምን ያህል እወድህ ይሆን ጌታዬ
ከአፌ ባለፈ በህይወት ተግባሬ
እንዴት ይሆን ክርስትናዬ
አንተን ምወድበት መጠኑ የፍቅሬ
የመስቀል ፍቅርህን መውደድህን አስበው
መጠማት መታረዝ ሁሉንም ታግሰው
ስለ አንዷ ህይወታቸው ከቶ ሳይሳሱላት
ፍቅራቸውን ገለጡ ተቃጥለው በእሳት
የኔስ እንዴት ይሆን አንተን የመውደዴ
እስከሞት መስዕዋት ልሆን ዝግጅቴ
ለአንተ መኖር እንጂ መሞት ካልቻልኩማ
የስም ክርስትያን ነኝ መቼ ወድህና
አዝ:-ምን ያህል እወድህ ይሆን ጌታዬ
ከአፌ ባለፈ በህይወት ተግባሬ
እንዴት ይሆን ክርስትናዬ
አንተን ምወድበት መጠኑ የፍቅሬ
291
ሰላም ለእናንተ የተወደዳችሁ የህብረታችን አባላት😊
የካታኮምብ ሰማዕታት የተሰኘውን የመፅሀፍ ትረካ በህብረቱ የቴሌግራም "Group" እና "channel" ለስምንት ሳምንታት ማክሰኞ እና ሐሙስ እያስተላለፍን የቆየን መሆኑ ይታወቃል፤ እነሆ እግዚአብሄር ረድቶን ዛሬ የመጨረሻውን ክፍል የምንለቅ ይሆናል። መፅሐፋን ለማንበብ የምትፈልጉ ሁላችሁ ደግሞ ዛሬ ከመጨረሻው ክፍል ጋር አያይዘን መፅሐፉን የምንለቅ ስለሚሆን አንብባችሁ ተባረኩበት እንላለን።
📖 መዝሙር 65፥4📖
“አንተ የመረጥኸው በአደባባዮችህም ለማደር የተቀበልኸው ምስጉን ነው፤ ከቤትህ በረከት እንጠግባለን።”
291
ሰላም ይብዛላችሁ! የተወደዳችሁ
ከሃዋሳ ወንጌልን በሃረር ለሚኖሩ ሰዎች ለመንገር አንድ የወንጌል ስርጭት ቡድን በዚህ ሳምንት እዚህ ሃረር ይገኛል።
ነገ(ሃሙስ) እና አርብ ጥዋት እና ፣ከሰአት በሃረር ጎዳናዎች ላይ በመዘዋወር ወንጌልን ለመስበክ ተዘጋጅተዋል ። እኛም ከ እነርሱ ጋር ይህንን የከበረ አገልግሎት ለመካፈል ጥሪ ደርሶናል። ቅዳሜ ደግሞ በሃረር ማረሚያ ቤት ይህንን አገልግሎት ለማድረግ ታስቦአል።
አብሮ የጌታን ቃል ለህዝብ መናገር፣ ቦታዎችን ማሳየት ሌላም ሌላም ብዙ ቦታዎች ላይ የኛን መገኘት ያስፈልጋል ።ስለዚህ ከነገ ጥዋት ጀምሮ በዚህ አገልግሎት ተሳታፊ በመሆን ፣ ከወንድሞቻችን ጋር አብረን የጌታን ስራ እንድንሰራ ጥሪን ያቀርባሉ ።
ነገ 2:30 GC ፕሮግራሙ ይጀምራል
“ሁልጊዜ በጸሎቴ ሁሉ ስለ እናንተ ሁሉ በደስታ እየጸለይሁ፥ ከፊተኛው ቀን እስከ ዛሬ ድረስ #ወንጌልን_በመስበክ_አብራችሁ_ስለ_ሠራችሁ፥ ባሰብኋችሁ ጊዜ ሁሉ አምላኬን አመሰግናለሁ።”
— ፊልጵስዩስ 1፥3-5
መሳተፍ የምትፈልጉ በዚህ ስልክ0973980391 inbox or text አድርጉ
እግዚአብሔር ይባርካችሁ!!
291
ሰላም ለእናንተ የተወደዳችሁ የህብረታችን አባላት😊
የካታኮምብ ሰማዕታት የተሰኘውን የመፀሀፍ ትረካ በህብረቱ የቴሌግራም "Group" እና "channel" እያስተላለፍን መሆኑ ይታወቃል፤ ሆኖም ሰዓት ስላላከበርን የዛሬውንም የትረካ ክፍል አርፍደን ስለለቀቅን ይቅርታ እንጠይቃለን። እንደወደዳችሁት እና እየተባረካችሁበት እንደሆነ እምነታችን ነው።
📖 መዝሙር 65፥4📖
“አንተ የመረጥኸው በአደባባዮችህም ለማደር የተቀበልኸው ምስጉን ነው፤ ከቤትህ በረከት እንጠግባለን።”
291
የዛሬው የህብረት ጊዜያችን ይሄን ይመስል ነበር።
በኛ መካከል የተገኘው መንፈስ ቅዱስ ይባረክ🙏
ቀጣይ ሳምንት በዚህ መልክ እስኪያገናኘን ጌታ ከናንተ ጋር ይሁን🙌
291
ቡራኬ🙌
📖 1ኛ ጴጥሮስ 2:9-10 📖
በጌታ በኢየሱስ ስም
ከጨለማ ወደ ሚደንቀው ብርሀን የገባችሁበት ይህ የሚደንቅ ኪዳን ይግባችሁ!
የእግዚአብሔርን ታላቅ ስራ የምትናገሩበትን አቅም ይብዛላችሁ !
በእግዚአብሔር እንደተመረጠ ሰው ኪዳን እንደተሰጠው ሰው የምትኖሩባትን ፀጋ ይሰጣችሁ!
ስለ ንጉስ ብቻ ተናጋሪ፣ ከእሱም ተቀብሎ ለህዝብ አድራሽ ካህን አድርጎ በዚህ ትውልድ መሀል ይግለጣችሁ!
አሁን ካለው አመለካከት፣ ዘመን ካመጣው አስተሳሰብ የሚያልቅ ቅድስና ህይወታችሁን ይዋጅ!
እግዚአብሔር ከሁሉ ለይቶ የራሱ ያድርጋችሁ!
ስትንቀሳቀሱ የእግዚአብሔር የቅርብ ወገንነታችሁ ይሰማችሁ!
በኑሮአችሁ ውስጥ ለቀደሙ ምህረት በተገቢው ምልልስ ምላሽ መስጠት ይሁንላችሁ!
በ ሕዝቅኤል 37:26-24 ተብሎ እንደተፃፈ
የተደረገላችሁን ከእግዚአብሔር ጋር ያለን የሰላም ኪዳን እግዚአብሔር ለልባችሁ ያሳውቅ!
በእግዚአብሔር ኪዳን ውስጥ የምትፀኑበትን ሀይል ራሱ ይስጣችሁ!
በመሀከላችሁ ለመገኘት ቃልን የሰጠ ጌታ በህልውናው ያስገርማችሁ!
እግዚአብሔር ከናንተ ጋር ውሎ ይደርላችሁ!
እግዚአብሔር ህዝቤ ብሎ የግሉ ያድርጋችሁ!
በ 2ኛ ቆሮንቶስ 3 :5-6 ተብሎ እንደተፃፈ
በእርሱ ፊት የምቆሙበት ብቃታችሁ ጌታ ይሁንላችሁ !
ሁሉ ሰርቶ በፈፀመበት በዚህ ኪዳን ውስጥ ከኛ ብላችሁ የምጨምሩት ስራ አይኑርላችሁ!
አገልግሎታችሁን በመንፈሱ ይቅደምላችሁ!
ህይወትን የሰጣችሁን መንፈስ አስቀድማችሁ ብዙዎችን መማረክ ይሁንላችሁ!
ሰማይንና ምድርን የሠራ እግዚአብሔር፣ ከጽዮን ይባርካችሁ!
እግዚአብሔር ፊቱን ወደ እናንተ ይመልስ! እንድታፈሩና እንድትበዙም ያድርጋችሁ!
ቃል ኪዳኑንም ከእናንተ ጋር ያፅና።
እግዚአብሔር ማደሪያውን በመካከላችሁ ያድርግ፤ ነፍሱም አትጸየፋችሁ!
በመካከላችሁ ይመላለስ !
አምላካችሁ ይሁንላችሁ፤ እናንተም ሕዝቡ ሁኑለት!
ተባረኩ!
🙌 አሜን 🙌
