cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ቁርዐን የአላህ ቃል ነው።

ልጂቱ በሞተችበት ቀን እስከዛሬ ቁርአን ስትቀራበት በነበረችበት ክፍል ይለቀሳል ይነባል።ቤተሰቦቿ ደነገጡ በክፍሉ ማንም ሳይኖር እንዴት ይለቀሳል ይነባል ብለው በድንጋጤ ተውጠው።እናቲቱ ወደቤቱ በፍርሀት ድባባ በአውራ ጣታቸውና በተረከዛቸው እየተራመዱ ከበሩ ደረሱ፣ see more https://t.me/joinchat/AAAAAEwuosJoIZHLMHPT5g

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
213
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ክፍል ሁለት የሀድረት ሁሰይን (ረ·ዐ) ህልፈት የወዳጆቻቸው አስተያየት ለእርሳቸው በጎ የሚያስቡ፣ወዳጆቻቸውና ቤተ ዘመዶችም ጭምር የሁሰይንን ረ·ዐ ወደ ኩፋ ለመሄድ መነሳት በማየት ያንን በማድረግ እንደሌለባቸው ሊያግቧቧቸው ሞከሩ።የኩፋን ሰዎች ከዳተኛነት፣ተለዋዋጭነትና ቃል ኪዳንን የማፍረስ የጠለሸ ታሪክ ባለቤትነት እየጠቀሱ ይህን እቅዳቸውን እንዲሰርዙ እንደሚሻል ወተወቱ።ይህም ብቻ ሳይሆን የበኑ ኡመያንም የክህደት ልማድ በማስታወስ በኩፋ መልካም ነገር እንደማይጠብቃቸው አሳሰቧቸው።ከእነኝህ ቀራቢዎቻቸው መካከልም የአባታቸው የአጎት ልጅ የሆኑት አብደላህ ኢብኑ አባስ (ረ·ዐ)የሚከተለውን ብለዋቸው ነበር። " የአጎቴ ልጅ ሆይ!አሁን ወደ ኢራቅ ልታደርገው ባስብከው ጉዞ ምክንያት ሰዎች በጣም ተረብሸዋል።እባክህ ይህን አደገኛ የሆነ ጉዞ ለህዝቡ ስትል ሰርዝ!!" ሀድረት ሁሰይን (ረ·ዐ)ለዚህ ጥያቄ የሰጡት መልስ " በዚህ ጉዳይ ላይ ደጋግሜ በማሰብ ለመሄድ ውሳኔዬን አድርጌያለው።ከአንድ ቀን ወይም ከተወሰኑ ቀናት በሆላ ጉዞየዬን ጀምራለው።"የሚል ነበር።ኢብን አባስም ለዚህ አባባልፈጠን ያለ መልስ እንዲህ በማለት ሰጡ " አላህ ከክፉ ነገር ይጠብቅህ! አሚራቸውን ከመጥፎ አደጋ ሊከላከሉ ከማይችሉ ሰዎች መካከል ሄደህ ትገባለህን? ወይስ ጥላቶችህን ዶጋ አመድ አድርገውና አካባቢውን ነፃ አውጥተው የሚጠብቁህ መሰለህ? እንዲያ ቢሆን እንኳን ወደ ኩፋ በደስታ ልትጓዝ በቻልክ ነበር።ካልሀነ ግን ያአሁኑ ግዞህ እጅግ አደገኛና በኡመያዎች ላይ ግልፅ ጦርነት የማ ወጅ ያክል ነው።የኩፋ ሰዎች ይክዱሀል ብዬ አሰጋለው።" ሀድረት ሁሰይን ግን ይህን የኢብን አባስን በትህትና የቀረበ ልመና ከጉዳይ አልቆጠሩትም እናም በውሳኔያቸው ፀኑ። የኢብኑ አባስ የመጨረሻ ልመና:– ይቀጥላል ክፍል ሶስት ማዕከሉን ሊረዱ የሚችሉ ወንድምና እህቶችን ይጋብዙልን።ኑ የኸይር ተቋዳሽ እንሁን። ከናተ በላጩ ቁርዓን ተምሮ ያስተማረ ነው ‼ ሸይኩል ኢስላም ሂፍዝ ማእከል: 👉 ተጅዊድ ትምህርት 👉 አቂዳ " " 👉 ሀዲስ " " 👉 ፊቂሕ " " 👉 ሥነ–ፅሁፎች በየግዜያቸው የሚለቀቁበትና ማእከሉን የምንረዳበት ውድ ቻናል ነው። ከትምህርቱ ባሻገር ማእከሉን በሀሳብም በፋይናንስም ለመርዳት የምትሹ ወደ ዚቻናል ጋብዘነዎታል!@Abdulhakim94 መልእክት ካለዎት 👇👇👇👇 @Abdelhakim42
إظهار الكل...
አሰላሙአለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ ውድ እና የተከበራችሁ የቻናላችን ቤተሰቦች ይህ ቻናል ለትልቅ አላማ ስለተፈለገ ለዛ አላማ ሲባል የቻናሉን ይዘት ለመቀየር ተገደናል‼ ይህ ቻናል አሁን የሸይኩል ኢስላም ሂፍዝ ማዕከል ሆኗል ወደፊት በዚህ ቻናል ላይ ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ ቁርአንን እንዴት መቅራት እንችላለን? የቁርአን ህጎች ምንድን ናቸው? 🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟 ሸይኩል ኢስላም ሂፍዝ ማእከል ላይ የሚደረጉ ቂርአቶች የሀፊዞች የቁርአን ውድድር 🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟 አጠቃላይ የማእከሉ አያያዝ በስፍት ይቀርብበታል በተጨማሪም የተለያዩ ፈተዋዎች በስፋት ይቀርብበታል። ሀላል ትዳር❤️ ወደ አዲስ ቻናል ተሸጋግሯል! ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇👇☝️☝️ https://t.me/joinchat/AAAAAFFLK97o3L1-0pN_JQ
إظهار الكل...

ያጀማአ አሰላሙአለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ ይህ ግሩፕ ከተከፈተ የሰነበተ ቢሆንም እዚህ ባለኝ ስራ ውጥረት አንድ ፍሬ ሳያፈራ ለብዙ ግዝያት ቆይቶል።ውድ ወንድሞችና እህቶች በቁርአን ጉዳይ ተጅዊድም ሆነ ሌላ ነገር ለማስተማር ፍቃደኛ የሆነ ግሩፑን ለማስረከብ(የስልጣን ሽግግር)ስለምፈልግ በጎኛ ካለ ከታች ባለው በውስጥ መስመሬ ያግኘኝ።@abdelhakim42
إظهار الكل...
ቁርአንን ማንበብ የትክክለኛና እውነተኛ ሙእሚኖች መገለጫ መሆኑ ጥርጥር የለውም። የአላህንም እዝነት ተላብሰው የሚገኙት እነዚሁ ሰዎች ናቸው። አላህ ሱብሀነሁ ወተአላ መልእክተኛውን ሰ.አ.ወቁርአን ያነቡ ዘንድ እንዲህ በማለት ያዛቸዋል። "ቁርአንንምበዝግታአንብብ"። (ሙዘሚል4) አላህ (ሱ.ወ)ቁርአንን በመቅራት ተግባር ላይ የታተሩ ሰዎችን ሲያወድስ እንዲህ ይላል! "እነዚያየአላህን መጽሐፍ የሚያነቡ፣ሰላትንም አስተካክለው ያደረሱ፣ከሰጠናቸውም ሲሳይ በሚስጥርም ኾነ በግልፅ የለገሱ፣በፍፁም የማትከስር ንግድን ተስፋ ያደርጋሉ። ምንዳዎቻቸውን ሊሞላላቸው፣ከችሮታውም ሊጨምርላቸው(ተስፋያደርጋሉ)።እሱ በጣም መሀሪ አመስጋኝ ነውና።"(ፋጢር19-30) በሀዲስም በተመሳሳይ መልኩ ቁርአንን በማንበብ የሚገኘውን ክብርና ጥቅም በተመለከተ ባሉ አጋጣሚዎች ተወስቷል።ከዚህ ተያይዞ ከሁሉም በፊት ሊታወቅ የሚገባ አንድ ትልቅ ቁም ነገር አለ። እሱም ይህን ድንቅ መፅሐፍ ማንበብ ጥቅሙ የሚጎላው ውስጡ ባዘለው መልክትና አስተምህሮ የሰራንበት እንደሆነ ነው። ቁርአን የማንበብ ፍሬዎች 1-የአላህ መልእክተኛ ሰ.አ.ወበመጥፎ ተምሳሌትነት ከገለጿቸው ሰዎች ከመሆን ያድናል። ኢብን አባስ አላህ መልካም ስራቸውን ይዉደድላቸውና እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ ሰ.ዐ.ወእንዲህ ብለዋል፦"ያ በውስጡ ከቁርአን አንዳች ነገር የሌለው (ምሳሌው)እንደወና ውሃ ነዉ።"ቲርሚዚ 2-ቁርአንን በመቅራት ያዘወተረ ሰው ደጋግ ሰዎች ከሚቀኑባቸዉ ሰዎች ተርታ ይሰለፋል። ከኢብን ዑመር አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና እንደዘገቡት የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ "በሁለት ነገሮች ካልሆነ በስተቀር ቅናት የለም(አይፈቀድም)።እነሱም አላህ የቁርአን እውቀት ሰጥቶት ቀን ተለሊት በሱ የቆመበት(ሰላትየሰገደበት)ግለሰብእንዲሁም ገንዘብ ሰጥቶት ቀን ከለሊት የሚሙፀዉት" ቡኻሪና ሙስሊም እዚህ ቦታ ላይ የተጠቀሰው "ቅናት" ወንድምህ ዘንድ ያለውን መልካም ነገር ከሱ አንዳች ሳይቀንስ አሊያም እንዲወገድበት ሳትከጅል ላንተም እንዲኖርህ መመኘት ማለት ነው። #3-ቁርአን መቅራት በዚህኛውም ሆነ በቀጣዩ አለም ልቅናን የመጎናፀፊያ መንገድ ነው። #ኡመር ቢን ኽጣብ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል በማለት ዘግበዋል፦ "አላህ በዚህ መፅሃፍ ሕዝቦች ከፍ ያደርግበታል ሌሎችን ደግሞ ያዋርድበታል።" ሙስሊም
إظهار الكل...
#አህለን ቢከ ያ ረመዳን# #ታላቁ እንግዳችን! የተከበረውንየረመዳንወርለመቀበልሁሉም በየፊናው ተፍተፍ እያለ ይገኛል። ከፊሉ ቤቱን በማሰናዳት፣ ሌላው የምግብ አይነቶችን በመሸመት፣ እኩሉም የወሩን ትሩፋት ለመጠቀም እቅድ እያወጣ…ወዘተ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። ለመሆኑ ይህ አያሌ የፈጣሪ ትሩፋትን በውስጡ ይዞ የመጣውን ይህን ወር ለመቀበል ትክክለኛው መንገድ የትኛው ነው? በወሩውስጥያሉትንእያንዳንዱንየጦዓ (አምልኮ)ወቅቶችንሁሉአሟጦለመጠቀም ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? በነዚህበተከበሩጊዜያትውስጥ በኸይር ነገሮች መሽቀዳደም ያስፈልጋልና፤ አላህ (ሱ.ወ)እንዲህይላል፡- وَفــــــــِيذَٰلــــــــِكَفــــــــَلــــــــْيَتــــــــَنــــــــَافــــــــَســــــــِ الــــــــْمــــــــُتــــــــَنــــــــَافــــــــِســــــــُونــــــــَ “በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ።” (አል-ሙጦፊፊን83፤26) በመሆኑምከዚህበመቀጠልየረመዳንንወር በተሻለ መንገድ ለመቀበል የሚረዱ መንገዶች እንጠቁማለን፡- 1- ዱዐ ማድረግ፡- በፆም፤ በሶላትና በዚክር ላይ እንድትጠነክር አላህ (ሱ.ወ)በሙሉጤንነትናአቅምላይ ሆነህ ረመዳን ወር እንዲያደርስህ ከአሁኑ ዱዓ አድርግ፤ አነስ ቢን ማሊክ (ረ.ዐ)ነቢያችን(ሰ.ዐ.ወ)የረጀብወርሲገባእንዲህ ይሉ ነበር ብለዋል፡- الــــــــلــــــــهم بــــــــارك لــــــــنــــــــا فــــــــي رجــــــــب وشــــــــعــــــــبــــــــان وبــــــــلــــــــغــــــــنــــــــا رمــــــــضــــــــانــــــــ “አላህ ሆይ!ረጀብንናሸዕባንንብሩክአድርግልን፤ ረመዳንንም አድርሰን”(አህመድናጦብራኒዘግበውታል)። ሰለፎች(ቀደምትደጋግአቦዎች)ረመዳንንእንዲያደርሳቸውናከዚያምሥራቸውን እንዲቀበላቸው አላህን (ሱ.ወ)ይለምኑነበር፤ስለዚህአንተም የረመዳን ጨረቃ ስትወጣ እንዲህ ብለህ ዱዓ አድርግ፡- الــــــــلــــــــه أكبــــــــر الــــــــلــــــــهم أهلــــــــه عــــــــلــــــــينــــــــا بــــــــالــــــــأمــــــــن والــــــــإيمــــــــان والــــــــســــــــلــــــــامــــــــة والــــــــإســــــــلــــــــام ,والــــــــتــــــــوفــــــــيقــــــلــــــــمــــــــاتــــــــحــــــــبــوتــــــــرضــــــــى ربــــــــي وربــــــــك الــــــــلــــــــه “አላሁ አክበር አላህ ሆይ!ይህንጨረቃየአማንናየኢማን፣ የሰላምና የኢስላም፣ እንዲሁም አንተን የሚያስደስት ተግባር መስራት የምንችልበት ጊዜ አድርግልን፤ የኔም የአንተም ጌታ አላህ ነው፤” (ቲርሚዚዘግበውታል)።
إظهار الكل...
አ ወ ወ
إظهار الكل...
የተረሱ ሱናዎች ☞ የ40 ዓመት ሴት ማግባትም ሱና ነው። የፈታች ሴት ማግባትም ሱና ነው። ልጅ ያላት ሴት ማግባትም ሱና ነው። ባሏ የሞተባት ሴት ማግባትም ሱና ነው። ቤት ዉስጥ ሥራ ማገዝም ሱና ነው። ለሚስት ምርጥ ባል መሆንም ሱና ነው። ሚስት ማጉረስም ሱና ነው። ከሚስት መጨዋወትም ሱና ነው። ለሚስት ፍቅር መግለፅም ሱና ነው። ሚስትን ማቆላመጥም ሱና ነው። ለሚስት ማዘንና መለሳለስም ሱና ነው። የሚስትን ስህተት ማለፍም ሱና ነው። ሚስትን ማክበርም ሱና ነው። ለሚስት መዋብም ሱና ነው። የሚስትን ቤተሰብ ማክበርም ሱና ነው። የሚስትን ዉለታ ማውሳትም ሱና ነው። ጨምሩበት... ቁርዐን የአላህ ቃል ነው።: የፈረንካ ነገር ሴቶቹ ፈረንካ እያሉ አስቸገሩ አለኝ አንዱ ስለ ጋብቻ ስጠይቀው፡፡ ‹ያለ ሁለቱ ቪ እሺ አይሉም› ብሎም ጨመረልኝ፡፡ 2ቱ ቪ ቪላ እና ቪትዝ መሆኑ ነው፡፡ እኔም ደግ አረገች አልኩት፡፡ ወዳጄ! ታዲያ ፈረንካን የማይወድ ማን አለ? ድህነትንስ የሚወድ ማን አለ?፡፡ ዛሬ እኮ ወንዱም ጭምር እየጠየቀ ነው፡፡ መልክ ላይ አልቆመም፡፡ ከመልክ በተጨማሪ ምን አላት እያለ ነው፡፡ በሀብቷ የማገባት ካለች ፈልጉልኝ ብሎ እያጠያየቀ ነው፡፡ እኔ የምለው ያውም በዲኑ የጠነከረ አላህን የሚፈራ ሰው በጠፋበት ዘመን ከሁለቱም ያጣ ከምንሆን ብለው ፈርተው ሴቶቹ ለፈረንካ እጅ ቢሠጡ ምኑ ነው ችግሩ፡፡ ግና አንተስ ብትሆን ልጅህን ለድሃ ትድራለህ ወይ!፡፡ ልጅህ በትዳር ዓለም ተቸግራ ልታያት ትሻለህ ወይ?፡፡ ወዳጄ ድህነት ሰውን ከሰው በታች እንደሚያደርግ አታውቅም እንዴ!፤ ለብቻ ያስወራል፣ ያነጫንጫል፤ አላህን እስከመካድ ሁሉ ያደርሳል፡፡ ባገኘው እገድለዋለሁ ይሉ ነበር ዐሊ ኢብኑ አቢጣሊብ ሰይፋቸውን እያመቻቹ፡፡ ድህነትን ነው፡፡ … እና ቺኮቹ አንድ ሰው ሀብት ከሌለው ይልቅ ያለውን ቢመርጡ አጠፉ ማለት ይከብዳል፡፡ በኢማን ድክመትም መወቀስ የለባቸውም፡፡ አንድም መብታቸው ነው፤ ሁለትም ማንም ቢሆን ጥሩ ነገር ይወዳል፡፡ ረሱሉ ሴት ልጅን አራት ነገሮችን አይቶ ማግባት እንደሚቻል ሲናገሩ ከአራቱ አንዱ ‹ለሀብቷ› ነው ያሉት፡፡ ‹ዲን ላላት ቅድሚያ ስጥ› አሉ እንጂ ሀብት ያላት ትጠላለች አላሉም ነቢዩ፡፡ ‹ሰፊ ቤት፣ አሪፍ መኪና፣ መልካም ሴት፣ ጥሩ ጎረቤት… የደስታ ምንጮች ናቸው፡፡› ያሉትም እርሣቸው ናቸው፡፡ እርሣቸውም ቢሆኑ የናጠጠች ሀብታም ነው ያገቡት፡፡ ኸዲጃን፡፡ ኸዲጃ ደግሞ በብዙ መልኩ ረድታቸዋለች፡፡ በገንዘቧ ደግፋቸዋለች፡፡ ጉዳዩ ተገልብጦ ሲታይ ለሴቶቹም እንዲያ ነው፡፡ ሀብት ኑሮን ያቀላል፣ ልብን ይሰበስባል፣ ደስታን ይጨምራል፣ ቤት ጥላ ነው፣ በሰፊ ሳሎን ዉስጥ የሚሰገድ ሶላት ራሱ ያረጋጋል፡፡ ዱንያ ስትመቻችልህ አንድ ሀሳብ ቀለልልህ፡፡ ካንተ የሚጠበቀው ማመስገንና ተረጋግቶ ጌታህን ማምለክ ነው፡፡ እናም ሀብት አይጠላም ወዳጄ፡፡ በተለይ ከኢማን ጋር ሲሆን ሀብት ማሻአላህ ሊባል ነው የሚገባው፡፡ ድህነት ግን ሀሳብን ይበትናል፤ የእጅ ማጠር ያለ እንቅልፍ ያሳድራል፣ ሙሉ ቀን ያኳትናል፣ ገላን እንጂ ቀልብን አያሳርፍም፡፡ ኪስ ታያለች፤ ሰው ታማርጣለች፣ ጥቅመኛ ነች … ብሎ መወንጀል ተገቢ አይደለም፡፡ ስለ ዲን እና ስለ ኢማን አለመጨነቅም ሊሆን አይችልም፡፡ በቃ አንተ መልክ እያማረጥክ አይደል! እሷም ሀብት ብታማርጥ ሊገርም አይገባም። አሁን ላይ ከወንዶቹ የሚጠበቀው ነገር ሴቶቹን ከመተቸት ይልቅ ሀብታም ሆኖ መገኘት፡፡ ልቤ የሻትን ቆንጆና ኢማነኛ እንጂ አላገባም ያለ ከወዲሁ መህሩን ያጠራቅም፣ ቤቱን ይስራ፣ መኪናውን ይግዛ፡፡ ዉድ ነገር በዉድ እንጂ አይገኝምና፡፡ ወዲህ ግን አብሮ ሠርቶ ማደግም መልካም እንደሆነ መታወቅ አለበት፡፡ በተለይ ሰውዬው ኢማነኛ ከሆነ ጥያቄውን መቀበል የረሱሉን (ሰ.ዐ.ወ.) ምልከታ መቀበል እንደሆነ መታወቅ አለበት፡፡ በሀብት ተመሳሳይ ሰው ከመጣልሽ ዲን ያለውን ለመቀበል ዐይንሽን አትሽ፡፡ አላህ በረከቱን ያብዛላችሁ፡፡ የተብቃቃ ልቦናም ይስጣችሁ፡፡@abdelhakim42
إظهار الكل...
የፈረንካ ነገር ሴቶቹ ፈረንካ እያሉ አስቸገሩ አለኝ አንዱ ስለ ጋብቻ ስጠይቀው፡፡ ‹ያለ ሁለቱ ቪ እሺ አይሉም› ብሎም ጨመረልኝ፡፡ 2ቱ ቪ ቪላ እና ቪትዝ መሆኑ ነው፡፡ እኔም ደግ አረገች አልኩት፡፡ ወዳጄ! ታዲያ ፈረንካን የማይወድ ማን አለ? ድህነትንስ የሚወድ ማን አለ?፡፡ ዛሬ እኮ ወንዱም ጭምር እየጠየቀ ነው፡፡ መልክ ላይ አልቆመም፡፡ ከመልክ በተጨማሪ ምን አላት እያለ ነው፡፡ በሀብቷ የማገባት ካለች ፈልጉልኝ ብሎ እያጠያየቀ ነው፡፡ እኔ የምለው ያውም በዲኑ የጠነከረ አላህን የሚፈራ ሰው በጠፋበት ዘመን ከሁለቱም ያጣ ከምንሆን ብለው ፈርተው ሴቶቹ ለፈረንካ እጅ ቢሠጡ ምኑ ነው ችግሩ፡፡ ግና አንተስ ብትሆን ልጅህን ለድሃ ትድራለህ ወይ!፡፡ ልጅህ በትዳር ዓለም ተቸግራ ልታያት ትሻለህ ወይ?፡፡ ወዳጄ ድህነት ሰውን ከሰው በታች እንደሚያደርግ አታውቅም እንዴ!፤ ለብቻ ያስወራል፣ ያነጫንጫል፤ አላህን እስከመካድ ሁሉ ያደርሳል፡፡ ባገኘው እገድለዋለሁ ይሉ ነበር ዐሊ ኢብኑ አቢጣሊብ ሰይፋቸውን እያመቻቹ፡፡ ድህነትን ነው፡፡ … እና ቺኮቹ አንድ ሰው ሀብት ከሌለው ይልቅ ያለውን ቢመርጡ አጠፉ ማለት ይከብዳል፡፡ በኢማን ድክመትም መወቀስ የለባቸውም፡፡ አንድም መብታቸው ነው፤ ሁለትም ማንም ቢሆን ጥሩ ነገር ይወዳል፡፡ ረሱሉ ሴት ልጅን አራት ነገሮችን አይቶ ማግባት እንደሚቻል ሲናገሩ ከአራቱ አንዱ ‹ለሀብቷ› ነው ያሉት፡፡ ‹ዲን ላላት ቅድሚያ ስጥ› አሉ እንጂ ሀብት ያላት ትጠላለች አላሉም ነቢዩ፡፡ ‹ሰፊ ቤት፣ አሪፍ መኪና፣ መልካም ሴት፣ ጥሩ ጎረቤት… የደስታ ምንጮች ናቸው፡፡› ያሉትም እርሣቸው ናቸው፡፡ እርሣቸውም ቢሆኑ የናጠጠች ሀብታም ነው ያገቡት፡፡ ኸዲጃን፡፡ ኸዲጃ ደግሞ በብዙ መልኩ ረድታቸዋለች፡፡ በገንዘቧ ደግፋቸዋለች፡፡ ጉዳዩ ተገልብጦ ሲታይ ለሴቶቹም እንዲያ ነው፡፡ ሀብት ኑሮን ያቀላል፣ ልብን ይሰበስባል፣ ደስታን ይጨምራል፣ ቤት ጥላ ነው፣ በሰፊ ሳሎን ዉስጥ የሚሰገድ ሶላት ራሱ ያረጋጋል፡፡ ዱንያ ስትመቻችልህ አንድ ሀሳብ ቀለልልህ፡፡ ካንተ የሚጠበቀው ማመስገንና ተረጋግቶ ጌታህን ማምለክ ነው፡፡ እናም ሀብት አይጠላም ወዳጄ፡፡ በተለይ ከኢማን ጋር ሲሆን ሀብት ማሻአላህ ሊባል ነው የሚገባው፡፡ ድህነት ግን ሀሳብን ይበትናል፤ የእጅ ማጠር ያለ እንቅልፍ ያሳድራል፣ ሙሉ ቀን ያኳትናል፣ ገላን እንጂ ቀልብን አያሳርፍም፡፡ ኪስ ታያለች፤ ሰው ታማርጣለች፣ ጥቅመኛ ነች … ብሎ መወንጀል ተገቢ አይደለም፡፡ ስለ ዲን እና ስለ ኢማን አለመጨነቅም ሊሆን አይችልም፡፡ በቃ አንተ መልክ እያማረጥክ አይደል! እሷም ሀብት ብታማርጥ ሊገርም አይገባም። አሁን ላይ ከወንዶቹ የሚጠበቀው ነገር ሴቶቹን ከመተቸት ይልቅ ሀብታም ሆኖ መገኘት፡፡ ልቤ የሻትን ቆንጆና ኢማነኛ እንጂ አላገባም ያለ ከወዲሁ መህሩን ያጠራቅም፣ ቤቱን ይስራ፣ መኪናውን ይግዛ፡፡ ዉድ ነገር በዉድ እንጂ አይገኝምና፡፡ ወዲህ ግን አብሮ ሠርቶ ማደግም መልካም እንደሆነ መታወቅ አለበት፡፡ በተለይ ሰውዬው ኢማነኛ ከሆነ ጥያቄውን መቀበል የረሱሉን (ሰ.ዐ.ወ.) ምልከታ መቀበል እንደሆነ መታወቅ አለበት፡፡ በሀብት ተመሳሳይ ሰው ከመጣልሽ ዲን ያለውን ለመቀበል ዐይንሽን አትሽ፡፡ አላህ በረከቱን ያብዛላችሁ፡፡ የተብቃቃ ልቦናም ይስጣችሁ፡፡ የራሴ ሀሳብ ነው Comm..እስኪ ........@abdelhakim42
إظهار الكل...
  • File unavailable
  • File unavailable
"በቀደምቶች ሁኔታ "ቁርአን ላይ በመቸከል እንዴት ረዥም ሰዓታትን ማሳለፍ ተቻላቸው?" ስል እደነቅ ነበር። ሞባይል ላይ ለዥም ሰዓታት የሚቸክሉትን ባየሁ ጊዜ ግርምቴ ተወገደ። ለካንስ ልብ አንድን ነገር በወደደ ጊዜ ችክ ይላል!።" ﺩﻛﺘﻮﺭ ﺇﺣﻤﺪ ﻋﻴﺴﻰ ﺍﻟﻤﻌﺼﺮﺍﻭﻱ "ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገደብም" አለ ያገሬ ሰው! ከስር የምትመለከቷቸው ምስሎች "ምክንያት የለንም" የሚል ቃል የተከተበባቸው ሲሆኑ ለዚህ አባባል ምስክር ናቸው! ጊዜያቸውን በማንበብ ከሚያሳልፉቱ ያድርገነ
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.