cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ሆዛ የ ዜማ መሳርያዎች ማምረቻ እና ማሰልጠኛ ማዕከል

ሰላም ዉድ የ ሆዛ ቤተሰቦች ይሄ ግሩፕ 1, ሁሉንም ያሳተፈ ትምሀርት 2, የ መዝሙራት ልምምድ 3, የ ዘማርያን ታሪክ እንዲሁም 4, ነፃ የ online የ በገና እና ሌሎች የ ዜማ መሣርያዎች ትምህርት ሚሰጥበት እና ምንማማርበት ግሩፕ ነው በይበልጥ መረጃ ለማግኘት ከፈለጉ በ ቴሌግራም አድራሻ @yaredj4f8 ወይም በ ስልክ ቁጥር +251906131212 ላይ በመደወል ያናግሩን

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
3 452
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-187 أيام
-7030 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

#ሰሙነ_ሕማማት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ሰሙነ ሕማማት የጾመ ሁዳዴ የመጨረሻው ሳምንት፤ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማም የሚታሰብበት፤ ካህናትና ምእመናን በአጸደ ቤተክርስቲያን ተሰብስበው የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ የሚያዜሙበት፤ ግብረ ሕማም በመባል የሚታወቀውን መጽፍ የሚያነቡበትና የሚሰሙበት፤ በነግህ፣ በሠልስት፣ በስድስት፣ በተሰዓት /ዘጠኝ /ሰዓት፣ በሰርክ /በዐስራ አንድ/ ሰዓት እየመላለሱ የሚሰግዱበትና የሚጸለዩበት ልዩ ሳምንት ነው ከሆሳዕና ማግስት እስከ ትንሳኤ። በዚህ ሳምንት በተለይ ካህናት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ ምክንያቱም ጌታችን የደረሰበትን መከራና ስቃይ እንዲሁም የሰው ልጅ ፭ ሺ ፭ መቶ ዘመን በጨለማ ግዞት ይኖር እንደነበር ለማዘከርም ጭምር ነው። የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራና ሕማም በጽኑ እንድናስበው ያስተማሩን ሐዋርያት ናቸው። ለእነርሱም የነገራቸው ደግሞ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ሰሙነ ሕማማት የጌታችንን ሕማማት ከማሰብ ጋር በየዕለቱ በርካታ ድርጊቶች መፈጸማቸውን የምናስታውስበት ሳምንት ነው፦ #ሰኞ #መርገመ_በለስ_የተፈጸመበት_ሰኞ_ይባላል፦ በዚህ ዕለት ጌታችን ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ ቅጠል ያለባትን በለስ ተመልክቶ ወደ በለሲቱ ቢቀርብ ከቅጠል በቀር ምንም ነገር ባለማግኘቱ “ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ምንም ካንቺ ፍሬ አይበላ” ማር ፲፩፥፲፬ በማለት ስለረገማት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል። #አንጽሖተ_ቤተ_መቅደስ_ይባላል፡- ጌታ ወደ ቤተመቅደስ ሄዶ በቤተመቅደሱ የሚሸጡትን እና የሚለውጡትን “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች” ማቴ ፳፩፥፲፫ በማለት ከቤተመቅደስ ገርፎ አስወጥቷቸዋልና። #ማክሰኞ #የጥያቄ_ቀን_ይባላል፦ ሰኞ ዕለት በቤተመቅደስ ሲሸጡ እና ሲለውጡ የነበሩትን ሁሉ እየገረፈ በማባረሩ ምክንያት ለሰው ልጅ ሹመትንና ስልጣንን የሰጠ ጌታ “በምን ስልጣን ይህንን ታደርጋለህ?” ማቴ ፳፩፥ ፳፫ ተብሎ በፈሪሳውያን ተጠይቋልና የጥያቄ ቀን ይባላል። #የትምህርት_ቀን_ይባላል፡- በዚህ ዕለት በቤተመቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረም የትምህርት ቀን ይባላል። ሉቃ ፳፩ ፥፳፰ ፣ ማር ፲፪፥፪። #ረቡዕ #ምክረ_አይሁድ_ይባላል፦ ረቡዕ እለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ወቅቱ የፋሲካን በዓል የሚያከብሩበት ቀን በመሆኑ እና ብዙ ህዝብም ጌታን ይከተለው ስለነበር ሁከት እንዳይነሳ ስጋት ነበራቸው ። ነገር ግን ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ስለነገራቸው ሉቃ ፳፪፥፩-፮ ጭንቀታቸው ተወግዶ በጌታ መያዝ ተስማምተዋል። #የመልካም_መዓዛ_ቀንም_ይባላል፡- ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በሰምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯ የመዓዛ ቀን ይባላል። #የእንባ_ቀን_ይባላል፡- ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ እፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አርሳለችና ማር ፲፬፥፱ የእንባ ቀን ይባላል። #ሐሙስ #ጸሎተ_ሐሙስ_ይባላል፦ ጌታችን ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ ሲጸልይ በማደሩ ማቴ ፳፮፥፴፮ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል። #የምስጢር_ቀን_ይባላል፡- ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምስጢር ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል። #የሐዲስ_ኪዳን_ሐሙስ_ይባላል፡- መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ ሉቃ ፳፪፥፳ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል። #የነጻነት_ሐሙስ_ይባላል፡- ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም ዮሐ ፲፭፥ ፲፭ የነጻነት ሐሙስ ይባላል። #ዓርብ #የስቅለት_ዓርብ_ይባላል፦ ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና ማቴ ፳፯፥፴፭ የስቅለት ዓርብ ይባላል። #መልካሙ_ዓርብ_ይባላል፡- ከጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ የወንጀለኛ መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል ጌታችን በደሙ ቀድሶ የምህረት፣ የሕይወት አርማ፣ የዲያቢሎስ ድል መንሻ ስላደረገው፤ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል። #ቅዳሜ #ቀዳም_ስዑር_ትባላለች ፦ ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረች ቅዳሜ ይባላል። #ለምለም_ቅዳሜ_ይባላል፡- ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጤማ እስከ ትንሣኤ ለሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል። #ቅዱስ_ቅዳሜ_ይባላል፡- ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ያረፈበት ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ስራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዶ ሲኦልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ የነበሩትን ነፍሳት የዘላለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል። (ስምዐ ጽድቅ  መጋቢት ፳፻፪ ዓ.ም) https://t.me/gamechu_ye
إظهار الكل...
💥💥💥💥💥💥💥 አስቸኳይ የሚሸጥ ክራር 📌 ✅ውድ ቤተሰቦቻችን ከዚህ በፊት እንደተለመደው በ ትእዛዝ ከምንሰራቸው ክራሮች በተጨማሪ እንደዚህ አይነት በ ፍልፍል የተዋቡ እና ከ ዋንዛ ብቻ በ ጥራት የተሰሩ ክራሮችን የምናቀርብ መሆኑ የሚታወቅ ነው :: 🔰ዛሬ ደግሞ ይህን ውብ ክራር ለናንተ ለ ቤተሰቦቻችን ለመሸጥ አዘጋጅተናል:: ከናንተ ሚጠበቀው ደውሎ መውሰድ ብቻ ነው:: +251906131212 +251703634863 @yaredj4f8 ላይ ያናግሩን 🌐https://t.me/ho_zaa1
إظهار الكل...
Enkuan aderesachihu wed beteseboch
إظهار الكل...
إظهار الكل...
የጥምቀት በዓል መዝሙራት ዘማሪ ዲያቆን አሸናፊ ፈቃዱ እና ዘማሪት ፌበን ሰሎሞን [Timket Mezmur Collection]

የጥምቀት በዓል መዝሙራት ዘማሪ ዲያቆን አሸናፊ ፈቃዱ እና ዘማሪት ፌበን ሰሎሞን የጥምቀት በዓል መዝሙሮች ስብስብ - በዘማሪት ትግስት መብራቱ [Timket Mezmur Collection] #mezmur #orthodox #timket #የከተራና #የጥምቀት መዝሙሮች ስብስብ #timket #mezmur #orthodox የጥምቀት መዝሙሮች,የጥምቀት መዝሙሮች ስብስብ,የተመረጡ የጥምቀት መዝሙሮች,የ ጥምቀት መዝሙሮች ስብስብ 2012,የጥምቀት መዝሙር,የጥምቀት መዝሙራት,የጥምቀት እና የከተራ መዝሙሮች ስብስብ,ደስ የሚሉ የጥምቀት መዝሙራት,የአውዳመት መዝሙሮች ስብስብ,የከተራና የጥምቀት መዝሙሮች 2020,የጥምቀት በዓል መዝሙሮች,የጥምቀት በዓል መዝሙሮች [ collection],የጥምቀት እና የከተራ መዝሙሮች,የገና መዝሙሮች,የጥምቀት መዝሙር ስብስብ,ልዩ የጥምቀት መዝሙር,የጥምቀት,የጥምቀት ከተራ,የልደት መዝሙሮች,የበአል መዝሙሮች,ስብስብ,የጥምቀት በአል አከባበር,የ ጥምቀት መዝሙር,የገና መዝሙራት,የበዓል መዝሙራት,የበአል መዝሙራት,ጥምቀት መዝሙር,#የጥምቀት_እና_የልደት_/ገና_መዝሙሮች_ስብስብ,timket mezmur,timket mezmur orthodox,timket mezmur collection,orthodox mezmur,ye timket mezmur orthodox,ye timket mezmur,orthodox mezmur timket,ethiopian orthodox timket mezmur,ethiopian orthodox mezmur,timket,timket orthodox mezmur,orthodox timket mezmur,timket mezmur orthodox 2014,mezmur orthodox ethiopian timket,ye timket mezmur orthodox ethiopia,ethiopian orthodox mezmur timket,new ethiopian orthodox mezmur,mezmur orthodox,mezmur orthodox ethiopia

ዉድ የ ሆዛ ቤተሰቦች እንኳን ለ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን 🙏
إظهار الكل...