cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

🎵Ye🎙️ fkr zefen🎵

🎷🎶🎶🎶🎸old and new music 🎵🎵 Achachir tarikoch✍️✍️ Le pp mihon pic👩‍❤️‍ Vedio music📽️🎬& cover music Gerami ina aznagn ababaloch 📔 Ye fqr giximoch🗣️

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
253
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

💍ባሌ በ50 ብር ሸጠኝ !😢 #ክፍል6⃣ #ተከታታይ ልቦለድ ✍በወንድማገኝ ለማ . . መስታወቱ ጥቁር የሆነ ዶልፊን ውስጥ ገብተን ጉዞ ጀመርን። እኛ ስድስታችንም ሴት ህፃናት ከኋላ ተቀምጠናል። ሹፌሩና አንድ ፊቱ እንደ መርፌ የቀጠነ መነፀር ያደረገ ሰውዬ ጋቢና ተቀምጠዋል። ሁሉቱም እየተቀባበሉ ጋንጃ እየሳቡ ይጦዛሉ። ሁላችንም የሰዎቹ ሁኔታ ስላላማረን ልባችን ውስጥ ሚጢጢዬ ፍርሃት እየተፀነሰች ነወ። ልክ መስቀል ፍላወር ጋር ስንደርስ አንድ ስም ያለው ትልቅ ክለብ በር ጋር መኪናዋ ቆመች። ሹፌሩና ፊቱ እንደ መርፌ የቀጠነው ሰውዬ ስድስታችንንም እያንጠለጠሉን በጓሮ በር አስገቡን። በክለቡ ጓሮ በኩል አንድ ሰፋ ያለ አዳራሽ ይገኛል። እዛ አዳራሽ ውስጥ ለሰአታት እንድንቆይ ተደረግን። አዳራሹ የማየው ነገር እዚህ ምድር ላይ ያለው ሳይሆን ሲኦል ውስጥ ያለሁ እስኪመስለኝ ድረስ ዘገነነኝ። ዓይኔ በሚያየው ነገር አቅለሸለሸኝ አጥወለወለኝ!!! የፍርሀት ጥፍሮች ሀሞቴ ድረስ ዘልቀው ሲቧጥጡኝ ይሰማኛል። እዚህ የሲኦል ተምሳሌት በሆነ እሳት አልባ ቁመተ ረዥም አዳራሽ ውስጥ ወደ ሀያ የሚደርሱ ትንንሽ አልጋዎች በጎንና በጎን ተደርድረዋል። እያንዳንዱ አልጋ ላይ መሸፈኛ እንዲመስል ነው እንጂ ሁሉን ነገር ወለል አድርገው የሚያሳዩ መሀረም መሀረም የሚያህሉ መጋረጃዎች ተሰቅለዋል። ሁሉም አልጋዎች ላይ ከኛ በሁለት ና በሶስት ዕድሜ የሚበልጡ ታዳጊ ሴቶች (ሁሉም የጦዙ ይመስለኛል) አምላክ እንደፈጠራቸው መለመላቸውን ተጋድመውና ተቀምጠው ቦዘዝ ባለው ዓይኖቻቸው እኛን ይመለከቱናል። እያንዳንዷ ታዳጊ ሴት ስር ደግሞ በገንዘብ እንደሰከሩ የሚያስታውቁ ወዛም ሽማግሌዎች ቁና ቁና እየተነፈሱ የሴቶቹን ገላ እንደታቦት ይሰግዱለታል ይሳለሙታል። እዛው ፊትለፊታችን ብዙዎቹ ሲዋሰቡ አየን ያሚ ወዲያው ራሷን ሳተች። ያ መርፌ ፊት ሰውዬ አንጠልጥሏት ይዟት ወጣ። ሌሎቻችን በምናየው ነገር አፍረን አንገታችንን ስንደፋ ሹፌሩ በግዴታ ቀና እያደረገን እንድናይ ያስገድደን ነበር። የኛ ማየት ለምን እንዳስፈለገ በዛን ወቅት አልተገለፀልኝም ነበር። ለካ ከሰዓታት በኋላ ለተደገሰልን ልዩ ግብዣ እንዳንደናገጥ እንዳንረበሽ አእምሮአችንን እያለማመዱት ነው። አለ አይደለ? ወደንም ይሁን ተገደን ነገሮችን አስቀድመን ከተላመድናቸው እንደመጀመሪያው ያህል አያስደነግጠንም። ከጥቂት ቆይታ በኋላ ሁላችንም ቀይ መብራት ወደምትበራበት አንድ ጠባብ ክፍል ተወሰድን። "ልብሶቻችሁን አውልቁ!" አለን ያ መርፌ የመሰለ ሰውዬ ፤ በፍርሃት ውስጥ እየተደናበርን አወለቅን። ከዛ ልክ ልትወልድ እንደደረሰች ሴት ተኝተን መሀፀናችንን ከፍተን እንድናሳየው ትዕዛዝ ሰጠን። ሁላችንም እምቢ ስንለው ፊታችን እንዳይጎዳ እየተጠነቀቀ ፀጉራችንን እየጨመደደ ይጠፈጥፈን ጀመር። ሳንወድ ዱላው ሲበዛብን ሀፍረታችንን ከፈትንለት። ያ መርፌ ሰውዬ በእጁ ትንሽዬ ባትሪ ይዞ ጓንት አጠለቀና የጠፋበት ዕቃ ያለ ይመስል እጁን ከትቶ ይፈትሽ ጀመር። እኔ ማህፀኔ ውስጥ ምንም ነገር ገብቶ ስለማያውቅ እጁን ሲከተው ጮህኩኝ። ቀና ብሎ አይቶኝ በወልጋዳ ጥርሶቹ ሊስቅ ሞከረ። ሰው ሲቆጣ እንጂ ሲስቅ አስፈርቶኝ አያውቅም። ይሄ ሹል ራስ ግን ከቁጣው ይልቅ ሳቁ ያስፈራል። ያሚን እጁን ከትቶ በተደጋጋሚ ፈተሻትና ፣ እሷ ማህፀን ውስጥ ውድ ንብረት አስቀምጦ እንደጠፋበት ሁሉ ብስጭትጭት እያለ "አንቺ የማትረቢ ውሻ! በዚህ ዕድሜሽ ለማን ሰጥተሽው ነው?!" የሆነ ሻካራ ሳቅ ሳቀ "መቼስ ትራፊ ከሆንሽ አይቀር እኔም የድርሻዬን አንድ ጉርሻ ልቅመስልሽ" አሁንም ብላክቦርድ በወረቀት ሲጠረግ የሚያሰማው አይነት ዝግንንንን የሚል አይነት ሳቅ ሳቀ። እዛው እፊት ለፊታችን አይናችን እያየን ያሚን እየጠፈጠፈ ከሹፌሩ ጋር ሆነው አስገድደው ደፈሯት። አንዳንዴ ግን ወንዴ.......ተዳፈርሽ አትበለኝና ይሄ እግዜር የሚሉት ግን ይገርመኛል። ልጆቹ እንዲህ በስቃይ ስንዳክር ምን አይነት ጨካኝ አንጀት ቢኖረው ነው ዝም ብሎ የሚያየው እላለሁ። አይ እሱ አይሳሳት ነገር ሁሉ ለበጎ ነው ብዬ እንዳላስብ ፤ እኔን ጨምሮ የማውቃቸው ሴቶች በሙሉ አንድ ቀንም እፎይ ብለን አናውቅም። ሁሌም በስቃይ ማዕበል ውስጥ እንደዳከርን ነው። ሰነፍ በልቡ እግዚአብሔር የለም ይላል ........ይላል አይደል መዝሙረኛው ዳዊት እኔ ግን ይሄን ሁሉ በደላችንን እያየ ዝም የሚል አምላክ አለ ብዬ ከማመልክ የለም ብዬ ሰነፍ ብባል ይሻለኛል። ዓይኔ እያየ የኔን ጨምሮ የሌሎች የብዙ ህፃናት ህይወት በሱ ፀጥ ማለት የተነሳ ያለጥፋታቸው ሲበላሽና ሲቀጭ አይቻለሁ። ስለዚህ ለእኔ አምላክ የለም። ያሚ ራሷን ስታ ሳይቀር እነዚህ ርህራሄ ያልፈጠረባቸው እርኩሶች ሲደፍሯት ስናይ አምስታችንንም ሰቀጠጠን። እኔ ውስጥ ግን ቅድም የነበረው ፍርሃት ድራሽ አባቱ ጠፍቷል ፣ ምክንያቱም ቢያንስ ቢያንስ ልትፈራ የምትችለው ላመልጥ እችላለሁ ብለህ ስታስብ ወይንም ደግሞ የውሃ ጠብታ የምታህል ተስፋ እስካለህ ድረስ ብቻ ነው። ነገር ግን ምንም አይነት ማምለጫ እንደሌለህ ስታውቅ ፣ ጭልምልም ሲልብህ ፣ ተስፋ ስትቆርጥ መፍራትህን ታቆማለህ። እኔም ለዛ ይመስለኛል ምንም አይነት ስሜት እየተሰማኝ አይደለም። ጥቂት ቆይታ ያሚ በድጋሚ ራሷን ሳተች። በዛች ቅፅበት ግን አንድ ነገር ገባኝ። ይቺ ኮተታም ዓለም የወንዶች መፈንጪያ ብቻ እንደሆነች! ምድር ላይ ያለን ሔዋኖች በሙሉ በስሜታቸው ለሚነዱት ፣ ጭናቸው ስር ባለ ሸቀጣቸው ለሚያስቡት ለአዳሞች መደሰቻ ብቻ እንደተፈጠርን ገባኝ። የሴቶች እኩልነት እያሉ እስከ ምፅዐት ቀን ድረስ ይደልሉናል እንጂ ከጉልበታቸው በላይ እንኳን ከፍ እንደማያደርጉን በዚች በትንሿ የህይወት ልምዴ ተረድቻለሁ። ዛሬም ቢሆን ከኛ እኩል ሁኑ እያላችሁን ሴትነታችንን እያጠፋችሁብን ወንድ እያደረጋችሁን ነው። "ሪችዬ ይቅርታ አቋረጥኩሽ ይሄ የምታወሪው ነገር'ኮ ትልቅ ፍልስፍና ነው" ወሬዬን ሳልጨርስ ዳር ዳርታዬ ገብቷታል መሰለኝ። "አይ ወንዴ.......ለካ አንተም እንደሌሎቹ ሸሌ ስትባል ምንም የምታውቅ አይመስልህም አይደል?.......አንድ ያልነገርኩህን ነገር ልንገርህ ማንበብና መፃፍ የቻልኩት እንዳንተ ትምህርት ቤት ሄጄ ሳይሆን እዚሁ ሸሌዎች እንደ ህፃን ፊደል እያስቆጠርኩኝ ነው የተማርኩት ከዛ በኋላም ማንበብ ስለቻልኩኝ ብርቅ ሆኖብኝ ፤ ቀን ቀን ፍሪ ስለሆንኩኝ ብዙ መፅሐፍትን አነብ ነበር። ከዛልህ ሳላስበው ማንበብ ሱስ ሆነብኝ! ያገኘሁትን መፅሀፍትን ሁሉ መብላት ጀመርኩኝ! ስለዚህ ከኔ የማትጠብቀውን ነገር ስትሰማ እየዘባረኩ እንዳይመስልህ" እያፈርኩኝ "እሺ" አልኳት። "እና ምን ላይ ነበርኩ? አዎ ያ መርፌ ያሚን ሽንት እንደሸተተው በግ እደገለፈጠ ደፍሯት ጨረሰና ይዟት ወጥቶ ብቻውን ተመልሶ መጣ። (የት አድርጓት ይሆን?) አምስታችንንም በቅድሚያ አልኮል በግዴታ አጠጣንና ፣ ጃንኪና (የመርፌውን ሀሽሽ) ወጋን። ጥቂት እየቆየ ሁሉም ነገር ቢዥ እያለብኝ መጣ። ጭንቅላቴ ቀለለኝ። አየር ላይ እየተንሳፈፍኩ ያለሁ መሰለኝ። ልክ እንደ መላዕክት ክንፍ አውጥቼ ሰባተኛው ሰማይ ድረስ እየበረርኩ ያለሁ መሰለኝ ሚጢጢዋ ልቤ ስር የደስታ ምንጮች ሲፍለቀለቁ ይሰማኛል ሙሉ ሰውነቴ የዛለ ቢሆንም መፍንደቀን መዝለል ያሰኘኝ መሰለኝ። ያ መርፌ ሰውዬ እኔን በመናወዝ ዓለም ውስጥ እንዳለሁ ፒኪኒዬንና ጡቴ ማስያዢያዬን አድርጎልኝ ካለሁበት ክፍል ይዞኝ ወጣ። ክለቡ ውስጥ ወዳለው ሁለተኛ ክፍል ይዞኝ ገባ። በብዥታ ውስጥ ብሆንም ጥቂት የናጠጡ ሀብታሞች ሁለትና ሶስት ታዳጊ ህፃናትን እንዳሰኛቸው..👇
إظهار الكل...
ስለ_ፈገግታ_ምን_የህል_ያውቃሉ ? 😂😂😁😁😅😅😝😝😄😄 በሚልዮኖች የማንሸጠው እና የማንለውጠው ለሰው ልጆች ብቻ ተፈጥሮ ያደለን #ፈገግታ የተሰኘችው ድንቅ የስሜቶች መግለጫ እንዳለን እያመንን ፣ አምነንም ለእናንተ ለማሳወቅ እነሆ የሚከተሉትን ሀሳቦችን ፅፈናል ። ከምንለብሳቸው ያማሩ ልብሶችና ከምናጌጥባቸው እጅግ ውድ ጌጣጌጦች በላይ ዘወትር በፊታችን ገፅ ላይ የምንላበሰው ፣ ከውስጥ የሚመነጨውን ስሜታችንን ፈንቅሎ ፣ መልካም መልካሙን ብቻ የሚያስተጋባ ፣ #ፈገግታ😁 የተባለ ድንቅ ጌጥ አለን ። እስኪ ይህንን ፅሑፍ እያነበቡ #ፈገግ ለማለት ይሞክሩ? ( ምን አዲስ ነገር አለው ታድያ? ) እንዳትሉ ። በእያንዳንዷ አዲስ #ፈገግታ ውስጥ ፤ አዲስ ያላስተዋልነው እና ያልተለመደ ፣ የውስጥ ስሜታችንን በቅፅበት እናስተውላለን ። ለዚህም ነው " ድርጊት ከቃላት በላይ ሁኔታዎችን በይበልጥ ይገልፃል " ተብሎ የሚታመነው ። ቃል ሳንተነፍስ ፣ #ፈገግታን ላልተረዷትም ሰዎች እንኳን ሳይቀር ። #ፈገግ በማለታችን ብቻ ብዙ መልካም ስሜትን የሚያስተጋቡ ቃላትን ብቻ ሳይሆን አረፍተነገሮችን እናስተላልፋለን ። ለምሳሌም ........... # ደስ_ትለኛለህ # ደስተኛ_ታደርገኛለህ # ስላየውህ_ደስታዬ_ጨመረ .... ወ.ዘ.ተ እናም እነዚህን የመሳሰሉትን ገላጭ ሀሳቦችን ልናስተጋባ እንችላለን ። ከሰው ልጆች ጋር ለብዙ ዘመናት በቤት እንስሳትነት አብረው የኖሩት #ውሾች እንኳን ሳይቀሩ ፣ ፈገግታችን ከደመ ነፍሳዊው አዕምሮአቸው ዘልቆ በፈንጠዝያ ሚሆኑትን አሳጥቷቸው ሲያርመሰምሳቸው አስተውለናል ። የህፃናትንም ፈገግታ ቢሆን ከዚህ የተለዩ ማስረጃዎችን ማቅረብ ለቀባሪው ማርዳት ይሆናል እንጂ ብዙ ማለት ይቻላል ። በአጠቃላይ #ፈገግታ ማለት ...... ምንም የማይከፈልበት ፣ ብዙ የምናተርፍበት የስሜት መገበያያ ሀብት ነው ። ለሰጪው የማይጎድልበት ለተቀባዩ ደግሞ የውስጥ ሰላሙ የሚበለፅግበት የማንዋሰው (የማናውሰው) አልያም ቆፍረን የማናወጣው የስሜቶች ድንቅ ማዕድን ነው ። ፈገግታን የማይረዳ የሰው ልጅ ቢኖርም ፣ ነገር ግን ያ ሰው ገና አልተፈጠረም (ሰው ሆኖ አልኖረም) ከውስጡ የሞላውን የስሜት ንብረት ለማንም መስጠት ከማይሹት ጭምት ሰዎች ዘንድ የፈገግታ ዋጋ እምብዛም ሲሆን ይስተዋላል። Share share share Join👇👇 @ye_fkr_zefen @ye_fkr_zefen
إظهار الكل...
ፍቅር ማለት በምቶደዉ ሰዉ ❤️ ልብ ላይ እራስህን መግደል ማለት ነዉ። ፍቅር 👍ስንፈልገዉ ብቻ ምናገኘዉ👎 ሳንፈልገዉ ሲቀር ደሞ ምንተወዉ አይደለም🙏 ፍቅር❤️ መታመን ነዉ። የምቶደዉ ሰዉ ደስታ😍 መደሰት ነዉ። የምናፈቅረዉ ሰዉ ስናገኝ መደሰት ነዉ። ፍቅር በገዘብ 💶 አይለካም⚖ እዉነተኛ ፍቅር❤️ለመናገር ቃላቱች ያጥሮሃል የፍቅር ደስታ 💑 ያስለቅሳል😂 ያፈቀርከዉን ከማጣት ሞት እረፍት ነዉ። ያፈቀርከዉ ስያኮርፍህ 😌ታለቅሳለህ😰ሲያስደስትህ ደሞ እብድ እስክትመስል እየሳክ😃 ትሮታለህ🏃 ፍቅር ካለህ ሁሉ ነገር አለህ። ፍቅር ከሌለህ ባዶ ነህ። Join👇👇 @ye_fkr_zefen @ye_fkr_zefen
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.