ar
Feedback
Summit (1-8) Campus Parents' Group

Summit (1-8) Campus Parents' Group

الذهاب إلى القناة على Telegram

This group is designed to disseminate information to the parents of Summit(1-8) Campus only. Thank You!

إظهار المزيد
1 059
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1330 أيام
أرشيف المشاركات
REGiSTRATION for 2017.docx1.51 KB

ለቪዥን አካዳሚ ወላጆች በቦሌ ክ/ከተማ በ2017ዓ.ም ተማሪ መመዝገብ የሚችሉ ትምህርት ቤቶችን ዝርዝር የክፍለ ከተማው ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባሣወቀው  መሠረት፣ በሁሉም በቦሌ ክ/ከተማ በሚገኙት፦ 👉 ቪዥን አካዳሚ ቅድመ አንደኛ ደረጃ 👉ቪዥን አካዳሚ የመጀመሪያ ደረጃ (1-6)፣ 👉 ቪዥን አካዳሚ መካከለኛ ደረጃ (ከ7-8)                         እና   👉ቪዥን አካዳሚ ሁለተኛ ደረጃ ምዝገባ ማካሄድና የት/ት አገልግሎት መስጠት መቻላችን በተረጋገጠው  መሠረት፣ የልጆቻችሁን  አስፈላጊውን  መረጃ በመያዝ ከሐምሌ 1 - ሐምሌ 15 /2016 ዓ.ም በስራ ሰዓት ዋናው ግቢ በመገኘት  ማሥመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡ የት/ቤቱ አስተዳደር!

ውድ ወላጆች 📌ተሸላሚ ተማሪዎች እና የተሸላሚ ተማሪ ወላጆች እሁድ ሰኔ 30/2016 ዓም ለሚኖረን ፕሮግራም ጠዋት 3:00 ሰዐት ላይ ሰሚት ግቢ እንድትገኙ በአክብሮት እንገልፃለን ፡፡ 📌ፕሮግራም የሚያቀርቡ ተማሪዎች ደግሞ 2:00ሰዐት እንዲገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ፡፡ 📌ለሁሉም ተማሪዎች ሪፖርት ካርድ የሚሰጠው ከ 5:00-8:00 ሰዐት ይሆናል፡፡ከተጠቀሰው ሰዐት ውጪ ለማስተናገድ የምንቸገር መሆኑን እንገልጻለን ፡፡ ት/ቤቱ

ለቪዥን አካዳሚ ከ 1-12 ወላጆች እሁድ፣ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም የት/ት ዘመኑ መዝጊያና የሪፖርት ካርድ መስጫ ቀን  መሆኑን እያሳወቅን፤ በዕለቱ ልጆቹ በሚማሩበት ግቢ  5:00-8:00 በመገኘት የልጅዎን ውጤት የሚገልጽ ሪፖርት ካርድ እንድትወስዱ የአክብሮት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ የት/ቤቱ አስተዳደር!

ውድ ወላጆች 📌ነገ ማክሰኞ ሰኔ ፣19 ፣2016 ዓም ተማሪዎች ት/ቤት የማይመጡ ሲሆን ሀሙስ ሰኔ ፣20 ፣2016 ዓም የ ፈተና ግብረመልስ የሚሰጥበት ዕለት ይሆናል፡፡ 📌በዕለቱ ተማሪዎች ለ ግማሽ ቀን የሚቆዩ ሲሆን ልጆችዎን ከ 5:30 ጀምሮ እንድትወስዱ እናሳስባለን ፡፡ 📌የፈተና እርማት(Correction) እስከ አርብ 6:00 ሰዐት ድረስ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ ት/ቤቱ

ውድ የቪዥን ወላጆች የተቋማችን የ4ኛ ሩብ ዓመት የትምህርት አገልግሎት ክፍያ  የፈፀማችሁትን ወላጆች እያመሰገንን ላልከፈላችሁት እንድትከፍሉ በድጋሚ ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡   ህብረት ባንክ አካውንት ቁጥር 11707163655770023 የት/ቤቱ አስተዳደር!

ውድ ወላጆች ነገ ማክሰኞ ሰኔ 18 2016 ዓም ተማሪዎች ለፈተና ወደ ትምህርት ቤት ሲመጡ የግንኙነት ደብተር(Communication book) ይዘው እንዲመጡ ያድርጉ፡፡ እናመሰግናለን

ውድ ወላጆች የ 2ኛ ሴሜስተር ማጠቃለያ ፈተና ሰኞ ሰኔ 17፣2016 ዓ.ም እና ማክሰኞ ሰኔ 18፣ 2016 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን ልጆቾን ከ5:30 ጀምሮ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡ ት/ቤቱ Dear Parents The second semester final exam will continue on Monday, June 24, 2024 GC and Tuesday, June 25, 2024 GC. We recommend picking up your children at 5:30 LT . The school

ውድ ወላጆች የ6ኛ ተማሪ ወላጆች 📌ነገ አርብ ሰኔ 14/2016 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና የሚጠናቅቁት 4:30 ላይ ስለሆነ ልጆቻችሁን በሰዐቱ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡ 📌ተማሪዎች ሙሉ ቀን ግቢ ውስጥ እንዲቆዩ አይፈቀድላቸውም ፡፡

ለቪዥን አካዳሚ ነባር ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ፡፡ ትምህርት ቢሮ ባወጣው የ2017 ዓ.ም የትምህርት ካሌንደር  የነባርና  አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ከሰኔ 28 እስከ ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የምዝገባና የመጽሀፍት ስርጭት  የሚደረግበት ጊዜ መሆኑን ባሣወቀን መሠረት   በቦሌ ክፍለ ከተማ   መብራት ኃይል በሚገኙት በሁሉም (ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ) ትምህርት ቤቶቻችን  የነባር ተማሪዎች ምዝገባ (በ2016 በሰሚት ቪዥን ይማሩ የነበሩትን ተማሪዎቻችንን ጨምሮ) ይካሄዳል። ስለሆነም አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እያሳሰብን፣  የአዲስ ተማሪዎችንም ምዝገባ በተመለከተ ከት/ት ቢሮ በተገለጸውና በሚኖረን ቦታ መሠረት   ወስነን ተገቢውን መረጃ እንደምናሥተላልፍና፣   አስፈላጊ የሆኑ ሌሎች  ጠቃሚ መረጃዎችንም በቴሌግራም ቻናላችን በየጊዜው የምንልክላችሁ መሆኑን አውቃችሁ እንድትከታተሉ በትሕትና እናሣሥባለን። ስለምንጊዜውም ትብብራችሁ እናመሠግናለን! የት/ቤቱ አሥተዳደር፣

📩ውድ የ 6ኛ ከፍል ተማሪዎች እና ወላጆች (ሰሚት ግቢ)📨 እንደምታውቁት ነገ ከረቡዕ ፣ ሰኔ 12 እስከ አርብ ፣ ሰኔ 14፣ 2016 ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል ፈተና የሚጥ ይሆናል። ከፈተናው ጋር በተያያዘ የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ ይበሉ። 📌 ተፈታኝ ተማሪዎች ጧት 1:20🕰 ቪዥን ግቢ መገኘት ይጠበቅባቸዋል። 📌 ተማሪዎች ምሳቸውን በሚማሩበት ግቢ በማስቀመጥ ወደ ፈተና ጣቢያ ት/ቤቱ ባዘጋጀው ትራንስፖርት የሚሄድ ሲሆን የጧቱን ፈተና ሲጨርሱ ት/ቤቱ ባዘጋጀው ትራንስፖርት ወደ ግቢ ተመልሰው ምሳቸዉን ይመገባሉ። 📌 በተመሳሳይ ሁኔታ ከምሳ በኋላ ት/ቤቱ ባዘጋጀው ትራንስፖርት ወደፈተና ጣቢያ የሚሄዱ ሲሆን ፈተናው እንደ ተጠናቀቀ ወደ ት/ቤት ይመለሳሉ። 📌 ተማሪዎች ገንዘብ እንድይዙ አይፈቀድላቸውም ❌❌❌❌ የተከለከለ ነው ፡፡ 📌ወላጆች ልጆችዎን ጧት 1:20 ት/ቤት በማድረስ ከሰዓት 9:15 ጀምሮ ከሚማሩበት ግቢ መውሰድ ይጠበቅባቸዋል። 🆔 ተማሪዎች የመግቢያ ካርዳቸውን (admission card) መያዝ ይጠበቅባቸዋል። ✅ ተማሪዎች ቢያንስ ሁለት እርሳሶች፣ ላጲስ እና መቅረጫ ይዘው መምጣት አለባቸው። ✅ የፀጉር አቆራረጥን ጨምሮ ንፁህ የደንብ ልብስ እና ትክክለኛ የአለባበስ ስርዓት ግዴታ ነው። ⚠️ ማርፈድ ተፈታኝ ተማሪዎች ላይ ያለዉን የሥነ ልቦና ጫና በመረዳት ልጆችዎን በተጠቀሰው ሰዓት ት/ቤት እንድታደርሱ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን።

📩ዉድ ወላጆች📨 ረቡዕ፣ ሰኔ 12፣ 2016 ለሚጀምረው የ2ኛ ሩብ ዓመት ፈተና ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ ሲሰጥ የነበረው የክለሳ ትምህርት  ነገ ሰኞ፣ ሰኔ 10፣ 2016 እና ማክሰኞ፣ ሰኔ 11፣ 2016 የሚቀጥል ሲሆን ልጆች ያልስሩት  (Worksheet) ካለ በተጠቀሱት ቀናት ፈተና ከመጀመሩ በፈት ጨርሰው እንዲያሰገቡ እንዲሁም ለፈተና ዝግጅት ይረዳቸው ዘንድ ተማሪዎች ከ ኤሌትሮኒክስ በመራቅ ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ እናሳስባለን። ስለ ምንጊዜም ትብብርዎ እናመሰግናለን 🙏 የት/ቤቱ አስተዳደር!

Full Day Monday June 17 2024
Full Day Monday June 17 2024

ውድ የ6ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች 📌ማክሰኞ ሰኔ 11/2016 ስለ ፈተና ገለፃ(orentation) የሚሰጥበት ዕለት ይሆናል ፡፡ 📌 የመፈተኛ ጣቢያ በሻሌ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ሲሆን አድራሻ ሰሚት ፍርድ ቤት ከሸዋ ሱፐር ማርኬት ጀርባ 📌 ተማሪዎች እስከ 2:30 ድረስ ቪዝን አካዳሚ መድረስ ይጠበቅባቸዋል፡፡ 📌 ገለፃው የሚሰጠው ለግማሽ ቀን ስለሆነ ወላጆች ልጆቻችሁን 5:30 ላይ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡ ማሳሰቢያ፡ ዝርዝር መረጃ በዚሁ ቻናል የምንለቅ ስለሚሆን ይከታተሉ፡፡

የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች 1.የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት
+1
የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች 1.የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ 2.በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ 3.ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ 4.ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ 5. በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ 6) ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ 7.ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ 8.መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ 9. ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ @Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library

📩ውድ የ6ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች📨 ከፈተና በፊት በት/ቢሮ የሚሰጠውን የኦሬንቴሽን ቀን የምናሳውቅ ሲሆን ከኦሬንቴሽን ቀን በስተቀር ተማሪዎች ወደ ት/ቤት መምጣት የማይጠበቅባቸው መሆኑን እየገለጽን፣ ቤት በሚሆኑበት ቀናት:- ✍ ከማንኛውም ዐይነት ኤሌክትሮኒክስ በመራቅ ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ። ✍ እስከአሁን በት/ቤት እና በ ት/ቢሮ ተዘጋጅቶ ሲስጥ የነበራዉን ሞዴል ፈተናዎችን ባላቸው ጊዜ ደግመው በመስራት ከጥያቄዎቹ ባሕርይ ጋር ራሳቸውን እንዲያለማምዱ፣ ወላጆች ቤት ዉስጥ ከወትሮ በተለየ መልኩ እንድትረዷቸው    ከአደራ ጭምር እያሳሰብን፣ ⚠️ ክሊራንስ ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ከወላጅ  ጋር በመምጣት ከፈተናዉ ቀን በፊት መጨረስ ይጠበቅባቸዋል። ስለ ምንጊዜውም ትብብርዎ እናመሠግናለን! የት/ቤቱ አስተዳደር!

photo content