Summit (1-8) Campus Parents' Group
الذهاب إلى القناة على Telegram
This group is designed to disseminate information to the parents of Summit(1-8) Campus only. Thank You!
إظهار المزيد1 059
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1330 أيام
أرشيف المشاركات
ለመላው የቪዥን አካዳሚ ወላጆች፣ተማሪዎችና መምህራን፦
በቅድሚያ የአክብሮት ሠላምታችንን እያቀረብን በ2016ዓ.ም ለዪኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ከወሰዱት 151 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ውስጥ 142(94%) በማሳለፍ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገብን በመሆናችን የተሰማንን ደስታ እየገለፅን እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን።
ውድ ወላጆች
ቀደም ሲል ባሳወቅናችሁ መሠረት ትምህርት ቢሮ ባወጣው የተማሪ ምዝገባ መረሃ ግብር ከሐምሌ 1-15/11/2016 ዓ.ም ምዝገባ ሲደረግ የቆየ ሲሆን ያልተመዘገቡ ነባር ተማሪዎች በመኖራቸው ምዝገባውን አራዝመን ተማሪዎች ስንመዘግብ ቆይተናል።
የመጨረሻው የምዝገባ ቀን ሐምሌ 30/11/2016ዓ.ም መሆኑን እያሳወቅን ከዚህ ቀን ውጪ ለሚመጡ ወላጆች ት/ቤቱ ሀላፊነት የማይወስድ መሆኑን እናስገነዝባለን።
የት/ቤቱ አስተዳደር!
ውድ ወላጆች
የመጀ/ደረጃና መካከለኛ ደረጃ (ከ1ኛ -8ኛ) ክፍል የ2017ዓ.ም የተማሪዎች መማሪያ መፅሐፍት ዝግጁ ሥለሆኑ የከፈላችሁም ሆነ ያልከፈላችሁ ወደ ተቋሙ በመምጣት በክፍያ ደረሰኝ መሠረት ከነገ ሐምሌ 16/2016ዓ.ም ዋናው ግቢ እንድትረከቡ እናሳስባለን፡፡
Dear Parents
Congratulations!
All of our Grade 6 students have passed the ministry exam with outstanding result.
100%
የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
(ሀምሌ 13/2016 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ውጤቱ ዙሪያ ውይይት በማድረግ የማለፊያ ነጥቡን ወስነዋል።
በዚሁ መሰረት የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና የማለፊያ ነጥብ 50 ሲሆን ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ደግሞ 45 እንዲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በሙሉ ድምጽ አጽድቀዋል።
የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ተግባር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በመግለፅ ውጤቱ ታርም ቶሎ እንዲደርስ ቀንና ሌሊት በመስራት ለዚህ ቀን ላደረሱ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ክፍል ባለሙያዎች ምስጋና አቅርበዋል።
በ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 85,046 በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች በቀን እና በማታ ትምህርታቸውን ከተከታተሉ ተማሪዎች መካከል 94.3% ያህሉ 50% እና በላይ ማምጣታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ አስታውቀዋል።
Dear Parents
Congratulations!
All of our Grade 8 students have passed the ministry exam with outstanding result.
100%
ለቪዝን አካዳሚ ወላጆች!
ቀደም ሲል ባሳወቅነውና ትምሕርት ቢሮ ባወጣው መርሀ-ግብር መሠረት የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 1 ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የነባር ተማሪዎችን ምዝገባ የምናጠናቅቅበት የመጨረሻው ቀን ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ምዝገባ እንድታካሂዱ ከወዲሁ እናሥታውሳለን።
የት/ቤት አስተዳደር!
በ2017 ለ6ኛና 8ኛክፍል ተማሪዎችና ወላጆች
ከዚህ በፊት እንደተገለፀው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ሰኞ ሐምሌ 08 2016 ዓ.ም.ስለሚጀመር ሁሉም የ6ኛ ና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገው በእለቱ እንዲገኙ እናሳስባለን።
👉ተማሪዎች የት/ቤቱን የደንብ ልብስ እንዲለብሱ ይጠበቃል።
👉ትምህርቱ የሚሰጠው በግማሽ ቀን መርሀ ግብር መሆኑን እንገልፃለን።
📌6ኛ ክፍል ተማሪዎች በ በአዲሱ የቪዥን ካምፓስ የሚሰጥ ሲሆን የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ደግሞ በዋናው ግቢ ሚሰጥ ይሆናል ፡፡
📌ሌሎች የክፍል ደረጃ ያሉ ተማሪዎችን የክረምት ትት እንዲከታተሉ እናበረታታለን ፡፡
Dear Parents
Congratulations!
All of our Grade 8 students have passed the ministry exam with outstanding result.
100%
የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
(ሀምሌ 5/2016 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ውጤቱ ዙሪያ ውይይት በማድረግ የማለፊያ ነጥቡን ይፋ አድርገዋል።
በዚሁ መሰረት የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና የማለፊያ ነጥብ 50 ሲሆን ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ደግሞ 45 እንዲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በሙሉ ድምጽ አጽድቀዋል።
የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ተግባር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ገልጸው በቀጣይ ጥቂት ቀናት የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት በተመሳሳይ ይፋ የሚደረግ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 85,219 በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች በቀን እና በማታ ትምህርታቸውን ከተከታተሉ ተማሪዎች መካከል 67,903 የሚሆኑት ማለትም 78.9% ያህሉ 50% እና በላይ ማምጣታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ አስታውቀዋል።
ተማሪዎች ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን መለያ ቁጥርና ስም በማስገባት ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ፡፡
https://aa.ministry.et/account#/student-result
