ከፍቅር ደጅ 💕💞
@ke_feker_deje_©በዚ group: ~#የተለያዩ የህይወት ገጠመኝ እና ታሪኮች፤ ~#የፍቅር ግጥሞችና ደብዳቤዎች፤ ~#የታዋቂ ሰዎች ምርጥ ንግግርና ፍልስፍና፤ ~#የፍቅር ገጠመኞች ~ #ሀገርኛ ጉዳዮች፤ ~ #ስለ ጤና እና ቴክኖሎጂ መረጃ፤ ~#በ ሃገርኛ እና ኢንተርናሽናል ቋንቋዎች፤ ~Amharic,English, Afan Oromo,Tigregna
إظهار المزيد623
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-17 أيام
+330 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
አንዳንዴ ምን ሆነሀል ስትባል የማትመልሰው ብዙ መሆን አለ። ለመናገር የማይመች ለመተው የማይቀል ብዙ ስሜት አለ ..ለአንተ የከበደ ለሌላው የቀለለ ነገር አለ ።
💡እንዴ ይሄ እኮ ቀላል ነው ይሄ እኮ አያስጨንቅም በሚባል ቃል የሚሸነፍ ለአንተ/አንቺ ግን የከበደ ስሜት አለ ።
ምን ሆነሀል ስትባል ምንም ብለክ የምታልፈው ውስጥህ ብቻ የምታንሸራሽረው እያዳመጥክ የምትታመምበት ። ከባድ ስሜት አለ ከባድ.......
❤️ምናልባት የምትፈልገው ስፍራ ላይ አልተቀመጥክ ወይንም የምትመኘውን ነገር አላገኘህ ይሆናል፣ ቢሆንም ተስፋ አትቁረጥ ፣ ተስፋ የመኖር ምክንያት ነውና፣
እየኖርን ነው አይደል? በሰው ሳይሆን በፈጣሪ!!
ትላንት የኖርነው ህይወት በነበር ይተካል፣
ሰዎችም ኖረው ነበሩ ይባላሉ፣
ፈጣሪን ግን ነበር ብለን አናወራውም ፤ ያለና የሚኖር ፣ በዛሬያችን ,በነጋችን አልፎም በዘላለም ውስጥ ኗሪ ነው ።
" የትላንት ነበሮቻችን በእሱ መኖር ተረስተዋል"
እናም ወዳጄ
አትድከም ፣ አትዘን ። ማንያውቃል ሸክምህ ህመምህ ሁሉ ተራግፎ ሌላ ሰው ሆነህ ትነሳ ይሆናል። ያለን ፈጣሪ እንኳን በአንድ ሙሉ ቀንና ሌሊት፣ በቅጽበት ጊዜ ዉስጥም ብዙ ተዓምር ይሠራል።
💡ንፋስ የማይወዘዉዘው ዛፍ የለም። ችግር ፣ ፈተና ፣ ሀሳብ ወስዶ የማይመልሰው ሰዉም የለም። እንዲህም ሆኖ የማይወድቅ ዛፍ አለ። በፈተና የሚፀና የሚበረታ ሰዉም አለ። ዐሳብህ ጉልበትህ ሥሮችህ ታክቶዋቸው በደከሙ ጊዜ ልብህ ብቻ ፈጣሪን ይዞ ይበርታ።
ውብ ምሽት❤️
@natani273
ከባዱ ፀፀት!
የህይወት የመጨረሻ ምዕራፍ ፀፀት እና የእድሜ ልክ ፀፀት!
ስዎች በእድሜያቸው መጨረጫ ላይ ወደኃላ ዞር ብለው ሲመለከቱ አጅግ የሚጸጸቱባቸው፥ መጽናናት ፈጽሞ የማይችሉበት ስህተቶች አሉና በህይወት ዘመን ጉዞ ላይ እጅግ ጥንቃቄ ያስፈልጋል ወንድሜ!
በስቃይና በለቅሶ ወደ መቃበር መውረድ ፈጽሞ አይሁንልህ።
ይህ ከፍተኛ የጸጸት ህይወት በህይወት ዘመን ለሚገጥሙህ ምርጫዎችና ውሳኔዎች ከምትመልሰው አርምጃ ይጀምራል።
ሰዎች በህይወታቸው ዘመን መጨረሻ የሚጸጸቱበት ነገር ዋነኞቹ:
👉ያላመኑትን ነገሩ እያደረጉ መኖር፥
👉የተሳሳተ የትደር አጋር ምርጫ ፥
👉 የተመኙት ህልም አለመኖር፥
👉በልባቸው ያመኑትን ህይወት ለዋጭ እርምጃ ምንም አደጋ እያለ አለመውሰድ፥
👉አላማ መሪ ህይወት አለመኖር
👉እየፈሩ መኖር ከፈለጉት ህይወት ወደኅላ መቅረት...የመሳሰሉት ናቸው።
አንተ ግን ስለጉዞህ ጥንቃቄ አድርግ ወንድሜ !
አመሰግናለሁ ስለሰማሄኝ!!
@natani273
🩷❤️🧡 የምናማርረው የተሰጠንንና የሆነልንን ’ረስተን ፣ ያልጎደለን ነገር ላይ "ጎደለን" ብለን በጥያቄ ስለምንሞላ ነው ፣ ባለው ነገር አመስጋኝ የሆነ ይጨመርለታል ። በማማረር መባረክ የለም ። ሰላምና ጤና ፣ ከመልካም አስተሳሰብና በጎ ህሊና ጋር ምንጊዜም ከዘመንህ አይለዪ።
ውብ ቀንን ተመኘሁ ❤️
@natani273
#አንድ_ቀን_ታረጃለህ!
በወጣትነትህ ሽማግሌውን አክብር
ጠንካራ ስትሆን ደካሞችን እርዳ
ሰዎች ሲሳሳቱ አታሳቃቸው
ምክንያቱም አንድ ቀን በህይወት ታረጃለህ፣
ደካማ ትሆናለህ፣ ትሳሳታለህም!!! @natani273
አንድ ሰው ሲሞት መቃብሩ ላይ ሄዳችሁ
ምን ያህል እንደምትወዱት አትንገሩት
ምክንያቱም እነዚህን ቃላቶች መስማት
የሚፈልገው በህይወት እያለ ነበር!🥺
የምትወዱትን ሰው በህይወት እያለ
እንደምትወዱት ንገሩት!❤️
ለእኔም ንገሩኝ🙄🤗😂
@natani273
እንኳን ለጌታችንና ለመድኅኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሳኤ በሰላም አደረሳችሁ።
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤
አሰሮ ለሰይጣን፤
አግዐዞ ለአዳም፤
ሠላም፤
እምይዕዜሰ፤
ኮነ፤
ፍስሐ ወሰላም፡፡
መልካም የትንሣኤ በዓል!🙏
@natani273
አንተ_ሰው-ሆይ
👉በሐብት ብትንበሸበሽ
👉መልክህ የተፈለቀቀ ፅጌረዳ ቢመስል
👉አለምን የሚገዛ ስልጣን ቢኖርህ
👉በልጆችና በዘመድ አዝማድ ብትከበብ
👉በእውቀትህ አለምን ብታበራ
🗣መጀመሪያ ፈራሽ ገላ መያዝክን መጨረሻክን
🗣40 ክንድ መሬት ላይ እንደምትገባ አትርሳ...
🗣እናም ወዳጄ በኩራት፣ ሰዎችን በመናቅና በመኮፈስ ከኔ ሌላ ማን አለ አትበል"!
ልትኮራ የሚገባው በሃያሉ ፈጣሪ በልዑል እግዚአብሔር ብቻና ብቻ ነው።
@natani273
"........የሰው ልጅ ዘመኑ ሁሉ መጠኑና ስፋቱ ቢለያይም፤ ራሱ በሰራው አልያም ሌሎች ሰዎች ባጠሩለት እስር ቤት ይኖራል፡፡ እንደ ራሱ አሳብና አመለካከት ግን ትልቅ እስር ቤት የሚኾንበት አንዳች ነገር የለም፡፡ ለካስ እስር ቤት ቦታ ሳይሆን አስተሳሰብ ነው፡፡ በዚች ምድር እጅግ ብዙ ሰው በአእምሮ እስር ቤት ውስጥ በአሉታዊ አስተሳሰብ ታስሮ በከንቱ እንቶ ፈንቶ ፍርሃት ተይዞ ማንም እንዳይረዳው ኾኖ የእስር ቤት ቁልፋን ራሱ ደብቆ ይኖራል፡፡
☑️ ምንጭ፦ሜሎሪና
ሰላም ጤናና ፍቅር፣
ከመልካም አስተሳሰብና በጎ ህሊና ጋር ምን ጊዜም ከዘመንህ አይለይ፡፡
🕊 መልካም ውሎ🕊
👇👇👇👇👇👇👇👇
☑️@natani273
☑️@natani273
👇👇👇👇👇👇👇👇
☑️@natani273 bot
አንዳንድ ጊዜ ዝም አይነቅዝም!
#በዝምታህ_አሸንፋቸው!
አንድ ሰው እየተጣላህ ከሆነ፥ በጸጥታ ተቀምጠህ አስተውለው። በምንም መንገድ ምላሽ አትስጠው።
ዝምታ ቁልፍ ነው!
የሆነ ትወና እየተመለከትክ እንደሆነ አስብ። እንዲህ ዓይነቱ ገጠመኝ እውነተኛ ማንነታቸውን ለማጋለጥ ጥሩ አጋጣሚ ነው።
@natani273
#አንድ_ቀን_ታረጃለህ!
በወጣትነትህ ሽማግሌውን አክብር
ጠንካራ ስትሆን ደካሞችን እርዳ
ሰዎች ሲሳሳቱ አታሳቃቸው
ምክንያቱም አንድ ቀን በህይወት ታረጃለህ፣
ደካማ ትሆናለህ፣ ትሳሳታለህም!!!
@natani273