2 056
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
#ታላቅ _ #መንፈሳዊ_#የአዳር #ጉዞ _ወደ _ደብረ ብስራት #አቡነ ዜና #ማርቆስ አንድነት #ገዳም
ገዳሙ የኢትዮጵያዊ ጻድቅ የአቡነ ዜና ማርቆስ የተጋድሎ ስፍራ ሲሆን ታላቁ ጻድቅ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖትም በገዳሙ የጸለዩበ ተጨማሪም በዚህ ገዳም ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራት ዛሬም ድረስ ያሉ የተከናወነበት ቅዱስ ስፍራ ነው፡፡ ይህን ለማረጋገጥ ደግሞ ገዳሙን በማየት ብቻ መረዳት ይቻላል፡፡ ከምናያቸው በገዳሙ ከተከናወኑት ድንቅ ድንቅ ተአምራት መካከል ጥቂቶችን እንኳ ብንመለከት ገዳሙን ለማየት እንናፍቃለን ፣ ገዳሙንም ለመርገጥና የቃል ኪዳኑ ተጠቃሚ ለመሆን እንጓጓለን ፡፡
በገዳሙ ከተከናወኑት ተአምራት መካከል ፡-
+++ የዛፎችና የድንጋዮች ምስክርነት +++
✝• ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክለሃይማኖት ከአገልግሎት በኋላ ከደብረ ብስራት ገዳም ተለይተው ሲሄዱና አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስን ተሰናብተው ጉዞ ሲጀምሩ ዛፎችና ትልልቅ ድንጋዮች አቡነ ተክለሃይማኖትን ተከትለዋቸው ፡፡ በዚህ ጊዜ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ‹‹ ወንድሜ ዜና ማርቆስን ትታችሁ እኔን አትከተሉኝ ›› በማለታቸው ዛፎቹ አዝመው ቀሩ ፡ አሁን ድረስ እነዚህ ግዑዛን ፍጥረቶች ምስክርነታቸውን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
+++ ስጋ የለበሰውን አጋንት ጻድቅ መሆኑ +++
✝• ሁለቱ ቅዱሳን ማለትም አቡነ ተክለሃይማኖትና አቡነ ዜና ማርቆስ ጼዋ ለጽድቅ የተባለውን ስጋ ለበስ አጋንት አጥምቀው አስተምረው ጻድቅ አድርገውታል፡፡
+++ ጻድቁን የተማጸኑ ሁሉ የልቡናው መሻት መፈጸም +++
✝• የመቃብር አፈራቸው ሙታንን ማስነሳት፣ ዐይነ-ስውራንን ዐይናቸውን ማብራት፣ ከልዩ ልዩ ደዌ የተፈወሱ እነዚህና የመሳሰሉት ድንቅ ድንቅ ተአምራት በገዳሙ ተፈጽመዋል፡፡
+++ በአንድ አይሁዳዊ ሰው ላይ የተደረገ ድንቅ ተአምር +++
✝• በደብረ ብስራት ገዳም የምትገኘውን የእመቤታችን ስዕል ( ስዕለ ማርያምን ) የአባ ጽጌ ድንግል ጓደኛ የነበረ ስዕለ ማርያምን በበትር መታት በዚህ ጊዜ ይህ አይሁዳዊ ወድያውኑ ሞተ ምድርም ተሰጥቃ ዋጠችው፡፡ እነዚህና መሰል ድንቅ ድንቅ ተአምራት የተፈጸመባት ቅድስት ስፍራ ደብረ ብስራት አቡነ ዜና ማርቆስ አንድነት ገዳምን በቦታው ተገኝቶ የቃል ኪዳኑ ተጠቃሚ መሆን ከእኛ ይጠበቃል፡፡
✝ ማህሌተ ጽጌም የተደረሰው በዚህ ድንቅ ገዳም ነው
✝ ሌላው ድንቅ ነገር በዚህ ገዳም ውስጥ የሚገኘው አጣብቂኝ ዋሻ ነው ይህም ዋሻ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ በጸሎት የሰነጠቁት ዋሻ ነው ይህም ዋሻ ግፍ እና በደል የሰራ ሊያልፍበት የማይችል በድፍረትም ለማለፍ ቢሞከር አጣብቆ የሚይዝ ካህንም መጥቶ ሀጥያቱን ካልተናዘዘ የማይለቅ ተአምረኛ ዋሻ ነው
+++ ለጻድቁ አቡነ ዜና ማርቆስ የተሰጠ ቃል ኪዳን +++
ጻድቁ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ የክርስቶስን መከራ መስቀል ተሸክመው በብዙ ተጋድሎ ከኖሩ በኋላ በ ፻፵ ዓመታቸው አረፉ፡፤ ብዙም ቃል ኪዳን ከልዑል እግዚአብሔር ተቀበሉ፡፡ ከተቀበሉት ቃል ኪዳን መካከል ፡-
፩• ደጅህን ለረገጠ ስምህንም የጠራ እስከ 160 ፣ 140 ፣ 100 ፣80 የንስሃ ዘመን እሰጠዋለሁ፣
፪• በገዳምህ በደብረ ብስራት የእናቴ ስዕል ባለበት የእናቴን ስም ጠርቶ ጸሎት ያደረገ የገሃነም እሳት አያገኘውም ፣
መላው ኢትዮጵያን ሰማያዊት ኢየሩሳሌም አደርግልሃለሁ
፫ ° የጸበሌ ፍንጣቂ የነካው ወንድ ልጅ የ40ቀን ልጅ ፥ሴት ልጅ የ80ቀን ልጅ አድርጋቸዋለሁ፣
፬° ቦታየን የረገጠ የሰራውን ሁሉ ሀጢያት ይቅር እለዋለሁ።
በማለት ጌታችን ለአባታችን ለአቡነ ዜና ማርቆስ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፤
ይህን ገዳም ተሳልመን ፡ የጻድቁን የአቡነ ዜና ማርቆስን ተጋድሎና ቃል ኪዳን እናጣጥም ዘንድ ኑ ብለናል
ሌላው በእለተ #ህዳር 11 እናታችን ቅድስት ሀና ስለምትነግስ እዛው አንግሰን በበረከት ተሞልተን እንመለሳለን
የጉዞ ዋጋ:-#550 መስተንግዶን ጨምሮ
የጉዞ ቀን:- #ህዳር 10 ተነስተን ከንግስ ቡሀላ በ11 እንመለሳለን
ጉዞው ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ከስር ባሉት ስልኮች አሳውቁን ያሉን ቦታዎች ውስን ናቸው
#ዳንኤል : 0910324822
#አስቻለው : 0975369402
የጻድቁ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ በረከትና ቃል ኪዳን ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
Watch "Ethiopia ዘማሪ አስቻለው ተስፋዬ new Ethiopian Orthodox Mezmur 2022" on YouTube
https://youtu.be/azlT5j8zAEY
Ethiopia ዘማሪ አስቻለው ተስፋዬ new Ethiopian Orthodox Mezmur 2022
#Lebelet mereja @Enate0
Weyim beslk kutr 0921172563
0920525586
0940035297
اختر خطة مختلفة
تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.