ar
Feedback
የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.

إظهار المزيد
447
المشتركون
+224 ساعات
+87 أيام
+3030 أيام
أرشيف المشاركات
#ጆሮ_ፍለጋ👂 የሚያወራው ብዙ ስለሆነ የሚሰማው ጥቂት ነው። ከሚያወሩት ይልቅ የሚሰሙት ይፈለጋሉ። ብዙዎች ወደ እኛ የሚመጡትና የልባቸውን ጭንቀት የሚያካፍሉን ጆሮ ፈልገው እንጂ ምክር ፈልገው አይደለም። እርግጥ ነው ሁሉም ሰው "ጆሮ ብቻ" አይደለም የሚፈልገው። ምክራችንንና ሀሳባችንን የሚፈልጉም ይኖራሉ፤ ነገር ግን ጥቂቶች ናቸው። በተለይ አገልጋዮች መንጋውን የመስማት አገልግሎት ሊኖራቸው ይገባል። ሊያናግሩ የሚመጡት ሁሉ የግድ የእኛን ምክር የሚፈልጉ አይደሉም። በሀሳባቸውና በውጣ ውረዳቸው ሳንፈርድባቸው ብንሰማቸው፣ ፍቅር ሰጥተን እንደተረዳናቸው እንዲያውቁ ብናቅፋቸው ይሄ ብቻውን የሚፈውሳቸው ብዙ ናቸው። አገልጋይ ስለሆንን ብቻ ጥቂት ሰምተን ብዙ መስበክ አያስፈልገንም። እንስማ ፣ እንረዳ፣ ፍቅር እናሳይ፣ በበራ ፊት እንቀበላቸው፣ እንሸኛቸውም። የጆሮ ያለህ የሚል አንድም ወዳጅ አይኑረን። የሚሰማን ያጣንም፣ እኛ ያጣነውን ያን "አዳማጩን ሰው" እንሁን። እኛ በምናልፍበት ሌላው አይለፍ። እኛ ያጣነውን ሌላው አይጣ። “ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን፤”— ያዕቆብ 1፥19 በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 28-07-2016 የጌታ ዓመት ✍

የፀሎት ሃይል .pdf6.24 MB

#አሉ_ነገር_ግን_የሉም ሰዎች ነን። ውስንነት የባሕርይ ገንዘባችን ነው። ውስንነታችን ግን ስለማንችል ብቻ የሚፈጠር ሳይሆን አለመቻልን ስለምንመርጥም ጭምር የሚፈጠርም ነው። ያልጠበቅናቸው ደርሰውልን፤ ወዳጆች ያልናቸው ደርሰውብን ተደንቀናል።በሕይወታችን አንዱ ይመጣል፣ ሌላኛው ይሄዳል። ቋሚና ዘላቂ ወዳጅነት ፋሽኑ ያለፈበት ይመስላል። ጓደኝነት ትርጉሙን አጥቷል። መተማመን ጠፍቷል። ሸንጋይ ፍቅር ተንሰራፍቷል። አሁን ላይ ሰዎቻችን የምንላቸው፦ 🤷‍♂ ሠርጋችን ላይ አሉ፤ ትዳራችን ላይ የሉም 🤷‍♂ ኑሮአችን ላይ የሉም፤ ቀብራችን ላይ አሉ 🤷‍♂ ልካችን ላይ የሉም፤ ስሕተታችን ላይ አሉ 🤷‍♂ በሰላማችን ጊዜ አሉ፤ የሆነ ነገር ስንሆን የሉም 🤷‍♂ ስንበረታ አሉ፤ ስንደክም የሉም 🤷‍♂ ውጤታችን ላይ አሉ፤ መንገዱ ላይ አልነበሩም 🤷‍♂ ስንችል አሉ፤ ሲያቅተን የሉም 👉 ካለን እንኑር። ከኖርን እናኑር። ወዳጅ ሆነን ወዳጅ እናትርፍ። ለሰው ሰው እንሁን። የተጎዳ በዛ። የጎዳም ኃላፊነት አልወስድ አለ። ፈውስ ዘገየ። ይቅርታም ሽንፈት ሆነ። ስሕተትንም ማመን አዋራጅ ሆነብን። 🤝ወዳጅነትም ተሐድሶ ያሻዋል። ጓደኝነትም ወደ ቦታው ይመለስ።🤝 በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 22-07-2016 የጌታ ዓመት ✍

#ጥያቄ፦ በሃይማኖት ሀሳብ የተለያዩ ያም የኔ፤ ይህም የኔ ነው እውነቱ እያሉ በወሬና በጥቅስ ብዛት ልቤን ሲያስቸግሩብኝ ምን ማድረግ ይሻለኛል? #መልስ፦ ሰዎች የጌታቸውን መልክ በሩቅ ሆነው ሲመለከቱ
#ጥያቄ፦ በሃይማኖት ሀሳብ የተለያዩ ያም የኔ፤ ይህም የኔ ነው እውነቱ እያሉ በወሬና በጥቅስ ብዛት ልቤን ሲያስቸግሩብኝ ምን ማድረግ ይሻለኛል? #መልስ፦ ሰዎች የጌታቸውን መልክ በሩቅ ሆነው ሲመለከቱ አንዱ "እንዲህ ያለ ነው" ሁለተኛው "አይ እንዲህ ያለ ነው" ብለው ባንድ ሰው መልክ ላይ ቢከራከሩ፤ ጌትነቱን አምነው፣ ሥልጣኑን ፈርተው ከተገዙለት ጌትየው ከነሱ ላይ የሚፈልግባቸው የጌትነቱን መጠንና የትእዛዙን መፈጸም ብቻ ነው እንጂ በመልኩ ቅርጽ ላይ የሚከራከሩት ግን ርቀው በሚመለከቱበት በየዐይናቸው ብርሃን መጠን በሚያዩት የመሰላቸውን ብቻ የሚያወሩ ስለሆነ አላዋቆች ሕፃናት እንደሚጫወቱበት ቃል እያደረገ፤ ንግግራቸውን እየናቀ ያልፈዋል እንጂ የሚከራከሩበት ምክንያት ለኵራት ካልኾነ በውነት ለልባቸው ለእግዚአብሔር ክብር የሚኾን እየመሰላቸው የሚነጋገሩበትን ማየት የማይችሉትን መልኩን ማወቅ የማይችሉትን ጠባዩን ካላወቁ ብሎ አይፈርድባቸውም። ይህንም ልትረዳ ብትሻ ሀልዎቱን የሚያምኑ ክርስቲያኖች ሁሉ ምንም እርስ በእርሳቸው መናፍቅ እየተባባሉ ቢነቃቀፉ ሁሉም በያዙት ሃይማኖት በእግዚአብሔር ስም እየጸለዩ ተአምራትን ለመሥራት የሚችሉ መሆናቸውን አስተውል(ጣ፡ ጸ፡ ም፡ ፮) (ልዑል ራስ ካሣ ኃይሉ/ ፎኖተ አእምሮ፥ ገጽ. 15-16)

የታዋቂነት በረከትና እዳ አንዳንድ ጊዜ እንኳን ታዋቂ አልሆንኩ እላለሁ። እዳው ብዙ ነው። ነጻነት ሲያጡ፣ ትንሹ ስሕተታቸው ትልቅ ሲሆን፥ የት ገቡ? ማንን አገቡ? ለምን አገቡ? ምን ገዙ? ምን ለበሱ? የት ሄዱ? ከማን ጋር ታዩ? እየተባሉ ክትትል ሲበዛባቸው ሳይ "ተመስገን፥ አለመታወቅ ነጻነት ነው" እላለሁ። ነጻነት በምንና በስንት ዋጋ ይተመናል? ወዲ ደግሞ የታዋቂ ሰው በረከት ስትቆጥር… አንተ ስለ ኢየሱስ፣ ሕይወት ስለሚገኝበት ጠቃሚ ነገር ፖስተህ 20 like ከቅርብ ሰዎችህ ታገኛለህ… ታዋቂው ሰው ግን Hi Guys ብሎ ብቻ እንኳን ቢፖስት ስንትና ስንት ምናምን k like 😅 የአሽቃባጩ ብዛትስ ብትል። ቢታመም አዋጥተው አድናቂዎቹ ያሳክሙታል…ስትናገር ተሰሚ ነህ…ብዙ ብዙ የታዋቂነትን ጥቅሞችን መዘርዘር ይቻላል ታዋቂ ልሆን ነው መሰል… የታዋቂነት ትርፍና ኪሳራው እያሳሰበኝ ነው…… በነገራችን ላይ ይሄን የፖሰትኩት ለእናንተ ለሃያዎቹ ታማኝ ጓደኞቼ ነው… እንዳታሳፍሩኝ like አርጉ 😅

እረኛዬ.m4a47.35 MB

በፈተና ዋስትና.m4a28.55 MB

#መቅደም_ሲያቅት_መጥለፍ በወንጌላዊ ክርስትና ውስጥ አሁናዊ በሆነው የአገልግሎት መንገድ ሁለት ተግዳሮቶች አሉ።የመጀመሪያው ከእኛ የተሻለ አቅም ያለው ሰው ቢመጣ ምንቃወምበት ክፉና ቅናተኛ ልብ ፤ የ
#መቅደም_ሲያቅት_መጥለፍ በወንጌላዊ ክርስትና ውስጥ አሁናዊ በሆነው የአገልግሎት መንገድ ሁለት ተግዳሮቶች አሉ።የመጀመሪያው ከእኛ የተሻለ አቅም ያለው ሰው ቢመጣ ምንቃወምበት ክፉና ቅናተኛ ልብ ፤ የተሳሳተ ሰው ሲገጥመን ደግሞ የምናርምበት የተሳሳተ መንገድ ነው።ሁለቱም ፈውስ ያስፈልጋቸዋል።ወንድምን መቀበል ራስን ከመቀበል ነው የሚጀምረውና እንደተሰጠን የጸጋ ስጦታ መጠን በፍቅር እንድናገለግል፤ የተሳሳተን ሰው የምናርምበት ስሕተታችን እንዲታረም ከረጅም ዓመታት የአገልግሎት ልምድ ካላቸው ጉምቱ ጸሐፊና አሳቢ ከሆኑት ከዶክተር መለሰ ወጉ የቀረበልን ምክርና የመፍትሔ አሳብ። አገልጋዮችንና አገልግሎትን የምትወዱ ቅዱሳን፤ እንዲሁም አገልጋዮች በእጃችሁ ልታስገቡት የሚገባ ድንቅ መጽሐፍ፦ "መቅደም ሲያቅት መጥለፍ" በዶክተር መለሰ ወጉ መጽሐፉን የምትፈልጉ ልታናግሩኝ ትችላላችሁ🙏