Addis Ababa City Manager Office
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 474
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-2130 أيام
أرشيف المشاركات
መዲናችን አዲስ አበባ ፅዱ፣ብርሃን የነገሰባትና ከአደጋ ስጋት የተጠበቀች እንድትሆን በከተማው ስራ አስኪያጅ ጽ/ ቤት እና በተጠሪ ተቋማቱ በሩብ አመቱ የተከናወኑ አበረታች ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ም/ቤት የመሠረተ ልማትና የማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካ አስገነዘቡ።
የምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር ግዛቸው አይካ የስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት የሩብ አመት የእቅድ አፈፃፀም በዛሬው እለት በተገመገመበት ወቅት እንደተናገሩት በፅ/ቤቱና በተጠሪ ተቋሟቱ መዲናችን አዲስ አበባ በፅዳቷ ያሳየችው እምርታዊ ለዉጥ በማጠናከር ረገድ ፣ዉበቷን በይበልጥ ያደመቀዉ የመብራት መሠረተ ልማት ዝርጋታ እና የአደጋ ስጋት ቀነሳ ስራዎቿ ከሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጋር ተቀናጅቶ ዉጤታማ አፈፃፀም እንደተመዘገበባቸዉ ገልፀዋል። እነዚህ ተግባራትም ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም አስምረውበታል።
የተከበሩ ዶ/ር ግዛቸዉ አይካ በመሩት በዚህ የግምገማ መድረክ ላይ የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤትንና የተጠሪ ተቋማት የ2018 በጀት አመት የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥናትና ልማት ትግበራ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ አቅርበዋል።
በሪፖርቱም በበጀት አመቱ ሩብ ዓመት የተከናወኑ የ90 ቀናት የልዩ ንቅናቄ እቅድ አፈፃፀም፣ የዝግጅት ምእራፍ ስራዎች፣ የጳጉሜ ቀናት፣የየአዲስ አመትና የመስከረም ወር የአደባባይ ህዝባዊና ሃይማኖታዊ በአላት አከባበር ፣የመልካም አስተዳደር እና የብልሹ አሰራርን ከመከላከል፣የበጎ ፈቃድና የኢንሼቲቭ ፣የቅንጅታዊና ፣የድጋፍና ክትትል ስራዎችና ሌሎች አፈፃፀሞችም ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።
በዚሁ ወቅት የተከበሩ ዶ/ር ግዛቸው አይካ የስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት መዲናችን በፅዳቷ ህዝብ የሚመሰከርላትና ንፅህናዋ በሚገባ የተጠበቀ፣ ብርሃናማ፣ ከአደጋ ስጋት የተጠበቀች እንድትሆን እና እንዲሁም የነዋሪዎች የማንነት አስተዳደር ስርአት (Identity management system) የተጠናከረ እንዲሆን በማድረግ ረገድ በበጀት አመቱ የመጀመሪያ ሩብ አመት የተከናወኑ ተግባራት አመርቂ የሚባል አፈፃፀም የተመዘገበበት እንደሆነ ገልፀዋል።
አያይዘውም በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት እየተሰጡ ያሉ አገልግሎቶች የከተማችንን ነዋሪዎች አዳጊ ፍላጎት የሚያረካ እንዲሆን በማድረግ ረገድ የአገልግሎት አሰጣጡን ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ፍትሃዊ ለማድረግ እየተተገበሩ ያሉ አሰራሮችን ከማጎልበት ጎን ለጎን ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን እና መልካም አስተዳደርን የማጠናከር ጉዳይ አሁንም በልዩ ትኩረት ተጠናክሮ ሊፈፀም እንደሚገባውም አስገንዝበዋል።
"ቀን ብቻ የምትሰራ ከተማ ሳትሆን አዲሰ አበባ በምሸትም የምትሰራ ከተማም የማድረግ ሥራ ለውጥ እያስመዘገበ ነው"ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ከጥቅምት 8-9/2018 ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የ1ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ሪፓርት ግምገማ እና ውይይት ተጠናቋል።
በዝግጀት ይባክን የነበረ ጊዜን ወደ ተግባር በመቀየር፣ በሩብ ዓመቱ የህዝብ ጥያቄን ሞላሽ መስጠት የሚያስችሉ ሥራዎች መፈፀም መቻሉን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልፀዋል።
ፈጠራ እና ፍጥነት ለተመዘገቡ ስኬቶች መሰረት መሆናቸውን የገለፁት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የኑሮ ጫናን ማቃላል ፣ የገበያ ቁጥጥር ማድረግ እና አማራጭ ምርት እንዲቀርቡ ተደርጓል።
በተጨማም አገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል ፥ በአረንጓዴ ልማት ፣ በፅዳትና ጐርፍ መከላከልን ትኩረት ተደርጐ በመሠራቱ ውጤት ተመዝግቧል ።
በእውቀት የታነፀ ትውልድ ለመንንበት በ ትምህርት ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን የተናገሩት ከንቲባ አዳነች፣ ቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
ወጣቶች በአእምሮም በአካልም ብቁ እንዲሆኑ ፣ ህፃናት ቦርቀውና ተጫውተው እንዲያድጉ ፣ ታለንታቸዉን አወእጥተው እንዲያሳዩና እንዲያሳድጉ የሚያስችሉ መጫወቻ ስፍራ እና መሰልጠኛ የስፓርት ማዘውተሪያዎች ተገንብተዋል።
የሴቶችን ማህበራዊ ተጋላጭነት ለመቅረፍም በነገዋ የክህሎትና ስብዕና መገንቢያ ማዕከል ሴቶችን በማስልጠን ወደ ሥራ ማስገባት ተችሏል። አሁንም ተጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል።
አዲሰ አበባ ቀን ብቻ የምትሰራ ከተማ ሳትሆን፣ በምሸትም የምትሰራ ከተማ የማድረግ ሥራ ለውጥ እያስመዘገበ ነው ።
አገልግሎት አስጣጥን ለማሻሻል ውጤታማ የሆነ ሥራዎች የተሰሩ ቢሆንም፣ አሁንም አመራሩ ይበልጡን ትኩረት ሰጥቶ ኃላፊነት ወስዶ ሊሰራ እንደሚገባ አመልክተዋል።
በተቋም መካከል የአፈፃፀም ልዩነቶች በዋናነት የሚፈጠሩት ከአመራር ብቃት እና ስንፍና ጋር የሚያያዙ በመሆኑ ለተሻለ ለውጥ ያለ እረፋት 24/7 የሚሰራ ፥ አገልጋይ አመራር መሆን እንደሚገባም አሳስበዋል ።
በከተማችን የመሰረተ ልማት ጥያቄ አዳጊ ትክክለኛ መሆኑን የገለፁት ከንቲባ አዳናች አቤቤ በቀጣይም አጠቃላይ ሥራዎቻችን በቅደም ተከተል በእቅድ የሚመሩ ይሆናል ብለዋል ።
በቀጣይም የከተማችንን ሠላም ከህዝባችን ጋር ማረጋገጥ ፥ የቤት አቅርበትን ማሳደግ፥ አገልግሎትን ለማሻሻል መሶብ የእንድ ማዕከል ዲጅታል አግልግሎት መገንባትና በሰዉ ሃይልና በቴክኖሎጂ ብቁ ማድረግ ፥ የኑሮ ውድነትን ማቃላል የሚያስችሉ ሥራዎችን ትኩረት ሰጥቶ መስራት ፥ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር፥ ገቢ የመሰብሰብ አቅም ማሳደግ ፥ አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች ማጠናከር፥ የትራንስፖርት ሰርዓቱን ማዘመን ፣ በኮሪደር የለሙ መሰረተ ልማቶች ህዝብ እንዲጠቀምባቸው በአግባቡ ማስተዳደር የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አመላክተዋል።
‘የሶፍ ኡመር ወግ’ ዛሬ ምሽት 2:30 ይጠብቁ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የቀድሞ እና በሥራ ላይ ካሉ አመራሮች ጋር ያደረጉት ውይይት።
#PMOEthiopia
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ዛሬ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ስራ ለማከናወን ሲባል በአዲስ አበባ እና ሸገር ሲቲ ሀይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :-
👉ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 አያት ፈረስ ቤት ፣ አበበች ጎበና መታሰቢያ ሆስፒታል ፣ አያት ጨፌ፣ 49 ማዞሪያ ፣ ገመናይ ማርያም፣መቄዶኒ፣ አበበች ጎበና ሆስፒታል፣ አያት ፀበል ቁፅር -1 ኮንደዶሚኒየም ፣ አየር መንገድ መኖሪያ ቤቶች በከፊል፣ለገጣፎ፣ ሲዲሲ ፣ ኮሰሮ፣የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም፣
👉ከጠዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 9:30 አኔ ዲማ፣ ወጣቢቻ፣ ጉዱ፣ ሙሎ፣ ከሚሴ፣ ቡራዩ መስጊድ አካባቢ ፣ ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ፣ ፀርሐ ፅዮን ቤ/ክ አካባቢ፣ ቡራዩ ወለጋ ሰፈር፣ ድሬ ከአስፋልት በታች፣ ጉዳ፣ ኬላ፣ ጉዮ፣ ታጠቅ ኢንዱስትሪ መንደር በከፊል ፣ቶልቻ፣ድሬ ከአስፋልትበላይ፣ ገፈርሳ ውሀ ግድብ እና አካባቢው፣ ሲሊ፣ ከረላ፣ መናገሻ እና አካባቢያቸው ላይ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ Ethiopian Electric Utility -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ስለሆነም አገልግሎቱ "በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለንም" ብሏል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
የሶፍ ኡመር ወግ’ ዛሬ ምሽት 2:30 ይጠብቁ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የቀድሞ እና በሥራ ላይ ካሉ አመራሮች ጋር ያደረጉት ውይይት።
#PMOEthiopia
