ar
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 474
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-2130 أيام
أرشيف المشاركات
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ ቤት የጥቅም ወር የስራ እንቅስቃሴን ያካተተውን የዜና መፅሄት በቀጣዩ ሊንክ በቴሌግራም ገፃችን ይከታተሉ። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.e
የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ ቤት የጥቅም ወር የስራ እንቅስቃሴን ያካተተውን የዜና መፅሄት በቀጣዩ ሊንክ በቴሌግራም ገፃችን ይከታተሉ። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በመዲናችን አዲስ አበባ ብሎኮችና ወረዳዎችን ፅዱ;- ውብ:- ማራኪ ለነዋሪዎች ምቹና ሁሉንም አይነት መሠረተ ልማት የተሟሉላቸው ሞዴል ብሎኮችና ወረዳዎች በማድረግ ረገድ ባለፉት 90 ቀናት ህብረተሰቡን በማሳተፍ አየተከናወነ ያለው አበረታች… See more

ባለፉት 3 ዓመታት በሐሰተኛ መረጃ ለመገልገል በሞከሩ 188 ተገልጋዮችና የአሠራር ጥሰት በፈጸሙ 589 ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ። ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ የሚደረገው ጥረት በአዳዲስ ቴክኖሎጂ ተደግፎ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ኤጀንሲው አስታውቋል። በኤጀንሲው የተሟላ ሪፎርም ካደረገባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ የቴክኖሎጂ አሠራርን ማስፋት መሆኑም ተመላክቷል ። በአሁኑ ወቅት በኤጀንሲው የተሻለ የቴክኖሎጅ አገልግሎት እየበለጸገ መሆኑን ኤጀንሲው ገልጾ ይህም በተለይም ወረዳ ላይ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ማዕከል ላይ ሆኖ ማየት የሚያስችል የተሻለ የቴክኖሎጂዎች ሲስተም እየበለፀገ እንደሆነና በቅርቡም ወደ ሥራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነም ተጠቁሟል። በኤጀንሲው ከብልሹ አሠራር ጋር በተያያዘ እየተወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ በማስቀጠል ረገድም ከ2015 - 2017 ባሉት 3 ዓመታት በሐሰተኛ መረጃ ለመገልገል በሞከሩ 188 ተገልጋዮችና በአሠራር ጥሰት ደግሞ 589 ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደተወሰደ በኤጀንሲው የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አስናቀች ሙህዬ ገልጸው በ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመትም በ17 ባለሙያ እና አንድ ባለጉዳይ ላይ የተለያየ እርምጃ መወሰዱንና በሕግ ሂደት ላይ የሚገኝ እንዳለም አመልክተዋል ። አክለውም ብልሹ አሠራርን በመከላከልና መቆጣጠር ሂደት የቴክኖሎጂ ሚና የጎላ መሆኑን እና ለአብነትም ድርጊቱ በየዓመቱ እየቀነሰ እንዲሄድ ማስቻሉን ተናግረዋል። በኤጀንሲው የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተሯ ተገልጋዮች በኤጀንሲው ትክክለኛ መረጃና ማስረጃ አቅርበው አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ አስገንዝበው፤ ሕገ ወጥ አሠራር ሲያጋጥምም በ7533 ነጻ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

አንጋፋው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ላዺሶ ጌ. ዴሌቦ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ማለፋቸውን በታላቅ ኀዘን ሰማሁ። ነፍሳቸውን በዐጸደ ገነት እንዲያኖርልን እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንዲሰጥልን እመኛለሁ።

በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ለተከታታይ 11 ቀናት ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና ክቡር የፓርቲያችን ፕሬዚዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በሰጡት ማጠቃለያ እና የስራ መመሪያ ዛሬ ተጠናቅቋል ። ክቡር የፓርቲያችን ፕሬዝዳንት የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልፅግና በአጭር ጊዜ ለማረጋገጥ ፣ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን ይበልጡን ለማስፋት እና ለማላቅ ፣ የሕዝባችንን ሁለንተናዊ የመልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ስራዎችን በፈጠራ እና ፍጥነት መርህ በማብዛት መከወን እንደሚገባ አንስተዋል ። እንዲሁም በቀጣይ የአመራሩን ትኩረት የሚሹ ግቦችን ጭምር በየፈርጁ በመለየት አቅጣጫ የተቀመጡ ሲሆን አመራሩም በከፍተኛ መነሳሳት ለመፈፀም ቃል ገብቷል ። ይህ በአዳማ ከተማ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና ከትላንት በስተያ በኦሮምያ እንዲሁም በትላንትናዉ እለት በመዲናችን በአዲስ አበባ በፓርቲያችን እሳቤ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በመጎብኘት እና ልምድ የመለዋወጥ መርሃ ግብር ጭምር የተካሄደ ነበር ። በመስክ ጉብኝታችን ያገኘናቸው በርካታ ስኬቶች በምናብ ከፍታ፣ በአመራር ትጋትና በህዝባችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ የኢትዮጵያ ብልጽግና አይቀሬነት ማሳያ መሰረቶች ናቸዉ ። የተገኙ ዉጤቶች እንደተጠበቁ ሆነዉ ገና አዳዲስ ግኝቶችን እንፈጥራለን! እንፈጥናለን! የኢትዮጵያ ብልጽግና እናረጋግጣለን!!! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! "Ilaalcha Mootummaa Ida'amuutiin Guddina Dameewwanii"! Mata duree jedhuun leenjiin guyyoota walitti aanan 11f hooggantoota olaanoo Paartii Badhaadhinaaf kennamaa ture cuunfaa fi adeemsa hojii kabajamoo pireezidaantii Paartii keenyaa fi Ministira Muummee Dr.Abiy Ahimad kennaniin xumurameera. Kabajamoo pireezidaantiin paartii keenyaa Badhaadhina hundagaleessa biyya keenyaa yeroo gabaabaa keessatti mirkaneessuuf hojiiwwan misooma dam-daneessaa hojjetamaa jiran daran babal'isuu fi ol guddisuuf gaafiiwwan uummataa dam-daneessaan misoomuu deebisuuf hojiiwwan qajeelfama kalaqaa fi ariitiitiin baay'isuun raawwatamuu akka qabaatu kaasaniiru. Akkasumas fuulduratti galmawwan xiyyeeffannoo hooggansaa barbaadan dabalatee ramaddiidhaan adda baahuun kallattiiin kan kaa'ame yemmuu ta'u hooggansis kaka'uumsa olaanaan raawwachuuf waada seeneera. Leenjiin dhimmoota adda addaa irratti magaalaa Adaamaatti laatamaa ture kuni guyyaa dheengadda Oromiyaatti, akkasumas guyyaa kaleessaa Finfinneetti yaada paartii keenyaatiin hojiiwaan misoomaa adda addaa hojjetaman daaw'achuun fi sirni muuxannoo wal jijjiiruus kan itti gaggeeffame ture. Daaw'annaa keenyaan kan arganne milkaa'inoonni hedduun abjuu guddaan,cimina hooggansaa fi hirmaanna hundagaleessa uummata keenyaan Badhaadhinni Itoophiyaa kan hin oolle ta'uu bu'uurota mul'isaniidha. Milkaa'inoonni argaman akkuma eegamanitti ta'ee fuulduratti waan haaraa baay'ee ni uumna. Ni saffisna. Badhaadhina Itoophiyaa ni dhugoomsina.!!! Waaqni Itoophiyaa Fi Uummata Ishee Haa Eebbisu!

የአመራሩ ቁርጠኝነት፣ በፈጠራ፣ በፍጥነትና በጥራት መስራት ለሁለንተናዊ ብልፅግና መረጋገጥ አስፈላጊ እንደሆነ የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ገለፁ "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ከፌደራል፣ ከክልል፣ ከዞን እንዲሁም ከከተማ አስተዳደሮች ለተወጣጡ ከፍተኛ አመራሮች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለተከታታይ 11 ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል። የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) በመደመር መንግሥት ላይ የማጠቃለያ ስልጠና ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) በማጠቃለያ ስልጠና ላይ እንደገለፁት የአመራሩ ቁርጠኝነት፣ በፈጠራ፣ በፍጥነትና በጥራት መስራት ለሁለንተናዊ ብልፅግና መረጋገጥ አስፈላጊ ነው። በስልጠናው የመደመር መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ፣ መንገድና መዳረሻ ግቦቹ የተዳሰሱ ሲሆን በዚህም በመደመር መንግሥት መርህ የሚመራው ፓርቲያችን አመራሮች በፈጠራ በፍጥነት በብዛት ስራዎችን በማከናወን የህዝባችን ሁለንተናዊ ጥያቄ ከመመለስ በላይ የሀገራችን ራዕይ ለማሳካትና ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በሚረዳ መንገድ መምራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትኩረት የሚሹ ግቦችን በየፈርጁ በመለየት አቅጣጫ ያስቀመጡ ሲሆን ፋይዳ፣ 5 ሚሊዮን ኮደሮች፣ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች፣ የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች፣ የምርጫ ምቹነትና የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም አጀንዳዎች በ100 ፕርሰንት ለማሳካት መትጋት የሚገባን ግቦች ናቸው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) በማጠቃለያ ገለጻ እንዳብራሩት መደመር ትውልድን ወደ ብልፅግና የሚያደርስ መንገድ ነው። የመደመር መንግሥት ለሀገር ብልፅግና ባለአደራ መሆኑንም ተናግረው በፈጠራና በፍጥነት ጥራትና ብዛትን እውን ማድረግ ይገባል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለው እንዳብራሩት በብዝሀ ዘርፍ ትስስር ወደ ስልጣኔ ሽግግር ማምጣት ይገባል። የሀሳብ ሉዐላዊነት የብልፅግና መሰረት እንደሆነ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ሁሉም የፓርቲው አመራር በዚህ አግባብ በመትጋት ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ አለበት ብለዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ባለፉት 11 ቀናት በስልጠና በውይይትና በመስክ ጉብኝትና በማጠቃለያው ገለጻ ያገኟቸውን እውቀትና ልምዶች በዕቅድ በማካተትና ወደ ስራ በመቀየር የሀገራችን ሁለንተናዊ ብልፅግና እውን ለማድረግ በሚደረግ ጥረት ውስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። #prosperity

ኤሌክትሪክ እንዳይቋረጥና ሲቋረጥም ፈጣን መረጃ የሚሰጥ "ስካዳ" የተሰኘ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ሊተገበር ነው ኤሌክትሪክ እንዳይቋረጥና ሲቋረጥም ፈጣን መረጃ በመስጠት የሃይል ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችል "ስካዳ" የተሰኘ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመተግበር እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለጸ፡፡ የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አንዋር አብራር ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት የዜጎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻልና የኢንዱስትሪ ልማትን በማስፋፋት ለኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ ነው፡፡ የለውጡ መንግስት አዳዲስ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማትንና ብዝኃ የሀይል ማመንጫዎችን በማስፋፋትና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ፍትሐዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ ያረጁ የኤሌክትሪክ መስመሮችን መልሶ በመገንባት እንዲሁም በአዲስ በመተካት የትራንስፎርመሮችን አቅም በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነቱን ከዚህ በላይ ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ የአራት ሺህ ትራንስፎርመሮችን አቅም ማሳደግና ከ625 ኪሎ ሜትር በላይ ያረጁ መስመሮችንና ፖሎችን በአዲስ መቀየራቸውን ጠቅሰው፤ በክልሎችም ተመሳሳይ ሥራ በማከናወን የሀገሪቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽፋን 54 በመቶ ማድረስ እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመትም ለ800ሺህ ደንበኞች ቆጣሪ ለማሰራጨት እቅድ መያዙንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ አገልግሎቱ የዜጎችን ፍትሐዊ የሀይል ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ጭምር እየተጠቀመ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ በዚህም አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ማሳደግ የሚያስችል ዘመኑን የዋጀ "ስካዳ" የተሰኘ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ለመማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ "ስካዳ" በየትኛውም ቦታ የኤሌክትሪክ ሃይል ሲቋረጥና ከመቋረጡ በፊት ቢሮ ውስጥ ሆኖ መቆጣጠር የሚያስችል ቴክኖሎጂ መሆኑን ገልጸው፤ የትኛው መስመር የትኛው ቦታ ላይ እንደተበላሸ ለማወቅ ያግዛል ብለዋል፡፡ ቴክኖሎጂው የኤሌክትሪክ ሃይል እንዳይቆራረጥ ቀድሞ መረጃ በመስጠት ደንበኞች ከመደወላቸው በፊት ፈጣን ምላሽ መስጠት እንደሚያስችልም ገልጸዋል፡፡ ጥቅምት 30 /2018 #Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ለብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና የፓርቲው ፕሬዚዳንት እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሰጡት የስራ መመሪያ ተጠናቀቀ ለብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና የፓርቲው ፕሬዚዳንት እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሰጡት የስራ መመሪያ ተጠናቋል። የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋናው ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አደም ፋራህ እንዳስታወቁት "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ከጥቅምት 19 እስከ 30 በአዳማ ከተማ እና በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሰጡት የስራ መመሪያ ዛሬ በስኬት ፍፃሜውን አግኝቷል ብለዋል። ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ ወደ 2000 የሚጠጉ የፓርቲያችን አመራሮች የተሳተፉበትና የአስተሳሰብ አንድነት ከመፍጠርና የተግባር አፈፃፀምን ከማላቅ አኳያ እጅግ ከፍተኛ ፋይዳ በተገኘበት በዚህ ስልጠና ፓርቲያችን እውነተኛ የህብረ ብሔራዊነት ተምሳሌት መሆኑም በተጨባጭ የተንፀባረቀበት ነበር ሲሉም ገልጸዋል። ይህ የስልጠና መርሀ ግብር ከዝግጅት እስከ ገለፃ፣ የቡድን ውይይት፣ ተሞክሮ ልውውጥ፣ የልማት ሥራዎች የመስክ ጉብኝት እና ማጠቃለያ ድረስ ዓላማውን በሚገባ አሳክቶ እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታችሁን ለተወጣችሁ አስተባባሪዎች፣ አሰልጣኞች፣ አወያዮች፣ የፀጥታ ተቋማት፣ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና ልዩ ልዩ ተቋማቱ፣ የአዳማ ከተማ አስተዳደር፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የስልጠናው ተሳታፊ አመራሮች በሙሉ ላበረከታችሁት ከፍተኛ አስተዋፅዖ በብልፅግና ፓርቲ ስም ልባዊ ምስጋና ለማቅረብ እወዳለሁ ብለዋል አቶ አደም ፋራህ በመልዕክታቸው።

መፍጠር እና መፍጠን - በአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ… See more

አዲስ አበባ ለኑሮ፣ ለስራ እና ለጉብኝት ምቹ ከተማ እየሆነች ነዉ :- አቶ ኦርዲን በድሪ በብልጽግና እሳቤ እና በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የብልጽግና እሳቤዎች በአዲስ አበባ በተጨባጭ እየታዩ መሆኑን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገልጸዋል፡፡ በተለይም ከኮሪደር ልማት አኳያ አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ እና የብልጽግና ተምሳሌት እናደርጋለን የሚለው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳብ በአዲሰ አበባ በተጨባጭ መተግበሩን አይተናል ብለዋል፡፡ ከዚህ በፊት አዲስ አበባ ላይ በቂ መሰረተ ልማት አልነበረም፣ የመኖሪያ ቤቶች በጣም የተጎሳቆሉ፣ ለኑሮ የማይመቹ፣ ለሰው ልጅ ክብር የማይመጥኑ እንዲሁም ከፍተኛ ጥግግት ያላቸው እንደነበሩ አስታውሰዋል፡፡ አሁን ላይ ግን ያ ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ ተቀይሮ ማየት መቻላቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ለኑሮ፣ ለስራ እና ለጉብኝትም ምቹ ከተማ እየሆነች መምጣቷን ነው ያመላከቱት፡፡ ከመሠረተ ልማትም አንፃር በከተማዋ በርካታ የመሠረተ ልማት ስራዎች በአስደናቂ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡

Addis Ababa City Manager Office - إحصائيات وتحليلات قناة تيليجرام @aacitymanager