Addis Ababa City Manager Office
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 474
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-2130 أيام
أرشيف المشاركات
ከጃፓኖች የንጽህና አጠባበቅ ምን እንማራለን?
አዲስ አበባን እንደ ቶክዮ!...
"ማነው ትምህርት ቤቱን ማጽዳት ያለበት? ራሱ ያቆሸሸው!". አንድ ጃፓናዊ ተማሪ “አንዳንድ ጊዜ ትምህርት ቤቴን ማጽዳት አልፈልግም ነበር፤ ነገር ግን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን አካል ስለሆነ ተቀበልኩት። ትምህርት ቤቴን ማጽዳት በጣም ጥሩ ነገር ነው ብዬ አስባለሁ ምክንያቱም የምንጠቀመውን ነገሮች እና ቦታዎችን የማጽዳት ሃላፊነት ልንወስድ አስፈላጊ መሆኑን እንደሚገባን ስለምንማር ነው."
"ተማሪዎቹ ከሰባት የ50 ደቂቃ ክፍለ ጊዜ የረዥም ቀን ቆይታ በኋላ ወደ ቤታቸው ለመመለስ ጓጉተው በመማሪያ ክፍሎቻቸው ወንበርና ጠረጴዛዎቻቸው ላይ ተቀምጠዋል።
ተማሪዎቹ መምህራቸው ስለ ነገው የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ ጥቂት መርሐግብሮችን ሲናገር በትዕግስት አያዳመጡ ናቸው.... ከዚያም ቀጠለና መምህሩ አስከትሎ የዛሬው የጽዳት መርሐግብራችን :-አለና
“እሺ ሁላችሁም ተማሪዎች ፣
የዛሬውን የጽዳት መርሐግብር ዝርዝር ቀጥሎ እኖደሚከተለው እገልፃለሁ አለ....
" አንደኛ እና ሁለተኛ ረድፍ የተቀመጣችሁ ተማሪዎች:-
የመማሪያ ክፍላችሁን ታጸዳላችሁ። ሶስተኛ እና አራተኛ ረድፍ የተቀመጣችሁ "ኮሪደሩ እና ደረጃዎች"ን በማለት ቀጠለ አምስተኛ ረድፍ ላይ የተቀመጣችሁ መጸዳጃ ቤቱን ታጸዳላችሁ....
ከአምስተኛው ረድፍ ጥቂት ጩኸቶች ከመሰማታቸው በስተቀር ሁሉም ህጻናት ተማሪዎች ተነሥተው ከክፍል ጀርባ ካለው ቁም ሳጥን ውስጥ መጥረጊያዎቹን፣ ጨርቆችን እና ባልዲዎችን ያዙና ወደ መጸዳጃ ቤት ሄዱ።
ተመሳሳይ ትዕይንቶች በመላው ጃፓን በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የዘወትር የእለት ተእለት ተግባር ነው።
በዚህ መንገድ በጃፓን በፅዳት ላይ በህፃናት ላይ በተሰራው ስራና መላው የጃፓን ህዝብ ጽዳትን ባህል በማድረጉም ለመጀመሪያ ጊዜ ጃፓንን የጎብኘ ሁሉ በአገሪቷ ጽዳትና ንጽህና ይማርካሉ ይላሉ የቢቢሲ ዘጋቢዎች ስቲብ ጆን እና አንጀልስ ማሪን ካቤሎ።
የጃፓን ተማሪዎች “ለ12 ዓመታት የትምህርት ቤት ሕይወት ከአንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጽዳት የሁልጊዜ የተማሪዎች የዕለት ተዕለት መርሃ ግብር አካል ነው” ። በቤታቸው የተማሪዎች ወላጆች የመኖሪያ ክፍላቸውን እና እቃዎቻቸውን ንፁህ አለማድረግ መጥፎ እንደሆነ ለልጆቻቸው ያስተምሯቸዋል።" ይላሉ ዘጋቢዎቹ
የጽዳትና የንጽህና ጉዳይ በትምህርት ቤት ሥርዓተ-ትምህርት ውስጥ በማካተቱ ልጆቹ ስለ አካባቢያቸው ንጽህና ግንዛቤ እንዲያዳብሩ እና እንዲኮሩ ይረዳቸዋል።
በጃፓን ጎዳናዎች ላይ ቆሻሻ አይታይም የመንገድ ጠራጊዎች እንዲሁ አይታዩም። ለምን ጃፓናውያን በሙሉ እራሳቸውን ከጽዳት ጋር በማለማመድ ጽዳትና ንፅህናን ባህላቸው ሰላደረጉ።
በአዲስ አበባም በመላው የመጀመሪያና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሁልጊዜ በየሳምንቱ አርብ የጽዳት ንቅናቄ ይካሄዳል። በዚህ ንቅናቄ ህጻናት የትምህርት ቤት ግቢያቸውንና መማሪያ ክፍላቸውን ራሳቸው ያጸዳሉ። ይህም ከልጅነታቸው ከጽዳት ጋር እንዲላመዱ በማደረረግ ጽዳትን በማህበረሰቡ ዘንድ ባህል እንዲያደርግ ለሚደረገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ጽዳትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰበ እንፍጠር!
ብሎክን ማዕከል ያደረገ ሳምንታዊ የበጋ ወራት የጽዳት ንቅናቄ በወረዳ 13 ተካሄደ።
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ብሎክን ማዕከል ያደረገ ሳምንታዊ የበጋ ወራት የጽዳት ንቅናቄ በወረዳ 13 ተካሂዷል ።
በመርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ታከለ ደሲሳ፣የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ፋኪሀ ሸሪፍ፣የኃይማኖት አባቶች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣የጽዳት አምባሳደር አርቲስቶች፣የወረዳና የክፍለ ከተማ አመራሮች እና ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ታከለ ደሲሳ መልዕክት ሲያስተላልፉ እንደጠቆሙት አከባቢን በጋራ ማጽዳት ፍቅርን፣አንድነትንና በጋራ መስራትን ያጎለብታል በማለትገልጸዋል።
በተያያዘም በክፍለ ከተማው አከባቢን በጋራ ማጽዳት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረና እየጎለበት ነው በማለት ቆሻሻን ምን ግዜም በአይነት በመለየት መያዝና ማስወገድ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የክፍለ ከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ፋኪሃ ሸሪፍ እንደገለጹት ቆሻሻን በየቀኑ እንደምናመነጨው ሁሉ ሁልጊዜ በተገቢው መንገድ ማስወገድ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ኃላፊዋ አያይዘውም ሁሉም አከባቢውን እና ብሎኩን በማጽዳት ውብ፣ጽዱና ለነዋሪዎቿ ተስማሚ፣እንደስሟ አበባ የሆነች ከተማ እየተፈጠረ ባለው ተግባር ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት በማለት ወ/ሮ ፋኪሃ ሸሪፍ አሳስበዋል።
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በየነ ቱሉ የጽዳት ስራ ከግለሰብ እና ሰፈር በአግባቡ ማጽዳትና ቆሻሻ ሀብት መሆኑን በመረዳት በተገቢው መንገድ መያዝና ማስወገድ ይገባል በማለት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
አዲስ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ በፍጥነት እና በጥራት መሃል ፒያሳ ላይ የገነባውን ባለ 11 ወለል ዘመናዊ ህንፃ በዛሬው እለት መርቀን ስራ አስጀምረናል ።
ከተማችን ጀምሮ የመጨረስ እና ቃልን በተግባር የመፈፀም ማሳያ በመሆኗ በየሳምንቱ አዳዲስ የነዋሪውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤቶችን እያበሰርን ነው።
አዲስ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ የከተማዋ ወጣቶችና ሴቶች የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እያደረገ ያለ፤ በተተኪ ምርት ፣ የውጭ ምንዛሪ ሊያስገኙ የሚችሉ ምርቶችን ማምረት ፣ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ሽግግርን እያስፋፋ ያለ አማራጭ የፋይናንስ አገልግሎት ነው።
አዲስ የተገነባው ህንፃ ለባንክ፣ ለኢንሹራንስ እና ለቢሮ አገልግሎት ምቹ ሆኖ የተገነባ ሲሆን፤ የህፃናት ማቆያ፣ የአካል ማጎልበቻና ካፍቴሪዎችን ጨምሮ ለሰራተኞች ምቹ የስራ ከባቢ እንዲሆን ተደርጎ ተገንብቷል ።
ለውጤታማነቱ የለፋ የቦርድ አባላት፣ የማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች ፣ ኮንትራክተር እና አማካሪውን በድጋሚ እንኳን ደስ ያላችሁ፤ ደስ አለን ለማለት እወዳለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ከለውጡ ማግስት ጀምሮ መዲናችን አዲስ አበባን ፅዱ፣ ውብና ለኑሮ ተስማሚ ምቹ ከተማ በማድረግ ረገድ ስኬታማ ስራ ተሰርቷል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ደሲሳ አስገነዘቡ።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ደሲሳ ይህን ያስገነዘቡት በዛሬው እለት በልደታ ክ/ከተማ የህዳር ወር የፅዳት መርሐግብር አካል የሆነ የጽዳት ንቅናቄን በክ/ከተማው ወረዳ 10 በተለምዶ
"ቢርሞ ሜዳ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባስጀመሩበት ወቅት ነው ።
አቶ ገዛኸኝ አክለውም ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ለመፍጠር የቤት ለቤት ግንዛቤ ማስጨበጥ ስራም በስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተው በዚህም ውብ ፅዱና ለኑሮ ተስማሚ ከተማን በመፍጠር ረገድ አበረታች ውጤቶች እየተገኙ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ማህበረሰቡ ውብና ፅዱ ከተማ ለመፍጠር ፅዳትን ከግቢው መጀመር አለበት ያሉት አቶ ገዛኸኝ ማህበረሰቡ ከፅዳት ባለፈ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓቱንም እንዲያሻሽል ጥሪ አቅርበዋል።
በጽዳት ንቅናቄው ላይ የልደታ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሰፋ ቶላ ባስተላለፉት መልእክት ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ለመፍጠርና ከተማችን የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን ለማድረግ እየተሰራ ባለው ስራ አስደማሚ ውጤቶችን አስመዝግበናል ሲሉ አመልክተዋል።
ስማርት ሲቲን ለመገንባት የተያዘው ስራ እንዲሳካ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓታችንን የማዘመን ስራ እየተሰራ መሆኑንም አቶ አሰፋ ገልፀዋል።
የልደታ ክ/ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ያየህ ዓለም እንደተናገሩት ንፁህ አካባቢን ለመፍጠር በትኩረት እየሰራን ነው ብለው በዚህም ቆሻሻን የሚፀየፍ ትውልድ እየገነባን ነው በማለት ገልፀዋል።
ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ትውልድ ለመፍጠር በትምህርት ተቋማትም የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ያየህ ገልፀዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 5ኛ ዓመት 5ኛ መደበኛ ስብሰባ፣ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ዉሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡ በዚህ መሰረት፦
1ኛ. የሁሉንም ስፓርት መሰረተ ልማቶችን ለከተማዉ ነዋሪ ተደራሽ ለማድረግ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራ አነስተኛ ክፍያ ተመን እና በነፃ መጠቀም የሚቻልበት አሰራር ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል::
2ኛ. የጤና ተቋማት የሥራ አማካሪ ቦርድ ማቋቋሚያ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳተላልፏል፡፡
3ኛ.በመንግስት እና የግል አጋርነት (PPP) የሚተዳዳሩ ሆስፒታሎች የቦርድ የውስጥ አሰራር ደንብ ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል፡፡
4ኛ. ሃገራዊ ፋይዳ ላላቸው ፕሮጀክቶች የቀረበ የመሬት ምደባ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ላለፉት ተከታታይ ቀናት በመዲናችን አዲስ አበባ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ውጤታማ በሆነ መንገድ ተጠናቅቋል።
የስልጠናው መሪ ሀሳብም "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እመርታ" ሲሆን፣ ለብልፅግና ፓርቲያችን ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተሰጠ የሁለተኛ ዙር ስልጠና ሲሆን፣አመራሩ በሁሉም መስኮች በስልጠናዉ ያገኘዉን ግንዛቤ በተጨባጭ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን እና የተገኙ አበረታች ውጤቶችንም የመስክ ምልከታ አካሂዷል።
በሁሉም መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠልና ተግዳሮቶችን ወደ ድል በመቀየር፣ የተሻለችና የብልፅግና ተምሳሌት የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ትኩረት እንዲደረግባቸዉ በለየናቸዉ የትኩረት ዘርፎች የግብርና እና ገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ የኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ እንዲሁም የቱሪዝምና ከተማ ልማት ዘርፍ እምርታን ለማስመዝገብ መግባባት ፈጥረናል።
በማያቋርጥ “መፍጠር እና መፍጠን “ መርህ እየሰራን የኢትዮጵያን ብልፅግና እናረጋግጣለን!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ኤጀንሲው ከፍተኛ የመብራት መቆራረጥ ባለባቸዉ 22 ወረዳ የሶላር ሲስተም ገጠማ ስራ ጀመረ።
የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ እያደረገ ባለው የተቋም ግንባታ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ቴክኖሎጂ ማሸጋገሩ ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በከተማዉ በሚገኙ በተመረጡና በተከታታይ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ የሚገጥማቸዉ 22 ወረዳዎችን በመለየት አማራጭ በፀሃይ ብርሃን የሚሰራ የሶላር ሲስተም ገጠማ ስራ ዛሬ አስጀምሯል ።
ይህንኑ መነሻ በማድረግ አማራጭ ታዳሽ የፀሃይ ብርሃን ሃይል ተጠቅሞ አገልግሎት በወረዳዎች እንዳይቋረጥ ማድረግ የሚያስችል ሙከራ ከፍተኛ የተገልጋይ ፍሰት ካለባቸው ወረዳዎችና በተከታይ የመብራት መቆራረጥ የሚከሰትባቸዉ ወረዳዎች ላይ ስራዉን ያስጀመሩ ሲሆን በአቃቂ ቃሊቲ ወረዳ 5 ዛሬ ተግባራዊ ተደርጓል። በወረዳዉ 18 ፓናል ገጠማ እንሁም 2 ባትሪዎች የተገጠሙ ሲሆን የእያንዳንዱ ወረዳ 20ሺ KW ሃይል ማመንጨት የሚያስችል አቅም ተፈጥሮለታል።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ ተገኝቶ ባስተላለፉት መልዕከት ኤጀንሲዉ ለአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆ ሊሆኑ የሚችሉ የግብዓት ችግሮችን በመቅረፍ አገልግሎትን ሊያቀላጥፉ የሚችሉ አሰራሮችን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ አክለዉም በ22ቱም ወረዳዎች የተጀመረዉ በቀጣይ ሌሎች የሃይል መቆራረጥ ሊገጥማቸዉ የሚችሉ ወረዳዎችን ተጠቃሚ የማድረግ ስራ ሚቀጥል መሆኑን ጭምር ተናግረዋል፡፡
ህዳር 17/2018 አ.ም
ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ በነጻ የስልክ መስመር 7533 ይደውሉ።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በመንገድ መብራት ኬብል ላይ ስርቆት ሲፈፅሙ የተገኙ ተጠርጣሪዎችን ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ከፍየል ቤት ወደ ሰሚት በሚወስደው መንገድ ኩዊንስ አጠገብ ካለው የታክሲና ባስ ተርሚናል ላይ ከፍተኛ መጠን ያለው ኬብል ስርቆት የፈፀሙ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን የአዲስ አበባ መብራት አገልግሎት አስተዳደር ባለስልጣን አስታውቋል፡፡
ባለስልጣኑ በመንገድ መሰረተ-ልማቱ ላይ በተዘረጉ ኬብሎች ላይ በተደጋጋሚ በሚፈፀም ስርቆት ምክንያት መንገዶች ጨለማ እንዲሆኑ በማድረግ በህብረተሰቡ የምሽት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ጫና ከማሳደር ባለፈ በከፍተኛ ወጪ በለማው መሰረተ-ልማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ላይ ይገኛል ሲል ገልጿል፡፡
ህብረተሰቡ፣ የፀጥታና ባለድርሻ አካላት በከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ ፈሶባቸው የተዘረጉ የመንገድ መብራት መሰረተ-ልማቶችን ከስርቆትና ህገ-ወጥ ተግባራት በመጠበቅ፤ ለተገቢው አገልግሎት እንዲውል በማድረግ በኩል የሚሰሩትን ስራዎችና ኃላፊነታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ባለስልጣኑ በዚህ አጋጣሚ ያስታውቃል፡፡
ባለስልጣኑ ለአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈጸም ማንኛውንም ስርቆትና ህገ-ወጥ ተግባራት ላይ በባለስልጣኑ ነፃ ስልክ መስመር 9101 እና የማህበራዊ ትስስር ገፆችን በመጠቀም ጥቆማ በመስጠትና መረጃውን በማድረስ የተለመደ ትብብር ነዋሪው እንዲያደርግ ጥሪውን አቅርቧል ፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
