ar
Feedback
ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት

ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት

الذهاب إلى القناة على Telegram

በወንጌል ኮነ ህይወትነ ህይወታችን በወንጌል ሆነ ቅ / ያሬድ

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
2 006
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ በዐፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡ በመጨረሻም ጥቅምት 2 ቀን ተፀንሰው ሐምሌ 3 ቀን ተወለደው ጥር 3 ቀን ባላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ ቅዳሴ ቤታቸው ደግሞ ሐምሌ 3 ቀን ነው፡፡ ይኸውም ለመጀመሪያ ጊዜ በዐፄ ገብረ መስቀል ጊዜ በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶ የተመረቀበት ዕለት ነው፡፡ የአባ ሊባኖስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን! እኛንም በአማላጅነታቸው የምንታመን የተዋሕዶ ልጆች የሆንን ሁላችንን ዛሬ ከአባ ሊባኖስ፣ ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ (ምንጭ፡- ገድለ አቡነ ሊባኖስ፣ ስንክሳር ዘወርሃ ጥር፣ የቅዱሳን ታሪክ) Share @meskal

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን፡፡ እንኳን አደረሳችሁ ፡፡ ጥር ፫ ከሚከበሩት በዓላት አንዱ የአባታችን አባ ሊባኖስ ዕረፍት ነው፡፡ አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ በሃገራችን እጅግ ዝነኛ ከሆኑ ቅዱሳን ከዐለት ላይ ውኃ እያፈለቁ ድውያንን የሚፈውሱት ተአምረኛውና ታላቁ አባት አንዱ አባ ሊባኖስ ናቸው :: ጥር 3 በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡ :እርሳቸው እንደ ተስዓቱ (ዘጠኙ) ቅዱሳንና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሁሉ ከውጪ ሃገር የመጡ ናቸው:: የነበሩበት ዘመንም 5ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻና 6ኛው መቶ ክ/ዘመን ውስጥ ነው:: ጻድቁ አባ ሊባኖስን 'አባ መጣዕ' እያሉ መጥራት የተለመደ ነው:: 'መጣዕ' ማለት ኤርትራ ውስጥ የሚገኝና ጻድቁ በተጋድሏቸው የቀደሱት ቦታ ነው ሌላው የአባታችን የተክለ ሃይማኖት ገዳም ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› በስማቸው የተሰየመላቸው ናቸው፡፡በተጨማሪ 8ዐ ዋሻዎች እና አብያተ ክርስቲያናት አንፀዋል ሥርዓተ ምንኵስናን ያስፋፉ የኢትዮጵያ ባለውለታ ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል በገድላቸው ላይ ተጠቅሶ ከምናገኛቸው ገዳማት ባለ ረጅም እድሜዋ ሰሚዋና ፈዋሷ ከከ 1500 በላይ እድሜ ያስቆጠረችው አዲስ አበባ የምትገኘው እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት አንድነት ገዳም አንዷ ናት፡፡ ጥንተ ታሪካቸውስ እንደ ምን ነው አባ ሊባኖስ፡- በብሥራተ መልአክ ተጸንሰው ስለ ተወለዱ ስማቸውም በዚያው 'ሊባኖስ ተብሏል::ሊባኖስ' እመ ብርሃን የተወለደችበት ቅዱስ ሥፍራ ሲሆን በጥሬ ትርጉሙ 'ደጋ' ማለት ነው:: ምሥጢራዊ ትርጉሙ ግን ለጻድቅነት ያገለግላል:: አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ይባላሉ፡፡ እነርሱም በወርቅና በብር እጅግ የበለጸጉ ሮማዊ ናቸው፡፡ ልጃቸውን አባ ሊባኖስን በሃይማኖት በምግባር ኮትኩተው ካሳደጓቸው በኋላ ዕድሜያቸው ሲደርስ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ያጋቧቸው ዘንድ ከቁስጥንጥንያ አገር ሚስት ባመጡለት ጊዜ እርሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፡፡ ወደጫጉላቤትም መግባትን እምቢ አለ፡፡ በዚህም ጊዜ ነቢዩ ሳሙኤልን እንደጠራው አባታችንንም እግዚአብሔር ሦስት ጊዜ በስማቸው ጠራቸውና ‹‹ከአባትህ ተለይ አንተ የመንግሥተ ሰማያት ሙሽራ ነህ እንጂ የዚህ ምድራዊ ዓለም ሙሽራ አይደለህም›› አላቸው፡፡ አባታችንም ‹‹ወዴት እሄዳለሁ? ምንስ ላድርግ?›› ባሉ ጊዜ ወዲያው የታዘዘ መልአክ በሌሊት መጥቶ ከአባታቸው ቤት አውጥቶ +"እነሆኝ ጌታየ!" ቢሉት ከአባታቸው ጐን ነጥሎ እያጫወተ ሳይታወቃቸው ከሮም ግብጽ (ገዳመ ዳውናስ) አደረሳቸው::ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስም ለአባ ሊባኖስ በዓት በመስጠት ገዳመ ሥርዓትን፣ አስኬማ መላእክትን፣ ቅናተ ዮሐንስን አስተምረዋቸው አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡ አሏቸው::በልጅነቱ በዲቁና ሲያገለግል ቆይቶ ወደ ግብፅ በመምጣት ሥርዓተ ምንኵስና ተፈጸመለት፡፡ ወደ እስክንድርያ በመጓዝም እስከ ቁምስና ማዕረግ የደረሰ አባት ነው፡፡ ከዚህም በኋላ ያ ከአባታቸው ቤት ወስዶ አባ ጳኩሚስ ገዳም ያደረሳቸው ያ መልአክ ድጋሚ ተገለጠላቸውና ‹‹ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድለህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአክሱም ተቀመጡ፡፡ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው ከዓመታት ቆይታ በኋላ ተመልሰው አክሱም ሄዱ፡፡ በአክሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአክሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል ‹‹ተራ ውሃ ነው›› ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ ‹‹አምላከ አባ ሊባኖስ›› ብሎ አመሰገነ፡፡ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው ‹‹ምትሃት ነው የሚያሳየው›› ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአክሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው ‹‹አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን›› ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው ‹‹ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኮሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል›› አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አክሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም ‹‹ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ›› አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ ‹‹ሊባኖስ ዘመጣዕ›› የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ ብዙ አርድእትንም አፈሩ:በሃገራችን በ486 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት 8ዐ ዋሻዎች አንፆ ሥርዓተ ምንኵስናን አስፋፍቶ በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት: በዚያም በቅድስናና በገቢረ ተአምራት ኑረው ጥር 3 ቀን በ140 ዓመታቸው ዐርፈዋል:: የላሊበላውን ቤተ አባ ሊባኖስን ጨምሮ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት አሏቸው፡፡ ፡ በወቅቱ የነበረው ዐፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡

Watch "መንፈስን የሚያድስ ልዩ የሊቃውንት ማኅሌት በመኃትው ቱዩብ mehatew tube" on YouTube https://youtu.be/he_EkHAMbDM

#ጾመ_ነቢያት_ (#የገና_ጾም_) የ2014 ዓ.ም. የገና (የነቢያት) ጾም፤ ፠ #ጾሙ_ኅዳር_15_ይጀምራል_!! #Share ፠ ከ7ቱ አጽዋማት (ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ፍልሠታ፣ ጾመ ሐዋርያት፣ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌ ና ጾመ ገሃድ) መካከል አንዱ ነው፡፡ ፠ ኅዳር 15 ቀን ተጀምሮ እስከ ልደት ዋዜማ ለአርባ ሦስት ቀናት የሚጾም ጾም ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ ስለ መልበሱ፤ ወደ ግብጽ ስለ መሰደዱ፤ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ፤ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፤ ለሰው ልጆች ድኅነት ልዩ ልዩ መከራን ስለ መቀበሉ፤ ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ሞቱ፣ ትንሣኤው፣ ዕርገቱና ዳግም ምጽአቱ በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው ትንቢት ተናግረዋል፤ ትንቢቱ ደርሶ፣ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው የሚኾንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ ፠ ይህንን ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል፤ በዚህም ምክንያት የሚከተሉት ስያሜዎች አሉት፡፡ እነርሱም፤ † ፩. #ጾመ_አዳም_፤ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገት ከተባረረ በኋላ; በፈጸመው በደል አዝኖ ፥ ተክዞ፤ አለቀሰ (እንባ ቢያልቅበት እዥ እስከሚያፈስ፤ እዥ ቢያልቅበት ደም በዓይኑ እስከሚፈስና ዓይኑ ይቡስ ወይም ደረቅ እስከሚሆን ድረስ አለቀሰ) ፥ ጾመ፣ ጸለየ፡፡ ከልብ የሆነ ጸጸቱን፣ ዕንባውን፣ በራሱ መፍረዱንም እግዚአብሔር አይቶ ተስፋ ድኅነት ሰጠው፡፡ ‹‹ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ፣ በደጅህ ድኼ፣ በዕፀ መስቀል ተሰቅዬ፣ ሞቼ አድንሃለሁ፡፡›› የሚል ነው፡፡ /ገላ. ፬፥፬፣ መጽ.ቀሌምንጦስ/ ስለዚህ ጾሙ የተሰጠው ተስፋ ፥ የተቆጠረው ሱባኤ ስለተፈጸመበት ‹‹ጾመ አዳም›› ይባላል፡፡ † ፪. #ጾመ_ነቢያት_፤ ነቢያትም የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር ተገለጦ ስለታያቸው፣ ክርስቶስ ለሰው ልጅ የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ በትንቢት ተመልክተው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡፡ ይህ ጾም ከአባታችን አዳም እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ድረስ የተነሱ አበውና እናቶች: ድኅነትንና ረድኤትን ሲሹ የጾሙት ጾም ነው:: በተለይ አባታችን አዳም: ቅዱስ ሙሴ: ቅዱስ ኤልያስ፣ ቅዱስ ዳንኤል ና ቅዱስ ዳዊት በጾማቸው የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው:: (ዘዳ 9:19, ነገ. 19:8, ዳን. 9:3፣ መዝ. 68:10, 108:24) ቅዱሳን ነቢያት በጭንቅ በመከራ ሆነው የጾሙት ጾም ወደ መንበረ ጸባኦት ደርሶ: ወልድን ከዙፋኑ ስቦታል:: ለሞትም አብቅቶታል:: † ፫. #ጾመ_ሐዋርያት_፤ ሐዋርያት ‹‹ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብራለን፣ ልደትን ምን ሥራ ሠርተን እናከብረዋለን?›› ብለው ከልደተ ክርስቶስ በፊት ያሉትን ፵፫ ዕለታት ጾመዋልና፡፡ † ፬. #ጾመ_ማርያም_፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ቅድስናዋን አይቶ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ወልደ አምላክን ያለ ሰስሎተ ድንግልና በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ እንደምትወልደው ቢነግራትም የትሕትና እናት ናትና ‹‹ምን ሠርቼ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ እችለዋለሁ?›› ብላ ጌታን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማለችና ‹‹ጾመ ማርያም›› ይባላል፡፡ † ፭. #ጾመ_ፊልጶስ_፤ ሐዋርያው ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ እያስተማረ ሳለ በሰማዕትነት ሲሞት፤ አስክሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ፤ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስክሬን እንዲገለጽላቸው ከኅዳር ፲፮ ጀምረው ጾመው በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስክሬን ተመልሶላቸዋል፤ ነገር ግን አስከሬኑ ቢመለስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል፡፡ † ፮. #ጾመ_ስብከት_፤ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት፥ የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት፥ የምስራች የተነገረበት ስለሆነ ጾመ ስብከትም ይባላል፡፡ † ፯. #ጾመ_ልደት_፤ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት ስለሆነ ‹‹ጾመ ልደት›› ይባላል፡፡    ጾምን ትእዛዝ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የፍቅርና የበረከት ምንጭ በመሆኑ ጭምር ደስ እያለን ብንጾመው የቅዱሳኑ በረከት ያድርብናል፡፡ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን፤ መንግሥቱንም እንዲያወርሰን ዅላችንም በዚህ በጾመ ነቢያት ወቅት በጾም በጸሎት ተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባል፡፡ ኦርቶዶክሳዊ ወንድሞች ሆይ ለኦርቶዶክሳዊ ወንድምዎ ሼር በማድረግ የቤተክርስቲያናችንን ቀጥተኛ ትምህርት ያሳውቁ ይመስክሩ ። 👇👇👇👇👇👇👇👇 👇 @meskal 👇 👇 @meskal 👇 👇 @meskal 👇 👆👆👆👆👆👆👆👆

Watch "እንደዚህ አይነት ድምፅም አለ🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔🤔ድንቅ ቅዳሴ ዜማ በደብረ ፀሀይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ዲያቆናት" on YouTube https://youtu.be/bJvrULmGJDg

Watch "የፕሮቴስታንቱ ጉድ ተጋለጠ።እጅግ አሳፋሪ video" on YouTube https://youtu.be/r8lIGEX-Ckc

Watch "አጠር ያለ ቅኔ በደብረ ፀሀይ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን።እንዲህ በልጅነት ድንቅ ቅኔ" on YouTube https://youtu.be/sa_BlX2oatI

በስመአብ  ወወልድ  ወመንፈስ ቅዱስ  አሃዱ  አምላክ  አሜን [ኅዳር 8 የእግዚአብሔርን ዙፋን የሚሸከሙ የኪሩቤልና የሱራፌል ዓመታዊ በዓል፤ ክብራቸውና ስማቸው]  ክብራቸው ታላቅ የኾኑት የኪሩቤልን ነገር ሊቁ ኤጲፋንዮስ “ወለዳግም ጾታ ዐሠርቱ ስሞሙ ኪሩቤል ካህናተ ቅዳሴ ወውዳሴ እምታሕተ ሐቌሆሙ አሐዱ ወእምላዕለ ሐቌሆሙ አርባዕቱ እለ ግሉፋን በአዕይንት” ብሎ  እንደገለጸው ኹለተኞቹ አመስጋኞች የኾኑት ዐሥሩን ነገድ ስማቸው ኪሩቤል ሲባሉ ከወገባቸው በታች አንድ ከወገባቸው በላይ አራት አድርጎ ሲፈጥራቸው ዐይናቸው ብዙ ነው፤ አለቃቸውም ኪሩብ ሲኾን የሰው መልክና የአንበሳ መልክ ያለው ነው፡፡ ❖ ሦስተኛውን ዐሥሩን ነገድ ስማቸው ሱራፌል ሲባል የእነዚኽ አለቃቸው የንስር መልክና የእንስሳ መልክ ያለው ነው፤ አለቃቸውም ሱራፊ ሲባል ሲፈጥራቸውም ስድስት ስድስት ክንፍ አድርጎ ፈጥሯቸዋል፨ ❖ ልዑል እግዚአብሔር ከነገደ ኪሩቤል ኹለት ገጸ ሰብእ እና ገጸ አንበሳን፤ ከሱራፌል ኹለት ገጸ ንስርና ገጸ እንስሳን አንሥቶ ከኢየሩሳሌም ሰማያዊት በላይ ከሰማይ ውዱድ በታች አቁሞ በነርሱ ላይ ሰማይ ውዱድን እንደ መረሻት ጫነባቸው፤ በላይም ሕብሩ በረድ የመሰለውን ዙፋን እንደ ሠረገላ ጭኖባቸዋል፤ እነዚኽንም በምሥራቅ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን፣ በደቡብ በአራቱ መኣዝን ዠርባቸውን ወደ ውስጥ ፊታቸውን ወደ ውጪ እያደረገ አቁሟቸዋል። ❖ነቢዩ ሕዝቅኤል ስለዚኽ ነገር በምዕ ፩፥፲፪ ላይ “እያንዳንዱም ወደ ፊት ቀጥ ብሎ ይኼድ ነበር መንፈስም ወደሚኼድበት ኹሉ ይኼዱ ነበር ሲኼዱም አይገላመጡም ነበር” በማለት እንደተናገረ ገጽ ለገጽ ሳይተያዩ ሥላሴ በፈቀዱት ፍኖት አንዱ በኼደበት ሦስቱ እየተከታተሉ ይኼዳሉ፡፡ ❖ እነዚኽንም እንደ ነቢዩ ሕዝቅኤል ገለጻ ፲፮ ሲኾኑ የቀሩት ከውስጥ ስለኾኑ ስለማይታዩ አራቱ ግን ብቅ ብቅ ብለው ስለሚታዩ ዮሐንስ አራት ብሏቸዋል እንጂ እንደ ሕዝቅኤል ገጻቸው ፲፮ ነው ይላሉ መተርጉማን፡፡ ❖  ሊቁ “እምርእሶሙ እስከ ሐቌሆሙ አርባዕቱ ወእምሐቌሆሙ እስከ እግሮሙ አሐዱ ከመ ርእየተ እለ ቄጥሩ ዘውእቱ ዖፍ ዘይነብር በሀገረ ፋርስ” እንዲላቸው፤ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም “ከመ ርእየተ እለቄጥሩ ገጸ በገጽ ኢይትናጸሩ” ብሎ እንደገለጻቸው በፋርስ ሀገር የሚኖረው እለቄጥሩ የተባለውን ዎፍ ከወገቡ በታች አንድ ከወገቡ በላይ አራት እንደኾነ እነዚኽንም ከወገባቸው በታች አንድ ከወገባቸው በላይ አራት አድርጎ ፈጥሯቸዋል ፡፡ ❖ ኪሩቤልን “እለ ብዙኃት አዕይንቲሆሙ” አላቸው፤ ከላይ እስከ ታች ድረስ ዐይንን የተመሉ ናቸውና፤ ይኽስ አይደለም እንደ ብርሌ እንደ ብርጭቆ እያብለጨለጨ ለዐይን ባልተመቸም ነበር ብሎ ዐልፎ ዐይን ዐልፎ ዐይን ነው፤ እንደ አልጋ መለበሚያ እንደ ሱቲ መጠብር እንደ ቀሽመሪ መታጠቂያ፣ እንደ ነብር ለምድ፣ እንደ ዐይነ በጎ፣ እንደ ማር ሰፈፍ ይላሉ፤ ይኽስ አይደለም ብሎ ዐይናቸው ከአንገታቸው በላይ ሰድ ነው፤ ይኽም እንደ መስታዮት እያወለወለ እንደ ብርጭቆ እያንጸበረቀ አይደለም ብሎ ኀላፍያትን መጻእያትን የሚያውቁ ስለኾነ እንዲኽ አለ እንጂ ዐይናቸውስ ኹለት ነው ይላሉ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቀደምት መተርጉማን ፡፡ ❖ በኢሳ ፮፥፩-፫ ላይ፡- “ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን በረዥምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየኹት የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን መልቶት ነበር፤ ሱራፌልም ከርሱ በላይ ቆመው ነበር ለእያንዳንዱም ስድስት ክንፍ ነበረው በኹለት ክንፍ ፊቱን ይሸፍን ነበር በኹለቱም ክንፍ እግሮቹን ይሸፍን ነበር በኹለቱም ክንፍ ይበር ነበር፤ አንዱም ለአንዱ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ኹሉ ከክብሩ ተመልታለች እያለ ይጮኽ ነበር” ይላል ይኽ መሸፈናቸው ያድናቸዋል ቢሉ? ትእምርተ ፍርሀት ነው፤ ዛሬ በዚኽ ዓለም ሴቶችን ሕፃናትን እንመታችኋለን ባሏቸው ጊዜ እጃቸውን መጋረዳቸው የሚያድናቸው ኾኖ ሳይኾን ትእምርተ ፍርሀት እንደኾነ ኹሉ፡፡ አንድም በኹለት ክንፋቸው ፊታቸውን መሸፈናቸው ፊትኽን ማየት አይቻለንም ሲሉ በኹለት ክንፋቸው እግራቸውን መሸፈናቸው ከፊትኽ መቆም አይቻለንም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ ያደርጋሉ አለ ትእምርተ ተልእኮ ነው፡፡ አንድም በኹለት ክንፋቸው ፊታቸውን መሸፈናቸው ባሕርይኽን መመርመር አይቻለንም ሲሉ፤ በኹለት ክንፋቸው እግራቸውን መሸፈናቸው ባሕርይኽን መረማመድ መተላለፍ አይቻለንም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወዲያ ወዲኽ ያደርጋሉ ከእእምሮ ወደ አእምሮ ለመፋለሳቸው፡፡  አንድም ኹለት ክንፋቸውን ወደ ላይ አድርገው ይታያሉ አለ ወደላይ ቢወጡ ቢወጡ አትገኝም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወደታች አድርገው ይታያሉ ወደታች ቢወርዱ ቢወርዱ አትገኝም ሲሉ፤ ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ ያደርጋሉ ወዲያና ወዲኽ ቢሉ አትገኝም ሲሉ፤ አንድም ወደላይ መዘርጋት በሰማይ ምሉእ ነኽ ሲሉ ወደታች መዘርጋቸው በምድርም ምሉእ ነኽ ሲሉ፤ ወዲያና ወዲኽ መዘርጋታቸው በኹሉ ምሉእ ነኽ ማለታቸው ነው፤ አንድም ወደላይ መዘርጋት ትእምርተ ተመስጦ ወደታች መዘርጋት ትእምርተ ትሕትና፤ ወዲያና ወዲኽ ረብቦ መታየት ትእምርተ ተልእኮ ነው ❖ በአጠቃላይ ኹለት ክንፋቸውን ወደላይ ኹለት ክንፋቸውን ወደታች ኹለት ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ አድርገው ትእምርተ መስቀል መሥራታቸው በብሉይ ኪዳን ከኾነ እንዲኽ ባለ መስቀል ተሰቅለኽ ዓለምን ታድነዋለኽ ሲሉ በዘመነ ሐዲስ የኾነ እንደኾነ እንዲኽ ባለ ትእምርተ መስቀል ተሰቅለኽ ዓለምን አድነኸዋል ሲሉ ነው፡፡ ❖  የእነዚኽ አርባዕቱ እንስሳ መላእክት ፊታቸው በርካታ ምስጢራትን ሲያመለክቱ ገጸ ሰብእ በማቴዎስ፤ ገጸ አንበሳ በማርቆስ፤ ገጸ ላሕም በሉቃስ፤ ገጸ ንስር በዮሐንስ ተመስሏል። ❖  በሌላ ምስጢር የሰው ገጽ ያለው የጌታን ሰው የመኾንን ነገር፤ የላም መልክ ያለው በቀራንዮ ላይ ደሙን ማፍሰሱ፤ የአንበሳው መልክ ያለው የጌታችንን ትንሣኤ፤ የንስር መልክ ያለው የጌታን ዕርገት እንደሚያመለክቱ ቀደምት መተርጒማን ይተነትኑታል። ❖ዐምደ ሃይማኖት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም እጅግ ምጡቅ በኾነው ዕውቀቱ ዕጓለ አንበሳ የተባለው የወልድ የባሕርይ አባቱን አብን በአንበሳ ይመስለዋል። ❖ሥጋን ተውሕዶ ፍጹም ሰው የኾነው ወልድን የሰው መልክ ባለው መስሎ ገልጾታል፡፡ ❖ በአምሳለ ርግብ ወርዶ በወልድ ራስ ላይ ተቀምጦ የታየው መንፈስ ቅዱስን የንስር መልክ ባለው መስሎ አብራርቶ ጽፎታል። ❖በቀንዱ የማይበራታ ላሕም ተብሎ የተመሰገነው የወልደ እግዚአብሔር ቅዱስ ሥጋው የሚፈትትባት፤ ክቡር ደሙ የሚቀዳባት በአራቱ ኪሩቤል አምሳል አራት መአዝን ያላት ቤተ ክርስቲያንን በገጸ ላሕም አምሳል ገልጦ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ ስማቸውን በመጥቀስ ሲያወድሳቸው፦ [“ሰላም ለ፬ እንስሳሁ ለአብ እለ ይጸውሩ መንበሮ እለ ስሞሙ አግርሜስ ገጸ አንበሳ፡፡ አግርሜጥር ገጸ ሰብእ፡፡ ባርቲና ገጸ ላሕም፡፡ አርጣን ገጸ ንስር፡፡ ለቀዳማዊ ገጹ ከመ አንበሳ፤ በአምሳለ ፈጣሪሁ ዘውእቱ አብ፡፡ ለካልዕ ገጹ ከመ ሰብእ በአምሳለ ወልድ፤ ዘውእቱ ነሥአ ፍጹመ ስባኤ፡፡ ለሣልስ ገጹ ከመ ንስር በአምሳለ መንፈስ ቅዱስ ዘውእቱ አስተርአየ በርእየተ ርግብ በሥጋ፡፡ ወለራብእ ገጹ ከመ ላሕም በአምሳለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፤ እስመ ፬ቱ መኣዝኒሃ”፡፡] (የአብ ዙፋኑን ለሚሸከሙና ስማቸውም የአንበሳ መልክ ያለው አግርሜስ፤ የሰው መልክ ያለው አግርሜጥር፤ የላም መልክ ያለው ባርቲና፤ የንስር መልክ ያለው አርጣን ለተባሉ ለአራቱ እንስሳ ሰላምታ ይገባል፤ 👇👇👇👇 @meskal

Watch "🔴ወቅታዊ ትምህርት በዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ "ለክርስቲያን ሁሉ የእመቤታችንን ተአምር መስማት ቀላል አይምሰለው" መኀትው ቲዩብ _mehatew tube" on YouTube https://youtu.be/wwFU54Wslu8

ጥቅምት 27   - መድሃኔአለም(ጥንተ ስቅለት) - አቡነ መባጽዮን( መድሃኔአለም በስቅለቱ አምሳል ሁኖ የተገለጠላቸዉ) በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት በእነዚህ አብያተ ክርስትያናት በአለ ንግሱ ይከበራል። ይህ ቻናል በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ስር በሚገኙ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ የሚከበሩ ዓመታዊ የንግሥ በዓላትን የሚገልፅ ነው።   ይቀላቀሉን::    🤲 መባዓ ፅዮን ይጠብቁን 🤲   🤲  መድሃኔአለም ይጠብቀን 🤲 1) ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሚካኤል ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ /ክ/ከ ማሞ አካባቢ 2) ድልበር መካነ ጎልጎታ መድሃኔአለም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ጉለሌ ድልበር 3) ደብረ ቀራንዮ መድሃኔአለም እና ገብርኤል ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ ቀራንዮ 4) ፍኖተሎዛ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ ብርጭቆ ኮንዶሚንየም 5) ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ልዩ ስም፦አዲስ ከተማ/ክ/ከ አውቶብስ ተራ 6)  አስኮ ደብረ መድሃኒት መድሃኔአለም እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ አስኮ አዲስ ሰፈር 7) ደብረ መድሃኒት መድሃኔአለም እና ቅድስት ኪዳነምህረት ቤ/ክ ልዩ ስም፦የካ አባዶ 8) አያት መካነ ህይወት መድሃኔአለም እና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ልዩ ስም፦ቦሌ /ክ/ከ አያት ጠበል 9) ምስራቀ ፀሐይ መድኃኔአለም ቀበና ካቴድራል ልዩ ስም፦አራዳ /ክ/ከ ቀበና 10) ቦሌ ሰሚት መካነ ሰላም መድኃኔአለም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ቦሌ ክ/ከሰሚት ወጂ 11) ኮዬ መካነ  ህይወት አቡነ ገብረመንፈስቅዱስ ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ /ክ/ከ ኮዬ 12) ካራ አሎ ደብር ቅዱስ ደብረ ቀርሜሎስ መድኃኔአለም እና ጻድቁ አቡነ ገሪማ ልዩ ስም፦የካ ክ/ከ ኮተቤ ካራ 13) ቃሊቲ ደብረ መድሃኒት መድሃኔአለም እና አቡነ አረጋዊ ቤ/ክ ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ ወረዳ 12 ሰሪቲ 14) ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድሃኔአለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ ልዩ ስም፦ጉለሌ /ክ/ከ ቀጨኔ መድሃኔአለም 15) መንበረ ንግስት ቁስቋም ማርያም ልዩ ስም፦ጉለሌ ክ/ከ  እንጦጦ ቁስቋም 16) ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ልዩ ስም፦የካ /ክ/ከ ፈረንሳይ ብረት ድልድይ 17) ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔአለም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ቦሌ ክ/ከ  ቦሌ ቡልቡላ 18) ብሔረ ፅጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያምና መድኃኔአለም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ብሔረ ፅጌ 19) ረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔአለም ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ ወረዳ 2 ካራ ቆሬ 20) ጎፋ ቤዛ ብዙሃን ቅድስት ኪዳነምህረት  ካቴድራል ልዩ ስም፦ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ጎፋ ካምፕ 21) ቶታል ፈለገ ህይወት ቅድስት ኪዳነምህረትና መድኃኔአለም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ ቶታል 3 ቁጥር ማዞሪያ 22)  ማህደተ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኃነት መድኃኔአለም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ልደታ /ክ/ከ ልደታ 23) ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ ልዩ ስም፦ቂርቆስ /ክ/ከ መስቀል ፍላወር 24) ደብረ ፍስሃ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ልዩ ስም፦ቂርቆስ /ክ/ከ ቂርቆስ 25) ላፍቶ ደብረ ኢያሪኮ መድኃኔአለም እና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አብያተክርስትያናት ልዩ ስም፦ ንፋስ ስልክ ላፍቶ (ላፍቶ) 26) ፉሪ ደብረ ሰላም መድኃኔአለምቤ/ክ ልዩ ስም፦ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ጀሞ 1 ኮንዶሚንየም 27) ደብረ ሰሊሆን መጥምቀ መለኮት  ቅዱስ ዮሐንስ እና መድኃኔአለምቤ/ክ ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ /ክ/ከ በርታ ሰፈረሰላም 28)  አቃቂ መንበረ ህይወት መድኃኔአለም ቤ/ክ ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ /ክ/ከ ጋራው መድኃኔአለም 29)  ፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ አቃቂ ቃሊቲ /ክ/ከ ፈጬ 30)  ቃሊቲ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል እና ደብረ ቁስቋም ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ አቃቂ ቃሊቲ/ክ/ከ ሰፈረ ገነት 31)  ቃሊቲ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል እና ደብረ ቁስቋም ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ልዩ ስም፦ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከ ሰፈረ ገነት 32) ጽርሐንግስትቅድስትሐናቤ/ክ ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ፉሪ ሐና ማርያም

Watch "🔴ድንቅ ትምህርት በዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ |ዕፀ መስቀል|_መኀትው ቲዩብ_mehatew tube" on YouTube https://youtu.be/fzkfyKYSJZM

Watch "ፈረንሳይ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ድንቅ ማህሌት።መሰማት ያለበት_መኀትው ቲዩብ_mehatew tube..ethiopan orthodox tewahdo" on YouTube https://youtu.be/tJwHuyDBoj4

Watch "ይህንን video ካዩ በኋላ ለግዕዝና ለቅኔ ያላቹ አመለካከት ይለወጣል።መታየት ያለበት መኀትው ቲዩብ።ኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ" on YouTube https://youtu.be/jmrFgDB2b3U

መስከረም 29 የት ማክበር አስበዋል ? 💚ቅድስት💛 አርሴማ❤ በአዲስ አበባበ አህጉረ ስብከት በእነዚህ አብያተክርስትያናት በአለ ንግሱ ይከበራል። ይህ ቻናል በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ስር በሚገኙ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ የሚከበሩ ዓመታዊ የንግሥ በዓላትን የሚገልፅ ነው።      🤲ቅድስት አርሴማ ትጠብቀን 🤲 1)     ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ            ልዩ ስም፡-ኮ/ቀ/ክ/ከ ዊንጌት ጠሮ አራት መንታ            2)     ገዳመ ኢየሱስ            ልዩ ስም፡-ልደታ ክ/ከ ሆላንድ ኤምባሲ            3)     ኮልፌ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለሐይማኖት እና  ቅዱስ ገብርኤል            ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ ፊሊዶሮ            4)    ደብረ መድሃኒት አቡነ ሐብተማርያም ወቅድስት ልደት ወቅድስት አርሴማ ገዳም            ልዩ ስም፦ኮ/ቅ/ክ/ከ አስኮ ካኦጄጄ ዱቄት ፋብሪካ ከፍ ብሎ ቃሌ ተራራ ላይ            5)   አያት መካነ ህይወት መድሃኔአለም እና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ            ልዩ ስም፦ቦሌ /ክ/ከ አያት ጠበል            6)    ምስራቀ ፀሐይ መድኃኔአለም ቀበና  ካቴድራል            ልዩ ስም፦አራዳ /ክ/ከ ቀበና            7)    ኮተቤ ማህደረ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስቅዱስ እና ቅዱስ ሚካኤል  ቤ/ክ            ልዩ ስም፦የካ ክ/ከ ሉቄ             8)     ኮተቤ ሀገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ቅድስት ድንግል ማርያም እና ቅድስት መግደላዊት ማርያም ቤ/ክ            ልዩ ስም፦የካ ክ/ከ አንቆርጫ             9)     ጉራራ ምስራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምህረት እና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ            ልዩ ስም፦የካ ክ/ከ ፈረንሳይ ጉራራ             10)   ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም            ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ ታቦት ማደሪያ            11)    ደብረ ቢታንያ አቡነ ተክለሐይማኖት እና ቅድስት ልደታ ለማርያም            ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ቆሬ 5 ቁጥርና 2 ቁጥር ማዞርያ            12)   አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምህረት እና ደብረ ፍስሃ  ቅዱስ ገብርኤል            ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ሳሪስ አዲስ ሰፈር            13) ጀሞ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ              ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ  ጀሞ            14)     ምስራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል፤ቅድስት አርሴማ እና አቡነ አዳም ቤ/ክ            ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ መካኒሳ ጀርመን አደባባይ            15)  ሐመረ ወርቅ ቅድስት ማርያም እና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ            ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ /ክ/ከ ወረዳ 5 ወርቁ ሰፈር            16) አለም ባንክ ጀሞ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል            ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ አለም ባንክ            17)    አቃቂ ፈንታ ደብረ ፅጌ  ቅዱስ ሩፋኤል  እና ቅድስት አርሴማ            ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ /ክ/ከ ፈንታ            18)   ቃሊቲ ደብረ መድሃኒት መድሃኔአለም እና አቡነ አረጋዊ ቤ/ክ            ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ ወረዳ 12 ሰሪቲ 19) መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል፤ጻድቁ አቡነ ተክለ ሐይማኖት እና ቅድስት አርሴማ ልዩ ስም፦ጉለሌ /ክ/ከ ቀጨኔ 20) የቃሊቲ መካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ልዩ ስም:- አ/ቃ/ክ/ከ/ ወረዳ 5 ሰፈረ ሰላም (አባኮት) 21) ደብረ መዊዕ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ\ክ ልዮ ስም:- ን/ስ/ላ/ክ/ከ ሀና ማንጎ ሰፈር 22)ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ዑራኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ልዩ ስም:- ቦሌ ክፍለ ከተማ ከገርጂ መብራት ሀይል ወደ ጎሮ በሚሄደው መንገድ አለማየሁ ህንፃ ገባ ብሎ 23) መንበረ ልኡል ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት ድንግል ማሪያም ቤተ ክርስቲያን ልዩ ስም:-ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ላፍቶ 58 ማዞሪያ 24) ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ልዩ ስም:- ቦሌ ክ/ከተማ አዲሱ ስታዲየም 25) የግራር ደብረ ዐባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ልዩ ስም:- ኮ/ቀ/ክ/ከ ግራር ኮንዶሚኒየም አካባቢ 26) ቦሌ አራብሳ ዋሻ መካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፣ ቅድስት ልደታ ለማርያም ፣ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ፣ ቅዱስ ሚካኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን 27) የካ አባዶ ደ\ል ቅድስት አርሴማ እና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዩሐንስ ቤተ ክርስቲያን 28) ገነተ ሰማይ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ እጨጌ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን 29) ጎፋ መካነ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤል ወቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያ 30) ጎጆ አርሴማ ወአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን 31) ቦሌ ሰሚት ምስራቀ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ልዩ ስም፦ ቦሌ ክ/ከ ሰሚት ኮንዶሚንየም አካባቢ ሼር ማድረግ አይዘንጉ ኦርቶዶክሳዊ ወንድሞች ሆይ ለኦርቶዶክሳዊ ወንድምዎ ሼር በማድረግ የቤተክርስቲያናችንን ቀጥተኛ ትምህርት ያሳውቁ ይመስክሩ ። 👇👇👇👇👇👇👇👇 👇 @meskal 👇 👇 @meskal 👇 👇 @meskal 👇 👆👆👆👆👆👆👆👆

መስከረም 29 💚ቅድስት💛 አርሴማ❤ በአዲስ አበባበ አህጉረ ስብከት በእነዚህ አብያተክርስትያናት በአለ ንግሱ ይከበራል። ይህ ቻናል በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ስር በሚገኙ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ የሚከበሩ ዓመታዊ የንግሥ በዓላትን የሚገልፅ ነው።      🤲ቅድስት አርሴማ ትጠብቀን 🤲 1)     ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ            ልዩ ስም፡-ኮ/ቀ/ክ/ከ ዊንጌት ጠሮ አራት መንታ            2)     ገዳመ ኢየሱስ            ልዩ ስም፡-ልደታ ክ/ከ ሆላንድ ኤምባሲ            3)     ኮልፌ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለሐይማኖት እና  ቅዱስ ገብርኤል            ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ ፊሊዶሮ            4)    ደብረ መድሃኒት አቡነ ሐብተማርያም ወቅድስት ልደት ወቅድስት አርሴማ ገዳም            ልዩ ስም፦ኮ/ቅ/ክ/ከ አስኮ ካኦጄጄ ዱቄት ፋብሪካ ከፍ ብሎ ቃሌ ተራራ ላይ            5)   አያት መካነ ህይወት መድሃኔአለም እና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ            ልዩ ስም፦ቦሌ /ክ/ከ አያት ጠበል            6)    ምስራቀ ፀሐይ መድኃኔአለም ቀበና  ካቴድራል            ልዩ ስም፦አራዳ /ክ/ከ ቀበና            7)    ኮተቤ ማህደረ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስቅዱስ እና ቅዱስ ሚካኤል  ቤ/ክ            ልዩ ስም፦የካ ክ/ከ ሉቄ             8)     ኮተቤ ሀገረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ቅድስት ድንግል ማርያም እና ቅድስት መግደላዊት ማርያም ቤ/ክ            ልዩ ስም፦የካ ክ/ከ አንቆርጫ             9)     ጉራራ ምስራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምህረት እና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ            ልዩ ስም፦የካ ክ/ከ ፈረንሳይ ጉራራ             10)   ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም            ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ ታቦት ማደሪያ            11)    ደብረ ቢታንያ አቡነ ተክለሐይማኖት እና ቅድስት ልደታ ለማርያም            ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ቆሬ 5 ቁጥርና 2 ቁጥር ማዞርያ            12)   አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምህረት እና ደብረ ፍስሃ  ቅዱስ ገብርኤል            ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ ሳሪስ አዲስ ሰፈር            13) ጀሞ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ              ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ  ጀሞ            14)     ምስራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል፤ቅድስት አርሴማ እና አቡነ አዳም ቤ/ክ            ልዩ ስም፦ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ መካኒሳ ጀርመን አደባባይ            15)  ሐመረ ወርቅ ቅድስት ማርያም እና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ            ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ /ክ/ከ ወረዳ 5 ወርቁ ሰፈር            16) አለም ባንክ ጀሞ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል            ልዩ ስም፦ኮ/ቀ/ክ/ከ አለም ባንክ            17)    አቃቂ ፈንታ ደብረ ፅጌ  ቅዱስ ሩፋኤል  እና ቅድስት አርሴማ            ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ /ክ/ከ ፈንታ            18)   ቃሊቲ ደብረ መድሃኒት መድሃኔአለም እና አቡነ አረጋዊ ቤ/ክ            ልዩ ስም፦አቃቂ ቃሊቲ ወረዳ 12 ሰሪቲ 19) መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል፤ጻድቁ አቡነ ተክለ ሐይማኖት እና ቅድስት አርሴማ ልዩ ስም፦ጉለሌ /ክ/ከ ቀጨኔ ኦርቶዶክሳዊ ወንድሞች ሆይ ለኦርቶዶክሳዊ ወንድምዎ ሼር በማድረግ የቤተክርስቲያናችንን ቀጥተኛ ትምህርት ያሳውቁ ይመስክሩ ። 👇👇👇👇👇👇👇👇 👇 @meskal 👇 👇 @meskal 👇 👇 @meskal 👇 👆👆👆👆👆👆👆👆

††† እንኳን ለጻድቃን ቅዱሳን አባ አጋቶን ወአቡነ ያሳይ ዘመንዳባ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† አባ አጋቶን ዘዓምድ ††† ††† ታላቁ ጻድቅ በትውልድ ግብጻዊ ሲሆኑ የነበሩበት ዘመንም ከ4ኛው ክ/ዘመን መጨረሻ እስከ 5ኛው መቶ ክ/ዘመን አጋማሽ አካባቢ ነው:: በእርግጥ 'አጋቶን ' በሚባል ስም የሚጠሩ ብዙ አበው አሉ:: ቅድሚያውን 2ቱ ይወስዳሉ:: አንደኛው አባ አጋቶን ለ30 ዓመታት ድንጋይ ጐርሰው የኖሩት አባት ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ ዛሬ የምናከብራቸው ናቸው:: እኒህኛው 'ዘዓምድ ' ይባላሉ:: ምክንያቱም ለ50 ዓመታት አንድ ምሰሶ ላይ ያለ ዕረፍት ጸልየዋልና ነው:: አባ አጋቶን ገና ከልጅነታቸው መጻሕፍትን የተማሩ ሲሆኑ ምናኔን አጥብቀው ይፈልጓት ነበር:: በዚህም ራሳቸውን በትሕርምት እየገዙ: በዲቁና ማዕርጋቸውም እያገለገሉ እስከ 35ዓመታቸው ቆዩ:: በዚህ ጊዜ ደግሞ 'ይገባሃል' ብለው ቅስናን ሾሟቸው:: የማታ ማታ የለመኑትን የማይነሳ ጌታ ተምኔተ ልባቸውን ፈጽሞላቸው ወደ በርሃ ሔዱ:: ወቅቱ የግብጽ ገዳማት በቅዱሳን ሕይወት የበሩበት ነውና እዚህም እዚያም አበውና እናቶች ይገኙ ነበር:: አባ አጋቶንም የከዋክብቱ አበው አባ ገዐርጊና አባ አብርሃም ደቀ መዝሙር ሆነው ገቡ:: አስፈላጊውን የምንኩስና ፈተና ካለፉ በኋላም ምንኩስናን ከእነዚህ አባቶች ተቀበሉ:: በዚያው በገዳመ አስቄጥስ በጽኑ ገድል ተጠምደው ለ15 ዓመታት አገለገሉ:: ጻድቁ ከእርሳቸው በፊት የነበሩ ቅዱሳንን ተጋድሎ ጠዋት ማታእያነበቡ መንፈሳዊ ቅናትን ይቀኑ ነበር:: በተለይ የታላቁን ስምዖን ዘዓምድን ገድል ሲያነቡ ሕሊናቸውን ደስ ይለው: ይህንኑ ገድል ይመኙ ነበር:: እድሜአቸው 50 ዓመት በሞላ ጊዜ በልቡናቸው እንደ አባ ስምዖን ዘዓምድ ለመጋደል ወሰኑ:: ይህን ለገዳሙ አባቶች ቢያማክሯቸው አበው:- "ይበል! ሸጋ ምክር ነው:: እግዚአብሔር ያስፈጽምህ!" ብለው መርቀው አሰናበቷቸው:: አባ አጋቶን የዳዊትን መዝሙር እየዘመሩ ከገዳሙ ወጡ:: በጣምም ወደ ዓለም ሳይገቡ: ከዓለም (ከከተማም) በጣም ሳይርቁ አንድ ረዥም ምሰሶ አገኙና ከላዩ ላይ ወጡ:: ከዚህች ዕለት ጀምረው ጻድቁ ለ50 ዓመታት ከዚያች ዓምድ (ምሰሶ) ወርደው: ለሥጋቸውም ዕረፍትን ሰጥተውት አያውቁም:: ማዕከለ ገዳም ወዓለም ናቸውና ለምዕመናንም ሆነ ለመነኮሳት አጽናኝ አባት ሆኑ:: ለአካባቢውም የብርሃን ምሰሶ ሆኑ:: የታመመ ቢኖር ይፈውሱታል:: የበደለውን በንስሃ ይመልሱታል:: ሰይጣን የቋጠረውን ይፈቱታል:: ለራሳቸው ግን ከጸሎት: ከጾምና ከትሕርምት በቀር ምንም አልነበራቸውም:: በተለይ እነዚህ ስራዎቻቸው ይዘከሩላቸዋል:: 1.አጥማቂ ነን እያሉ ሕዝቡን ያስቱ የነበሩ ሰዎችን እየጠሩ እንዲህ የሚያስደርጋቸውን ጋኔን ከእነሱ አስወጥተዋል:: 2.እርሳቸውን ያልሰሙት ግን መጨረሻቸው ጥፋት ሆኗል:: 3.ፍጹም ወንጌልን በሕይወትና በአንደበት መስክረዋል:: 4.ሕዝቡን በንስሃ አስጊጠዋል:: 5.ተግሳጽ የሚገባውን ገስጸዋል:: ጻድቁ አባ አጋቶን ዘዓምድ ከእነዚህ የቅድስና ዘመናት በኋላበተወለዱ በ100 ዓመታቸው በዚህች ቀን ዐርፈው በክብርና በዝማሬ ተቀብረዋል:: ††† አቡነ ያሳይ ዘመንዳባ ††† ††† እኒህ ኢትዮዽያዊ ጻድቅ በ14ኛው መቶ ክ/ዘ በጣና ገዳማትውስጥ ያበሩ ኮከብ ናቸው:: ከ7ቱ ከዋክብት (አባ ዮሐንስ፣ አባ ታዴዎስ፣ አባ ያፍቅረነ እግዚእ፣ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አባ ሳሙኤል ዘቆየጻና አባ ሳሙኤል ዘጣሬጣ ) እርሳቸው አንዱ ናቸው:: እነዚህ አበው ከገዳማዊ ሕይወታቸው ባሻገር በምስጉን የወንጌል አገልግሎታቸው የሚታወቁ ናቸው:: ገድላቸው እንደሚለው አቡነ ያሳይ የዐፄ ዐምደ ጽዮን ቀዳማዊ ልጅ ሲሆኑ የተወለዱትም በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን ሽዋ: ተጉለት ውስጥ ነው:: ገና በልጅነታቸው ወደ አባታቸው ቤተ መንግስት የሚመጡ መነኮሳትን እግር እያጠቡ ሥርዓተ ምንኩስናን በድብቅ ያጠኑ ነበር:: ብሉይ ከሐዲስ የጠነቀቁ ናቸውና የአባታቸውን ዙፋን (ልዑልነት) ስለ ፍቅረ ክርስቶስ ንቀውት እየዘመሩ ጠፍተው ወደ ትግራይ ተጓዙ:: በዚህም ምክንያት 'መናኔ መንግስት' ይባላሉ:: በዚያም ወደ ደብረ በንኮል ገዳም ውስጥ ገብተው የታላቁ አባት የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ደቀ መዝሙር ሆኑ:: ቀደም ሲል የጠቀስናቸው 7ቱ አበው በዚያ ነበሩና 7ቱም በአንድ ቀን ሲመነኩሱ ገዳሙ የተቃጠለ እስኪመስል ድረስ ብርሃን ወርዶ ነበር:: አቡነ ያሳይ በረድእነት በቆዩበት ዘመን ዛፎችን መትከል ይወዱ ነበር:: ከትሩፋት መልስም በልብሳቸው ውሃ እየቀዱ ያጠጡ ነበር:: በተለይ "ምዕራገ ጸሎት" የሚባለው ተአምረኛ ዛፍ ዛሬ ድረስ አለ ይባላል:: አቡነ ያሳይ ጊዜው በደረሰ ሰዓት ከአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ተባርከው: ከ2ቱ ባልንጀሮቻቸው (አቡነ ሳሙኤል ዘዋሊና አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ) ጋር ወደ ጣና ሐይቅ መጡ:: በዚያም አካባቢ ተአምራትን እየሠሩ ሕዝቡንም እያስተማሩ ከቆዩ በኋላ ጌታ ወደየፈቀደላቸው ቦታ ተለያዩ:: አቡነ ሳሙኤል ወደ ዋልድባ: አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ወደ ገሊላ: ከዚያ ወደ ጉጉቤ ሲሔዱ አቡነ ያሳይ መንዳባ ውስጥ ገቡ:: ጻድቁ ወደ አርባ ምንጭ ሒደው ታቦተ መድኃኔ ዓለምን ይዘው ሲመጡ ጣናን የሚሻገሩበት አጡ:: ጌታን ቢማጸኑት:- "ምነው እሷን ድንጋይ ባርከህ አትቀመጥባትም?" አላቸው:: እሳቸውም በእምነት: ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ጣናን ተሻገሩት:: ይህንን ከርቀት ያዩ የዘመኑ ሰዎች "ብዙ ተአምር አይተናል: ነገር ግን ማን እንደ አባ! ጣናን በድንጋይ የተሻገረ" ሲሉ አድንቀዋቸዋል:: ጻድቁ ጣናን ተሻግረው: ገዳም መሥርተው: ብዙ አርድእትን አፍርተው: በተጋድሎ ሕይወታቸው ቀጥለዋል:: በተለይ ዛሬ ድረስ የሚተረከው የ'አትማረኝ' ታሪክም የሚገኘው እዚሁ ገዳም ውስጥ ነው:: ታሪኩም በየዋህነት "አትማረኝ" ብለው ጸልየው ጣናን ያለ ታንኳ በእግራቸው የረገጡ አባትን የሚመለከት ሲሆን ከአቡነ ያሳይ ጋርም ወዳጅ ነበሩ:: አባታችን አቡነ ያሳይ ለዘመናት በቅድስና ኑረው: ቅዱሳንንም ወልደው መስከረም 14 ቀን ታመሙ:: "ጌታ ሆይ!" ብለው ቢጠሩት መድኃኔ ዓለም መጣላቸው:: ጣና በብርሃን ተከበበች:: ጌታም "ወዳጄ! ስለ ድካምህ: ደጅህን የረገጠውን: መታሰቢያህን ያደረገውን: በስምህ የተማጸነውን ሁሉ ከነትውልዱ እምርልሃለሁ" ብሏቸው ነፍሳቸውን አሳረገ:: አበውም ሥጋቸውን ገንዘው እዚያው መንዳባ መድኃኔ ዓለም ውስጥ ቀበሩት:: ዐጽማቸው ዛሬም ድረስ ይገኛል:: ††† አምላከ ጻድቃን በምልጃቸው የበዛች ኃጢአታችንን ይቅር ይበለን:: በረከታቸውንም ያብዛልን:: ††† መስከረም 14 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.አባ አጋቶን ዘዓምድ 2.አቡነ ያሳይ ዘመንዳባ 3.አባ ጴጥሮስ መምሕረ ጻና (ጣና) 4.ቅዱስ ዴግና ቀሲስ ††† ወርሐዊ በዓላት 1.አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) 2.ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ 3.ቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ 4.ቅዱስ ሙሴ (የእግዚአብሔር ሰው) 5.አባ ስምዖን ገዳማዊ 6.አባ ዮሐንስ ጻድቅ 7.እናታችን ቅድስት ነሣሒት ††† "ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል:: ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል:: ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ውሃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ እውነት እላቹሃለሁ ዋጋው አይጠፋበትም::" ††† (ማቴ. ፲፥፵፩) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

Watch "የመስቀል ደመራ መዝሙሮች ስብስብ#1 Ethiopian meskel demera mezmur collection _መኀትው ቲዩብ_mehatew tube" on YouTube https://youtu.be/AyVTnGU9zxc

Watch "አፈታሪኮች እና አስፈላጊነታቸው / Meskel special / Free talk on Folklore" on YouTube https://youtu.be/r1If3oyJ8GA