ar
Feedback
Ministry of innovation and technology (MinT)

Ministry of innovation and technology (MinT)

الذهاب إلى القناة على Telegram

Ministry of innovation and Technology (MinT) is a governmental institution ...

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ministry of innovation and technology (MinT)

تُعد قناة Ministry of innovation and technology (MinT) (@mintethiopia) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 11 390 مشتركاً، محتلاً المرتبة 4 553 في فئة السياسة والمرتبة 2 920 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 11 390 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 06 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 281، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 17، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 9.99‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 5.03‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 1 138 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 573 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 5.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Ministry of innovation and Technology (MinT) is a governmental institution ...

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 07 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة السياسة.

11 390
المشتركون
+1724 ساعات
+497 أيام
+28130 أيام
أرشيف المشاركات
ኢኒሼቲቩ ከታቀደው ጊዜ ቀድሞ ግቡን በማሳካቱ ወደ ሰባት ሚሊዮን ተሳታፊዎች መስፋፋቱ፣ የአጋርነቱን ስኬትና ትርጉም ያለው አዎንታዊ ተጽዕኖ የሚያንጸባርቅ ከመሆኑም በላይ፣ ሁለቱ መንግሥታት ወጣቶችንና
ኢኒሼቲቩ ከታቀደው ጊዜ ቀድሞ ግቡን በማሳካቱ ወደ ሰባት ሚሊዮን ተሳታፊዎች መስፋፋቱ፣ የአጋርነቱን ስኬትና ትርጉም ያለው አዎንታዊ ተጽዕኖ የሚያንጸባርቅ ከመሆኑም በላይ፣ ሁለቱ መንግሥታት ወጣቶችንና የነገ መሪዎችን ያማከሉ የጋራ ፕሮጀክቶችን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያመላክት ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ልዩ ውጤት መሆኑን ገልጸው፣ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ስትራቴጂካዊ አጋርነት ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው የፓርላማ ውሎ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዟችን የ5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሸቲቭ ፕሮግራም ካስብነው በላይ አሳክተናል ማለታቸው ይታወቃል። https://www.abudhabinews.net/news/279170589/uae-ethiopia-expand-5-million-ethiopian-coders-initiative-to-7-million

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሚኒስትር የኢትዮጵያን ዲጂታል ስኬት አድንቀዋል —የኢትዮ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ወደ 7 ሚሊዮን አድጓል ==================== የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የካቢኔ ጉዳዮ
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሚኒስትር የኢትዮጵያን ዲጂታል ስኬት አድንቀዋል —የኢትዮ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ወደ 7 ሚሊዮን አድጓል ==================== የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ክቡር መሐመድ ቢን አብደላ አል ገርጋዊ የ«5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ» ወደ 7 ሚሊዮን ተሳታፊዎች ማደጉን መግለጻቸውን የአቡዳቢ ኒውስ፣ ሐምሌ 6 ቀን 2026 እ.ኤ.አ. ዘግቧል። በዘገባው ይህ ውሳኔ በሁለቱ ወዳጅ አገራት መካከል ያለው አጋርነት ያስመዘገበው ልዩ ውጤት የሚያንጸባርቅ መሆኑን ክቡር ሚኒስትር መሐመድ ቢን አብደላ አል ገርጋዊ መግለጻቸው ተጠቁሟል። ክቡር አል ገርጋዊ በመንግሥት ዘመናዊነት ዘርፍ የተመሠረተው የኢትዮጵያ–ኤምሬቶች አጋርነት፣ በሁለቱም አገራት አመራሮች ራዕይና መመሪያ ልዩ ውጤቶችን ማስመዝገቡን የገለጹ ሲሆን፤ ሁለቱ አገራትም በተለያዩ ዘርፎች የላቀ የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዳላቸውም አስታውሰዋል። ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ያለው አጋርነት ዓለም አቀፍ ትብብር ማህበረሰቦችንና መንግሥታትን በማሳደግ፣ የሰው ሀብትን በማብቃት እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን በመደገፍ ረገድ ያለውን ተጨባጭ ተጽዕኖ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተጠናቀቀው ዓመት የሀገር አቀፍ የሞባይል ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን እንዲሁም የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች 61 ሚሊዮን የደረሱ ሲሆን፣ 183 አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በለሙበትና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታርት
+6
በተጠናቀቀው ዓመት የሀገር አቀፍ የሞባይል ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን እንዲሁም የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች 61 ሚሊዮን የደረሱ ሲሆን፣ 183 አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በለሙበትና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታርትአፖች ድጋፍ አግኝተው 18,173 አዳዲስ የሥራ ዕድል የፈጠሩበት ስኬታማ የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራ ተከናውኗል። ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለ1,200 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ፣ በሐረር ከተማ ለአቅመ-ደካማ ዜጎች የሚሆኑ 12 መኖሪያ ቤቶችን በ26 ሚሊዮን ብር ወጪ የመገንባት ሥራ አጠናቆ ለአቅመ ደካሞች ያስተላለፈ ሲሆን በተለያዩ አካባቢወች ከ50 ሺህ በላይ ችግኞች መተከላቸው ሪፖርት ቀርቧል። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የስትራቴጂ ጉዳዮች ሥራ አስፈፃሚ አቶ አዝማች ደሳለኝ እቅዶቻችንን ለማሳካት በተደረገው ጥረት የተገኙ ውጤቶችን በዝርዝር በማቅረብ፣ በቀጣይ ይህንን በማጠናከር የላቀ ውጤት እንደሚጠበቅ ገልፀዋል። አክለውም ጠንካራ ጎኖችን በማስፋት ሥራዎችን በእቅድ ይዘን ከሰራን፣ በቀጣይ የምንሻውን ውጤት ለሀገራችን ኢኮኖሚ ዕድገት ለማዋል ከዚህ በላይ መትጋት ይጠበቅብናል ብለዋል። በመጨረሻም መድረኩን ያጠቃለሉት ከፍተኛ አመራሮች የተመዘገቡ ጠንካራ ጎኖችን በማጠናከር በአዲሱ በጀት ዓመት የአሠራር ስረአትን በማሻሻል፣ ቀልጣፋና የተቀናጀ አገልግሎት ለመስጠትና የተጀመረውን ሁለንተናዊ የሪፎርም ሥራ በጋራ ርብርብ ለማስቀጠል ጽኑ የጋራ አቋም በመያዝ ውይይቱን በስኬት አጠናቀዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የጋራ ውይይት አካሄደ። ================ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አጠቃላይ አመራሮችና
+7
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የጋራ ውይይት አካሄደ። ================ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አጠቃላይ አመራሮችና ሰራተኞች በተሳተፉበት መድረክ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማን በጥልቀት በማካሄድ፣ በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቷል። በመድረኩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት ሚኒስትር ዴኤታዋ ዶ/ር ፎዚያ አሚን፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደ ሀገር ሊያሳካቸው የሚገቡ ዘርፈ-ብዙ ስራዎች በእቅዳቸው መሰረት ስኬታማ ውጤት መመዝገባቸውን ገልፀዋል። አክለውም ተቋማዊ ሪፎርሙን ለማሳካት የሰው ኃይል አቅምና ምቹ የሥራ ከባቢ መፍጠር ወሳኝ መሆኑን በመጠቆም፣ አሁን ላይ የተደረሰበትን ስኬት በማስፋት በቀጣዩ ዓመት የመንግሥት አገልግሎቶችን ይበልጥ ዲጂታላይዝ ማድረግና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) መሠረተ-ልማትን ማስፋፋት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሥራ አመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አይነማር፤ ዓለም በቴክኖሎጂው ዘርፍ በከፍተኛ ፍጥነት እየረቀቀ ባለበት በዚህ ዘመን ተወዳዳሪ ለመሆን፣ ዕቅዶችን ከግብ የሚያደርስ አቅም በመገንባት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ሊያሳድጉ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ በትኩረትና በትብብር መሰራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በበጀት ዓመቱ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ 420 የንግድ ተቋማት ወደ ኤሌክትሮኒክ ግብይት እንዲቀላቀሉ ሪፖርት የተደረገ ሲሆን፣ በ"መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት" አማካኝነት የኦንላይን የመንግሥት አገልግሎቶችን 32 በመቶ ማድረስና የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ተመዝጋቢዎችን ቁጥር 48 ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል ተብሏል።

We're looking for idea-stage AI startups. Not polished products, not finished projects. Just a real problem, real users, and
We're looking for idea-stage AI startups. Not polished products, not finished projects. Just a real problem, real users, and a team ready to build fast. If you've been sitting on an idea, this is the weekend to start it. You'll have 20 hours to turn it into a working MVP, with credits and AI tools from Cursor and our AI credit sponsors: Addis AI, ElevenLabs, Fal, Whisperflow, and more. Food, mentors, and support are covered the whole time. We're taking 60 teams. Have a team? Register with your team code. Coming alone? Tell us your skills and we'll match you into a team of 5, or fill your team's open spots. Incubation partners will be in the room too, including Cursor, the Addis Ababa University Startup Center, Gheero, and others, ready to back promising teams with mentorship, workspace, and follow-up. Investors will be there looking for ideas worth funding. Before you apply, read the overview on the Luma page carefully. Apply here: https://luma.com/qr9ljv2c

Come with an idea. Leave with a startup. Cursor AI Hackathon Ethiopia is happening July 25–26 at Adwa Museum. We’re partnerin
Come with an idea. Leave with a startup. Cursor AI Hackathon Ethiopia is happening July 25–26 at Adwa Museum. We’re partnering with Cursor and Ethio telecom to bring builders together for Ethiopia’s largest AI hackathon.

በብሔራዊ የጥናትና ምርምር (R&D) ወጪ ጥናት ማስፈጸሚያ ላይ የምክክር አውደ ጥናት ተካሄደ። ================ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጋር
+9
በብሔራዊ የጥናትና ምርምር (R&D) ወጪ ጥናት ማስፈጸሚያ ላይ የምክክር አውደ ጥናት ተካሄደ። ================ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጋር በመተባበር በብሔራዊ የጥናትና ምርምር (R&D) ወጪ ጥናት ማስፈጸሚያ ላይ የምሁራንና የባለድርሻ አካላት የምክክር አውደ ጥናት ተካሂዷል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ባይሳ በዳዳ በመድረኩ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ይህ አገራዊ ጥናት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ጥራቱን የጠበቀ የጥናትና ምርምር ስታቲስቲክስ መረጃን ለማፍራት የላቀ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። አያይዘውም ሚኒስትር ዴኤታው የዚህን ታላቅ አገራዊ ጥናት ውጤታማነትና ስኬት ሙሉ በሙሉ ማረጋገጥ የሚቻለው በየዘርፉ ያሉ ባለድርሻ አካላት በንቁ ተሳትፎ ኃላፊነታቸውን መወጣት ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጀሚላ መሐመድ በበኩላቸው፣ ጥናቱ የተሟላና ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን የጠበቀ እንዲሆን ተቋማቸው ከሚኒስቴሩ ጋር በመቀናጀት አስፈላጊውን የስታንዳርድና የጥራት ቁጥጥር ድጋፍ በቁርጠኝነት እንደሚያደርግ አብራርተዋል። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሀገራዊ ምርምር ልማት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሀብታሙ አበራ በበኩላቸው፣ በኢትዮጵያ የጥናትና ምርምር ታሪካዊ ጉዞና በጥናቱ ወቅት ሊወሰዱ በሚገባቸው ዓለም አቀፍ መልካም ተሞክሮዎች ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ ለመድረኩ አቅርበዋል። ይህ አገር አቀፍ የምክክር መድረክ የእያንዳንዱን ዘርፍ የመረጃ ክፍተት የሚሞሉ ውይይቶችን በማጠናቀቅ፣ የወደፊት የጋራ የድርጊት መርሃ ግብር በማውጣትና ለጥናቱ ስኬታማነት በጋራ እንደሚሰራ ተጠቁሟል።

ይህ አገራዊ ሰነድ ይበልጥ የተሟላ እንዲሆንና ለፖሊሲ ቀረጻ ስልታዊ ጠቀሜታ እንዲሰጥ ለማድረግ፣ በተነሱት አንዳንድ ይዘቶች ላይ የማረሚያ ሥራዎች እንዲካተቱበት በገምጋሚዎቹ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ በመጨ
+5
ይህ አገራዊ ሰነድ ይበልጥ የተሟላ እንዲሆንና ለፖሊሲ ቀረጻ ስልታዊ ጠቀሜታ እንዲሰጥ ለማድረግ፣ በተነሱት አንዳንድ ይዘቶች ላይ የማረሚያ ሥራዎች እንዲካተቱበት በገምጋሚዎቹ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ በመጨረሻም የቀረቡት ገንቢ አስተያየቶች ተካተውበት ሰነዱ በላቀ ደረጃ ተጠናቆ ለይፋዊ አገልግሎት እንዲበቃ የጋራ መግባባት ላይ በመደረስ አውደ ጥናቱ በስኬት ተጠናቋል፡፡

በቴክኖሎጂ ልማትና እውቀት ሽግግር ጥናት ላይ ያተኮረ የማረጋገጫ አውደ ጥናት ተካሄደ። ================ በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት እና የእውቀት ሽግግር ሥነ-ምህዳር ዙሪያ የሚስተዋሉ ተግ
+6
በቴክኖሎጂ ልማትና እውቀት ሽግግር ጥናት ላይ ያተኮረ የማረጋገጫ አውደ ጥናት ተካሄደ። ================ በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት እና የእውቀት ሽግግር ሥነ-ምህዳር ዙሪያ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችንና መፍትሄዎቻቸውን ለመለየት የተካሄደውን የዳሰሳ ጥናት የመጨረሻ ሪፖርት ለመገምገም የሚያስችል የማረጋገጫ አውደ ጥናት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማሕበር አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኮምፓስ ኤኢፒኢዲ (Compass AEPED) አማካሪ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጋር በመተባበር ያጠናው የዚህ አውደ ጥናት ዋና ዓላማ የጥናቱን ግኝቶችና ምክረ-ሀሳቦች ከሀገሪቱ ነባራዊ እውነታ ጋር ማጣጣምና የቁልፍ ባለድርሻ አካላትን ቁርጠኝነት ማረጋገጥ ነው፡፡ በመድረኩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር መሪ ስራ አስፈፃሚ ተክለማርያም ተሰማ (ዶ/ር) ጥናቱ በሀገር ውስጥ የለሙ ቴክኖሎጂዎችን አቀባበል ዝግጁነት ለመለካትና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያለውን ፋይዳ ገልጸው፣ ተሳታፊዎች ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ጥልቅ አስተያየቶችን እንዲሰጡበት አሳስበዋል፡፡ አማካሪ ኩባንያው ከሚኒስቴሩ በተሰጠው ፕሮፖዛል መነሻነት የዘርፉን ወቅታዊ ገጽታ፣ መልካም አጋጣሚዎችና ተግዳሮቶች በዝርዝር በመለየት የቀጣይ አቅጣጫዎችን ያመላከተ ሙያዊ፣ ስነ-ምግባራዊና ስልታዊ ትንታኔ አቅርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በውይይቱም የተመደቡ የዘርፉ ገምጋሚዎች የሰነዱን ይዘት፣ አቀራረብና ስልቶች በዝርዝር በመተቸት፣ ጥናቱ በራስ አቅም የሚመራ የቴክኖሎጂ ሥነ-ምህዳር ለመገንባትና ለፖሊሲ አውጪዎች እንደ ጠቃሚ ግብዓት ለማገልገል የሚያስችል መሆኑን በምክረ-ሀሳባቸው አረጋግጠዋል፡፡

በመጨረሻም ሁለቱ ወገኖች በቀጣይ በሚኖራቸው የሥራ ግንኙነት መግባባት ላይ የሚደረስባቸውን ልዩ ልዩ የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎችን በመለየት፣ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በጋራ ለመግባት ሙሉ ስምምነት
+2
በመጨረሻም ሁለቱ ወገኖች በቀጣይ በሚኖራቸው የሥራ ግንኙነት መግባባት ላይ የሚደረስባቸውን ልዩ ልዩ የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎችን በመለየት፣ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በጋራ ለመግባት ሙሉ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአፕል ኩባንያ የአውሮፓ-እስያና አፍሪካ የንግድ ፖሊሲና የመንግስት ግንኙነት አመራር ጋር በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮ ዙሪያ ተወያዩ። ================
+6
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአፕል ኩባንያ የአውሮፓ-እስያና አፍሪካ የንግድ ፖሊሲና የመንግስት ግንኙነት አመራር ጋር በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮ ዙሪያ ተወያዩ። ================ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ የአፕል ኩባንያ የአውሮፓ-እስያና አፍሪካ የንግድ ፖሊሲና የመንግስት ግንኙነት ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ሚስተር ዓሊ ካናፈር (Ali Khanafer) ጋር በኢትዮጵያ የአፕል ቴክኖሎጂዎችን በኢንቨስትመንትና ንግድ ዘርፍ ለመሰማራት በሚቻልባቸው ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል። በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ዘለቄታዊና ባለብዙ ዘርፍ የኢኮኖሚ ግንባታ በተጠናከረ መልኩ እየተተገበረ እንደሚገኝ የገለጹት ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ፣ በዲጂታል ኢኮኖሚው መስክ ለሚሰማሩ የውጭ አገር ኩባንያዎች በሀገሪቱ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ፖሊሲ የተደገፉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን አስገንዝበዋል። አክለውም ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በዲጂታል 2025 ያስመዘገበችውን ስኬት እና ስኬቱ ለዲጅታል ኢንቨስትመንት የፈጠረውን መልካም አጋጣሚ እንዲሁም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የሚተኮርባቸውን ጉዳዮች ለኩባንያው ተወካዮች አብራርተዋል ። በውይይቱ ላይ ሚስተር ዓሊ ካናፈር በበኩላቸው፣ በዲጂታል ኢኮኖሚው ዘርፍ የአፕል ቴክኖሎጂዎችን ኢንቨስትመንት ይበልጥ ለማስፋፋትና አብሮ ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አብራርተው፣ አፕል ኩባንያ እያደገ በመጣው የኢትዮጵያ ዲጅታል ኢኮኖሚ ውስጥ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳለው በመግለጽ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተባብሮ ለመስራት እንዲችል ሁኔታዎች እንዲመቻቹለት ጠይቀዋል ።

የአሜሪካው AGOGE Partners LLC ኃላፊ ቲዮዶር ቲኦሃሪስ በበኩላቸው፤ የሚኒስቴር መስሪያቤቱ የፖሊሲ ትግበራና ቁጥጥር ሚና ከአጎጌ ፓርትነርስ የኢንቨስትመንት ቅልጥፍና ጋር የሚያጣመረው ይህ ስ
+2
የአሜሪካው AGOGE Partners LLC ኃላፊ ቲዮዶር ቲኦሃሪስ በበኩላቸው፤ የሚኒስቴር መስሪያቤቱ የፖሊሲ ትግበራና ቁጥጥር ሚና ከአጎጌ ፓርትነርስ የኢንቨስትመንት ቅልጥፍና ጋር የሚያጣመረው ይህ ስምምነት፣ በሀገሪቱ የስታርትአፕ ሥነ-ምህዳርን በማነቃቃት ለወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠርን ዋና ዓላማው ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ትብብሩ የአካዳሚክ ምርምሮችን ወደ ገበያ ለመለወጥ የሚያስችሉ የማበጸጊያ (Incubation) ፕሮግራሞችን ከመቅረጽ ባለፈ፣ አጎጌ ፓርትነርስ ጅምር ዕድገት ድረጃ ላይ ለሚገኙ የሀገር ውስጥ ሥራ ፈጣሪዎች ወሳኝ የሆነ የካፒታልና የቴክኒክ ድጋፍ እንዲያመቻች ያደርጋል። በዚህም ሁለቱ ወገኖች በጋራ በሚያከናውኗቸው ምርምሮችና የፓይለት ፕሮጀክቶች አማካኝነት በባዮቴክኖሎጂ፣ በሕዋ ሳይንስ፣ በአየር ንብረት ተጸኖን በሚቋቋሙ ዘመናዊ ግብርና እንዲሁም በዲጂታል መሠረተ ልማት ዘርፎች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሠሩ ተመላክቷል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የአሜሪካው AGOGE Partners LLC በስትራቴጂካዊ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንቨስትመንት ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ================ የኢኖቬ
+5
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የአሜሪካው AGOGE Partners LLC በስትራቴጂካዊ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንቨስትመንት ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። ================ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአሜሪካው አጎጌ ፓርትነርስ ኤልኤልሲ (AGOGE Partners LLC) ጋር በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራና በኢንቨስትመንት ዘርፎች በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን ስትራቴጂካዊ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ እንደገለጹት፤ ይህ ስምምነት የሀገር ውስጥ የስታርትአፕ እና የኢንቨስትመንት ሥነ-ምህዳሩን በከፍተኛ ደረጃ በማጎልበት፣ ለወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል የሚፈጥርና ጀማሪ ኩባንያዎች ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲስፋፉ ምቹ ሁኔታን የሚያመቻች ነው። ይህ ስምምነት በባዮና ታዳጊ ቴክኖሎጂዎች፣ በሕዋ ሳይንስ፣ በአይኦቲ (IoT) እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በሚመራ ዘመናዊ ግብርና እንዲሁም በዲጂታል መሠረተ ልማት ዙሪያ ከፍተኛ ተፅዕኖ ባላቸው የጋራ የምርምርና ልማት (R&D) ሥራዎች ላይ ልዩ ትኩረት ያደርጋል። አጋርነቱ በቡራዩ የክህሎት ልማት ማዕከል (BTDC) ውስጥ የሚተገበሩ የወጣቶች የፈጠራ አቅም ግንባታ፣ የክህሎት ማሳደጊያና የሥራ ፈጠራ ማፋጠኛ ፕሮግራሞችን በልዩ ትኩረት ለመደገፍና ለማስፋፋት የተለየ ኃላፊነት ወስዶ እንደሚንቀሳቀስም ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያን ዲጂታል መጻኢ ዕድል እየቀየሩ ያሉትን ቁጥሮች ለማየት ወደ ጎን ይግለጡ → #PMOEthiopia@MinTEthiopia
+1
የኢትዮጵያን ዲጂታል መጻኢ ዕድል እየቀየሩ ያሉትን ቁጥሮች ለማየት ወደ ጎን ይግለጡ → #PMOEthiopia@MinTEthiopia

የኢትዮጵያን ዲጂታል መጻኢ ዕድል እየቀየሩ ያሉትን ቁጥሮች ለማየት ወደ ጎን ይግለጡ →
+1
የኢትዮጵያን ዲጂታል መጻኢ ዕድል እየቀየሩ ያሉትን ቁጥሮች ለማየት ወደ ጎን ይግለጡ →

የቻይና-ብሪክስ የሳይንስና ኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ፓርክ ሁለንተናዊ አገልግሎት ማዕከል ዳይሬክተር ዣንግ ዲያንሁይ በበኩላቸው፣ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በጋራ ለመሥራት በመቻላቸው የተሰማቸውን የላቀ
+2
የቻይና-ብሪክስ የሳይንስና ኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ፓርክ ሁለንተናዊ አገልግሎት ማዕከል ዳይሬክተር ዣንግ ዲያንሁይ በበኩላቸው፣ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በጋራ ለመሥራት በመቻላቸው የተሰማቸውን የላቀ ምስጋና አቅርበው፤ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በክህሎት ልውውጥ ዙሪያ የረጅም ጊዜ የትብብር ሥርዓት ለመዘርጋት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። አያይዘውም፣ የሁለቱን አገራት የምርምር ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎችን ለማስተሳሰር በትጋት እንደሚሠሩ ጠቁመው፣ የላቁ የቻይና የዘመናዊ ግብርና መፍትሔዎችና የምግብ ደህንነት መመርመሪያ መሣሪያዎች ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡበትን መንገድ እንደሚያመቻቹ አስታውቀዋል። ሁለቱ ወገኖች በጋራ ምክክራቸው ማጠቃለያ ላይ ቅድሚያ የሚሰጧቸውን የትብብር አጀንዳዎች በመለየትና ትስስራቸውን ይበልጥ በማጠናከር በቅንጅት ለመሥራት የሚያስችል አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከቻይና-ብሪክስ የሳይንስና ኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ፓርክ ጋር በጋራ ለመሥራት መከረ፡፡ ================ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የቻይና-ብሪክስ የሳ
+9
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከቻይና-ብሪክስ የሳይንስና ኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ፓርክ ጋር በጋራ ለመሥራት መከረ፡፡ ================ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የቻይና-ብሪክስ የሳይንስና ኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ፓርክ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዘርፎች ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ምክክር አካሂደዋል፡፡ ይህ በፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ አነሳሽነት የተቋቋመው ታዋቂ ፓርክ፣ በብሪክስ አገራት መካከል የቴክኖሎጂ ሽግግርን፣ የገበያ ትስስርን እና የኢንዱስትሪ አጋርነትን ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሠራ የሚገኝ ተቋም ነው። የተጀመረው አዲስ የትብብር መድረክ በቻይና እና በኢትዮጵያ መንግሥታት መካከል የተፈረሙ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስምምነቶችን እንዲሁም የብሪክስ የኢኖቬሽን ተነሳሽነቶችን በተጨባጭ ወደ ተግባር ለማሸጋገር ያለመ ነው፡፡ በውይይቱ ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ባይሳ በዳዳ ይህ አጋርነት የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ከማፋጠኑም በላይ፣ ለአገር በቀል የቴክኖሎጂ ስታርትአፖች እና ተመራማሪዎች ዓለም አቀፍ ዕድሎችን ይፈጥራል ብለዋል። አክለውም፣ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል የተቀናጀ የጋራ አሠራር እንዲሰፍን አስፈላጊውን መዋቅራዊና ተቋማዊ ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ የምርምርና ልማት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሀብታሙ አበራ፤ ከፓርኩ ምርምርና ልማት ጋር የሚደረገው ትስስር የሀገር በቀል ተመራማሪዎቻችን የፈጠራ ሥራዎች ወደ ምርትና ገበያ እንዲቀየሩ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል። የቻይና-ብሪክስ የሳይንስና ኢኖቬሽን ኢንኩቤሽን ፓርክ ሁለንተናዊ አገልግሎት ማዕከል ዳይሬክተር ዣንግ ዲያንሁይ በበኩላቸው፣ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በጋራ ለመሥ