ar
Feedback
ዜና ቤተክርስቲያን

ዜና ቤተክርስቲያን

الذهاب إلى القناة على Telegram

የተለያዩ በቅድስት በቤተክርስቲያን ዙሪያ መነሻ ያደረጉ ዜናዎችን ከቤተክርስቲያን ልሳናት ከሆኑ ምንጮች በማቅርብ መረጃ መለዋወጥ።

إظهار المزيد
1 464
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+47 أيام
-530 أيام
أرشيف المشاركات
የቀን : እረኛ : የሌሊት : ጠባቂ : ቅዱስ : ሚካኤል #ሰኔ_12_ቀን ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎሚያን ከዲያብሎስ መንጋጋ ያስጣለበት እንዲሁም የባሕራንን የሞቱን ጦማር ቀዶ ሠርግ ያደረገበትን እለት
የቀን : እረኛ : የሌሊት : ጠባቂ : ቅዱስ : ሚካኤል #ሰኔ_12_ቀን ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎሚያን ከዲያብሎስ መንጋጋ ያስጣለበት እንዲሁም የባሕራንን የሞቱን ጦማር ቀዶ ሠርግ ያደረገበትን እለት ነው ። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ልጆቿን ሰብስባ በዓልን ሰርታ በታላቅ ድምቀት ከዓመት ዓመት ታከብረዋለች ። መጋቤ ብሉይ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በተአምራቱ ዘወትር እንደሚጠብቀን ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ እንዲህ እያለ ይመሰክራል ፦ « የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የቀን እረኛ የሌሊት ጠባቂ ክንፎቹ የእሳት የሆነ ዘወትር የሚጠብቀን ቅዱስ ሚካኤል የእውነት የድንኳን ከተማ ነው ። » በማለት ተናግሯል ። በዚህ መሠረት ድንኳን ከቀን ሐሩር ከሌሊት ቁር እንደሚከለሉበት ሁሉ #ቅዱስ_ሚካኤልም በቃል ኪዳኑም የሚታመኑትን ሁሉ ከምሕረት አልባው ከዲያብሎስ ደባ ከአጋንንት ድብደባ ከዚህ ዓለም ፈተና ያድነናል ይታደገናል። ቅዱስ ሚካኤልም በቃል ኪዳኑ የሚታመኑትን ሁሉ ከምሕረት አልባው ከዲያብሎስ ደባ ከአጋንንት ድብደባ ከዚህ ዓለም ፈተና ያ ይጠብቀን። አሜን 🤲❤

photo content

እደምን ዋላችሁ ዛሬ የእናንተን መልካም ፍቃድ ለመጠየቅ ነው የምትችሉ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ይህን ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ዩቲዩብ ቻናል ሰፕስክራይብ ኡድርጉልን። https://www.youtube.com/@LikanatTube እግዚአብሔር ያክብራችሁ!!

ቃለ ህይወት ያሰማልን!!

የሚስማማ!! ሀገር በስው ሳይሆን እንደ ሰው በሚያስብ ትመራለች!

አንድ የዜን መምህርና ደቀ መዝሙሩ በጫካ ውስጥ ሲጓዙ፣ አንድ ትልቅ እባብ አንዲትን እንቁራሪት አፎቶ ሊውጣት ሲታገል ያያሉ። እንቁራሪቷ በስቃይ ትጮኻለች። ... ደቀ መዝሙሩ በመገረም መምህሩን ጠየቀ
አንድ የዜን መምህርና ደቀ መዝሙሩ በጫካ ውስጥ ሲጓዙ፣ አንድ ትልቅ እባብ አንዲትን እንቁራሪት አፎቶ ሊውጣት ሲታገል ያያሉ። እንቁራሪቷ በስቃይ ትጮኻለች። ... ደቀ መዝሙሩ በመገረም መምህሩን ጠየቀው። ... "መምህር ሆይ፣ እንደ ዜን ፍልስፍና በተፈጥሮ ህግ ውስጥ ጣልቃ መግባት የለብንም። እባቡ መብላት አለበት፣ እንቁራሪቷም መሞት ተፈጥሮዋ ነው። ታዲያ እዚህ ጋ ገለልተኛ ሆነን ዝም ልንል ይገባል ወይስ ልናድናት?" ... መምህሩ ምንም ሳይናገር በዱላው እባቡን መትቶ እንቁራሪቷን አስመለጣት። እባቡም ተቆጥቶ ወደ ጫካው ሄደ። ... ደቀ መዝሙሩ ግራ ገብቶት፡ "መምህር፣ ታዲያ ገለልተኝነትና የተፈጥሮ ህግስ የት ሄደ?" አለው። ... "እባቡ እንቁራሪቷን ሲይዛት፣ ገለልተኝነት የሚባል ነገር አብቅቷል። አንተ ዝም ብለህ በመቆምህ 'ገለልተኛ' የሆንክ መስሎሃል፤ ነገር ግን በዝምታህ እባቡ እንቁራሪቷን እንዲበላት እየረዳኸው ነበር። በበደል ፊት ዝምታ ምርጫ እንጂ ገለልተኝነት አይደለም።" ... ፍትህ ሲጓደል፣ ሰብዓዊነት ሲበደል፣ ዝም ማለት ልክ አይደለም። ዝምታ ወይም ገለልተኝነት በራሱ ለጨቋኙ የተሰጠ ድምፅ ነው። ምንም አላደረግኩም የሚለው ደቀ መዝሙር፣ በተግባር ግን ከእባቡ ጎን ቆሞ ነበር። ... ክፉ ነገር ሲደረግ እያዩ ምንም እንዳላዩ መሆን፣ ክፋቱ እንዲቀጥል መፍቀድ ነው። ጥፋትን አለማስቆም ጥፋቱን እንደመደገፍ ይቆጠራል። ስለዚህ ግፉ ስናይ ስንመለከት ዝም ልንል አይገባም። #nomore #ethiopianorthodoxunderattack #አርሲ #ኦርቶዶክስ

ይፈርዳል!

በየኔታ በአማን ነጸረ በአዘቦቱ፥ መንበር ከካህኑ በቀር ምዕመን ቀርቶ ዲያቆንም መንካት አይፈቀድለትም። ክፉ ቀን ሲመጣ ግን የማይሆነውም ይሆናል። ይህ ግፉዕ ማኅበረ ምዕመን ቤቱን፣ ከብቱን፣ ግማሽ ሕ
በየኔታ በአማን ነጸረ በአዘቦቱ፥ መንበር ከካህኑ በቀር ምዕመን ቀርቶ ዲያቆንም መንካት አይፈቀድለትም። ክፉ ቀን ሲመጣ ግን የማይሆነውም ይሆናል። ይህ ግፉዕ ማኅበረ ምዕመን ቤቱን፣ ከብቱን፣ ግማሽ ሕይወቱን የኋሊት ጥሏል፣ ተነጥቋል። መንበሩን፣ ደመ ክርስቶስ የሚሠዋበትን ግን በክፉ ቀን እንኳ አልዘነጋም። ልቤን የደቃኝ ምስል። ወገኖቻችሁ ድኩማን ብንሆንም፥ ይህን መታመናችሁን መገፋታችሁን ከሰማይ የሚያይ አምላክ አላችሁ።

የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ!!

What Causes Conflict? / የግጭት መንስኤዎች ምንድን ናቸው? ================ ​Poor Communication — ደካማ የመገናኛ ዘዴ / የሐሳብ ልውውጥ እጥረት ​Lack of C
What Causes Conflict? / የግጭት መንስኤዎች ምንድን ናቸው? ================ ​Poor Communication — ደካማ የመገናኛ ዘዴ / የሐሳብ ልውውጥ እጥረት ​Lack of Compromise — የአስተማማኝ ስምምነት / የመወያየት እጥረት (እልህኝነት) ​Needs not Met — ፍላጎቶች አለመሟላት ​Prejudice — አድልዎ / ቅድመ-ፍርድ ​Intolerance — ያለመቻቻል ​Self-Interest — የግል ጥቅም / ራስን መውደድ ​Ignorance — አለማወቅ / ድንቁርና ​Desire for Power — የስልጣን ጥማት / የስልጣን ፍላጎት ​Lack of Empathy — ለሌሎች ሰዎች ስሜት አለማዘን (የእርህራሄ እጥረት) ​Making Assumptions — ያለማስረጃ መገመት / ግምታዊ አስተሳሰብ

አርሴናል ወጣቱን አስለቅሷል #ጸሎት #viralvideochallenge #መንፈሳዊ #Ethiopia #viralvideo #ኦርቶዶክስ #አርሴናል

ኢየሱስ የተነበበባት ፊደላችን ተወለደች። የትኛውም ከአንደበታችን የሚወጣ ቃል ረቂቅ ነው። አይታይም አይጨበጥም። "ኢየሱስ" ብለን በቃላችን ብቻ ብንናገር ስሙ አይዳሰሰም አይታይም። ይህን ስም ማየትና
ኢየሱስ የተነበበባት ፊደላችን ተወለደች። የትኛውም ከአንደበታችን የሚወጣ ቃል ረቂቅ ነው። አይታይም አይጨበጥም። "ኢየሱስ" ብለን በቃላችን ብቻ ብንናገር ስሙ አይዳሰሰም አይታይም። ይህን ስም ማየትና መንካት ከፈለግን የግዱን ኢየሱስ ብለን በፊደል መጻፍ ያስፈልገናል። በወንጌል "እግዚአብሔር መንፈስ ነው" ተብሎ ተጽፏል።መንፈስ ማለት ረቂቅ ማለት ነው። ረቂቁ አምላክ እንዴት ገዘፈ? እንዴት ታየ? በፊደል ስለተገለጠ ነዋ። ፊደል ያልናት ድንግል ማርያምን ነው። ረቂቁ አምላክ ሰው ስለሆነባት ስለታየባት ቤዛ ሊሆነን ግዙፍ ሥጋን ስለነሳባት። እሷ ፊደል ከሆነች ልጇ ወንጌል ነው። ወንጌልን ያለ ፊደል ምን ብለህ ታነበዋለህ? እንዴትስ ታየዋለህ? ወንጌላችን የሚጻፍባት ፊደል ዛሬ ከሐና ማሕፀን ከኢያቄም አብራክ ተገኘች። ሰአሊ ለነ ቅደስት!

photo content

ቁርአን ክርስቲያን አደረገኝ አንድ ቀን "ኢየሱስ አምላክ አይደለም" እያልኩ በአደባባይ ስሰብክ ነበር። ከዚያም ሲሰሙኝ ከነበሩት መካከል አንዲት ሴት "ኢየሱስ ራሱ ማነው" ብላ ጠየቀችኝ። ስለዚህ ከዚያ ሰአት ጀምሮ ስለኢየሱስ ብዙ ለማወቅ ማሰብ ጀመርኩ። መጀመር ያለብኝም ከቁርአን እንደሆነ ስለተሰማኝ ከቁርአን ጀመርኩ። 👉በቁርአን 114 ሱራዎችና 6666 አያዎች አሉ 👉የሚገርመው ግን በቁርአን ውስጥ የኢየሱስ ስም 25 ጊዜ የተፃፈ ሲሆን በእስልምና የነብያት መደምደሚያ የተባለው ነብዩ መሐመድ እንኳን 4 ጊዜ ብቻ ነው የተጠቀሱት። ◉ ግን ለምን ይሆን የእስልምና ዋነኛ ነብይ ከሆነው በላይ የኢየሱስ ስም የተጠቀሰው ?? ◉ቁርአን ከመሐመድ በላይ ስለኢየሱስ መናገር የፈለገው ለምንድነው ?? 👉በቁርአን አንድም የሴት ስም አልተጠቀሰም። የመሐመድ እናት አልተጠቀሰችም፤ ሚስቶቹ አልተጠቀሱም፤ ግን የሚገርመው የኢየሱስ እናት ማርያም በቁርአን ውስጥ ስሟ የተፃፈ ብቸኛዋ ሴት ናት። ◉ግን ለምን ይሆን ቁርአን የኢየሱስን እናት ብቻ የጠቀሰው ?? ◉ ለምንድነው ቁርአን ትኩረቱ ኢየሱስ ላይ የሆነው ?? 👉ቁርአን በሱራ 3:45-55 ውስጥ ስናነብ ኢየሱስ ➜የእግዚአብሔር ቃል ➜የእግዚአብሔር መንፈስ ➜እና መሲሕ እንደሆነ ይናገራል 👉የሚገርመው ግን ታላቁ ነብይ መሐመድ የእግዚአብሔር ቃል አይደለም፣ የእግዚአብሔር መንፈስ አይደለም፣ እንዲሁም መሲህ አይደለም። 👉በቁርአን ውስጥ ➜ኢየሱስ በህፃንነቱ ወይም ከተፈጥሯዊ ዕድሜ ቀድሞ ማውራት እንደጀመረ ይናገራል ➜ኢየሱስ ከጭቃ ወፍ ሰርቶ ለወፏ ሕይወት እንደሰጠ ይናገራል ➜ኢየሱስ በሽተኞችን እንደፈወሰ ይናገራል ➜ኢየሱስ ሙታንን እንዳስነሳ ይናገራል ➜ኢየሱስ ሳይሞት ወደሰማይ እንዳረገ ይናገራል ➜አሁንም በሰማይ ህያው ሆኖ እንዳለና ዳግም ተመልሶ እንደሚመጣ ይናገራል 👉ነገር ግን ስለታላቁ የእስልምና ነብይ እንዲህ አይልም ➜መሐመድ በህፃንነቱ ማውራት አልጀመረም ➜መሐመድ ከጭቃ ወፍ ሰርቶ ሕይወት መስጠት አልቻለም ➜መሐመድ በሽተኞችን አልፈወሰም ፤ አንድስ እንኳን!!! ➜መሐመድ ሙታንን አላስነሳም ፤ ኸረ እንዲያውም እራሱ ሞቷል። ➜ መሐመድ ሳይሞት ወደሰማይ አላረገም ፤ በመቃብር በስብሷል ➜ መሐመድ አሁን ህያው አይደለም ፤ ተመልሶም አይመጣም 🔹በነዚህ በሁለቱ ነብያት መካከል ትልቅ ልዩነት አለ ማለት ነው። በመካከላቸው ይኸን ያህል ከፍተኛ ርቀት እንዴት ሊኖር ቻለ ?? ➜በዚህ ሀሳብ ተሞልቼ 🔹ቁርአን ወዳስተማረኝ ወደ ኮሌጅ መምህሬ ሄጀ አምላክ አፅናፈ አለሙን እንዴት እንደፈጠረ ስጠይቀው በቃሉ እንደፈጠረ ነገረኝ። 🔹አሁን ጥያቄዬ "ቃል ፈጣሪ ነው ወይስ ፍጡር" የሚል ሆነ፤ ቁርአኔ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ይናገራል። 🔹መምህሬ ቃል ፈጣሪ ነው ካለ ኢየሱስ ፈጣሪ ነው ማለት ነው። ፍጡር ነው ማለትም አይችልም ፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ዘላለማዊ ነው። 🔹ስለዚህ መምህሬ ግራ ስለገባው "ቃል ፍጡርም ተፈጣሪም አይደለም" ከዚህ ውጣ አለኝ። 🔹እኔም ቃል ፈጣሪም ፍጡርም ካልሆነ ክርስቲያኖች ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ማለታቸው ልክ ነው አልኩት። 🔹መምህሬም ተናዶ "ቃል የእግዚአብሔር ልጅ ከሆነ" የእግዚአብሔርን ሚስት አሳየኝ ምክንያቱም ያለሚስት ልጅ መውለድ አይቻልም አለኝ"። 🔹እኔም ቁርአን "እግዚአብሔር ያለ አይን ማየት ፤ ያለ ምላስም መቅመስ እንደሚችል ከተናገረ ያለሚስት ልጅ የማይወልድበት ምንም ምክንያት የለም አልኩት። 🔹በጣም ከተከራከርን በኋላ አምላኬ ሆይ እውነቱን ንገረኝ በማለት ቁርአኔን ወደ ደረቴ ይዤ ፀለይኩ ። 🔹ከዚያም ቁርአኔን ስገልጥ በሱራ 10:94 ላይ ከፈትኩት። እንዲህ ይላል:- فَإِن كُنتَ فِي شَكٍّ مِّمَّا أَنزَلْنَا إِلَيْكَ فَاسْأَلِ الَّذِينَ يَقْرَءُونَ الْكِتَابَ مِن قَبْلِكَ ۚ لَقَدْ جَاءَكَ الْحَقُّ مِن رَّبِّكَ فَلَا تَكُونَنَّ مِنَ الْمُمْتَرِينَ ወደ አንተም ካወረድነው በመጠራጠር ውስጥ ብትሆን እነዚያን ከአንተ በፊት መጽሐፉን የሚያነቡትን ጠይቅ፡፡ እውነቱ ከጌታህ ዘንድ በእርግጥ መጥቶልሃል፡፡ ከተጠራጣሪዎቹም አትሁን፡፡ 🔹ከዚያም ቁርአን ራሱ ቁርአንን ከተጠራጠርክ መፅሐፍ ቅዱስን አንብብ ስላለኝ መፅሐፍ ቅዱስን ማንበብ ስጀምር ኢየሱስ አምላክ መሆኑ ተረዳሁና ክርሰቲያን ሆንኩ። 🙏"ስለዚህ ክርስቲያን ያደረገህ ማነው" ካላችሁኝ:-እኔን ክርስቲያን ያደረገኝ ቁርአን ነው።

photo content

በፍፁም ግፍ አትስሩ! በማንም ይሁን በምንም በፍፁም አትሳቁ!! ቀን ቆጥሮ ዋጋችሁን እንዳይከፍላችሁ።

photo content

"ገብርኤል ብሂል ብእሲ ወአምላክ፤እምኀበ እግዚአብሔር ዘተፈነወ ላዕክ፤ ሥጋዊ ቃል ለድንግል ይሰብክ" እንኳን ለገናናው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ! የመ
"ገብርኤል ብሂል ብእሲ ወአምላክ፤እምኀበ እግዚአብሔር ዘተፈነወ ላዕክ፤ ሥጋዊ ቃል ለድንግል ይሰብክ" እንኳን ለገናናው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ! የመልአኩ ጥበቃና አማላጅነት አይለየን ! እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ !