ar
Feedback
ዜና ቤተክርስቲያን

ዜና ቤተክርስቲያን

الذهاب إلى القناة على Telegram

የተለያዩ በቅድስት በቤተክርስቲያን ዙሪያ መነሻ ያደረጉ ዜናዎችን ከቤተክርስቲያን ልሳናት ከሆኑ ምንጮች በማቅርብ መረጃ መለዋወጥ።

إظهار المزيد
1 461
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-17 أيام
+430 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

"ነገ ሐምሌ 22 መልአከ ብርሃናት ቅዱስ ዑራኤል ቅዳሴ ቤቱ ተከብሮ ይውላል ብርሃኑን ያብራልን🙏 ✥ቅዱስ ዑራኤል ከሊቀ መላእክት አንዱ ነው። መላእክት በስማቸው ቅጥያ ኤል የሚል ቃል አለ ይኸውም እግዚአብሔር ማለት ነው። "ዑር" ማለት ብርሃን፤ "ኤል" ማለትም እግዚአብሔር ማለት ነው።ዑራኤል ማለት የብርሀን ጌታ፣ የብርሀን አምላክ ማለት ነው። ✥ የሰማይን ሚስጥር ለሄኖክ እውቀትን የገለጸለት መልአክ ነው። የፀሐይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል። መ.ሄኖክ 28፥13 ✔️በብርሃናት ሁሉ ሊቀ ብርሃናት ሆኖ የተሾመው ቅዱስ ዑራኤል ነው። ✔️ቅዱስ ዑራኤል በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ ስለሆነ እርሱም መባርቅትን ለጥጋብና ለበረከት እንዲሁም ነጎድጓድን ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። መ.ሄኖክ ፮፥፪ ➕ ምስጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት የፀሐይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል። ✥ቅዱስ ዑራኤል ልቡናን የሚያበራ እውቀትን የሚገልጽ ርሑሩህ መልአክ ነው። ቅዱስ ዑራኤል ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋአ ልቡናን አጠጥቶት ሰማያዊ ሚስጥራትን ገልፆለታል። ነብዩ እጅግ ብዙ ቁጥር ያላቸውን መጻሕፍት ደርሷል። በሰዓታቱም "ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ኤልያስ ወኤልሳዕ ነቢያተ እስራኤል ወምስለ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋዓ ልቡና ዘአስተዮ ዑርኤል፡፡" "ነይ ወደ እኛ ድንግል ሆይ ከእስራኤል ነብያት ከኤልያስና ከኤልሳ እንዲሁም ዑራኤል ጽዋ ልቡናን ካጠጣው ከእዝራ ሱቱኤል ጋር።" ✥ሌላኛው ቅዱስ ዑራኤል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእጸ መስቀል ላይ በቀራንዮ በአምስቱ ቅንዋት (ሳዶር፣አላዶር፣ዳናት፣አዴራ፣ሮዳስ) ሲቸነከር ይህ ብርሃናዊ መልአክ ነው ከጎኑ የክርስቶስን ደም በጽዋ ቀድቶ በዓለም ሁሉ የረጨው። ✥እመቤታችን ወደ ግብፅ በተሰደደች ጊዜ በዚህ የጭንቅ ጊዜ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን እየተራዳ መንገድን እየመራት በብርሃን ወደ ሀገረ ግብፅ ቀጥሎም ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም አስራት ወደ ሆነቻት ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ እየመራት መጥቷል። ማቴ 2÷13-15 ✥ሌላው የእውቀትን ብርሃን የገለጸላቸው የእውቀትን ጽዋ ያጠጣቸው ለሊቁ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ነው። እኚም አባታችን በመልአኩ ተራዳኢነት ብዙ ድርሰቶችን ደርሰዋል። እመቤታችንም በምልጃዋ ቅዱስ ዑራኤል የእውቀትን ጽዋ ያጠጣቸው ዘንድ አድርጋለች። አባ ጊዮርጊስ እመቤታችንን ይወዷት ስለነበረ አርጋኖን ሌሎችንም ደርሰዋል። የሊቀ ብርሃናት ቅዱስ ዑራኤል በረከት ተራዳኢነት አይለየን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር 🙏

የሚፈላው ውሃ ቢሰማ እንደመብረቅ🎤 በእምነት ፀንተናል ስፍራውን ሳንለቅ🙏❤️ ባለንበት እንቁም በእምነት በተስፋ ገብሪኤል ይመጣል እሳቱን ሊያጠፋ የስሙ ትርጓሜ ሠው የሆነ አምላክ ነው ደስታን ያበሰረን ገብሪኤል እሱ ነው ባለንበት እንቁም #ሊቀ_መዘምራን_ቴዎድሮስ_የሴፍ❤️

‹‹ሐምሌ 7›› አጋዕዝተ ዓለም ስላሴ በአብርሃም ቤት ተገኝተው ቤቱን የባረኩበት የአንድነታቸውንና ሶስትነታቸው ሚስጢር የገለጹበት ታላቅ በዓል ነው። በዚችም ቀን ልዩ የሆኑ ሦስቱ አካላት /ቅድስት ሥ
‹‹ሐምሌ 7›› አጋዕዝተ ዓለም ስላሴ በአብርሃም ቤት ተገኝተው ቤቱን የባረኩበት የአንድነታቸውንና ሶስትነታቸው ሚስጢር የገለጹበት ታላቅ በዓል ነው። በዚችም ቀን ልዩ የሆኑ ሦስቱ አካላት /ቅድስት ሥላሴ/ በኦሪት መጽሐፍ እንደ ተጻፈ ወደ አብርሃም ቤት ገቡ ያቀረበላቸውንም ተመገቡ፡፡ የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት ለመረዳት በሥላሴ ፈቃድ መጻሕፍት እንዳስተማሩ ሊቃውንት እንደተረጉሙልን እንጂ ማንም በገዛ ፈቃዱ ተመራምሮ አይደርስበትም፡፡ የሐምሌ 7 ቀንም ሥላሴ በአብርሃም ቤት ገብተው ቸርነታቸውና ፍቅራቸውን የገለጹበት፣ ስለሆነ በዓሉን ስናዘክር ሥላሴን እናመሰግናለን፡፡ በአጠቃላይ በዚህ ዕለት በአብርሃም ቤት እግዚአብሔር የተስተናገደበት፣ አንድነቱና ሦስትነቱ የተገለጠበት፣ አብርሃም እና ሣራ ካረጁ በኋላ ልጅ እንደሚወልዱ የተበሠረበት፣ ይሰሐቅንም እንደሚወልድ የተነገረበት ዕለት ነወ። ለአብርሃም ምሥጢሩን የገለጠ እግዘአብሔር ለሁላችን ይግለጥልን🙏

ሐምሌ 5 ቀን የቅዱሳን ሐዋርያት ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓለ እረፍታቸው ነው በረከታቸው ይድረሰን።

👉ሲያስተምር እንባ ከአይኖቹ ይቀድሙታል ተስፋ የቆረጠውን ወጣት ተስፋ ይሰጠዋል በእግዚአብሔር ቃል ተስፋውን ያለመልማል።
👉ሲያስተምር እንባ ከአይኖቹ ይቀድሙታል ተስፋ የቆረጠውን ወጣት ተስፋ ይሰጠዋል በእግዚአብሔር ቃል ተስፋውን ያለመልማል።

ድሮ ድሮ ቀስት ሲሰራ ሚዛኑን ጠብቆ ቀጥታ ኢላማውን እንዲመታ ጫፉ ላይ ላባ ይደረግለት ነበር። ታዲያ አንድ ጭልፊት በጠንካራ ቀስት ተመትቶ ከሰማይ ወደ መሬት እየተመዘገዘገ እያለ ፣ ቁስሉን ለማየት
ድሮ ድሮ ቀስት ሲሰራ ሚዛኑን ጠብቆ ቀጥታ ኢላማውን እንዲመታ ጫፉ ላይ ላባ ይደረግለት ነበር። ታዲያ አንድ ጭልፊት በጠንካራ ቀስት ተመትቶ ከሰማይ ወደ መሬት እየተመዘገዘገ እያለ ፣ ቁስሉን ለማየት ዞር ብሎ የተመታበትን ቀስት አየ። .... የቀስቱ ጫፍ ላይ የተሰካው የራሱ ዓይነት ላባ ነበር። ጭልፊቱም "በጠላት እጅ ከመውደቅ በላይ፣ በራስ ወገን መጥፋት እጅግ ያማል።" አለ። ... ብዙውን ጊዜ ለውድቀታችን ሰበብ የሚሆኑት የራሳችን ጥንካሬዎች፣ በቅርብ የምናምናቸው ሰዎች ወይም እኛ ራሳችን ያሳደግናቸው ናቸው። ከውጭ ጠላት ይልቅ የውስጥ መከዳዳት ያደማል። ... (የአዳም ረታ፥ የስንብት ቀለማት፤ ቃል በቃል የተፃፈ አይደለም።)

የቀን : እረኛ : የሌሊት : ጠባቂ : ቅዱስ : ሚካኤል #ሰኔ_12_ቀን ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎሚያን ከዲያብሎስ መንጋጋ ያስጣለበት እንዲሁም የባሕራንን የሞቱን ጦማር ቀዶ ሠርግ ያደረገበትን እለት
የቀን : እረኛ : የሌሊት : ጠባቂ : ቅዱስ : ሚካኤል #ሰኔ_12_ቀን ቅዱስ ሚካኤል ቅድስት አፎሚያን ከዲያብሎስ መንጋጋ ያስጣለበት እንዲሁም የባሕራንን የሞቱን ጦማር ቀዶ ሠርግ ያደረገበትን እለት ነው ። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ልጆቿን ሰብስባ በዓልን ሰርታ በታላቅ ድምቀት ከዓመት ዓመት ታከብረዋለች ። መጋቤ ብሉይ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በተአምራቱ ዘወትር እንደሚጠብቀን ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ እንዲህ እያለ ይመሰክራል ፦ « የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የቀን እረኛ የሌሊት ጠባቂ ክንፎቹ የእሳት የሆነ ዘወትር የሚጠብቀን ቅዱስ ሚካኤል የእውነት የድንኳን ከተማ ነው ። » በማለት ተናግሯል ። በዚህ መሠረት ድንኳን ከቀን ሐሩር ከሌሊት ቁር እንደሚከለሉበት ሁሉ #ቅዱስ_ሚካኤልም በቃል ኪዳኑም የሚታመኑትን ሁሉ ከምሕረት አልባው ከዲያብሎስ ደባ ከአጋንንት ድብደባ ከዚህ ዓለም ፈተና ያድነናል ይታደገናል። ቅዱስ ሚካኤልም በቃል ኪዳኑ የሚታመኑትን ሁሉ ከምሕረት አልባው ከዲያብሎስ ደባ ከአጋንንት ድብደባ ከዚህ ዓለም ፈተና ያ ይጠብቀን። አሜን 🤲❤

photo content

እደምን ዋላችሁ ዛሬ የእናንተን መልካም ፍቃድ ለመጠየቅ ነው የምትችሉ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ይህን ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ዩቲዩብ ቻናል ሰፕስክራይብ ኡድርጉልን። https://www.youtube.com/@LikanatTube እግዚአብሔር ያክብራችሁ!!

ቃለ ህይወት ያሰማልን!!

የሚስማማ!! ሀገር በስው ሳይሆን እንደ ሰው በሚያስብ ትመራለች!

አንድ የዜን መምህርና ደቀ መዝሙሩ በጫካ ውስጥ ሲጓዙ፣ አንድ ትልቅ እባብ አንዲትን እንቁራሪት አፎቶ ሊውጣት ሲታገል ያያሉ። እንቁራሪቷ በስቃይ ትጮኻለች። ... ደቀ መዝሙሩ በመገረም መምህሩን ጠየቀ
አንድ የዜን መምህርና ደቀ መዝሙሩ በጫካ ውስጥ ሲጓዙ፣ አንድ ትልቅ እባብ አንዲትን እንቁራሪት አፎቶ ሊውጣት ሲታገል ያያሉ። እንቁራሪቷ በስቃይ ትጮኻለች። ... ደቀ መዝሙሩ በመገረም መምህሩን ጠየቀው። ... "መምህር ሆይ፣ እንደ ዜን ፍልስፍና በተፈጥሮ ህግ ውስጥ ጣልቃ መግባት የለብንም። እባቡ መብላት አለበት፣ እንቁራሪቷም መሞት ተፈጥሮዋ ነው። ታዲያ እዚህ ጋ ገለልተኛ ሆነን ዝም ልንል ይገባል ወይስ ልናድናት?" ... መምህሩ ምንም ሳይናገር በዱላው እባቡን መትቶ እንቁራሪቷን አስመለጣት። እባቡም ተቆጥቶ ወደ ጫካው ሄደ። ... ደቀ መዝሙሩ ግራ ገብቶት፡ "መምህር፣ ታዲያ ገለልተኝነትና የተፈጥሮ ህግስ የት ሄደ?" አለው። ... "እባቡ እንቁራሪቷን ሲይዛት፣ ገለልተኝነት የሚባል ነገር አብቅቷል። አንተ ዝም ብለህ በመቆምህ 'ገለልተኛ' የሆንክ መስሎሃል፤ ነገር ግን በዝምታህ እባቡ እንቁራሪቷን እንዲበላት እየረዳኸው ነበር። በበደል ፊት ዝምታ ምርጫ እንጂ ገለልተኝነት አይደለም።" ... ፍትህ ሲጓደል፣ ሰብዓዊነት ሲበደል፣ ዝም ማለት ልክ አይደለም። ዝምታ ወይም ገለልተኝነት በራሱ ለጨቋኙ የተሰጠ ድምፅ ነው። ምንም አላደረግኩም የሚለው ደቀ መዝሙር፣ በተግባር ግን ከእባቡ ጎን ቆሞ ነበር። ... ክፉ ነገር ሲደረግ እያዩ ምንም እንዳላዩ መሆን፣ ክፋቱ እንዲቀጥል መፍቀድ ነው። ጥፋትን አለማስቆም ጥፋቱን እንደመደገፍ ይቆጠራል። ስለዚህ ግፉ ስናይ ስንመለከት ዝም ልንል አይገባም። #nomore #ethiopianorthodoxunderattack #አርሲ #ኦርቶዶክስ

ይፈርዳል!

በየኔታ በአማን ነጸረ በአዘቦቱ፥ መንበር ከካህኑ በቀር ምዕመን ቀርቶ ዲያቆንም መንካት አይፈቀድለትም። ክፉ ቀን ሲመጣ ግን የማይሆነውም ይሆናል። ይህ ግፉዕ ማኅበረ ምዕመን ቤቱን፣ ከብቱን፣ ግማሽ ሕ
በየኔታ በአማን ነጸረ በአዘቦቱ፥ መንበር ከካህኑ በቀር ምዕመን ቀርቶ ዲያቆንም መንካት አይፈቀድለትም። ክፉ ቀን ሲመጣ ግን የማይሆነውም ይሆናል። ይህ ግፉዕ ማኅበረ ምዕመን ቤቱን፣ ከብቱን፣ ግማሽ ሕይወቱን የኋሊት ጥሏል፣ ተነጥቋል። መንበሩን፣ ደመ ክርስቶስ የሚሠዋበትን ግን በክፉ ቀን እንኳ አልዘነጋም። ልቤን የደቃኝ ምስል። ወገኖቻችሁ ድኩማን ብንሆንም፥ ይህን መታመናችሁን መገፋታችሁን ከሰማይ የሚያይ አምላክ አላችሁ።

የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ!!

What Causes Conflict? / የግጭት መንስኤዎች ምንድን ናቸው? ================ ​Poor Communication — ደካማ የመገናኛ ዘዴ / የሐሳብ ልውውጥ እጥረት ​Lack of C
What Causes Conflict? / የግጭት መንስኤዎች ምንድን ናቸው? ================ ​Poor Communication — ደካማ የመገናኛ ዘዴ / የሐሳብ ልውውጥ እጥረት ​Lack of Compromise — የአስተማማኝ ስምምነት / የመወያየት እጥረት (እልህኝነት) ​Needs not Met — ፍላጎቶች አለመሟላት ​Prejudice — አድልዎ / ቅድመ-ፍርድ ​Intolerance — ያለመቻቻል ​Self-Interest — የግል ጥቅም / ራስን መውደድ ​Ignorance — አለማወቅ / ድንቁርና ​Desire for Power — የስልጣን ጥማት / የስልጣን ፍላጎት ​Lack of Empathy — ለሌሎች ሰዎች ስሜት አለማዘን (የእርህራሄ እጥረት) ​Making Assumptions — ያለማስረጃ መገመት / ግምታዊ አስተሳሰብ

አርሴናል ወጣቱን አስለቅሷል #ጸሎት #viralvideochallenge #መንፈሳዊ #Ethiopia #viralvideo #ኦርቶዶክስ #አርሴናል

ኢየሱስ የተነበበባት ፊደላችን ተወለደች። የትኛውም ከአንደበታችን የሚወጣ ቃል ረቂቅ ነው። አይታይም አይጨበጥም። "ኢየሱስ" ብለን በቃላችን ብቻ ብንናገር ስሙ አይዳሰሰም አይታይም። ይህን ስም ማየትና
ኢየሱስ የተነበበባት ፊደላችን ተወለደች። የትኛውም ከአንደበታችን የሚወጣ ቃል ረቂቅ ነው። አይታይም አይጨበጥም። "ኢየሱስ" ብለን በቃላችን ብቻ ብንናገር ስሙ አይዳሰሰም አይታይም። ይህን ስም ማየትና መንካት ከፈለግን የግዱን ኢየሱስ ብለን በፊደል መጻፍ ያስፈልገናል። በወንጌል "እግዚአብሔር መንፈስ ነው" ተብሎ ተጽፏል።መንፈስ ማለት ረቂቅ ማለት ነው። ረቂቁ አምላክ እንዴት ገዘፈ? እንዴት ታየ? በፊደል ስለተገለጠ ነዋ። ፊደል ያልናት ድንግል ማርያምን ነው። ረቂቁ አምላክ ሰው ስለሆነባት ስለታየባት ቤዛ ሊሆነን ግዙፍ ሥጋን ስለነሳባት። እሷ ፊደል ከሆነች ልጇ ወንጌል ነው። ወንጌልን ያለ ፊደል ምን ብለህ ታነበዋለህ? እንዴትስ ታየዋለህ? ወንጌላችን የሚጻፍባት ፊደል ዛሬ ከሐና ማሕፀን ከኢያቄም አብራክ ተገኘች። ሰአሊ ለነ ቅደስት!