cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የግጥም ደብተሬ( ye getm debterae)

ለግጥም አፍቃሪዎችና ወዳጆች የግጥም ጥማቹን ለማርካት እንሆ ጀባ ብለናችሁል

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
423
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

​​#የአምላክ_እንባ (በላይ በቀለ ወያ) @Mgetem . . ከላይ ከሰማያት... በሰው ተበድሎ ፤ ፈጣሪ ያለቅሳል ከታች ያለ ፍጥረት... "ዝናብ ጣለ" ብሎ ፤ ምድሪቱን ያርሳል። ወራትን ጠብቆ፤ ርሀቡን አስታግሶ የሀገሬ ገበሬ... በፈጣሪ እንባ ነው ፤ የሚበላው አርሶ። እንዲያው በተለምዶ፤ ዝናብ የምንለው ትእግስት አጠራቅሞት... ለወራት የቆየ ፤ የአምላክ እንባ ነው። ።።። ከማንባቱ በፊት... ማዘኑን ሊያረዳ፤ ሰማይ ጠቁሮ ሳለ፤ ፈጣሪ ሲቆጣ... ትውልድ ያማትባል፤ "መብረቅ" ነው እያለ። የሀገሬ ገበሬ..... ሰማዩን እያየ፤ ምድሪቱን ያርሳል የገበሬው በሬ... ሳር ሳሩን እያየ፤ ከገደል ይደርሳል በፈጣሪ እንባ በሰው ልጆች ደባ የታረሰ መሬት... ስንዴና እንክርዳዱን፤ባንድ ላይ ያበቅላል ከላይ ከሰማያት... ስንዴን ከእንክርዳዱ ፤ሊለይ ይታገላል ከታች ያለ ፍጥረት ርሀቡን ሊያስታግስ ስንዴና እንክርዳድን፤ ደባልቆ ይበላል። ።።። ለእንደገና ክረምት ለእንደገና በደል ፣ ለእንደገና ለቅሶ የሀገሬ ገበሬ…… ሰማይ ሰማይ ያያል፤ ደረቅ መሬት አርሶ። ።፣ ከላይ ከሰማያት. የፈጣሪ እናት ልጇን ለማባበል ፤ ፈገግ ትላለች ከታች ያለች እናት... "ፀሐይ ወጣ"ብላ ፤ ብቅል ታሰጣለች። እንዲያው በተለምዶ፤ ፀሀይ የምንላት ልጇን ለማባበል…. ብርሀን የሰጠች፤ የአምላክ እናት ናት። @Mgetem @Mgetem @Mgetem_Bot
إظهار الكل...
2.51 KB
Some say this covid-19 is the 13th Apostle sent to Earth to bring us and our consciousness Back to GOD. are they right?
إظهار الكل...
Water can boil and freeze at the same time Seriously, it's called the 'triple point, and it occurs when the temperature and pressure is just right for the three phases (gas, liquid, and solid) of a substance to coexist in thermodynamic equilibrium. @Minutephysics
إظهار الكل...
እሱ :የህይወቴን ተስፋ ፍቅሬ አታዋት ብዙ ጊዜ አለፈኝ አይኑአን ... እሷ፦እንዴ አሁን አይድል እንዴ ከonline የወታሁት እሱ፦ዝም በይ ባክሽ አንቺን አይድለም 😜😜😜😜😁😁😂😝😋😀😱
إظهار الكل...
አችሬ ግጥም ቁመተ ዶሮ ምትንተራራ ወደ ሰው ጆሮ short man😳😍
إظهار الكل...
#ስንቴ_ገረዝኩት ✂️ : #ክፍል_አራት (የመጨረሻ ክፍል) : : ✍ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ : : ....“ባለቤትሽ? ኢሳያስ?…………” “ቢሮዬ ድረስ እየመጣህ ለምን ትረብሸኛለህ ኢሳ?” “ናፈቅሽኝ!! ከዚህ በላይ ሳላይሽ መቆየት አልችልም።” ከዩንቨርስቲ ጀምሮ የማውቀው ሰው ነው ኢሳያስ ። ለ6 ዓመት አብሮኝ የቆየ የትዳር አጋሬም ነው። አብረን በኖርንባቸው ጊዜያት መጀመሪያዎቹ አመታት በፍቅር ያጌጡ ነበሩ። እየሰነባበተ ግን ሳንጨቃጨቅ ያለፉ ቀናት ውስን ሆኑ። የሁለት ዓመት ልጃችን በሞት ስትለየን ሰላማችን ይብስ ደፈረሰ። ልጃችን የሞተችው በምግብ መመረዝ ነው። ታማ ስትሰቃይ ሁለታችንም ልንደርስላት አልቻልንም ነበር። ሰራተኛዋ ስትደውልልኝ ስራ ላይ ነበርኩ። ስልኬን እየሰማሁት ቆይቼ ለመደወል አስቤ ተውኩት። ግን ቆይቼም አልደወልኩም። ሌላ ስራ ያዝኩ። እናም ልጄን ሳልደርስላት ሞተች። እሱም በተመሳሳይ ምክንያት ስልክ ሳይመልስ ቀረ። ቆይቼ ስደርስ ዘግይቼ ነበር። ለዚህ በደሌ አንድ ሚሊየን ጊዜ ራሴን ብቀጣውም በቂ አይሆንም። ከኢሳያስ ጋር መወቃቀሱ አቁሳይ ስለነበር በሆነው ባልሆነው ሰበብ እየፈለጉ መነታረክ ሆነ ምሽታችን። ቤቱን ለቆ ከወጣ ሶስት ወር አለፈው። “ቁጭ ብለን እንድናወራ እፈልጋለሁ።” አለኝ አይን አይኔን በልመና እያየ። ምንድነው ልለው የነበረው? ‘ውጣልኝ‘ ነበር ሌላ ጊዜ ቢሆን የምለው። አሁን የምትሸሸዋን ሴት አይደለሁም። ምንም ቢሆን የምትጋፈጠዋን ማህደር እየተለማመድኳት ነው። “እደውልልሃለሁ።” ያልኩትን ያመነኝ አይመስልም። ተገርሞ እያየኝ ተሰናብቶኝ ወጣ። የገባኝ አንድ ነገር ሲሳይ በብዙ ፍጥነት ማንነቴን እያሾረው መሆኑ ነው። ወደ ቤቴ ገብቼ ሲሳይ ያለኝን አደረግኩ። «በህይወትሽ የምትሸሺው ነገር ምንድነው? መስታወት ፊት ቁሚና ለራስሽ ንገሪው። እመኚው!! መቀየር የማትችዪውን ነገር መቀበል ነው የሚፈውሰው።» ነበር ያለኝ የልጄን ፎቶዎች ከደበቅኩበት አወጣኋቸው። በመጀመሪያው ቀን ቀላል አይሆንም ነበር ያለኝ። ቀላል አልነበረም። ሁሉንም ፎቶዎች በፊት የተሰቀሉበት መለስኳቸው። መሸሽም መደበቅም መድሃኒት አይሆንም። ስሸሽ የተጠራቀመው እንባዬ ገደቡን ጥሶ አይኔን አደፈራረሰው። ስልኬ መጥራቱን እንኳን የሰማሁት ብዙ ከጠራ በኋላ ነበር። «ምን ሆነሻል? አልቅሰሽ አይደለምኣ?» ሲሳይ ነው። «ነው! አልቅሼ ነው።» እያልኩት ጭራሽ መንፈቅፈቅ ጀመርኩ። «እህህህ ምን ተፈጠረ ቆይ?» እቤቴ ደጅ ድረስ አድርሶኝ ነበር የተመለሰው። መልስ መመለስ እስኪያቅተኝ ሲቃዬ አነቀኝ። « በቃ በቃ እሺ መጣሁ። ስልኩን አትዝጊው እያወራሁሽ እደርስልሻለሁ። እኔ አጠገብሽ ሆኜ እንደፈለግሽ እንድታለቅሺ ፈቅድልሻለሁ። እስከዛ ግን ስወድሽ አታልቅሺ?» ብሎኝ ሊያስቀኝ እየሞከረ ከቤቱ ሲወጣ፤ «ብርድ እንዳይመታህ በደንብ ልበስ» ስለው «አትስጊ ካልሲ አጥልቄለታለሁ» ሲለኝ ታክሲ ሲያናግር «የኔ እመቤት ደሞ ስስ ፒጃማ ፍለጋ ቁምሳጥኑን ዘረጋግፊው አሉሽ!» ሲለኝ ሲከፍል «ስንቴ መስታወት አየሽ?» ሲለኝ ሲደርስ እውነትም ማልቀሴን ትቼ ልቤ ተሰቅሎ እየጠበቅኩት ነበር። በሩን ከፍቼ ተጠመጠምኩበት። ሙሽራውን በሰርጓ እለት ወደ መኝታ ቤታቸው እንደሚያስገባ ሙሽራ አቅፎኝ ወደሳሎኑ ገባ! ማልቀሴን እረሳሁት። ሳሎኑ ውስጥ የተሰቀለውን የእኔንና የኢሳያስን የሰርግ ፎቶ አይቶታል። ግን አልጠየቀኝም። ሌላ ነገር እያወራ ሲያስቀኝ ቆየ። «ሲስ?» «ወዬ እመቤቴ?» «ስለእኔ ማወቅ ያለብህ ነገር አለ።» «ምኑን ትነግሪኝ? በፎቶ አሳየሽኝኮ አስጎበኘሽኝ።» አለ ወደፎቶው እየጠቆመኝ። «እየቀለድኩ አይደለም ሲስ! ከምሬ ነው።» « እሺ እመቤቴ ንገሪኝ! ይኸው! Am all yours!» ስለኢሳያስ እና ስለልጄ ነገርኩት ብቻዬን ስለፈልፍ ሲያባብለኝ እና ሲደባብሰኝ ብቻ ቆየ። ብዙ ደቂቃ እቅፉ ውስጥ ካቆየኝ በኋላ « ባንቺ ደረጃ ካሉ ሴቶች ይልቅ አንዲት ምንም የማታውቅ የቤት እመቤት የሰመረ ትዳር ለምን የሚኖራት ይመስልሻል?» አለኝ « ጭራሽ እንደዛ ስለመሆኑም እንጃልህ! ምን ለማለት ፈልገህ ነው?» «ይሄ ሀቅ ነው ብዙ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት በጋራ ስምምነት ባስቀመጥነው ደረጃ ብዙዎቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያሉ ሴቶች በትዳራቸው ስኬታማ አይደሉም።» «ምናልባት ከትዳራቸው ሌላ ትኩረታቸውን የሚሻ ሌላ ስራ ስላላቸው?» «እኔ አይመስለኝም። እነዛ በትዳር ውስጥ ለፍቅር ወይ ለልጃቸው አልያም በሌላ ምክንያት ዝቅ ማለትን ያውቁበታል። እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ? ክርስቶስ ለባል የሰጠው ትእዛዛ ሚስትህን ክርስቶስ ቤተክርስትያንን በወደደበት ፍቅር ውደድ የሚል ነው። ያ ማለት ነፍሱን እስከመስጠት። ለሚስት ያላት ግን ሚስት ለባሏ ትገዛ ነው። የቱ የሚከብድ ይመስልሻል?» ሳልመልስለት ራሱ ቀጠለ። «ባትወጂም መገዛት ትችያለሽ። ወደሽ አለመገዛት ግን በፍፁም አትችዪም።» ዝም ነበር መልሴ። ከአንዱ ስሜት ወደሌላው መሻገር ምንም አይከብደውም። መከፋቴን አስረስቶኝ አመሸን። «ያው እንደምታውቂው ድንግል ነኝ። በዛ ላይ ቁስሉ ራሱ ሰበብ አይፈልግም።» ብሎኝ እኩለ ለሊት አልፎ ወደ ቤቱ ሄደ። ★ ★ ★ በሚቀጥለው ቀን በስራ የደከመ ሰውነቴን እየጎተትኩ መኪናዬጋ ደረስኩ። መሽቷል። እቤቴ ገብቼ ማረፍ ነው ያማረኝ። ስልኬ ጠራ። ሲሳይ ነው። “እራት በላሽ?” “አልበላሁም። ግን ደክሞኛል በጣም።” “እማ ቆንጆ እራት ነው የሰራችው። እየጠበቀችሽ ነው።” “ትቀልዳለህ እንዴ? ማን ነኝ ብዬ ነው እናትህ ቤት እራት ልበላ የምመጣው?” “ማንም መሆን አይጠበቅብሽም። ሰው መሆን የእማን እራት ለመብላት በቂ ነው።” ★ ★ ★ አመመኝ። የቤተሰቡ ፍቅር አሳመመኝ። “ደህና ነሽ ግን?” “ምነው ደስ አላለሽም?” “ምነው ልጄ ከፋሽሳ?” ይሉኛል እየተቀባበሉ ። አመመኝ። የሚታገለኝን እንባ እየዋጥኩ የደመቀ እራት በላሁ። የቤተሰብ ፍቅር ህመሜ፣ ንጭንጬ ፣ ሽንፈቴ፣ ድክመቴ……… መሆኑ አልገባቸውም። ይሄን ፍቅር በዘመኔ አይቼው አንጊንቼው እንደማላውቅ አያውቁም። የሲሳይ እናት ፊቴን እያገላበጡ፣ ፀጉሬን እየዳበሱ የሆንኩትን ሲጠይቁኝ እናት እንደማላውቅ አያውቁም። አባትየው እየደጋገሙ ‘ልጄ‘ ሲሉኝ። አይኑ ለማያይ ያአረጀ አያቴ እየተላላኩ እና ምርኩዝ ሆኜ እንዳደግኩ አልገባቸውም። እህቶቹ እግሬ ስር በርከክ እያሉ ‘ሲሳይ አስከፍቶሽ ነው? እሱ እኮ ክፍት አፍ ነው።” ሲሉኝ አያቴ ሞቶ የአክስቶቼ ልጆች እንደምናምንቴ እየቆጠሩኝ ተምሬ መጨረሴን አያውቁም። ብዙ አወሩኝ። እቤት ይዟት የመጣ ብቸኛ ሴት መሆኔን ነገሩኝ። ★ ★ ★ እንደምንም ያመቅኩትን እንባዬን መኪናዬ ውስጥ ሲሳይ እቅፍ ውስጥ ዘረገፍኩት። አላባበለኝም። እየደጋገመ እንባዬን እየጠረገ ፣ ፀጉሬን እያሻሸ ጠበቀኝ። “አውሪኝ። የተሰማሽን ሁሉ አውሪኝ።” አለኝ። ሲቃዬ አላስወራ አለኝ። ጣቶቹን ፀጉሬ ውስጥ ሰዶ ወደራሱ አስጠጋኝ። ይበልጥ ሲቀርበኝ ከመቃወም ይልቅ ልስመው ፈለግኩ። በሌላኛው እጁ እንባዬን ከጉንጬ ላይ ጠራረገው። ከንፈሩ ከንፈሬን የሚነካበት ሰዓት ረዘመብኝ። መጠበቅ አቃተኝ። ሳምኩት። ነፍስ በሚያሳርፍ መሳሙ ለደቂቃዎች ሳመኝ። “ምንም ይሁን ንገሪኝ፣ አንድም ሳታስቀሪ የተሰማሽን ንገሪኝ፣ አንቺ ራስሽን ከምትረጂው በላይ እረዳሻለሁ። እንባሽ ከመጣ አልቅሺ ብቻ ልስማሽ!” አለኝ መረጋጋቴን ሲያይ “አሁን እኮ መሽቷል። ሌላ ቀን ላውራህ?” “ማደር ካለብኝ እየሰማሁሽ አድራለሁ።” አውርቼ የማላውቃቸውን ብዙ ነገሮች ነገርኩት። ሳለቅስ አያባብለኝም። እጄን እየደባበሰ ይሰማኛል። ስለቤተሰቦቼ ሁሉንም ነገርኩት። አያቴ ሲሞት ከልጅነቴ ጀም
إظهار الكل...
#ስንቴ_ገረዝኩት ✂️ : #ክፍል_ሶስት : : ✍ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ : : ....እግሬና ሀሳቤ ሳይስማሙ እግሬ ቀድሞ ሬስቶራንቱ ውስጥ ተገኘ። ሲሳይ ቀድሞኝ ተገኝቷል። ልጨብጠው የዘረጋሁትን እጄን ሳብ አድርጎ አቀፈኝ። የምቀመጥበትን ወንበር ሳበልኝ። እራትና ወይን አዘዝን። ከእርሱ ጋር መጨቃጨቁ ትርፉ የሌላ ሰው ትኩረት ከመሳብ ያለፈ ስለማይሆን ዝም ብዬ የሚያደርገውን ከማየት ውጪ ተቃውሞም መስማማትም አልተነፈስኩም። አፉ ከማውራት እጁ ከማጉረስ ሳይቦዝን ነበር እራት ተመግበን የጨረስነው። “እኔ ከዚህ በላይ አልጠጣም። ስራ መመለስ አለብኝ።” ያልኩትን የሰማ አይመስልም። ቀዳልኝ። በአትኩሮት ሲመለከተኝ ከቆየ በኋላ “ሴክስ ካደረግሽ ስንት ጊዜሽ ነው? ወራት? አመታት?” አለ ቀለል አድርጎ “አንተ? ያምሃል እንዴ? ” አልኩት ደንግጬ ይሁን አፍሬ ሳይገባኝ “ምነው? አንቺ? ጭራሽ… ……ዜሮ ዞሮ ነሽ እንዴ?” በማብሸቅ ለዛ ነው ያወራው ። ደሞ አብሽቆኛልም። “አንተ እኔን ለማንጓጠጥ የሚያስችለህ ቦታ ላይ እንዳለህ ነው የሚሰማህ?” ሳልጨርስ መንፈቅፈቁን ያዘው ” ማሂ ከእኔ ጋር ስታወሪ ጨዋ ቃል አትፈልጊ…… ሃሃሃሃ ‘ትናንት እጄ ላይ ሸለፈትህን ተገርዘህ፣ ልጅህን በማስገረዣ እድሜህ አንዠርግገኸው…ምናምን ……‘ በይው ” “እንደሱ ለማለት እንኳን አልነበረም።” መለስኩለት “በጨዋኛ ስለብድ ምን ታውቅና? እንደማለት አይደል?” “በየሱስ ስም!» ከመደንገጤ የተነሳ ወንበሬ ላይ ዘልያለሁ። እሱ ምንም እንዳላለ ሁሉ በሁኔታዬ ይንፈቀፈቃል። “ያልተገረዘ ሴክስ አያደርግም ያለሽ ማነው?” አባባሉ ቀዝቃዛ ስሜት ስለነበረው ስሜቱን የጎዳሁት ስለመሰለኝ ወንዶች ስለማይገረዙባቸው ሀገራት፣ ገጥመውኝ ስለሚያውቁ አጋጣሚዎች ነገርኩት። “ኮንዶም የለ፣ ምን የለ… … ጫፉን ሸብ አድርጎ መሰማራት ነው። ተፈጥሯዊ ኮንዶም በይው ሃሃሃ” ብልግና ያወራ፣ በራሱ ያላገጠ አይመስልም። ደንግጬ ፈጥጬ አየዋለሁ። “ኸረ ስቀልድሽ ነው አንቺ!!” አለ መሳቁን ሳያቆም። በህይወቱ ውስጥ የሚያስከፋው፣ የሚያፍርበት፣ ሊያወራው የማይፈልገው ነገሩ ምን ይሆን? ብዬ አሰብኩ። ሲያወራ ፍፁም ጨዋ፣ ደግሞ ፍፁም ባለጌ፣ ደግሞ ፍፁም አዋቂ፣ ደግሞ ፍፁም ህፃን………ሁሉንም ይሆናል። ሲሳይን ማወቅ ከበደኝ። ያልተገረዘው ቤተሰባቸው ወንድ ልጅ እየሞተ ሲያስቸግራቸው የሄዱበት ጠንቋይ እንዳይገረዝ ስለነገራቸው መሆኑን እንደለመደው በራሱና በቤተሰቡ እየቀለደ ነገረኝ። “እያደግኩ ከመጣሁ በኋላ መገረዙ አሳፈረኝ እና አረጀሁ።” “በፍፁም አፍረህበት የምታውቅ ግን አትመስልም ነበር።” “አንቺጋ ስመጣማ ከማፈር አልፎ አስጠልቶኝ ነበር።” ሲያወራ በራስ መተማመኑ ለሰከንድ አይለየውም። ደጋግሞ ከሚያወራቸው ነገሮች በወላጆቹና በ6 እህቶቹ የተለየ ፍቅር ተሰጥቶት እንደኖረ ገባኝ። ከብዙ ሰው ጋር መግባባቱ፣ ብዙ ጓደኞች ማፍራቱ ምናልባትም ከተማረው የሳይኮሎጂ ትምህርቱጋ ግንኙነት ይኖረው ይሆናል ስል አሰብኩ። “ጓደኞች የሉሽም? የሆነ አብረሻቸው አንዳንዴ ዘና የምትዪበት ምናምን?” “የሉኝም!!” “እሺ ሲደብርሽ፣ ሲከፋሽ፣ ደስ ሲልሽ ወይ የተለየ ነገር ሲገጥምሽ ለማን ታወሪያለሽ?” አለኝ አይኖቹ የሚያነቡኝ ስለሚመስሉኝ እሸሻቸዋለሁ “ለራሴ አወራዋለሁ።” አልኩት አይኑን ሳይሰብር አየኝ። “አንተስ?” አልኩት “ያ ስሜት በተሰማኝ ሰዓት አጠገቤ ላገኘሁት ሰው። ለምሳሌ በኋላ ሸኝቼሽ ስመለስ ለሆስፒታላችሁ ዘበኛ ደስ እንዳለኝ ልነግረው እችላለሁ።” ቀለል አድርጎ ነው የሚያወራው “እየቀለድክ ነው?” “የምሬን ነው። ምነው?” “የምልህ ከእኩዮችህ፣ ቢያንስ ከቤተሰብህ……… ባንተ ደረጃ ካሉ ሰዎች ጋር……… ” አላስጨረሰኝም። “ደረጃ ምንድነው? ደረጃ መዳቢውስ ማነው? እኔን ከኒኛ ዘበኛ ወይ ከዚህ አስተናጋጅ በላይ ወይ በታች ደረጃ የሰጠን ማን ነው? የኔ መማር እና ቢሮ መቀመጥ? የሳቸው የእኔን እድል አለማግኘትና ዘበኛ መሆን? ንገሪኝ እስኪ እሳቸው የሚያውቁትን ወይ የሚችሉትን ደረጃ ብለን ባወጣንላቸው ዘበኝነት እንዴት እንመዝነዋለን?” አይቼበት የማላውቅበትን የለበጣ ፈገግታ ፈገግ ብሎ ቀጠለ “አፈር ምን ደረጃ አለው? ነፍስስ ብትሆን ያው ነፍስ አይደለች? በምትሰራው ስራ ካልዳኘናት በቀር? የሰው ደረጃው ‘ሰውነቱ‘ ነው።” አለኝ። ዝም አልኩት። ምንስ ልለው እችል ነበር? “ቤተሰቦችሽ? የት ናቸው?” አለኝ ወዲያው ከዛኛው ስሜት ወጥቶ “ቤተሰቦቼ………?…… ” “ምነው? ሞተዋል? ተጣልታችኋል? ወይስ…… እንደ እህል ዘርተውሽ ነው የበቀቀልሽው?…” ተናድጄ አቋረጥኩት ቁስሌን እያወራ እንደሆነ አልገባውም። “ምንም ስነስርዓት አታውቅም። ባለጌ ነህ እሺ!!” አልኩት “እሺ!” አለኝ ቁጣዬን ከምንም ሳይቆጥረው እጄን እየዳበሰ። “እሺ ግን ንገሪኝ። ማወቅ እፈልጋለሁ። ምኑን ልንገረው? አባቴ ከእህቱ ልጅ እንደወለደኝ እና ወንድ አያቴ እንዳሳደጉኝ? አድጌ ራሴን እስከማውቅ አባትና እናቴን እንደማላውቅ? ቤተሰቡ ውስጥ እንደ አንዳች መዓት ሲፀየፉኝ እንደኖርኩ? አያቴ ሲሞት ያየሁትን አስቀያሚ የህይወት ገፅታ? የቱን ልንገረው? ለማንም ለማውራት የሚቀል አልነበረም። እንባዬ መጣ። እያየኝ ማልቀስ አልፈለግኩም። ፈርጣጭ ይበለኝ። ተነስቼ መውጣት እንደጀመርኩ እንባዬን ማስቆም አቃተኝ። ሬስቶራንቱን መግቢያ እንዳለፍኩ እሮጦ ደረሰብኝ። አቀፈኝ። እንደህፃን ደረቱ ላይ አጥብቆ አቀፈኝ። አለቀስኩ። አላባበለኝም። ፀጉሬን እየደባበሰና እየሳመ ለቅሶዬን እስክተው ጠበቀኝ። ያስለቀሰኝ ምን እንደነበረም አልጠየቀኝም። እንደተለመደው እያሳቀኝ የሆስፒታሉ መግቢያ ድረስ ሸኘኝ። ሲሰናበተኝ መልሶ አቀፈኝ። እቅፉ ውስጥ ብዙ መኖር ፈለግኩ። ከሆነ ነገር የሸሸገኝ መሰለኝ። ሰላም ያለበት ዓይነት። እሱም የገባው ይመስል አቅፎኝ ለደቂቃዎች ቆየ። ግንባሬን ሳመኝ። “ዶክተር ሰላም አይደለሽም እንዴ?” ሲስተር ቀለም መግባቷንም አላስተዋልኩም። “ሰላም ነው ሲስተር” “ዶክተር ታዴ እየፈለገሽ ነው ኢመርጀንሲ ነው። ስልሽ እኮ አልሰማሽኝም።” እያወራችኝ የሻከረ መዳፏን ታፍተለትላለች። እስከዛሬ እጇን አይቼው አላውቅም። ከድምፅዋ በቀር ምኗንም አስተውዬ አላውቅም። ለምንድ ነበር አውርቻት የማላውቀው? ለምንድነው ግንባሬን እንደቋጠርኩ ገብቼ የምወጣው? እንዲያከብሩኝ? ሲሳይ እንዳለኝ በራሴ ስለማልተማመን? ወይስ ደረጃዬን ስጠብቅ? “ሲስተር ቤተሰብ አለሽ እንዴ?” አልኳት ለመሄድ እየተሰናዳሁ “አዎን ባለትዳር ነኝ። አንድ ልጅም አለኝ። ምነው? ምን አጠፋሁ?” ጉልበቴ ከዳኝ። ዞሬ አየኋት። በደቂቃ ብዙ ነገር አሰብኩ። ትፈራኛለች ምክኒያቱም ስራዋን ማጣት አትፈልግም። ከስራ ውጪ ስለምንም ነገር አውርቻት አላውቅም።ደሜ ቀዘቀዘ። እንዴት አይነት ጭራቅ አድርገው ነው የሚያስቡኝ? “እንዲሁ ማወቅ ፈልጌ ነው።ለምን ትፈሪኛለሽ? አንቺ በጣም ታታሪ ሰራተኛ ነሽ እኮ!!” ትከሻዋን ዳበስ አድርጌ ወጣሁ። ★ ★ ★ ፈገግ እያልኩ መሆኔ ለራሴ ይታወቀኛል። ታካሚዎቼን እየፈገግኩ እንደማዋራቸው ገብቶኛል እያፏጨሁም መሰለኝ።ሰሞኑን በተደጋጋሚ ከሲሳይ ጋር እራቴን መብላቴን ተከትሎ እንደዚያ እየሆንኩ ነው ዶክተር ሰይፈን ይቅርታ መጠየቄ የሆነ ጭነት ከላዬ ላይ እንደማራገፍ ነበር ወደ ስራ እንዲመለስ የሚያስፈልገውን ሁሉ እንደማደርግ ስነግረው ግን «ይቅርብኝ» ካለው ቃል በላይ ከቃሉ ጋር ከንፈሩን ነክሶ የፈገገው ፈገግታ ራሴን ደጋግሜ እንድረግም አድርጎኛል ሲስተር ቀለም በተረኛ ታካሚ ፈንታ ገባች “ዶክተር ሰው ይፈልግሻል?” “ሲሳይ ነው? ትንሽ ታገሰኝ በይውና ተረኛ ታካሚ
إظهار الكل...
ጠበኛ(ጠቢበኛ) እውነቶች ልብ ወለድ መፃህፍ በደራሲት ሜሪ ከበደ ቀርቦልናሌ ሁላችንም ገዝተን ብናነበው እላለው
إظهار الكل...
#ስንቴ_ገረዝኩት ✂️ : #ክፍል_ሁለት : : ✍ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ : : ....“ዶክተር? ያው ሰውዬ ነው የላከልሽ………” ሲስተር ቀለም በፈገግታ በደመቀ ፊት ጠረጴዛዬ ላይ በፎይል የተጠቀለለውን ምሳ አስቀምጣው ወደ በሩ ተመለሰች “ሲስተር ከዛሬ በኋላ የሚያመጣውን ምሳ እንዳትቀበሉት።” አልኳት ለሁለተኛ ጊዜ ታክሞ ከሄደ ጀምሮ ሶስት ቀኑ ነው። የምሳ ሰዓት እየጠበቀ ምሳ ይልካል። ጠዋት ፅዳቶቹ አፅድተው ሲጨርሱ አበባ ይልካል። “አበባውንም ነው ዶክተር?” “አዎን። ምንም ነገር!!” “እሺ!!” ብላኝ ወጣች ሲስተር ለምንድነው የምትሽቆጠቆጥልኝ? ስለምታከብረኝ? ደሞዝዋን ስለምከፍላት? አለቃዋ ስለሆንኩ? እንጂ አትወደኝም…………… ትጠላኝም ይሆናል። ይሄ የተረገመ ሰው ምን እንዳስብ እያደረገኝ ነው? ★ ★ ★ ሆዴ ምግብ አስፈልጎታል። ሆስፒታሉ አቅራቢያ ያለ ሬስቶራንት እራቴን ለመብላት አዝዤ ተቀምጫለሁ። ከየት መጣ ሳልል ከፊቴ ያለውን ወንበር ስቦ ተቀመጠ። “ማሂ……ዬ……… ?” አለ በተሟዘዘ አጠራር “አንተ ሰው ለምን አትተወኝም?” “አቶ ሲሳይ ታፈሰ። ማዕረግ ያለኝ ሰው ነኝ እሺ።” “Whatever አቶ ሲሳይ ምን እያሰብክ እንደሆነ አልገባኝም። እኔና አንተ ግን ምንም መሆን የምንችል ሰዎች አይደለንም።” “ምክንያት? በእድሜ ስለምትበልጪኝ?” “አቤት? ” “በ18 ዓመትሽ ዩንቨርስቲ ብትገቢ፣ 7 ዓመት ዶክተር ለመባል ብትማሪ……” “ዶክተር ለመሆን ” አቋረጥኩት “ስፔሻሊስት ለመባል የሆነ ዓመት… …… ይሄን ሆስፒታል ከከፈትሽ 6 ዓመት… …… በስሱ 37 የግልሽ ነው። ” እንዲያውቅብኝ ባልፈልግም ተናድጃለሁ። ለምን ተናደድኩ? ትክክለኛ እድሜዬን ስለነገረኝ። እና ምን አናደደኝ? ምክንያት እንኳን የለኝም። “ቁስልህ ዳነልህ?” ወሬውን መቀየር ነው ፍላጎቴ “እየደረቀ ነው። ላሳይሽ?” ከመቀመጫው ብድግ አለ “ኸረ አንተ ሰው?” ለመቀመጥም ለመነሳትም በቀረበ አኳኋን አየሩ ላይ ተንሳፈፍኩ “አየር ላይ ነሽ! አረፍ ትዪ……” ብሎኝ ተመልሶ ተቀመጠ ያዘዝኩት ምግብ መጣ። ተነስቶ እጁን ታጥቦ እስኪመጣ ጠብቂኝ ባይለኝም ጠበቅኩት። የጠቀለለውን ሊያጎርሰኝ ዘረጋ “ጉርሻ አልወድም።” አልኩት “እንዴ? በሞቴ? በፍቅራችን?” ሆነ ብሎ ሬስቶራንት ውስጥ ያለው ሰው እንዲሰማ ጮክ ብሎ ነው የሚናገረው። ሰዎች እየዞሩ ያዩናል። ግማሾቹም ፈገግ እንደማለት ይላሉ። ጎረስኩለት። “ማሂዬ ለክብርሽ ይሄን ያህል አትጨነቂ። ……” አለ የተናገረው ተራ ነገር እንደሆነ ሁሉ ለሌላ ጉርሻ እየተሰናዳ። ተበሳጭቻለሁ። ይበልጥ ያበሳጨኝ ደግሞ ያለው እውነት መሆኑ ነው። “ክብር አንጃ ግራንጃህን ተወኝ። ባለትዳር ነኝ ለባለቤቴ …………” ሳቁ አቋረጠኝ። አስቂኝ ተረት እንደነገሩት ህፃን ተንፈቀፈቀ:: “ምን ያስቅሃል?” “ባለቤትሽ ነዋ ያሳቀኝ ሃሃሃሃ ” “ምን ለማለት ፈልገህ ነው?” ” እንዳንቺ አይነት ሴቶች ወይ አላገቡም፣ ወይ አግብተው ፈተዋል፣ ወይ ከባላቸው ጋር ሰላም አይደሉም።” “እኔ ምን ዓይነት ሴት ነኝ?” “ካልኳቸው ምድብ ውስጥ ከሌለሽ ልቀጣ? እ?” መልሴን ጠበቀ መልስ አልነበረኝም። ተነስቼ ጥዬው መሄድ ነበር ፍላጎቴ እግሮቼን ማዘዝ አቃተኝ። ሽንፈቴን መቀበልም መሰለኝ። ልከራከረውም አቅሙ አልነበረኝም። “እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? ” ድምፄ የቅድሙ ጥንካሬ የለው “እውቀትና ደረጃዋን ድክመትና ሽንፈቷን ለመሸፈን የምትጠቀም ዓይነት ሴት” ከዚህ በላይ መስማት የሚያሳምመኝ መሰለኝ። ተነስቼ ስወጣ ድምፁ ተከትሎኛል። “አየሽ አንቺ ይህቺ ነሽ። ትፈረጥጫለሽ።” እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? የትኛውን ሽንፈቴን ነው በደረጃዬ የሸፈንኩት? ★ ★ ★ ወትሮም ለእንቅልፍ እምብዛም የሆነው ዓይኔ ጭራሽ አልከደን አለ። እቤቴን ጠላሁት። ልብሴን ለመቀየር ካልሆነ በቀር አዳሬም ሆስፒታል ከሆነ ሰነባበትኩ። ምግቤንም የምመገበው እዛው እያስመጣሁ ሆነ። ከዛ ቀን በኋላ ሲሳይን አላገኘሁትም። ከዛ ቀን በኋላ ግን ስላወራናቸው ነገሮች አለማሰብ አቃተኝ። ሁኔታዬን ይብስ ያባባሰው ደግሞ ከቀናት በፊት የገጠመኝ ነገር ነው። ዶክተር ሰይፈ!!! በግምት የ12 አመት ልጅ የምትሆን ህፃን በዊልቸር እየገፋ ሲያልፍ ነበር ያየሁት። ደሜ ሰውነቴ ውስጥ ሲቀዘቅዝ ታውቆኝ ነበር። «ሲስተር? ዶክተር ሰይፈ ልጅ አለው እንዴ? » ቢሮ እንደገባሁ ጠየቅኳት። ጥያቄዬ ይሁን ሰይፈ የትኛው መሆኑ ግራ ያጋባት አልገባኝም። « ዶክተር ሰይፈ የህፃናት……………» «እኮ ገብቶኛል። መጠየቅሽ ገርሞኝ ነው። አዎን ሁለት ሴት ልጆች አሉት። አንዷ ልጁ የመኪና አደጋ ደርሶባት she is totally paralyzed እሱ ነው የሚንከባከባት። አይኗም የማየት አቅሙ እየተዳከመ ነው።» አነጋገሯ ውስጥ ያለው ድምፀት ያሳምማል። አንቺ ምን ግድ አለሽ አይነት ነው። « ሚስቱስ?» «ህምምም……. ሚስቱ እኮ ሞታለች ዶክተር!» « ለምን አልነገራችሁኝም? እንዴት አንድ ሰው አይነግረኝም?» ፀፀቴን ማራገፊያ አጥቼ እንጂ እሷ ላይ የምጮህበት ምክንያትም መብትም የለኝም። « ምን ብለን? ዶክተር አንቺ ልብ ስለማትዪ እንጂ እኮ ለህክምና እዚህ ትመላለሳለች።» ብላኝ በመገረም እያየችኝ ወጣች። ኡፍፍፍፍፍፍፍ በየሱስ ስም ምንድነው የሰራሁት? ዶክተር ሰይፈ በሙያው ማንም እንከን የማያወጣለት ጎበዝ ነው። በተደጋጋሚ እያረፈደ እና እየቀረ ስላስቸገረ ቦርዱን ሰብስቤ ከስራው እንዲባረር ያደረግኩት ቀን ያሳየኝን ፊት ትርጉም የምረዳው አሁን ነው። ምክንያቱን እንኳን ሊነግረኝ የደከመው ነበር የሚመስለው። እሺ ብቻ ነበር ያለኝ። ከቦርድ አባላቱ አንዱ ምክንያቱን እንድሰማው ጠይቆኝ ነበር። «ተውት ምክንያቴን ለእናንተ እያስረዳሁ ህመሜን አላበዛም። ለእስከዛሬው ቆይታችን አመሰግናለሁ!» ያለው በሰአቱ ምን ያለ መስሎኝ ነው ከምንም ያልቆጠርኩት? እንዴት ግን አንዳቸው እንኳን ልጁን እያስታመመ ነው አይሉኝም? ይሄን ያህል ድንጋይ ልብ ያለኝ ነው የምመስላቸው? ይጠሉኛል ማለት ነው አይደል? ማሰብ ይደክማል እንዴ? ማሰብ ደከመኝ:: ስልኬ መልዕክት መቀበሉን ነገረኝ። ከፈትኩት። የማላውቀው ቁጥር ነው። “ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ አይነኬ የህይወት ክፍል አለው። ያን ሽሽት የሆነ ነገር ውስጥ ይደበቃል። ሌት ተቀን ህሙማንን ማገልገልሽ ለብዙዎች ታታሪነትሽን ይነግራቸዋል። ስራሽ መደበቂያሽ መሆኑን ግን አሳምረሽ ታውቂዋለሽ።” ከሱ ውጪ ማንም አይሆንም። ቁጥሩን ደወልኩበት። ይሄ ደግሞ ሊያሳብደኝ ነው እንዴ ሀሳቡ? “ምንድነው ከኔ የምትፈልገው? ምንድነው ግን ችግርህ?” “ደህና እግዜአብሄር ይመስገን!! ምሳ እንኳን አይመቸኝም። እራት ቢሆንልኝ እመርጣለሁ።” አለኝ ዘና ብሎ። ምን ልለው ነበር የደወልኩት? ቁጣዬን ምላሴ ላይ ምን ያልከሰክሰዋል? “እራት ልጋብዝሽ?” አለኝ ዝምታዬን ተከትሎ። ምን እንደምመልስለት ግራ ገባኝ። “ማሂ ፕሊስ?……… እኔ ደስ ብቻ ነው የሚለኝ። ዶክተር ማህደር እራት ተጋበዘችልኝ ብዬ ቀላል ሴት የሆንሽ አይመስለኝም።” የማስበውን እኔ ከስቤ ሳልጨርሰው ከሱ አፍ እሰማዋለሁ። “የባለፈው ሬስቶራንት 12 ሰዓት ላይ ላግኝሽ! ውብ ቀን ዋዩ!!” ብሎኝ እንቢም እሺም ሳልለው ስልኩን ዘጋው። ⚫️ይቀጥላል⚫️ ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳችሁ Like👍👍 እያደረጋችሁ የኔ ምርጦች😘 ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.