ar
Feedback
ሙሉጌታ ንጉሴ ታደሰ ጠበቃ ና የህግ አማካሪ

ሙሉጌታ ንጉሴ ታደሰ ጠበቃ ና የህግ አማካሪ

الذهاب إلى القناة على Telegram

በማንኛውም ፍ/ቤት ጠበቃ ና የህግ አማካሪ ስልክ 0960024515

إظهار المزيد
2 007
المشتركون
-124 ساعات
-97 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
​አንቀጽ 7፦ የተዋዋይ ወገኖች መብትና ግዴታዎች ​1. የተበዳሪ ግዴታዎች፦ ​♦️የብድሩን ዋና ገንዘብ፣ ወለድ እና ሌሎች ክፍያዎች በተስማሙበት የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመክፈል። ​♦️አበዳሪው ስለብድሩ አከፋፈል እና ስለመያዣው ንብረት ሁኔታ መረጃ ሲጠይቅ ትክክለኛ መረጃ የመስጠት። ​♦️የመያዣነት የተያዘውን ንብረት ሳይበላሽ፣ ጉዳት ሳይደርስበት እና እሴቱ ሳይቀንስ በጥንቃቄ የመጠበቅ። ​2. የአበዳሪ መብትና ግዴታዎች፦ ​♦️ክፍያው በተደረገ ጊዜ ክፍያው ስለመፈጸሙ ለተበዳሪው ህጋዊ ደረሰኝ ወይም ማረጋገጫ የመስጠት። ​♦️ተበዳሪ ብድሩን ሙሉ በሙሉ ከፍሎ ሲያጠናቅቅ በመያዣነት የተያዙትን ሰነዶች (የቤት ካርታ/ሊብሬ) ወዲያውኑ ለተበዳሪው የመመለስና የመያዣ ዕገዳውን የማንሳት። ​♦️ተበዳሪ ክፍያውን ካዘገየ በሕግ መሠረት የማሳሰቢያ ደብዳቤ (Default Notice) የመላክ እና ሕጋዊ እርምጃ የመውሰድ መብት አለው። ​አንቀጽ 8፦ የውል ጥሰት እና የዘግይቶ መክፈያ ቅጣት ​የዘግይቶ መክፈያ ቅጣት፦ ተበዳሪው በዚህ ውል አንቀጽ 5 በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ክፍያ ሳይፈጽም ቢቀር፣ ላለፈበት እያንዳንዱ ዘግይቶ የመክፈያ ወር ያልተከፈለው ገንዘብ ላይ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2489 መሠረት ተጨማሪ ____% የቅጣት አበል (Default Rate/Penalty) ይከፍላል። ​የውል ማፍረስ ሁኔታዎች ፦ የሚከተሉት ሁኔታዎች ሲከሰቱ አበዳሪ የብድሩ ጊዜ ከማለቁ በፊት ብድሩ ሙሉ በሙሉ በአንድ ጊዜ እንዲከፈለው የመጠየቅ መብት ይኖረዋል፦ ​♦️ተበዳሪው ተከታታይ የ___ ወራት ክፍያ ሳይፈጽም ሲቀር፤ ​♦️ተበዳሪው በፍርድ ቤት የኪሣራ ውሳኔ ከተሰጠበት ወይም ንብረቱ በተያዘበት ጊዜ፤ተበዳሪው በዚህ ውል ውስጥ የሰጣቸው መረጃዎች፣ ዋስትናዎች ወይም ማረጋገጫዎች ሐሰተኛ ሆነው ሲገኙ፤ ​♦️ተበዳሪው በመያዣነት የተያዘውን ንብረት ከአበዳሪው ፈቃድ ውጪ ለሌላ ወገን ሲሸጥ፣ ሲያስተላልፍ ወይም በሁለተኛ ደረጃ መያዣነት ሲያዝ። ​አንቀጽ 9፦ ማስገደድ እና በህግ የመጠየቅ መብት ​ተበዳሪው ወይም ዋሱ በዚህ ውል መሠረት የተጣለባቸውን ግዴታ ሳይወጡ ቢቀሩ፣ አበዳሪው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1771 እና ተከታዮቹ መሠረት ውሉ በሕግ እንዲፈጸም (Specific Performance) የማስገደድ ወይም ውሉን አፍርሶ ካሳ የመጠየቅ መብት አለው። ​አበዳሪው ለውሉ ማስፈጸሚያ፣ ለጠበቃ አበል፣ ለፍርድ ቤት እና ለሌሎች ሕጋዊ ሂደቶች የሚያወጣቸውን ማንኛውንም ወጪዎች ተበዳሪው እና ዋሱ ሙሉ በሙሉ ለመሸፈን ተስማምተዋል። ​በመያዣነት የተያዘው ንብረት የብድሩን ዕዳ፣ ወለድ እና የፍርድ ቤት ወጪዎችን ሙሉ በሙሉ ለመሸፈን ካልበቃ፣ አበዳሪው ከተበዳሪው እና ከዋሱ ሌሎች ንብረቶች ላይ ዕዳውን የማስከፈል ህጋዊ መብቱ የተጠበቀ ነው። ​አንቀጽ 10፦ ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ (Force Majeure) ​በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1792 እና 1793 መሠረት፣ ከተዋዋይ ወገኖች ቁጥጥር ውጪ በሆኑ እንደ ተፈጥሮ አደጋዎች (የሬክተር ስኬል ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ጎርፍ)፣ ጦርነት ወይም የመንግሥት ድገተኛ ሕጎች ምክንያት ውሉን ለመፈጸም የማይቻል ከሆነ፣ ተዋዋይ ወገኖች ከተጠያቂነት ነፃ ይሆናሉ። ሆኖም ግን የገንዘብ እጥረት ወይም የኢኮኖሚ ውድቀት ከአቅም በላይ እንደሆነ ሁኔታ አይቆጠርም። ​አንቀጽ 11፦ የውል ማሻሻያ እና ሙሉ ስምምነት ​ሙሉ ስምምነት፦ ይህ ውል በተዋዋይ ወገኖች መካከል የተደረገውን ሙሉ ስምምነት የሚወክል ሲሆን፣ ከዚህ ውል በፊት የተደረጉ ማናቸውም የቃልም ሆነ የጽሑፍ ስምምነቶችን ይተካል (Supersedes)። ​ማሻሻያ፦ የዚህ ውል ማናቸውም አንቀጽ ሊሻሻል፣ ሊለወጥ ወይም ሊጨመር የሚችለው በሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች የጽሑፍ ስምምነት እና በውል አረጋጋጭ አካል ፊት ሲረጋገጥ ብቻ ነው። ​አንቀጽ 12፦ አለመግባባቶችን የመፍታት ሁኔታ ​በተዋዋይ ወገኖች መካከል በዚህ ውል አፈፃፀም፣ ትርጓሜ ወይም ውል ጥሰት ምክንያት የሚነሱ አለመግባባቶች በመጀመሪያ በሰላማዊ መንገድ እና በንግግር ለመፍታት ወገኖች ጥረት ያደርጋሉ።(ግዴታ አይደለም) ​አለመግባባቱን በስምምነት መፍታት ካልተቻለ፣ ጉዳዩ በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት ቀርቦ እልባት ያገኛል። ​አንቀጽ 13፦ የውሉ ማጠቃለያ እና የፀደቀበት ቀን ​ይህ ውል በኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1727 እና ተከታዮቹ መሠረት ተዋዋይ ወገኖች እና ምስክሮች ባሉበት፣ ይዘቱ ሙሉ በሙሉ ተነቦና ተረድተውት፣ በገዛ ፈቃዳቸው በሶስት (3) ኮፒ ተዘጋጅቶ በፊርማቸው ያረጋገጡት ሲሆን፤ አንዱ ኮፒ ለአበዳሪ፣ አንዱ ለተበዳሪ እና አንዱ ለውል አረጋጋጭ አካል ይሰጣል። ​አንቀጽ 14፦ የተዋዋይ ወገኖች እና የዋስ ፊርማ ​1. የአበዳሪ ፊርማ፦ ​ስም፦ ________ ​ፊርማ፦ ______ ​ቀን፦ ______ ​2. የተበዳሪ ፊርማ፦ ​ስም፦ ________ ​ፊርማ፦ ______ ​ቀን፦ ______ ​3. የዋሱ (የሰው ዋስ) ፊርማ፦ ​እኔ ስሜ ከዚህ በላይ የተጠቀስኩት ዋስ፣ የተበዳሪውን የብድር ግዴታዎች ሙሉ በሙሉ በመረዳት በጋራና በተነጠል ኃላፊነት ለመወጣት ተስማምቼ ፈርሜአለሁ። ​ስም፦ ________ ​ፊርማ፦ ______ ​ቀን፦ ______ ​አንቀጽ 15፦ የምስክሮች ስምና ፊርማ ​እኛ ከዚህ በታች ስማችንና ፊርማችን የተመለከተው ምስክሮች፣ ተዋዋይ ወገኖች እና ዋስ ይህንን ውል በገዛ ፈቃዳቸው ሲፈራረሙ በዓይናችን ማየታችንን እና በጆሯችን መስማታችንን በማረጋገጥ በምስክርነት ፈርመናል። ​ምስክር 1፦ ​ሙሉ ስም፦ ________ ​አድራሻ፦ ________ ​ፊርማ፦ ____ ቀን፦ ____ ​ምስክር 2፦ ​ሙሉ ስም፦ ________ ​አድራሻ፦ ________ ​ፊርማ፦ ____ ቀን፦ ____ ​ምስክር 3፦ ​ሙሉ ስም፦ ________ ​አድራሻ፦ ________ ​ፊርማ፦ ____ ቀን፦ ____ ይህ የብድር ውል ስምምነት (ከዚህ በኋላ "ውል" እየተባለ የሚጠራው) ዛሬ ____ ቀን 20 ዓ.ም. በ____ ከተማ ተደረገ። ♦️♦️ማሳሰቢያ ♦️♦️፦ ይህንን የብድር ውል ስምምነት የምትጠቀሙ በሙሉ ከውሉ ውስጥ የማትፈልጉት ካለ በራሳችሁ መቀነስ፣መቀየር፣መጨመር ፣መተው ይችላሉ ።​ይህንን ውል ኮፒ በማድረግ (Word ላይ Paste በማድረግ) መረጃዎችን ሞልታችሁ አስፈላጊ ከሆነም እንደ ጉዳዩ ዓይነት ማስተካከል ትችላላችሁ ። እናመሰግናለን ሙሉጌታ ንጉሴ ታደሰ ጠበቃ ና የህግ አማካሪ

ቀን................... ​የብድር እና የመያዣ ውል ስምምነት ​ተዋዋይ ወገኖች ​አበዳሪ፦ ________ (ሙሉ ስም)፣ አድራሻ፡ ክልል/ከተማ __፣ ክፍለ ከተማ __፣ ወረዳ _፣ የቤት ቁጥር _፣ ስልክ ቁጥር ____፣ የቀበሌ/የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥር ____ (ከዚህ በኋላ "አበዳሪ" እየተባሉ የሚጠሩ)፤ ​ተበዳሪ፦ ________ (ሙሉ ስም/የድርጅት ስም)፣ አድራሻ፡ ክልል/ከተማ __፣ ክፍለ ከተማ __፣ ወረዳ _፣ የቤት ቁጥር _፣ ስልክ ቁጥር ____፣ የቀበሌ/የብሔራዊ መታወቂያ____ (ከዚህ በኋላ "ተበዳሪ" እየተባሉ የሚጠሩ)፤ ​እኛ ተዋዋይ ወገኖች በፍ/ብ/ህ/ቁ 1675፣1731፣1721፣1771፣1792፣1793፣2005፣1922፣2471፣2489፣3041 ያለማንም አስገዳጅነት ወደን እና ፈቅደን በነፃ ፍላጎታችን በሚከተሉት ውሎች እና ግዴታዎች ላይ ተስማምተን ይህንን ውል ፈርመናል። ​አንቀጽ 1፦ የውሉ መሠረታዊ ውሎችና ትርጓሜዎች ​"የብድር ገንዘብ" ማለት አበዳሪ ለተበዳሪ በዚሁ ውል መሠረት በብድር መልክ ለመስጠት የተስማማው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን ነው። ​"ወለድ" ማለት ተበዳሪ የብድሩን ገንዘብ በመጠቀሙ ምክንያት ለብድሩ አጠቃቀም የሚከፍለውና በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2478 መሠረት የሚሰላ ተጨማሪ ክፍያ ነው። ​"የመያዣ ንብረት" ማለት የብድሩ መመለሻ ዋስትና እንዲሆን በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 3041 እና ተከታዮቹ መሠረት ለብድሩ ማረጋገጫ ተደርጎ የተያዘ ንብረት ነው። ​"ውል ማፍረስ/የውል ጥሰት" ማለት ተበዳሪ ወይም አበዳሪ በዚህ ውል ውስጥ የተጣሉባቸውን ግዴታዎች ሳይወጡ ሲቀሩ የሚፈጠር ሁኔታ ነው። ​አንቀጽ 2፦ የብድሩ መጠን እና የገንዘብ አሰጣጥ ​2.1 የብድሩ መጠን፦ አበዳሪ ለተበዳሪ የብር ____ (________ ብር) በብድር ለመስጠት የተስማማ ሲሆን፣ ተበዳሪም ይህንኑ የገንዘብ መጠን መበደሩን ያረጋግጣል። ​2.2 የገንዘብ አሰጣጥ ሁኔታ፦ የብድሩ ገንዘብ ለተበዳሪ የሚከተለውን መንገድ በመከተል ይከፈላል፦ ​በባንክ ሂሳብ ማስተላለፊያ (Bank Transfer) ከሒሳብ ቁጥር ______ (የአበዳሪ) ወደ ሒሳብ ቁጥር ____ (የተበዳሪ)፣ የባንክ ስም ____፣ የማጣቀሻ ቁጥር (Ref No.) ______፤ ​ወይም በጥሬ ገንዘብ የተከፈለ ከሆነ አበዳሪ እና ተበዳሪ ይህንን ውል ሲፈራረሙ በምስክሮች ፊት ገንዘቡ ገቢ መደረጉን የሚያረጋግጥ ደረሰኝ ይያያዛል። ​2.3 የመቀበያ ማረጋገጫ፦ ይህ ውል መፈረሙ እና ገንዘቡ ወደ ተበዳሪ የባንክ ሂሳብ ገቢ መሆኑ ተበዳሪ ገንዘቡን ሙሉ በሙሉ ስለመቀበሉ በቂ ማረጋገጫ ይሆናል። ​አንቀጽ 3፦ የብድር ዓላማ ​ተበዳሪ ይህንን የብድር ገንዘብ ለመጠቀም የተበደረበት ዋና ዓላማ ለ____________ (ለምሳሌ፡ ለንግድ ማስፋፊያ፣ ለቤት ግዢ/ግንባታ፣ ለግል ጉዳይ) ነው። ተበዳሪ ገንዘቡን ከዚሁ ዓላማ ውጪ ከህግ ወይም ከሞራል ጋር በሚጋጭ ነገር ላይ ላለማዋል ተስማምቷል። ​አንቀጽ 4፦ የወለድ መጠን እና አሰላሰል ​4.1የወለድ መጠን፦ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2478 እና 2479 መሠረት ተበዳሪ በዋናው የብድር ገንዘብ ላይ በየዓመቱ/በየወሩ % (___ percent) ወለድ ለመክፈል ተስማምቷል። ​4.2 የወለድ አሰላሰል፦ ወለዱ መቆጠር የሚጀምረው ገንዘቡ ለተበዳሪ ገቢ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ ሲሆን፣ በየወሩ/በየዓመቱ በዋናው ያልተከፈለ የብድር መጠን (Outstanding Principal Amount) ላይ ታስቦ ይከፈላል። ​(አማራጭ ከወለድ ነፃ ከሆነ)፦ ይህ ብድር በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2471 መሠረት የተደረገ ከወለድ ነፃ (Interest-Free) ብድር ሲሆን፣ ተበዳሪ የተበደረውን ዋና ገንዘብ ብቻ ለመመለስ ተስማምቷል። ​አንቀጽ 5፦ የክፍያ ሁኔታ እና የመልሶ መክፈያን በተመለከተ ​የክፍያ ጊዜ limit፦ ተበዳሪ የብድሩን ገንዘብ ከነወለዱ ሙሉ በሙሉ ከዛሬ ____ ቀን 20 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ____ ቀን 20____ ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍሎ ለማጠናቀቅ ተስማምቷል። ​5.1የአከፋፈል ሁኔታ፦ ​በክፍልፋይ (Installment)፦ ተበዳሪ በየወሩ በ__ኛው ቀን የብር ____ (______ ብር) ዋና ገንዘብ እና ወለድ አቀናጅቶ ለአበዳሪ የባንክ ሂሳብ ገቢ ያደርጋል። ​በአንድ ጊዜ (Lump Sum)፦ ተበዳሪ የብድሩን ዋና ገንዘብ ከነወለዱ በአንድ ጊዜ እስከ ____ ቀን 20__ ዓ.ም. ድረስ ገቢ ያደርጋል። ​5.2 የቅድመ ክፍያ መብት (Prepayment)፦ ተበዳሪ የብድሩ ጊዜ ከማለቁ በፊት የብድሩን ገንዘብ በሙሉ ወይም በከፊል የመክፈል መብት ያለው ሲሆን፣ ለዚህም ምንም ዓይነት ተጨማሪ ቅጣት ወይም ክፍያ አይጠየቅበትም። ቅድመ ክፍያ ከተፈጸመ ወለዱ የሚሰላው በቀረው ያልተከፈለ ገንዘብ ላይ ብቻ ይሆናል። ​አንቀጽ 6፦ ዋስትና እና የመያዣ ንብረቶች (Collateral & Guarantee) ​በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 3041 እና ተከታዮቹ መሠረት ለብድሩ አከፋፈል ማረጋገጫ የሚከተሉት ዋስትናዎች ተይዘዋል፦ ​የንብረት መያዣ (Mortgage / Pledge)፦ ​ተበዳሪ ለብድሩ ማረጋገጫ እንዲሆን የሚከተለውን ንብረት በመያዣነት ለአበዳሪ ሰጥቷል፦ ​የንብረቱ ዓይነት፦ ________ (ለምሳሌ፡ የመኖሪያ ቤት / መኪና / ቦታ) ​የባለቤትነት ማረጋገጫ (ካርታ/ሊብሬ) ቁጥር፦ _______የንብረቱ ቦታ/አድራሻ፦ ________ ​ተበዳሪ ንብረቱ ከማንኛውም ሌላ ዕዳ፣ ዕገዳ ወይም የመያዣ መብት ነፃ መሆኑን ያረጋግጣል። ​የሰው ዋስ (Personal Guarantee)፦ ​በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1922 እና ተከታዮቹ መሠረት የሚከተለው ግለሰብ የተበዳሪ ዋስ በመሆን ፈርሟል፦ ​የዋሱ ሙሉ ስም፦ ________አድራሻ፦ ________ስልክ ቁጥር፦ ________ ​የዋሱ ግዴታ፦ ዋሱ ተበዳሪው በዚህ ውል መሠረት መክፈል የሚገባውን የብድር ገንዘብ፣ ወለድ እና የዘግይቶ መክፈያ ቅጣት ተበዳሪው ሳይከፍል ቢቀር፣ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1930 መሠረት ከኃላፊነት ሳይሸራረፍ (In Solidum / Joint and Several Liability) ከተበዳሪው ጋር በአንድነት እና በተነጠል ለመክፈል ሙሉ በሙሉ ተስማምቷል።

#ጠበቃ_ሙሉጌታ_ንጉሴ_ታደሰ #ሙሉጌታ_ንጉሴ_ታደሰ_ጠበቃ_ና_የህግ_አማካሪ #ህጎቻችን_ምን_ይላሉ #lawyermulugetanigussie #lawyer_mulugeta_nigussie_tadesse #ህጎቻችን
#ጠበቃ_ሙሉጌታ_ንጉሴ_ታደሰ #ሙሉጌታ_ንጉሴ_ታደሰ_ጠበቃ_ና_የህግ_አማካሪ #ህጎቻችን_ምን_ይላሉ #lawyermulugetanigussie #lawyer_mulugeta_nigussie_tadesse #ህጎቻችን_ምን_ይላሉ_ #ህግ #ስራ #law

#ጠበቃ_ሙሉጌታ_ንጉሴ_ታደሰ #ሙሉጌታ_ንጉሴ_ታደሰ_ጠበቃ_ና_የህግ_አማካሪ #ህጎቻችን_ምን_ይላሉ #lawyermulugetanigussie #lawyer_mulugeta_nigussie_tadesse #ህጎቻችን_ምን_ይላሉ_ #ህግ #ስራ #law