Tsegaye Demeke - Lawyer
الذهاب إلى القناة على Telegram
Legal Service
إظهار المزيدلم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
5 673
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
የምርጫ ሥርዓት፣ መርሆች እና ዓይነቶች
=========================
#የምርጫ ሥርዓት
በፌደራል ህገ መንግሥት መሠረት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሚደረግ ምርጫ በአንድ የምርጫ ክልል ውስጥ ከሚወዳደሩት ዕጩዎች መካከል አብላጫ ድምጽ ያገኘው አሸናፊ ይሆናል። በክልል ህገ መንግሥታት መሠረት ለክልል ምክር ቤቶች የሚመረጡት ተወካዮች ከአንድ በላይ ሲሆኑ ከተወዳዳሪዎቹ መካከል በቅደም ተከተል አብላጫ ድምጽ ያገኙ ዕጩዎች አሸናፊ ይሆናሉ፡፡
የክልል ምክር ቤት አባላት ምርጫን የሚመለከቱ የክልል ህጎች በህገ መንግሥቱና በዚህ አዋጅ ከተቀመጡ ምርጫን የተመለከቱ ድንጋጌዎች ጋር የተጣጣሙ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
#የምርጫ መርሆዎች
ማንኛውም ምርጫ ሁሉን አቀፍ፣ ቀጥተኛ፣ በምስጢር ድምፅ አሰጣጥ መራጩ ፈቃዱን በነፃነት የሚገልጽበት እና ያለ ምንም ልዩነት በሚደረግ ህዝባዊ ተሳትፎ ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡
የመምረጥ ወይም የመመረጥ መብቱ በህግ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ ያልተገደበ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ መምረጥ ወይም መመረጥ ይችላል፣ ሆኖም ለመምረጥም ሆነ ለመመረጥ አይገደድም፡፡
እያንዳንዱ መራጭ የሚሰጠው ድምፅ እኩል ነው፡፡
እያንዳንዱ መራጭ ድምጽ መስጠት የሚችለው በአካል በመገኘት ነው፡፡
#የምርጫ ዓይነቶች
በኢትዮጵያ የሚካሄዱ የምርጫ ዓይነቶች የሚከተሉት ናቸው፣
1. ጠቅላላ ምርጫ፣
2. የአካባቢ ምርጫ፣
3. ማሟያ ምርጫ፣
4. ድጋሚ ምርጫ፣
5. ህዝበ ውሳኔ፡፡
1. #ጠቅላላ ምርጫ
ጠቅላላ ምርጫ በየአምስት ዓመቱ የሚካሄድ የህዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ነው፡፡
ጠቅላላ ምርጫ በመላ ሀገሪቱ በተመሳሳይ ጊዜ ይካሄዳል፡፡ ሆኖም ቦርዱ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው እና ጉዳዩ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ውሳኔ ሲያገኝ በተለያየ ጊዜ እንዲካሄድ ሊያደርግ ይችላል፡፡
ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአንድ የምርጫ ክልል አንድ ተወካይ ብቻ ይመረጣል፡፡
የክልል ምክር ቤቶች አባላት ቁጥር በየክልሉ ህግ መሠረት የሚወሰን ሆኖ ከአንድ የምርጫ ክልል ከአንድ ተወካይ በላይ ለክልል ምክር ቤቶች አባልነት ሊመረጥ ይችላል፡፡ ክልሎች የምክር ቤቶቻቸውን አባላት ቁጥር ለመቀየር የሚሰጡት ውሳኔ ከእጩዎች የምዝገባ የጊዜ ሰሌዳ ስድስት ወር አስቀድሞ መሆን ይኖርበታል፡፡
በህገ መንግሥቱ አንቀጽ 61(3) መሠረት አንድ የክልል ምክር ቤት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በቀጥታ በህዝብ እንዲመረጡ ሲወስን ምርጫው ከጠቅላላ ምርጫ ጋር አንድ ላይ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ ይህ ሲሆን የክልል ምክር ቤቱ ቀጣዩ ምርጫ ከመደረጉ ስድስት ወራት አስቀድሞ ውሳኔውን ለቦርዱ ማሳወቅ አለበት።
2. #የአካባቢ ምርጫ
የአካባቢ ምርጫ በህግ በተደነገገው መሠረት በየደረጃው የሚካሄድ የብሔረሰብ ዞን፣ የዞን፣ የወረዳ፣ የከተማ፣ የክፍለ ከተማ ወይም የቀበሌ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ነው፡፡
የአካባቢ ምርጫ ከአንድ ምርጫ ክልል በየደረጃው ለምክር ቤቶቹ የሚመረጡት ተወካዮች ቁጥር እያንዳንዱ ክልል በሚያወጣው ሕግ ይወሰናል፡፡
በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ህገ መንግሥት አንቀጽ 55 (2) (መ) እና አንቀጽ 51(15) መሠረት የአካባቢ ምርጫዎችን በተመለከተ ሁሉም ሊያደርጋቸው የሚገቡ መለኪያዎችን የሚያስቀምጥ ህግ ሊያወጣ ይችላል።
የአካባቢ ምርጫን የሚመለከቱ የክልል ህጎች በህገ መንግሥቱ እና በዚህ አዋጅ ከተቀመጡ ምርጫን የተመለከቱ ድንጋጌዎች ጋር የተጣጣሙ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
በዚህ አዋጅ ለጠቅላላ ምርጫ የተደነገገው እንደ አግባብነቱ በአካባቢ ምርጫ ላይም የሚፈጸም ሆኖ ቦርዱ በየደረጃው የምርጫ ክልሎች ወይም ጣቢያዎች አደረጃጀት፣ የምርጫ አስፈጻሚዎችና ታዛቢዎች አመዳደብ፣ የመራጭ እና የእጩዎችን ምዝገባ ቦታና ሂደት፣ የግል እጩ ተወዳዳሪዎች የድጋፍ ፊርማ ብዛት እና ሌሎች ጉዳዮችን ይህን አዋጅ መሠረት በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ ይወስናል፡፡
3. #የማሟያ ምርጫ
የማሟያ ምርጫ የሚካሄደው:-
በየደረጃው ያሉ ምክር ቤቶች በተለያየ ምክንያት የተጓደሉባቸው አባላት እንዲሟሉላቸው ለቦርዱ ጥያቄ ሲያቀርቡ፣ ወይም
ተፈጻሚነት ባለው ህግ መሠረት የቀረበ የይውረድልን ጥያቄ ተቀባይነት ሲያገኝ ነው፡፡
ቦርዱ ጥያቄው በደረሰው ስድስት ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የማሟያ ምርጫ ያካሂዳል፡፡
በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) እና (2) የተደነገገው ቢኖርም አንድ ምክር ቤት የሥራ ዘመኑ ሊጠናቀቅ የቀረው ጊዜ ስድስት ወርና ከዚያ በታች ከሆነ የማሟያ ምርጫ አይካሄድም፡፡
4. #ድጋሚ ምርጫ
ድጋሚ ምርጫ ከሚከተሉት ምክንያቶች በአንዱ ሊካሄድ ይችላል፣
በአዋጅ ቁጥር 1133/2011 እና በዚህ አዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ቦርዱ የምርጫ ውጤት እንዲሰረዝና ድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ ሲወስን ወይም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀረበለት አቤቱታ ላይ ተመስርቶ የምርጫ መደገም ውጤትን የሚያስከትል ውሳኔ ሲወስን፣
በዚህ አዋጅ አንቀጽ 61(3) መሠረት እጩ ተወዳዳሪዎች እኩል ድምፅ በማግኘታቸው ምክንያት አሸናፊውን መለየት ያልተቻለ እንደሆነ፡፡
ድጋሚ ምርጫ ሲካሄድ:-
ሌላ አዲስ የመራጮች ምዝገባ ሳያስፈልግ በምርጫ ክልሉ ወይም ችግሩ በተከሰተባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ተመዝግበው በነበሩ መራጮች እንደገና ይካሄዳል፣
በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) (ሀ) መሠረት ምርጫ እንዲካሄድ ሲወሰን አዲስ የእጩዎች ምዝገባ ሳያስፈልግ ቀድሞ በተመዘገቡ እጩዎች መካከል ብቻ ይደረጋል፣
ለድጋሚ ምርጫ የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
የድጋሚ ምርጫ ዝርዝር አፈፃፀም ቦርዱ በሚያወጣው መመሪያ ይወሰናል፡፡
5. #ህዝበ ውሳኔ
ቦርዱ በህገ መንግሥቱ ወይም በሌሎች ህጎች መሠረት አግባብ ባለው አካል ሲወሰን የህዝብን ፍላጎት ለመለካት ወይም ለመወሰን ድምጽ እንዲሰጥ ህዝበ ውሳኔ የሚሰጥበትን ምርጫ ያዘጋጃል፡፡
ህዝበ ውሳኔው እንዲካሄድ ከወሰነው አካል ጋር በመመካከር ቦርዱ ህዝበ ውሳኔ ያስፈለገበትን ጉዳይ ለመለየት በሚያስችለው መልኩ የድምጽ መስጫ ጣቢያዎችን በማደራጀት ህዝበ ውሳኔውን ያከናውናል፡፡
ቦርዱ በህገ መንግሥቱ ስልጣን ከተሰጠው አካል ጋር በመመካከር ድምጽ የሚሰጥበትን ቀን፥ በህዝበ ውሳኔው በድምጽ ሰጪነት ለመሳተፍ ማሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶች በድምጽ መስጫ ወረቀቱ ላይ የሚሠፍረው ለውሳኔ የቀረበው አማራጭ አጻጻፍ እና የህዝበ ውሳኔውን አስመልክተው የሚደረጉ የቅስቀሳ ዓይነቶችን ይዘት ይወስናል። ዝርዝር አፈፃፀሙ ቦርዱ በሚያወጣው መመሪያ ይወሰናል፡፡ ይህም በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 4-7 ድረስ ተደንግጓል።
©℗®
#Join_our_telegram_channel
https://t.me/Consultancy2012
Call us for #Legal_Service
©Tsegaye Demeke - Lawyer
ለ) የኣቀራረቡ ፎርም ሲታይ ደግሞ በቁ.130 (1) ወይም (2) መሰረት የሚቀርበው መቃወሚያም ሆነ ዓቃቤ ሕጉ ለመቃወሚያው የሚሰጠው መልስ ሁሉ በቃል መቅረብ እንዳለበት ከቁ.131 (1) መረዳት ይቻላል፡፡ ተደጋጋሚ ስልጠናዎች እየተሰጡ ኣሁን ኣሁን እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም በተግባር ሲሰራበት የነበረና ኣሁንም ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል ብሎ በኣስተማማኝ መናገር የማይቻለው፤ መቃወሚያ ለማቅረብ ጊዜ መስጠት ፣ መቃወሚያው በፅሑፍ ማቅረብ ፣ ዓ/ሕግ የመቃወሚያው ግልባጭ እንዲደርሰው ማድረግ ፣ ዓ/ሕግ በሚሰጠው ቀነ ቀጠሮ መልሱ በፅሑፍ ያቀርባል ፣ ተከሳሹ በበኩሉ የመልስ መልስ በፅሑፍ ለማቅረብ ጊዜ ይሰጠዋል ፣ በመጨረሻ ፍ/ቤቱ የተከሳሽ መቃወሚያና የዓ/ሕግ መልስ ከሕጉ ጋር ኣገናዝቦ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ይሰጣል፤ ምናልባት ምርመራው ያላለቀ ከሆነ ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠት እንደተጠበቀ ሆኖ ፍ/ቤቱ ብይን ይሰጣል፡፡ ይህ የተንዛዛ ኣካሄድ ሕጉ ከሚያዘው ውጭ መሆኑን ግንዛቤ ሊወሰድበት ይገባል፡፡
ሐ) ከመቃወሚያ ጋር ተያይዞ ሌላ መታየት ያለበት ነጥብ በመቃወሚያነት መቅረብ ያለበት በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ከተዘተዘሩት ምክንያቶች ሲገኝ ብቻ ነው ወይስ ከዚያ ውጭ የሆኑ ምክንያቶች ሲገኙም ማቅረብ ይፈቀደል የሚለው ነው፡፡ በዚህ ዙርያ ሁለት ኣስተሳሰቦች ይራመዳሉ፡፡ በአንድ በኩል በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ባይሸፈንም የክሱ መሰማት ሂደት እንዳይቀጥል የሚያደርጉ ሌሎቸ ምክንያቶች በተገኙ ጊዜም ተከሳሽ እንዲያነሳ ሊፈቀድለት ይገባል የሚሉ ኣሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ቁ.130 ሌላ የመቃወሚያ ነጥብ በማይጨምር ሁኔታ (exclusively) ዘርዝሮ ያስቀመጠ በመሆኑ ከዚያ ውጭ የሚቀር ተቃውሞ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባም የሚል ሓሳብ የሚያራምዱ አሉ ብቻ ሳይሆን ኣብዛኛው ጊዜ በተግባር የሚሰራበትም ይህ ኣቋም ነው ፡፡ እንደ የሞጁሉ ኣዘጋጅ እምነትም በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 130 ስር የማይሸፈን የተቃውሞ ነጥብ በሚነሳበት ጊዜ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባውም፤ ምክንያቱም በዛ ስር ያልተጠቀሰ ነጥብ በማያካትት እና በተሟላ ሁኔታ (exclusively and exhaustively) የተቀረፀ ነው፡፡
2. መቃወሚያውን ስለመመርመርና ስለመወሰን
በቁ. 13. (2) መሰረት የሚቀርበውን ማንኛውንም መቃወሚያ ፍርድ ቤቱ በመዝገቡ ከፃፈ በላ ዓ/ሕጉ መልስ እንዳለው ይጠይቃል፡፡ የቀረበውን መቃወሚያ ሕግን በመጥቀስ ለመወሰን የሚቻል ከሆነ ወይም ዓ/ሕጉ መቃወሚያውን ካልተቃወመ ፍ/ቤቱ ወድያው ይወስናል (ቁ. 131 (1)) ፡፡ ፍ/ቤቱ ጉዳዩን ለማጣራት ማስረጃ መቅረቡ ኣስፈላጊ ሆኖ ካገኘውና ማስረጃ ሳይቀርብ ወድያው ውሳኔ (ብይን) መስጠት የማይቻል በሆነ ጊዜ ኣስፈላጊው ማስረጃ እንዲቀርብ ማዘዝ ይችላል (ቁ. 131 (3)) ፡፡ የተፈለገው ማስረጃ አስቀርቦ ከመረመረ በላ ፍ/ቤቱ ወዲያው ውሳኔ መስጠት እንዳለበት ቁጥር 131 (4) ይደነግጋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በመቃወሚያው ላይ የሚሰጠው ውሳኔ /ብይን/ እንደየ መቃወሚያው ዓይነት ሊለያይ ይችላል፡፡ ይኸዉም፡-
ሀ) የቀረበው መቃወሚያ የሕግ ድጋፍ የሌለው ከሆነ ወይም በማስጃ ካልተደገፈ መቃወሚያውን ውድቅ ያደርጋል ፣
ለ) በቁ. 130/ 2/ለ/፣ /ሐ/፣ ወይም/ሰ/ መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱን ዘግቶ ተከሳሹን ያሰናብታል ፣
ሐ) በቁ.130/2/ሀ/ መሰረት የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ጉዳዩ በተጀመረበት ፍ/ቤት እንዲቀጥል በማዘዝ መዝገቡን ይዘጋል ፣
መ) በቁ. 130(2) (መ) መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱ ተነጥሎ እንዲታይ ያዝዛል ፣
ሠ) በቁ. 130 /2/ሠ/ የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ኣስፈላጊው ፈቃድ እስኪሰጥ መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል ፣
ረ) በቁ. 130/2/ረ/ የቀረበ ከሆነ ደግሞ ኣስቀድሞ መፈፀም ያለበት ስርዓት እስኪፈፀም መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል፡፡
ከዚህ በላይ በፊደል “ለ” የተጠቀሰውን እንዳለ ሆኖ ተከሳሹ ሙሉ በሙሉ ሃላፊ ባለመሆኑ ክሱ በተዘጋ ጊዜ የተከሳሹ ሁኔታ በፀጥታ ወይም በህዝብ ሰላማዊ ኑሮ ላይ ሁከት ወይም ኣደጋ የሚያደርስ መስሎ ከታየው ተከሳሹ ተገቢ በሆነ ስፍራ ወይም ሕክምና በሚያገኝበት ቦታ ተወስኖ እንዲቀመጥ ፍ/ቤቱ ያዝዛል ( የወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 208 እና የወ/ሕግ ዓንቀፅ 130 እስከ 132 ) ፡፡
©℗®
#Join_our_telegram_channel
https://t.me/Consultancy2012
Call us for #Legal_Service
©Tsegaye Demeke - Lawyer
በወንጀል ክርክር የመጀመርያ ደረጃ መቃወሚያ አቀራረብና በፍ/ቤቱ የሚሰጥ ብይን/ትእዛዝ
=========================
1. የመጀመርያ መቃወሚያ
ተከሳሹ ማንነቱ ካረጋገጠ በላ ፍ/ቤቱ ክሱን ለተከሳሹ ያነብለታል፡፡ ክሱ ግልፅ ስለመሆኑም ይጠይቀዋል፡፡ ተከሳሹ ክሱ ግልፅ መሆኑን ካረጋገጠ በላ የመጀመሪያ መቃወሚያ ካለው ይጠይቃዋል፡፡ የመጀመርያ መቃወሚያ ያለው መሆኑን ኣለመሆኑን ሳያረጋገጥ ፍ/ቤቱ የእምነት ክህደት ቃል ወደ መቀበል መሄድ የለበትም፡፡
በተከሳሹ ሊቀርብ የሚችል መቃወሚያ በሁለት መልኩ ሊታይ ይችልል፡፡ ኣንዳኛ በቁ.130 (1) እንደተመለከተው ተከሳሹ በክሱ ማመልከቻ ፎርም ወይም ይዘት ላይ የሚቀርብ መቃወሚያ ነው፡፡ይህ ዓይነቱ መቃወሚያ በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.111 እና 112 የተዘረዘሩትን ነገሮች የሚመለከት ነው፡፡
(1) በቁ. 111 ላይ የተመለከቱት ነገሮች ስናይ፤ ማንኛውም የክስ ማመልከቻ፡-
ቀንና ዓመተ ምህረት የተፃፈበትና የተፈረመበት ፣
የተከሳሹ ስም የያዘ ፣
ተከሳሹ የተከሰሰበት እና የወንጀሉ መሰረታዊ ነገር ያካተተ ፣
ወንጀሉ የተፈፀመበት ጊዜና ስፍራ ያመላከተ ፣
የተበደለው ሰው ስም ወይም ወንጀሉ የተፈፀመበት ንብረት (ተገቢ በሆነ ጊዜ) የሚያመለክት፣
ተከሳሹ ወንጀሉን በመፈፀም ተላልፏል የተባለበት የሕግ ዓንቀፅ የያዘ መሆነ አለበት፡፡
(2) በቁ.112 የተመለከተው ደግሞ ተከሳሹ የተከሰሰበትን ወንጀል ለይቶ ኣውቆ መልስ ለመስጠት እንዲችል እያንዳንዱ ክስ ወንጀሉንና ሆኔታውን በዝርዝር መግለፅ እንዳለበት ነው፡፡
ስለዚህ በቁ.111 ወይም 112 ላይ ከተመለከቱት ሁኔታዎች (ነገሮች) ኣንዳንዶቹ በክሱ ማመልከቻ ላይ ያልተካተቱ ሆኖው ያገኛቸው እንደሆነ ተከሳሹ በመቃወሚያ መልክ ሊያነሳቸው እንዲሚችል ነው፡፡
ሁለተኛውና በተግባርም በተደጋጋሚ ሲነሳ የሚስተዋለው መቃወሚያ በቁ.130 (2) ላይ የተደነገገውን ነው፡፡ በዚህ ንኡስ ዓንቀፅ ስር በመቃወሚያነት ሊነሱ የሚችሉ በርከት ያሉ ምክንያቶች ተዘርዝረው የሚገኙ ሲሆን፤ ኣብዛኛዎቹ የመቃወሚያ ነጥቦች በተከሳሹ ወይም በጠበቃው ብቻ ሊነሱ የሚችሉ ናቸው፡፡ በቁ.130(2) (ሐ) መሰረት የይርጋ ጊዜን ኣስመልክቶ የሚቀርብ ተቃውሞ ግን ተከሳሹ ባያነሳወም ዓቃቤ ሕጉ ሊያነሳው ይችላላ ወይም ፍ/ቤቱ በራሱ ውሳኔ ክሱን መዝጋት ኣለበት (የወ/ሕግ ዓንቀፅ 216 (2)) ፍ/ቤቱ ሌላ ማድረግ ያለበት የተከሳሹ ፍፁም ወይም ከፊል ሃላፊነት ኣጠራጣሪ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ሁሉ ተከሳሹ ተቃውሞ ባያቀርብም ስለዚሁ ነገር ልዩ እውቀት ያለውን የአዋቂ ኣሳብ መጠየቅ ነው፡፡ ቢያስፈልግም በተከሳሹ ጠባይ ፣ ባለፈ ህይወት ታሪኩና በሁኔታዎቹ ላይ ምርመራ እንዲደረግ ትዝዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡
በተለይ ተከሳሹ የኣእምሮ በሽታ ያለበት ወይም በሚጥል በሽታ የሚታወክ ለመሆኑ፤ ወይም መስማትና መናገር የሚሳነው ለመሆኑ ወይም ኣእምሮን በሚያደነዝዝ ነገር ወይም በመጠጥ አዘዉታሪነት በሽታ የተለከፈ ለመሆኑ የሚያመለክቱ ሁኔታዎች በተገኙ ጊዜ ፍ/በቱ ለዚሁ ልዩ እውቀት ያለውን ሰው ኣሳብ የመጠቅ ግዴታ ኣለበት ፡፡
(የወ/ሕግ ዓንቀፅ 51)
በመቃወሚያነት መቅረብ የሚችል ምን እንደሆነና መቃወሚያው ማንሳት ያለበት ማን እንደሆነ ካየን ዘንድ የሚቀርብበት ጊዜ መቼ ነው? የኣቀራረቡ ፎርምስ ምን መሆን ኣለበት የሚለውን ማየት ኣስፈላጊነቱ ኣጠያያቂ ኣይደለም፡፡
ተከሳሹ መቃወሚያ ካለው ማቅረብ ያለበት ክሱ ከተነበበለት በላ መሆኑን ከላይ ተገልፆዋል፡፡ ክሱ ከተነበበለት በላ ብቻ ሳይሆን መቃወሚያ ካለው ወድያው ማቅረብ አለበት፡፡ ይህ ኣባባል ታሳቢ የሚያደርገው ተከሳሹ ክሱ ከሚሰማበት ቀን ኣስቀድሞ እንዲደርሰው ስለሚደረግ ኣንብቦ ሊነሳ የሚችል መቃወሚያ ለማቅረብ ተዘጋጅቶ ይመጣል ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ ክሱን ወዲያው ካልተቃወመ መቃወሚያውን በላ ማንሳት እንደማይችልም በመርህ ደረጃ በስነ ስርዓት ሕጉ ተደንግጓል (ቁ.130 (3)) ፡፡ ሆኖም ይህ ንኦስ ቁጥር መርህ ብቻ ሳይሆን የመርሁን ልዩ ሁኔታም ደንግጓል፡፡ ይኸዉም፤
“… ፍርድ ቤቱ ሲጠይቀው ተከሳሹ የክሱን ማመልከቻ ወድያው ካልተቃወመ በቀር ቆይቶ እንዲህ ያለውን መቃወሚያ ነገሩ በሚሰማበት በሌላ ጊዜ ሊያነሳ ኣይችልም፡፡ ስለሆነም መቃወም የሚችለው መቃወሚያው የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግድ በሆነ ጊዜ ብቻ ነው፡፡” የሚል ነው፡፡
እዚህ ላይ መነሳት የሚገባው ጥያቄ “የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግድ” እና ዘግይተውም ቢሆን ሊቀርቡ የሚችሉ መቃወሚያዎች የተኞቹ ናቸው? የሚል ነው፡፡ ለዚህ ጥያቂ መልስ ሊሆኑ የሚችሉ ሶስት ምሳሌዎች መጥቀስ ይቻላል፡፡
ቁ.130 (2) (ለ) ተከሳሹ በዚሁ ክስ ከዚህ ቀደም ተከሶ ነፃ የወጣ ወይም የጥፋተኝነት ውሳኔ የተሰጠበት መሆኑ ወይም
ቁ.130 (2) (ሐ) ክስ የቀረበበት ወንጀል በይርጋ ሕግ የታገደ ወይም ምሕረት ወይም የኣዋጅ ምሕረት (ይቅርታ) የተደረገለት መሆኑን ወይም
ቁ.130 (2) (ሰ) ለፈፀማቸው ተግባሮች ሃላፊ ያለመሆኑን ባመለከተ ጊዜ ነው፡፡
የመጀመሪያው ምሳሌ ብንመለከት በስነ ስርዓት ሕጉ ብቻ የተቀመጠ ሳይሆን በኢፌዴሪ ሕገ መንግስት ዓንቀፅ 23 ላይም “ማንኛዉም ሰው በወንጀል ሕግና ስነ ስርዓት መሰረት ተከሶ የመጨረሻ በሆነ ውሰኔ ጥፋተኛነቱ በተረጋገጠበት ወይም በነፃ በተለቀቀበት ወንጀል እንደገና ኣይከሰስም ወይም ኣይቀጣም” በሚል መልኩ ተገልፆ ይገኛል፡፡ በሁለተኛው ምሳሌ የተጠቀሰ ይቅርታን በተመለከተም ሕገ መንግስተዊ እውቅና ያገኘ ነው (ዓንቀፅ 71 (7)) ፡፡ እንዲሁም የይርጋ ጉዳይ በፍርድ ቤት ሳይቀር መነሳት ያለበት መቃወሚያ በመሆኑና ሃላፊ ያለመሆን ጥያቄም ኣስገዳጅ ድንጋጌ ሆኖ በወንጀል ሕግ የሰፈረ በመሆኑ ክሱ እንደተነበበ ወድያው ባይቀርቡም የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግዱ በመሆናቸው በማንኛውም ጊዜ ሊነሱ የሚችሉ መቃወሚያዎች ናቸው፡፡
የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግድ መቃወሚያ ሲገኝ ጊዜ ዘግይቶም ቢሆን ሊነሳ ይችላል ብሎ ሕጉ ሲያስቀምጥ ይህን ተከትሎ የሚነሳ ጥያቄ በስር ፍርድ ቤት ሳይነሳ ቀርቶ በይግባኝ ፍርድ ቤት ይግባኙ በሚታይበት ጊዜ ቢነሳስ ተቀባይነት ኣለው ወይ የሚል ይሆናል፡፡ እንግዲህ ይህ ልዩ ሁኔታ ከኣጠቃላይ የሕገ መንግስቱ መርሆዎችና ከቅጣት ዓላማ ኣንፃር መታየት ስላለበት በይግባኝ ፍርድ ቤት በሚሰማበት ወቅት የተነሳ መቃወሚያ ቢሆንም እንኳ ተቀባይነት ሊያገኝ ይገባል፡፡ የመዝገብ ቁጥሩ ማስታወስ ባልችልም በ1967 ዓ.ም አንድ ሰው የግድያ ወንጀል ፈፅሟል በሚል በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን ማእከላዊ /ከፍተኛ/ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦበት ጥፋተኛ ሆኖ ስለተገኘ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት ይፈረድበታል፡፡ ፍርዱን በመቃወም ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባይ ያቀረበ ሲሆን የጠ/ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎትም መዝገቡ ከመረመረ በላ ክሱ በይርጋ ጊዜ የታገደ ሆኖ ስላገኘው በዞኑ ፍ/ቤት የተሰጠን የጥፋተኛነትና የቅጣት ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ይግባይኝ ባይን በነፃ እንዲለቀቅ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
የኢትዮጵያ ዜግነትን ስለማጣትና ፤ የሌላ ሀገር ዜግነት በማግኘት የኢትዮጵያ ዜግነት ስለሚቀርበት ሁኔታ
===========================
1. #ኢትዮጵያን ዜግነት ስለመተው
የሌላ አገር ዜግነት ያገኘ ወይም ሊሰጠው ቃል የተገባለት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን የመተው መብት አለው፤
ዜግነቱን ለመተው የፈለገ ኢትዮጵያዊ ባለሥልጣኑ በሚወስነው ቅጽ መሠረት አስቀድሞ ለባለሥልጣኑ ማሳወቅ አለበት፤
ለአካለ መጠን ያላደረሰ ሰው ዜግነቱን ለመተው የሚችለው በወላጆቹ የጋራ ውሳኔ ወይም ከወላጆቹ አንዱ የውጭ አገር ሰው ከሆነ ኢትዮጵያዊ በሆነ ወላጁ ውሳኔ ይሆናል፤
ዜግነቱን ለመተው መፈለጉን ያሳወቀ ኢትዮጵያዊ፣
የሚፈለጉበት ብሔራዊ ግዴታዎች ካሉ እነዚህኑ ከመወጣቱ፣ ወይም በወንጀል ተከስሶ ወይም ተፈርዶበት ከሆነ ከክሱ ነፃ ከመደረጉ ወይም የተወሰነበትን ቅጣት ከመፈጸሙ፤ በፊት የዜግነት መልቀቂያ አይሰጠውም።
ባለሥልጣኑ የዚህ አንቀጽ ድንጋጌዎች መሟላታቸውን ካረጋገጠ በኋላ ዜግነቱ የሚቋረጥበትን ቀን የሚገልጽ የዜግነት መልቀቂያ የምስክር ወረቀት ለባለጉዳዩ ይሰጠዋል፡
የዜግነት መልቀቂያ የምስክር ወረቀት ያልተሰጠው ማንኛውም ባለጉዳይ ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ይግባኝ የማቅረብ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
2. #የሌላ ሀገር ዜግነት በማግኘት የኢትዮጵያ ዜግነት ስለሚቀርበት ሁኔታ
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በራሱ ፍላጎት የሌላ አገር ዜግነት ካገኘ ዜግነቱን በራሱ ፈቃድ እንደተወ ይቆጠራል፣
ከወላጆቹ አንዱ የውጭ አገር ዜጋ በመሆኑ ወይም በውጭ አገር በመወለዱ የሌላ አገር ዜግነት ያገኘ ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን አስቀድሞ እንዲተው ካልተደረገ በስተቀር ለአካለ መጠን ካደረሰ በኋላ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የሌላ አገር ዜግነቱን ትቶ በኢትዮጵያዊነቱ ብቻ ለመቀጠል መምረጡን ለባለሥልጣኑ ካላሳወቀ ዜግነቱን በፈቃዱ እንደተወ ይቆጠራል፣
ራሱ ጠይቆ ሳይሆን በማናቸውም ሌላ ምክንያት ላይ ተመሥርቶ በሕግ ድንጋጌዎች ተፈጻሚነት የተነሳ የሌላ አገር ዜግነት ያገኘ ኢትዮጵያዊ፤
ባገኘው የሌላ አገር ዜግነት መብቶች መጠቀም ከጀመረ፣ ወይም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ያገኘውን የሌላ አገር ዜግነት ትቶ በኢትዮጵያዊነቱ ብቻ ለመቀጠል መምረጡን ለባለሥልጣኑ ካላሳወቀ ዜግነቱን በፈቃዱ እንደተወ ይቆጠራል።
ከኢትዮጵያ ዜግነቱ በተጨማሪ የሌላ አገር ዜግነት ይዞ የተገኘ ሰው የኢትዮጵያ ዜግነቱ ቀሪ እስከሚሆን ድረስ የኢትዮጵያ ዜግነት ብቻ እንዳለው ሆኖ ይቆጠራል፡፡
©℗®
#Join_our_telegram_channel
https://t.me/Consultancy2012
Call us for #Legal_Service
©Tsegaye Demeke - Lawyer
እግድ እና የመያዣ ወይም የቅድሚያ መብት
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 173079 ከፍርድ በፊት የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረትን አስመልክቶ የሚሰጥ የእግድ ወይም ንብረት የማስከበር ትዕዛዝ የመያዣ መብትን የማያቋቁም በመሆኑ የቅድሚያ መብትን ሊፈጥር እንደማይችል አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
ይህ የህግ ትርጉም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሰበር ሰሚ ችሎት ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁጥር 97206 እና በሰ/መ/ቁጥር 29269 በዚሁ ጉዳይ ላይ ሰጥቶት የነበረውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም አሻሽሏል ወይም ለውጧል፡፡
ከሟች ለወራሾቹ ሊተላለፉ የሚችሉና ሊተላለፉ የማይችሉ መብትና ግዴታዎች
======================
በመጀመሪያው ምእራፍ እንደተመለከተው የውርስ ሕግ ዋናው አላማና ግብ የሟች መብትና ግዴታዎች ወደ ወራሾቹ የሚተላለፍበትን ስርዓት መልክ ማስያዝ ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ሟች የነበረው መብት እና ግዴታ በሙሉ ወደ ወራሾቹ ይተላለፋል ማለት አይደለም፡፡
በፍትሐብሔር ሕጋችን ለሟች ወራሾች የሚተላለፉት የሟች መብቶችና ግዴታዎች በሟች መሞት ምክንያት ተቋርጠው የማይቀሩት ብቻ መሆናቸው በግልጽ ተደንግጓል፡፡ ይህንንም ፅንሰ ኃሣብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 826 ንዑስ አንቀጽ 2 '' በሟች መሞት ምክንያት ተቋርጠው ካልሆነ በቀር በዚህ አንቀጽ ደንቦች መሠረት በውርስ ውስጥ የሚገኙት የሟች መብቶችና ግዴታዎች ለወራሾቹ እና የኑዛዜ ባለስጦታዎች ይተላለፋሉ'' በማለት በግልጽ አስቀምጦታል፡፡
ከዚህ የሕግ ድንጋጌ የምንረዳው በሟች መሞት ምክንያት ተቋርጠው የሚቀሩ መብቶችና ግዴታዎች ወደ ወራሾቹ ሊተላለፉ እንደማይችሉ ነው፡፡ እነዚህ በሟች መሞት ምክንያት ተቋርጠው የሚቀሩ መብትና ግዴታዎች ምንድን ናቸው የሚለውን ጥያቄ ስንጠይቅ ሟች በግሉ ብቻ ሊጠይቃቸው እና ሊጠቀምባቸው የሚችሉ መብቶች /Personal rights/ እና ሟች በግሉ ሊፈጽማቸው የሚገቡ ግዴታዎች /Personal obligations/ ናቸው፡፡ የሟች ግላዊ መብቶችና ግዴታዎች የተለያዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ለምሣሌ ሟች በሙያው በመንግስት መስሪያ ቤት ወይም በአንድ የግል ድርጅት ተቀጥሮ የሚሰራ ሠራተኛ ቢሆን የሟቹ የመሥራት መብት ወራሾቹ ከእሱ ጋር ተመሣሣይ በሆነ ሙያ የሰለጠኑ ቢሆኑም እንኳን ለወራሾቹ በውርስ የሚተላለፍ አይደለM፡፡ አንደዚሁም ሟች ከልጆቹ ወይም ከዘመዶቹ የነበረው ቀለብ የመጠየቅ መብት ሟች ሲሞት የሚቋረጥና ለወራሾቹ ሊተላለፍ የማይችል መብት ነው፡፡ በሌላ በኩል ሟች በግል ችሎታው ለመፈፀም የገባቸው ግዴታዎች፣ ወራሾቹ በዚያ ሙያ ከእሱ የበለጠ ችሎታ እና ትምህርት ቢኖራቸውም እንኳን ሟች በግሉ ለመፈፀም የገባውን ግዴታ እነርሱ ተክተው እንዲፈጽሙ አያስገድዳቸውም፡፡ ይህም አንድ የህክምና ዶክተር ወይም ጠበቃ በሙያው ለመፈፀም የገባውን ግዴታ እሱ ሲሞት ወራሾቹ ዳክተሮች ወይም ጠበቃ ቢሆኑም እንኳን ሟች በገባው የውል ግዴታ እነርሱ ወርሰውና ተተክተው እንዲፈጽሙ መጠየቅና ማስገደድ አይችልም፡፡ ስለዚህ ከሟች ወደ ወራሾቹ የሚተላለፉ መብትና ግዴታዎችን ለመለየት መብትና ግዴታዎቹ በሟች መሞት ምክንያት የሚቋረጡ ናቸው ወይስ አይደሉም የሚለውን ጥያቄ በማንሣት መመርመር ያስፈልጋል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ሟች በውል ወይም በሕግ መሠረት ያገኘው የይዞታ መብት በውሉ ወይም በሕግ በተገለፀው የጊዜ ገደብ እስከሚደርስ ድረስ በአንድ ንብረት የመጠቀም መብት ሙሉ ወይም ሌጣ የንብረት ባለቤትነት፣የአክሲዮን፣ የንግድ መደብር እና የሌሎች የንግድ ማህበር ድርሻዎች ሟች ከሌሎች ሰዎች ሊጠይቀው የሚችል የገንዘብ እዳና በውል መሠረት የሚፈፀም ግዴታ እንደዚሁም ሌሎች አበዳሪዎች ከእሱ የሚጠይቁት የገንዘብ እዳና በሟች መሞት ምክንያት የማይቋረጥ የውል ግዴታ ለሟች ወራሾች የሚተላለፉ የሟች መብትና ግዴታዎች ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ሕግ የሟች ወራሾች የውርስ ንብረት ክፍል ናቸው በማለት የሟች ወራሾች ጥያቄ ማንሣት የማይችሉባቸውን የካሣና የጡረታ ገንዘብ ክፍያዎች እንደዘ!ሁም በሞት ጊዜ ሊከፈል ስለተገባ የህይወት ኢንሹራንስ ክፍያ ገንዘብ በምን መልኩ ለሟች ወራሾች እና የሟች ወራሽ ላልሆነ ሰዎች ሊተላለፉ እንደሚችሉ ገዥነት ያላቸውን ደንቦች ደንግጓል፡፡
©℗®
#Join_our_telegram_channel
https://t.me/Consultancy2012
Call us for #Legal_Service
አሁን በስራ ላይ ያለው የውርስ ህግ አጣሪ ስለሚሆኑ ሰዎች ሲደነግግ ቀዳሚውና የመጀመሪያው የውርስ አጣሪ የሚሆነው ሟች በኑዛዜ የውርስ አጣሪ አድርጎ የሾመው ሰው እንደሆነ ከገለጸ በኀላ ሟች በኑዛዜ የውርስ አጣሪ አድርጎ የሾመው ሰው ከሌለና በኑዛዜው የውርስ አጣሪ እንደሚሆንና ጠቅላላ ኑዛዜ የተደረገለት ሰው መገኘት የሟችን ያለኑዛዜ ወራሾች የአጣሪነት ስራ እንደሚያስቀረው በፍትህብሄር ህግ ቁጥር 948 ንኡስ ቁጥር 2 እና 3 የሚደነግግ ሲሆን የሟች ውርስ መዘጋት ማለት ደግሞ የሟችን ንብረት ለወራሾች በአግባቡ የማከፋፈል ስራን አይጨምርም፡፡
የውርስ አጣሪው ሀላፊነት ከላይ ያነሳናቸውን ተግባር በመፈጸምና የሟችን ወራሾችና የሟች ከእዳ ተከፍሎ የሚቀረውን ንብረት በማጣራት፣ ዝርዝርና የመጨረሻ ሪፖርት ለወራሾቹ ማቅረብ ብቻ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ የውርሱን ንብረት ማስተዳደርም ሆነ የሟችን ንብረት መከፋፈል የወራሾች መብትና ሀላፊነት እንጂ የውርሱ አጣሪ አይደለም፡፡
በመሆኑም ውርስ አጣሪ በዋነኛነት ሊፈጽማቸው የሚችላቸው ተግባራት፣
ከሟች ውርስ መብት አለን የሚሉትን ሰዎች ሁኔታ መወሰን፣
የሟችን የውርስ ንብረት ማስተዳደር፣
የሟችን የውርስ እዳ መክፈል፣ ናቸው፡፡
ውርስ አጣሪው የተሾመበት ኑዛዜ ዋጋ ያለው ኑዛዜ መሆኑ አከራካሪ ሆኖ ሲገኝ ወይም፣
በሌላ ምክንያት ውርስ አጣሪውን በመለየት ላይ የሚያጠራጥር ነገር ሲኖር ወይም፣
ብዙ ውርስ አጣሪዎች ለምሣሌ ስልጣናቸው 947 የሚመነጭ ብዙ ያለ ኑዛዜ ወራሾች ኖረው በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 958 በሚደነግገው መሠረት ውርሱን በመተባበር በመግባባት ለማስተዳደርና ለማጣራት ያልተስማሙ እንደሆነ ወይም፣ ከወራሾቹ መካከል አንዱ አካለ መጠን የላደረሰ ልጅ ወይም የተከለከለ ሰው ወይም በማናቸውም ሌላ ምክንያት ለምሣሌ በአገር ባለመኖሩ፣ እብደቱ በግልጽ ያልታወቀ ሰው በመሆኑና በሌሎች ምክንያቶች ጥቅሙን ለማስከበር የማይችል በሆነ ጊዜ ወይም፣
የውርሱ አስተዳዳር ወይም የማጣራቱ ስራ ልዩ ችግር ያስነሣና ልዩ ሙያ ያላቸውን ሰወች ወይም ሌላ ችግሩን ለመቅረፍ የሚችል የውርስ አጣሪ መሰየም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ወይም፣
በሕግ ሟች ኑዛዜ ወይም በዳኞች የተሰየመው አጣሪ ቸልተኛና ትጉህ ያልሆነ እንደሆነ ወይም የማጭበርበር ባህሪ የሚታይበትና ሀቀኝነት የጉደለው የሆነ አንደሆነ ወይም አጣሪው የማጣራት ስራውን በሚገባ ለመፈፀም ችሎታ የሌለው መሆኑ የታወቀ እንደሆነ፣
ዳኞች ከማናቸውም በጉዳዩ ያገባኛል ከሚል ባለጉዳይ ጥያቄ አቅራቢነት በሕግ፣ በኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት ውሣኔ ተሰይሞ የነበረውን የውርስ አጣሪ በመሻር በአካባቢው ውል ለማዋዋል ስልጣን የተሰጠውን ሰው ወይም ማናቸውንም ለስራው ብቁ ነው ብለው የሚመርጡትን ሌላ ሰው በውርስ አጣሪነት ለመሰየምና ለመተካት እንደሚችሉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 951 ተመልክቶ እናገኘዋለን፡፡
በውርስ ህጋችን በግልጽ እንደተመለከተው በህግ፣ በሟች ኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ የተመረጠ ወይም የተተካ የውርስ አጣሪ የሚከተሉት ግዴታዎችና ሀላፊነቶች ይኖሩበታል፡፡
ሟች በህይወት ዘመኑ ያደረገው ኑዛዜ ካለ ኑዛዜውን መፈለግና የሟችን የኑዛዜ ወይም ያለኑዛዜ ወራሾች እነማን እንደሆኑ ማረጋገጥ፣
የውርስ ንብረት ከብልሽትና ከብክነት ለመታደግ ተገቢውን የጥንቃቄ እርምጃ በመውሰድና ሌሎችንም አስፈላጊ ተግባራት በመፈጸም የውርሱን ሀብት ማስተዳደር፣
በግልጽ የታወቁ፣ ክርክርን የማያስነሱ መከፈል ያለባቸውን የውርስ እዳዎች በፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 1014 በተቀመጠው ቅደም ተከተል መሰረት መክፈል፣
ሟቹ በልዩ ኑዛዜ ያደረጋቸውን ስጦታዎች መክፈልና የሟችን የኑዛዜ ቃል ለመፈጸምና ውጤት ለመስጠት ማንኛውንም አስፈላጊ ጥንቃቄ ማድረግ፣
ጥያቄው ያገባኛል በሚል ማናቸውም ባለጉዳይ ሲቀርብና ዳኞችን የሚያሳምን ሆኖ ሲገኝ ስለስራው መልካም አፈጻጸም አንድ ዋስ ወይም ሌላ የመልካም ስራ አፈጻጸም ማረጋገጫ ሊሆን የሚችል መያዣ ማቅረብ፣
ስራውን ለመተው ሲፈልግ አዲስ አጣሪ እስከሚሰየምና ተተክቶ ስራውን እስከሚጀምር ድረስ የአጣሪነት ስራውን የማከናወን፣
ሟች በአደረገው ኑዛዜ ስለአጣሪነቱ የስልጣን ወሰንና ስለስራው አፈጻጸም የሰጠውን መመሪያና ትእዛዝ ተከትሎ የመስራትና ዳኞችም ስለስልጣኑ ወሰንና ስለስራው አፈጻጸም የሚሰጡትን ትእዛዞች በማክበር የአጣሪነት ስራውን ማከናወን፣
ውርሱን አጣርቶ ከጨረሰ በኋላ ለወራሾቹ ስለማጣራቱ የስራ ክንውን ሪፖርት ማቅረብ፣
ውርስ አጣሪው ማናቸውንም የህጉን ድንጋጌዎች በሟች ኑዛዜ የተሰጡትን መመሪያዎች ወይም በዳኞች የተሰጡትን ትእዛዞች በሚቃረን በጥፋቱ ወይም በቸልተኝነቱ መንገድ ለሚያደርጋቸው ጉዳዮችና በዚያ መሰረት ለሚደርስ ጉዳት በሀላፊነት የመጠየቅ ግዴታ እንዳለበት፣
ከፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 952፣ 954-957 እንደዚሁም የፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 960 እና 961 በማየት መረዳት ይቻላል፡፡
በሌላ በኩል ህጉ በህግ፣ በሟች ኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት ውሳኔ በውርስ አጣሪነት ለሚሰየሙ ሰዎች ያስቀመጠላቸው መብት አለ፡፡ ከመብቶቹ መካከል እጅግ በጣም አስፈላጊው የውርስ አጣሪነት ስራ ማንም ሰው በፈቃዱ ብቻ ሊያከናውነው የሚገባና ማንም ሰው ያለፈቃዱ የአጣሪነት ስራዎችን ለመቀበል የማይገደድ መሆኑ ነው፡፡ አንድን ተግባር አንድ ሰው ተገድዶ እንዲያከናውን ማድረግ የተከለከለና መሰረታዊ የሆነውን የሰው ልጅ ነጻነት መብት የሚነካ በመሆኑ የውርስ አጣሪነትን ተግባር አንድ ሰው ሳይፈልግ እንዲቀበልና እንዲሰራ ማድረግ እንደማይቻል የፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 953 በግልጽ ይደነግጋል፡፡ ሁለተኛው መብቱ ደግሞ ውርስ አጣሪው ስራውን እፍጻሜ ለማድረስ ወይም ለተወሰነ ጊዜ ለመስራት በግልጽ ግዴታ የገባ ካልሆነ በቀር በማናቸውም ጊዜ ስራውን መተው የሚችል መሆኑ ነው፡፡ እዚህ ላይ በጥንቃቄ መታየት ያለበት ጉዳይ ‹በግልጽ ግዴታ የገባ ካልሆነ በቀር› የሚለው ሀረግ ነው፡፡ በዝምታ በህግ፣ በሟች ኑዛዜ ወይም በዳኞች የውርስ አጣሪ ሆኖ እንዲሰራ መመረጡን ተቀብሎ ስራ መጀመሩ ብቻውን የማጣራት ስራውን በማናቸውም ጊዜ የመተው መብቱን አያስቀርበትም፡፡ ስራውን የመተው መብቱ ቀሪ የሚሆነው በግልጽ እራሱን ግዴታ ያስገባ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡
ሌላው እዚህ ላይ መታየት ያለበት ውርስ አጣሪው ይህንን የማጣራቱን ስራ የመተው መብቱን እንደፈለገው ሊጠቀምበት አይችልም፡፡ የሟች ውርስ ንብረት የግድ መጠበቅና በጥንቃቄ መያዝ ስለሚገባው ሌላ ተተኪ አጣሪ እስኪመረጥና ስራውን እስኪረከብ ድረስ ስራውን እየሰራ መቆየት ያለበት መሆኑ የፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 954 ድንጋጌዎችን በማየት ለመረዳት ይቻላል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ ለውርስ አጣሪ የተቀመጠለት መብት አጣሪው ውርሱን ለማጣራት ለሰራው ስራ የአገልግሎት ዋጋ የማግኘት መብት ያለው መሆኑ ነው፡፡ የውርሱ አጣሪ የአገልግሎት ክፍያውን የሚያገኘው ሟች በኑዛዜው ውስጥ በሰጠው መመሪያ ወይም ወራሾቹ በሚያደርጉት ስምምነት ወይም ዳኞች በሚሰጡት ውሳኔ መሰረት ሊሆን እንደሚችል የፍትሀ ብሄር ህግ ቁጥር 959 ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም አጣሪው ውርሱን በማጣራት ለሰራው ስራና ግልጋሎት ከውርሱ ንብረት ላይ ከላይ ባስቀመጥናቸው ሁኔታዎች ሲወሰንለት የአገልግሎት ዋጋ የማግኘት መብት እንዳለው መታወቅ ይኖርበታል፡፡
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የውርስ ህግ መሰረት ‹ውርሱን ስለማጣራት› የሚለው ጽንሰ ሀሳብ ምንነትና ይዘት እንደዚሁም ጠቀሜታ በጥንቃቄ ሊታይ የሚገባው ነው፡፡ የመጀመሪያው በምእራፍ ሁለትም ለመጠቆም እንደተሞከረው ‹የሟች ውርስ መከፈት› እና ‹የሟችን ውርስ ማጣራት› የሚሉት ጽንሰሀሳቦች እጅግ በጣም የተለያዩ ናቸው፡፡ የሟች ውርስ መከፈት የምንለው ሟች ህይወቱ ካለፈበት ቅጽበት ጀምሮ ምንም አይነት የሲቪል መብት ግዴታ ሊኖረው ስለማይችል ህጉ የሟች ህይወት ካለፈችበት ሰኮንድ ጀምሮ የሟች መብትና ግዴታ ለሟች ወራሾች ለማስተላለፍ የሚያደርጋቸውን ጥንቃቄ የሚመለከት ነው፡፡
የሟች ውርስ የሚከፈተውም ሟች መኖሪያ ስፍራና ሟች በሞተበት ጊዜ እንደሆነ በፍትሀ ብሄር ህግ ቁጥር 826 ተመልክቷል፡፡ የሟችን ውርስ ማጣራት የምንለው ደግሞ የሟችን ያለኑዛዜና በኑዛዜ ወራሾች የሚለዩበት፣ የሟች እዳ የሚከፈልበት፣ የሟች አበዳሪዎች እና ተበዳሪዎች የሚለዩበት፣ ንብረቱ በሟች ወራሾች እስኪተላለፍና ውርሱ እስከሚዘጋበት ቀን ድረስ የንብረት ማስተዳደር ስራዎች የሚከናወንበት ውስብስብ ተግባር ነው፡፡
ወራሽነትን ስለማጣራትና ስለ ውርስ አጣሪ
=======================
የሟች ውርስ ሟች በሞተበት ጊዜና ቦታ የሚከፈት ቢሆንም የሟች ውርስ እስከሚጣራ ድረስ የሟች ንብረት ''አንድ የተለየ ንብረት፣፣ አንደሆነ ይቆጠራል፡፡ ይኸም ማለት የሟች ንብረት ከሌሎች ሰዎች ንብረት ወይም ከወራሾቹ ንብረት ጋር ሣይቀላቀል የባለቤትነት መብቱ ለወራሾች ሣይተላለፍ እንደ አንድ ልዩ ንብረት፣ Distinct estate፣ ሆኖ መያዝ እንዳለበት የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 942 ይደነግጋል፡፡ ይኸም የሚሆነው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ የሟች ውርስ ሣይጣራ ንብረቱ ከሌሎች ሰዎች ንብረት ጋር ቢቀላቀል ውርሱን ለማስተዳደርም ሆነ ለማከፋፈል የሚያጋጥመው ችግር ከባድ በመሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም ውርስን የማጣራቱ ሥራ በሟች የውርስ ስርዓት አፈጻጸም ውስጥ በቀላሉ የማይታይና እጅግ በጣም አስፈላጊ ተግባር ነው፡፡ የውርስ ማጣራት ሥራ በሟች የውርስ ስርዓት ለማስፈፀም አስፈላጊ ተግባር ነው ካልን የውርስ ማጣራቱን ተግባር ሀላፊነት ወስዶ የሚያስፈጽም አንድ ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች መኖር አለባቸው፡፡ እነዚህ ውርሱን የማጣራት ተግባር የሚፈጽሙትን ሰዎች የውርስ አጣሪ በመባል ይታወቃሉ።
1.#ወራሽነትን ስለማጣራት
ውርስ ማጣራት ማለት፣
የሟች ወራሾች እነማን እንደሆኑ አጣርቶ መወሰን፣
የውርሱ ሀብት መጠን አይነትና ግምት እንደዚሁም የሚገኝበትን ቦታ አጣርቶ መወሰን፣
ሌሎች ሰዎች ከሟች የተበደሩትን ገንዘብ መሰብሰብና በሟች ውርስ ላይ ሊከፍላቸው የሚገቡ አስገዳጅ የሆኑ አዳዎችን አጣርቶ መክፈል፣
እንደዚሁም ሟች ልዩ የኑዛዜ ስጦታ ያደረጉላቸውን ሰዎች የተሰጣቸውን ልዩ የኑዛዜ ስጦታ መክፈል፣
ማለት እንደሆነ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 944 ድንጋጌዎች ያስረዳሉ፡፡
እነዚህ የውርስ ማጣራት ተግባራት በብቃት እስኪከናወኑ፣ የውርሱ ንብረት እንደ ናአንድ የተለየ ንብረትን እንደሚቆጠርና ከውርሱ ሀብት ላይ ገንዘብ ለመጠየቅ መብት ያላቸው ሰዎች ማለትም የሟች አበዳሪዎች እና የፍርድ ባለመብቶች ለገንዘባቸው ዋስትናና መያዥያ የሚሆናቸው ይኸው በመጣራት ላይ ያለው የውርሱ ንብረት ነው፡፡ ይኸም በመሆኑ ውርሱ በመጣራት ላይ እያለ ከሟች ወራሾች ገንዘብ ጠያቂ የሆኑ ሰዎች በውርሱ ንብረት ላይ አንዳችም የይገባኛል ጥያቄ ማቅረብ እንደማይችሉና ምንም አይነት መብት እንደሌላቸው ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 943/1/ እና 943/3/ ድንጋጌዎች ያመለክታሉ፡፡
እነዚህ ድንጋጌዎች የራሣቸው ጠቀሜታና ግብ አላቸው፡፡ ምክንያቱም የሟች ውርስ በሚጣራበት ጊዜ የሟች ወራሾች አበዳሪዎችና ገንዘብ ጠያቂዎች የውርሱን ንብረት በመያዥያነት አንዳይዙ የሚያደርገው የሟች ወራሾች ከውርሱ ንብረት ድርሻ ሊያገኙ የሚችሉት ከሟች እዳ የተረፈ ንብረት ሲኖር ብቻ በመሆኑ ነው፡፡
ህጉ የሟች ወራሾች አበዳሪዎች ውርሱ በመጣራት ላይ እያለ በውርሱ ንብረት ላይ የይገባኛል ጥያቄ እንዳያቀርቡ በሟች ወራሾች እዳ ምክንያት የውርሱ ንብረት በመያዣነት እንዳይያዝ የሚከለክል ነው፡፡
እንደዚሁም ውርሱ በመጣራት ላይ እያለ ከሟች ውርስ ገንዘብ የሚጠይቁ ሰዎች ከሟች ወራሾች የግል ሀብት ላይ አንዳችም መብት እንደሌላቸው እና የሟችን የውርስ ንብረት ብቻ መከታተል እንዳለባቸው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 943 ድንጋጌዎች ያሣያሉ፡፡
እዚህ ላይ ውርስን ማጣራት አስፈላጊነት በመጀመሪያ ከሟች ገንዘብ የሚጠይቁ ሰዎች ውርሱ ከመከፋፈሉ በፊት ገንዘባቸውን እንዲያገኙ ለማድረግ፣ በማስከተልም ከውርሱ በእዳነት የሚጠየቁ ለምሣሌ ለሟች የቀብር ስነ ስርዓት የወጣው ወጭ፣ ከውርሱ መከፈል ያለበት የቀለብ እዳ እና ሟች በልዩ ኑዛዜ የሰጣቸው ስጦታዎች በቅደም ተከተል ተከፍለው ሲያበቁ ነውና ከዚህ የተረፈ ንብረት ካለ ነው የሟች የሕግ ወራሾችና ጠቅላላ የኑዛዜ ተጠቃሚዎች ከሟች ውርስ ንብረት ድርሻቸውን ያገኛሉ፡፡
በመጨረሻም የውርስ ሕጋችን ወራሾችና የኑዛዜ ስጦታ የተደረገላቸው ሰወች ውርሱን ስለማጣራት ወይም ስለመካፈል በመካከላቸው በሚደረገው ክርክር ሁሉ አንድ ወይም ብዙ የዘመድ አስታራቂ ዳኞች እንዳያዩት ለመስማማት እንደሚችሉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 945 ይደነግጋል፡፡
2. #የውርስ አጣሪ
ከላይ እንደተገለፀው ውርስን ማጣራት በሟች የውርስ ስርዓት አፈጻጸም ወቅት እጅግ በጣም አስፈላጊ ተግባር ነው፡፡ ይህንን ውርሱን የሚያጣራው ሰው ወይም ሰዎች የውርስ አጣሪ ተብለው ይጠራሉ፡፡ የውርስ አጣሪ ከሶስቱ በአንደኛው መንገድ ሊሾም እንደሚችል የውርስ ሕጋችን ይደነግጋል፡፡ የውርስ አጣሪ፣
በሟች ኑዛዜ መሠረት፣
በሕግ ሊመረጥ ወይም ሥልጣኑን ከሕግ ሊያገኝ፣
በዳኞች ሊሾም ይችላል፡፡
የመጀመሪያውን በተመለከተ ሟች አንድ ኑዛዜ የተወ እንደሆነና ሟቹ በዚሁ ኑዛዜ ውስጥ የኑዛዜው አስፈጻሚ የሾመ እንደሆነ ሟች የመረጠው ሰው የውርሱ አጣሪ ሆኖ ያገለግላል፡፡ ሟች በኑዛዜ የውርስ አጣሪ የሾመ እንደሆነ ሟች በግልጽ በኑዛዜው ካላመለከተ በስተቀር በሟች ኑዛዜ ጠቅላላ የኑዛዜ ስጦታ የተደረገለት ሰው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ውርሱን የማጣራት መብት ይኖረዋል፡፡ ሟች የውርስ አጣሪውን በኑዛዜ የሾመ እንደሆነ ወይም ጠቅላላ የኑዛዜ ስጦታ አድርጐ እንደሆነ ጠቅላላ ኑዛዜ ስጦታ የተደረገለት ሰው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ውርሱን የማጣራት መብት በቅደም ተከተል ይኖራቸዋል፡፡ ሟች የውርስ አጣሪውን በኑዛዜ የሾመ እንደሆነ ወይም ጠቅላላ የኑዛዜ ስጦታ የተደረገለት ሰው የተገኘ እንደሆነ የሟችን ያሉ ኑዛዜ ወራሾች የውርስ አጣሪነት ስልጣን የሚያስቀረው እንደሆነ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 948 ተደንግጓል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ሟች በኑዛዜ የውርስ አጣሪ ያልሾሙ እንደሆነ ወይም ሟች ጠቅላላ የኑዛዜ ስጦታ ያደረገለት ሰው የሌለ እንደሆነ የሟች ያለ ኑዛዜ ወራሽ የሆኑ ሰዎች ሰውየው ከሞተበት ቀን አንስቶ ያለ አንዳች ፎርማሊቲ የውርስ አጣሪነት መብት እንደሚኖራቸው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 947 የሚደነግግ ሲሆን ብዙ ሰዎች የውርስ አጣሪ በሆኑ ጊዜ የአጣሪነቱን ተግባር በመተባበር መስራት እንዳለባቸው ወይም አንዱን በመወከል ለማሠራት እንደሚችሉ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 958 ይደነግጋል፡፡
ሶስተኛው የውርስ አጣሪ የሚሰየምበት ስርዓት በፍርድ ቤት ውሣኔ የውርሱ አጣሪ የሚሰይምበት ሁኔታ ነው፡፡ የውርስ አጣሪ በፍርድ ቤት የሚሰየመው፣
የሟች ወራሾች የማይታወቁ አንደሆነ፣
ያለ ኑዛዜ ወራሾች ውርሱን ለማጣራት የማይፈቅዱ መሆናቸውን ገልፀው ያሣወቁ እንደሆነ፣
ሟች የኑዛዜም ሆነ ያለ ኑዛዜ ወራሽ ያልተወና የሟችን ሀብት መንግስት የሚወርሰው በሆነ ጊዜ፣
የአስተዳደር ሕጐችን ወይም ደንቦችን መሠረት በማድረግ ዳኞች የውርሱን አጣሪ እንደሚሰይሙ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 949 ድንጋጌዎች ያስረዳሉ፡፡
እንደዚሁም ዳኞች በሟች ኑዛዜ፣ በሕግ ወይም በፍርድ ቤት የተሰየመውን የውርስ አጣሪ በሌላ የውርስ አጣሪ የመተካት ስልጣን እንዳላቸው የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 951 ይደነግጋል፡፡ የውርስ አጣሪን በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 949 መሠረት መሰየምንና በሕግ ወይም በሟች ኑዛዜ ወይም ፍርድ ቤቱ ራሱ የሰየመውን የውርስ አጣሪ መተካት /replacement / እና substitution/ ሁለት የተለያዩ ጽንሰ ሀሣቦች ናቸው፡፡ ፍርድ ቤቱ በሕግ በሟች ኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤቱ የተሰየመን አንድ የውርስ አጣሪ ስልጣንና ሀላፊነት በማንሣት ሌላ/ሌሎች/ የውርስ አጣሪ የሚሰይመው፣
e188b0e18a94_2013_e18b93_e1889d_e18aa0e18bb2e188b5_e18aa5e18a93.pdf3.14 MB
በማስረጃ የሚረጋገጥና ሊስተባበል የሚችል እውነት የተገኘ እንደሆነ ገለልተኛ የሆነ አካል ጉዳዩን ሊመረምረውና ተገቢውን ውሳኔ ሊሰጠው ይገባል ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም በዚህ ጉዳይ ላይ እንደጭብጥነት የሚነሳ ነጥብ አለና ይኄውም ‘’ ይዞታው በሕገ ወጥ መንገድ የተገኘ ነው ወይንስ አይደለም የሚል’’ ስለሆነም ይህ ጭብጥ በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 37 በተገለጸው አግባብ ፍትሃዊ የዳኝነት አካል ተገቢው ማጣራት ተደርጎ ውሳኔ እስከሚያገኝ ድረስ ክርክር የተነሳበት ንብረት ላይ እርምጃ መውሰድ ተገቢነት የሌለውና መንግስታዊ ሕገ-ወጥነት አመላካች ሊሆን ይችላል፡፡ ታዲያ ይህ ጭብጥ በሕግ መስመር ይፈታል ካልን የአቤቱታና ቅሬታ ሥነ ሥርዓቱ እንዴት ነው የሚለው ምላሽ የሚስፈልገው ነው፡፡
አንደኛ፡- በአዋጁ አንቀፅ 28 ላይ የማስለቀቂያ ትዕዛዝና ማስጠንቀቂያን የተመለከቱ አቤቱታዎች እንዴት መቅረብ እና ለማን መቅረብ እንዳለባቸው ጠቅሷል፡፡ ይኄውም
1. በዚህ አዋጅ አንቀፅ 27/1 መሰረት የማስለቀቂያ ትዕዛዝ የደረሰው ወይም ትዕዛዝ በተሰጠበት ንብረት ላይ መብቴ ወይም ጥቅሜ ይነካብኛል የሚል ማንኛውም ሰው ትዕዛዙ በደረሰው 15 የሥራ ቀናት ውስጥ ያለውን አቤቱታ ከዝርዝር ምክንያቱና ማስረጃው ጋር አግባብ ላለው አካል ማቅረብ ይችላል፡፡
2. በዚህ አወዘጅ አንቀፅ 26/4 መሠረት ማስጠንቀቂያ የደረሰው ሰው ማስጠንቀቂያው በደረሰው በ7 የሥራ ቀናት ውስጥ አቤቱታውን አግባብ ላለው አካል ማቅረብ ይችላል፡፡
3. አግባብ ያለው አካል የቀረበለትን አቤቱታ በአግባቡ በማጣራት ውሳኔ መስጠትና ውሳኔውን ለአቤቱታ ኣቅራቢው በጽሑፍ ማሳወቅ አለበት፡፡ የቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት ያላገኘ እንደሆነ ምክንያት በግልፅ በውሳኔው ውስጥ መገለፅ አለበት፡፡
ስለሆነም ከዚህ በላይ በአንቀፁ እንደተገለጸው ህጋዊ ባለይዞታ የሆነ እና በህጉ አግባብ ተገቢው የማስለቀቂያ ትዕዛዛ የተሰጠበት ሰው በ15/አስራ አምስት/ ቀናት ውስጥ አቤቱታ የማቅረብ መብት ያለው ሲሆን ሆኖም ግን በያዝነው ጭብጥ ላይ ሕገ-ወጥ ባለይዞታ ነህ የተባለ ሰው ማስጠንቀቂያው በደረሰው በ7/ሰባት/የሥራ ቀናት ውስጥ/ቅዳሜ እና እሁድ ጨምሮ/ በ9/ዘጠኝ/ ተከታታይ ቀናት ውስጥ ቅሬታውን ለሚመለከተው የከተማ አስተዳደር ማቅረብ ይችላል፡፡ ቅሬታውን የተቀበለው አግባብ ያለው የከተማ አስተዳደር ለቀረበው አቤቱታና ቅሬታ ተገቢውን ማጣራት በማድረግ ለአቤቱታው ተገቢውን ምላሽ በጽሑፍ የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡ ይህ የከተማ አስተዳደሩ የጽሑፍ ምላሽ ነው እንግዲህ ለቀጣዩ የሕግ የመብት ጥያቄ ስርዓትን ለመከተል አጋዥ የሚሆነው፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ለቀረበለት ቅሬታ የጽሑፍ ምላሽ ከሰጠ እና ውሳኔውን ያጸና መሆኑን ከገለፀ ቀጣዩ አካሃሄድ በአዋጁ አንቀፅ 29 መሰረት በክልሉ ወይም በከተማ አስተዳደሩ ለተቋቋመው ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ ውሳኔው በጽሑፍ ከደረሰበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30/ሰላሳ/ ቀናት የቅሬታ አቤቱታውን በመያዝ ይግባኝ ለመጠየቅ ይችላል፡፡ ጉባዔውም የቀረበለትን ይግባኝ መርምሮ በ30 ቀናት ውስጥ መርምሮ ውሳኔ መስጠት ያለበት ሲሆን የሰጠውንም ውሳኔ በጽሑፍ ለተከራካሪ ወገኖች ማሳወቅ ግዴታ አለበት ሲል ደንግጓል፡፡ ይግባኝ ሰሚ ጉባዔው አግባብ ያለውን የስር አስተዳደር አካሉን ውሳኔ ቢያጸና የህጉ ውጤት ምንድነው ቢባል ቀጣዩ አቤቱታ እሚሆነው በካሳ ክርክር ላይ ብቻ ለመደበኛ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ይግባኙን ማቅረብ እንደሚቻል ይገልፃል፡፡ ይህ ማለት ይግባኝ ሰሚ ጉባዔው በሕግና በፍሬ ነገር ክርክሮች ላይ የሚሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ በመሆኑ ይግባኝ የማይባልበት ነው በማለት ህጉ አትቷል፡፡
እንግዲህ ይህ ይግባኝ ሰሚ ጉባዔ የሚሰጠው ዳኝነት ከተፅዕኖዎች ነጻ ነው ወይ ተብሎ ቢጠየቅ አዋጁ በአንቀጽ 30/7/ ላይ ጉባዔው ከሕግ በስተቀር ከማናቸውም ተፅኖዎች ነፃ ይሆናል በማለት ደንግጓል በተቃራኒው ደግሞ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 8 ደግሞ ጉባዔው ስራውን በሚያከናውንበት ጊዜ በመደበኛው የፍትሃ ብሄር ሥነ ሥርዓት ሕግ አይመራም፡፡ ሆኖም በክልሉ ወይም በከተማ አስተዳደሩ በሚወሰን በተቀላጠፈ ሥነ ሥርዓት ይመራል ሲል በቀጥታ የከተማ አስተዳደሩ ወይም የክልሉ ውሳኔ ሰጭ አካል በጉዳዩ ላይ በሥነ- ሥርዓት ሰበብ ለጉዳዩ አቅጣጫ መስጠት እንደሚችል ይገልፃል፡፡ ይህም ጉባዔውን ከፖለቲካዊ ውሳኔዎችና ተፅዕኖዎች የጸዳ ነው ለማለት እንዳይቻል ያደርገዋል/በዚህ ጉዳይ ወደፊት በሰፊው እመለስበታለሁ/፡፡ ሆኖም ግን ማንኛውም ቅሬታ ያለበት ወገን ይህንን የሕግ ስርዓት በመከተል መብቱን ለማስከበር እንደሚችል ለማሳሰብ እወዳለሁ፡፡
ሆኖም ግን በዚህ አቤቱታ ሂደት ውስጥ አግባብ ያለው አካል በሕግ የተጣለበትን ኃላፊነት ማለትም ለሚቀርብለት አቤቱታ የጽሑፍ ምላሽ መስጠት ሲኖርበት ይህንኑ ባይሰጥ ሊኖር የሚችለው የሕግ ውጤት ምንድነው ቢባል መስርያ ቤቱ በራሱ ሕገ-ወጥ ነው በማለት አፍን ሞልቶ ምላሽ መስጠት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም አንድን ድርጊት ሕገ-ወጥ የሚያስብለው በሕግ የተደነገገን አድርግ የተባለን ነገር አለማድረግና አታድርግ የተባለን ነገር ማድረግ ነውና፡፡
በስተመጨረሻም፡- አግባብ ያለው አካል የሚባለው መንግስታዊ አካል አብዛናውን ጊዜ የሕግን አግባብ ከመከተል ይልቅ በደመ-ነፍስ ውሳኔዎችን መወሰን እና መተግበር የሚቀናው አካል ነው፡፡ ስለሆነም 7/ሰባት/ቀን ሰጥቶ በ7/ሰባት/ ቀን ውስጥ የዓመታት ጥሪት ውጤት የሆነውን ቤት የሚያፈርሱ አካላት ዜጎች ላይ የማይተካ ጉዳት እንደሚደርስ ቢያውቁም በቸልተኝነት ለሚወስዱት እርምጃ በፍትሃብሄር ከድርጊቱ በጊዜያዊነት እንዲቆጠቡ ለማድረግ ሁከት ይወገድልኝ አቤቱታ በማቅረብ ጊዜያዊ መፍትሄ ማግኘት ይቻላል፡፡ ስለሆነም2/ሁለቱን/ የሕግ መስመሮች በመከተል ዜጎች መብቶቻቸውን ማስከበር ይችላሉ ባይ ነኝ፡፡
ማጠቃለያ እና አስተያየት
መንግስት በአዋጁ አንቀፅ 31/2/ መሠረት የማስለቀቂያ ትዕዛዛ ወይም ማስጠንቀቂያ የተሰጠበትን መሬት መረከብ የሚችለው
ሀ. ትዕዛዙ ወይም ማስጠንቀቂያው የደረሰው ሰው በአዋጁ አንቀፅ 28/1/ እና 2/ መሠረት አቤቱታ ሳያቀርብ ከቀረ
ለ. አቤቱታው ቀርቦ ውሳኔውን ውድቅ የሚያደርግ ውሳኔ ሲሰጥ እና በውሳኔው ላይ ይግባኝ ሳይቀርብ ሲቀር፤ እና በመሳሰሉት ህጋዊ አግባቦች ብቻ መሆኑን በመገንዘብ ሕገ-ወጥ ተግባር ናቸው ያላቸውን ተግባራት በሕገ-ወጥ መንገድ እንዳያበላሸው እና መንግስታዊ ሕገ-ወጥነት እንዳይጎለብት ሙያዊ አስተያዬቴንና ምክሬን እየለገስኩ በዚህ ጽሑፍና ሙያዊ አስተያየት ላይ የመሰላችሁን አስተያየት ከዚህ በታች በተጠቀሰው አድራሻ ላይ መስጠት ትችላላችሁ፡፡
ማስታወሻ፡- ይህ ጽሑፍ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተዘጋጀ በመሆኑ ወደፊት በሰፊውና በጥልቀት የሃገሪቱንና የክልሎችን ሕገ-መንግስት፤ አዋጆች፤ ደንበች እና መመርያዎችን በማጣቀስ የተሻለ የሕግ አስተያየት ለማቅረብ የምሞከር መሆኔን ለማሳወቅ እወዳለሁ፡፡
Written by አያሌው ቢታኔ ሜንዛ on Abyssinia Law
ንብረት የማፍራት እና ፍትሐዊ ዳኝነት የማግኘት መብት: ከወቅታዊው የሕገ-ወጥ መሬትና ንብረት ማስመለስና ማፍረስ ጋር በተያያዘ
===========================
አሁን አሁን በተለያዩ የሃገራችን ክልሎች በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ ዙርያ በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ከተሞች ላይ ከዕለት ወደዕለት በዜጎች የመዘዋወር መብት፤ንብረት የማፍራት፤ የእኩልነት እና ፍትህ የማግኘት ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሕግ ማስከበር ሰበብ ሲጣሱ ማዬት የዕለት ተዕለት ተግባራዊ ኩነት እየሆነ መጥቷል፡፡
የዚህ አጭር ጽሑፍ መነሻ ነጥብም በሕግ ማስከበር ሰበብ ለረዥም አመታት ከማህበረሰቡ ጋር በመቀላቀል ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ንብረት ያፈሩ ዜጎች ላይ በሕገ ወጥነት ሰበብ እየተወሰደ ያለውን ከገዛ ቤታቸውና ንብረታቸው የማፈናቀል እርምጃን በተመለከተ ዜጎች መብቶቻቸውን በሕግ አግባብ እንዴት ማስከበር እንዳለባቸው የሚያሳይ ፍኖተ ሕግ ነው፡፡
የህጉን ዝርዝር ነጥብ ከመመልከታቸን በፊት አሁን መሬት ላይ ያለው እውነትን በጨረፍታ ለመመልከት መሞከሩ ተገቢ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ በቅርቡ በአዲስ አበባ ዙርያ የሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች መካከል የሰበታ ከተማ አስተዳደር፤ የቡራዩ ከተማ አስተዳደር፤ የለገጣፎ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የሱሉልታ ከተማ አስተዳደር የከተሞቻቸውን የማስተር ፕላን ጋር ተቃራኒ የሆኑ እንዲሁም ቀድሞ ካሳ የተከፈላቸው እና በሕገ ወጥ መንገድ ከመንግስት እውቅና ውጭ ንብረት ያፈሩ ወይም በተለምዶ ወቅታዊ አጠራሩ ሕገ ወጥ ግንባታዎችን አጭር የማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ነዋሪዎቹ ለዓመታት ይኖሩበት የነበረውን በጉልበታቸውና በጥሪታቸው ያፈሩትን ሃብቶቻቸውን በሃይል ድርጊት እንዲፈርስ በማድረግ በተጨባጭ ዜጎች ከሃብት ንብረታቸው እንዲፈናቀሉ መደረጉ ለብዙ ቅሬታ መነሻ ነጥብ ሆኖ መገኘቱ ነው የዚህ ጽሑፍ መነሻ ነጥብ፡፡ በመሆኑም ዜጎች ተመሳሳይ ድርጊት ሲፈጸምባቸው በምን አግባብ መብቶቻቻውን ማስከበር እንደሚችሉ ከኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት እና ከአዋጅ ቁጥር 721/2004 ጋር በማመሳከር ረጂ ናቸው ብዬ ያሰብኳቸውን ነጥቦች ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡
በቅድሚያ የኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 25 መሰረት ማንኛውም ሰው ልዩነት ሳይደረግበት በሕግ እኩል ያልተነጣጠለ እና አድሏዊ ባልሆነ መልኩ ጥበቃ እንደሚደረግለትና እኩልና ተጨባጭ የሕግ ዋስትና የማግኘት መብት እንዳላቸው በማያሻማ ቋንቋ የማይገረሰሰ ሰብዓዊ መብት እንደሆነ ደንግጎ ይገኛል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ከጉዳያችን ጋር ተያያዥነት ባለው መልኩ በዚሁ ሕገ መንግስት አንቀፅ 32 ላይ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በመረጠው የሃገሪቱ አካባቢ የመዘዋዋርና የመኖርያ ቤት የመመስረት እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከሃገር የመውጣት ነፃነት እንዳለውና በአንቀጽ 40/7ም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም በገንዘቡ በመሬት ላይ ለሚገነባው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው በማለት እርስ በርስ ተመጋጋቢ እና ተደጋጋፊ በሆነ መልኩ የዜጎችን ንብረት የማፍራትና በሃገራቸው በነፃነት የመዘዋወር ዲሞክራሲያዊ መብቶችን በዝርዝር ይጠቅሳል፡፡
ይህም የሚያሳዬው ማንኛውም ሰው ኢትዮጵያዊም /ኦሮሞ፤ አማራ፤ ትግሬ፤ ወላይታ፤ ጋሞ፤ ጉራጌ፤ ጋምቤላ፤ አፋር ወ.ዘ.ተ/ ሆነ በህጋዊ መንገድ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ የሚንቀሳቀስ የውጭ ዜጋ በሃገሪቱ የትኛውም ቦታ ተንቀሳቅሶ በእኩልነት ያለምንም አድሎ ንብረት የማፍራት ሙሉ መብት እንዳለው ገላጭ ነው፡፡ በመሆኑም ነባራዊ ሁኔታው ላይ ዝርዝር ጥናት የሚያስፈልገው ቢሆንም ከላይ ለዚህ ጽሑፍ መነሻ በሆኑት አካባቢዎች እየተወሰደ ነው ተብለው የተገለፁት በሕገ ወጥ ስም ቤት የማፍረሱ ተግባር ከሃገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በተለያየ ምክንያት የመጡና መኖሪያቸውን በነዚሁ አካባቢ ያደረጉ የተለያዩ ብሄር፤ብሄረሰቦች ነዋሪዎች መሆናቸውን ከተለያዩ ሚዲያዎች ለመገንዘብ እንችላለን፡፡ ይህም የዜጎች መግባቢያ እና መተዳደርያ ሰነድ በሆነውና የህጎች የበላይ ተደርጎ የሚቆጠረውን ሕገ መንግስቱ ላይ በግልፅ የተጠቀሰውን የእኩልነት ሰብዓዊ መብት የሚጥስ እና መንግስትንም የሚያስጠይቅ ድርጊት መሆኑን ልብ ይሏል፡፡
ከዚህ ባሻገር ከላይ የተጠቀሰውን ዜጎች ሕገ-መንግስታዊ መብት ተላልፎ መንግስት በዜጎች ላይ እርምጃ ቢወስድ ኤጎች መብቶቻቸውን ለማስከበር ሊከተሉት የሚገባ የሕግ መስመር ምንድነው ከተባለ ከዚህ በታች በተገለፀው ህጋዊ መስመር ዜጎች መብቶቻቸውን ማስከበር ይችላሉ መንግስትም ይህንን መንገድ የመከተል ግዴታ አለበት፡፡
በቅድሚያ በአዋጅ ቁጥር 721/2004 የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ መሰረት የከተሜነት እና የከተሞች ከዕለት ወደዕለት የማደግ ፍላጎት እንዲሁም መሬትውስን ሃብት በመሆኑ ይህንን ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ለተፈለገለት ዓላማ ብቻ በህጋዊ መንገድ ማስተላለፍ ተገቢ ስለሆነ አዋጁ ሊወጣ ችሏል፡፡ በዚህ አዋጅም መሰረት ከያዝነው ነጥብ ጋር የሚገናኙ ነጥቦች ላይ ትኩረት ማድረጉ አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ እንደሚከተለው ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡
በዋንኛነት የዚህ ጽሑፍ አንባቢ መገንዘብ ያለበት ሕገ ወጥነትን የሚደግፍ ጽሑፍ አለመሆኑንና ሕገ ወጥነት በራሱ በተገቢው የሕግ መስመር እርምጃ ሊወሰድበት የሚገባ መሆኑን ጽሑፊው ያምናል፡፡ ሆኖም ግን ለረጅም ጊዜያት መንግስት እና ተገቢው የአስተዳደር እርከንና መዋቅር ባለበት ከተማ ውስጥ አሁን ላይ ሕገ-ወጥ ተብለው ለፈረሱ እና ሊፈርሱ የተዘጋጁ ቤቶች ላይ ይኄው መንግስታዊ መዋቅር ከግንባታው ጊዜ አንስቶ ሳያውቀው የተፈጸመ አንዳች ድርጊት በሌለበትና ለነዚሁም ግንባታዎች አስፈላጊውን መሰረት ልማት ካሟላ በኃላ በተግባር ህጋዊነታቸውን ሲያረጋግጥ በሰነድ ግን ሕጋዊ አይደላችሁም ማለት ሥነ-አመክንዊ መሰረት የሌለው ድርጊት በመሆኑ ይህንኑ የሕግ መስመር ማስያዙ ተገቢ መስሎ ስለታየኝ ይህንን ጽሑፍ ለማዘጋጀት መገደዴን እንድትረዱት እፈልጋለሁ፡፡
እናም በሃገሪቱ ሕገ መንግስት አንቀፅ 37/1/ መሠረት ማንኛውም ሰው በፍርድ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ለፍርድ ቤት ወይም ለሌላ በሕግ የዳኝነት ስልጣን ለተሰጠው አካል የማቅረብና ውሳኔ ወይም ፍርድ የማግኘት መብት እንዳለው በመሰረታዊ መብቶች ውስጥ የገለፀ በመሆኑ ዜጎች መብታቸውን ሊያሳጣ የሚችል ሁኔታ ሲያጋጥም በተለይም በሕገ-ወጥነት ሰበብ ከቤት ንብረታቸው እንዲነሱ የሚያስገደድ ድርጊት ሲያጋጥም በአዋጅ ቁጥር 721/2004 ላይ የተጠቀሱትን ከዚህ በታች የተገለፁትን ህጋዊ ቅደም ተከተሎችን በመከተል መብቶቻቸውን ማስከበር ይችላሉ፡፡
በአዋጁ አንቀፅ 26/4/ መሰረት አግባብ ያለው አካል በሕገ ወጥ መንገድ የተያዘን የከተማ ቦታ በዚህ አዋጅ አንቀፅ 27 መሠረት የማስለቀቂያ ትዕዛዝ መስጠትና ካሣ መክፈል ሳያስፈልግ የ7 ስራ ቀናት የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ብቻ ለባለይዞታው በአካል በመስጠት ወይም በቦታው በሠፈረው ንብረት ላይ በመለጠፍ የማስለቀቅ ስልጣን ይኖረዋል በማለት ደንግጎ እናገኛለን፡፡ ሆኖም ግን በዚህ አንቀፅ ውስጥ ሰፊ ትርጉም የሚያሻውና በማስረጃ ተመዝኖ ሊረጋገጥ የሚገባ ነጥብ ያለ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ ይህም ‘’ በሕገ ወጥ መንገድ የተያዘን የከተማ ቦታ’’ ይህ ቃል አሻሚ ከመሆኑ ባሻገር ይህ ቦታ በሕገ ወጥ መንገድ የተያዘ መሆኑን የማረጋገጥ ኃላፊነት የመንግስት ድርሻ መሆኑን እና የማስረት ሸክሙም መንግስት ላይ የወደቀ መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለሆነም አግባ ያለው አካል የተባለው አካል በቂ ማስረጃ ሎኖረው ይገባል፡፡ ስለሆነም
እንደ ባልና ሚስት
===================
• አንድ ወንድና ሴት እንደባልና ሚስት ግንኙነት አላቸው የሚባለው የተጋቡ ሰዎችን ሁኔታ ሲያሳዩና ቤተዘመዶቻቸውና ማህበረሰቡ እንደተጋቡ ሰዎች የሚኖሩ ናቸው ብለው ሲገምቷቸው ነው፡፡
እንደባልና ሚስት አብሮ የመኖር ግንኙነት ስለመኖሩ ክርክር የተነሳ እንደሆነ ጉዳዩን ለማስረዳት የሚቀርበው ቀዳሚ የማስረጃ አይነት በሕጉ አልተመለከተም፡፡ በመሆኑም ጉዳዩን ለማስረዳት የሚቀርበው ማስረጃ የፍሬ ነገር ጉዳይ በመሆኑ ግንኙነቱን በማሳየት ብቻ ማስረዳት ይቻላል፡፡ የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 አንቀጽ 106/2/ ድንጋጌ ሲታይም ጋብቻ ሳይኖር እንደባልና ሚስት ለሚኖሩ ሰዎች የሚፈለገው ማስረጃ ወንዱና ሴትዩዋ የተጋቡ ሰዎችን ሁኔታ ሲያሳዩና ቤተዘመዶቻቸውና ማህበረሰቡ እንደተጋቡ ሰዎች የሚኖሩ ናቸው ብለው የሚገምቷቸው መሆኑን ማሳየት እንደአለበት ያመለክታል፡፡
ሰ/መ/ቁ. 50580 ቅጽ 11፣ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ. 213/1992 አንቀጽ 106/2/
መመሪያው ባንኮች ከእነዚህ ምክንያቶች ውጪየቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝን ለመቀበልም ሆነ ላለመቀበል ሌሎች ምክንያቶችን ከግምት ላያስገቡ እንደሚችሉ ጠቅሷል። በመሆኑም መመሪያው ምክንያቶቹን መሰረቅና መጥፋት ብቻ ብሎ ለመዝጋት መሞከሩ ከዚህ ውጪ በተለያዩ ምክንያቶች በሀይል፣ በጫናና በዛቻ ወይም በሌላ ምክንያት አንድ ግለሰብ ቼክን የጻፈ ከሆነ የቼክ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ በመስጠት ቼኩ እንዳይከፈል የሚያደርጉበትን መንገድ የዘጋ ነው። ሌላው መመሪያው የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ምክንያቶች የቼኩ መሰረቅ ወይም መጥፋት ብቻ መሆኑን በአንድ በኩል ለመግለጽ እየሞከረ በሌላ በኩል ባንኮች ሌሎች ምክንያቶችን ተቀባይነት ያላቸው ምክንያቶች ናቸው ብለው ላይቀበሉ ይችላሉ በማለት ሌላ ቀዳዳና መብት ለመስጠት ይዳዳዋል። ይህ ሁኔታም ባንኮች ምክንያቶቹን በአስገዳጅነት እንዳይፈጽሟቸው ቀዳዳ የሚፈጥር እና ለትርጉም የተጋለጠ ያደርገዋል። ሌላው ነጥብ ደግሞ የቼክ ክፍያ ይቁም ትዕዛዝ በንግድ ህገጉ ድንጋጌ መሰረት በምን ምክንያት ይሰጣል የሚለው ባልተገለጸበት ሁኔታ በመመሪያው ላይ ለማስቀመጥ መሞከሩ የንግድ ህጉ የሰጠውን እና በማናቸውም ምክንያቶች ይሁን የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ መስጠቱ ብቻ በቂ ነው የሚል የሚመስለውን ድንጋጌ የሚሽር አዋጅን በመመሪያ የመሻር ተግባር የሚያስመስል ነው የሚሉም አልጠፉም።
የቼክ ሂሳብ እንቅስቃሴን በተመለከተ
የቼክ ሂሳብ እንቅስቃሴ በንግድ ህጋችን በዝርዝር ባልተቀመጡት ጉዳዮች ላይ ብሔራዊ ባንክ በየጊዜው የቼክ እንቅስቃሴን የሚመለከቱ መመሪያዎችን ያወጣል። መመሪያዎቹ በተለይም የዘመናዊ ግብይት ስርዓቱ እየዘመነ እና ቀልጣፋ እየሆነ ሲመጣ በሚመጡ አዲስ የአሰራርና የቼክ አጠቃቀም እንዲሁም በየጊዜው የቼክ ተፈላጊነትን ለማስፋፋት በማሰብ የሚወጡ እንደሆኑ መመሪያዎቹን በመመልከት መገመት አያዳግትም።
በቅርቡ በብሔራዊ ባንክ የወጣው የቼክ አጠቃቀም መመሪያ ቁጥር SBB/64/2016 መግቢያ በግልጽ እንደሚያመለክተውም ቼክን በመገበያያነት መጠቀም ጥሬ ገንዘብን የማይጠቀም ማህበረሰብ (Cashless Society) ለመፍጠርና ቀልጣፋ የግብይት ስርዓትን ለመገንባት አስፈላጊ በመሆኑ እንዲሁም ብሔራዊ ባንክም ቀልጣፋ፣ ውጤታማና የተረጋጋ የክፍያ ስርዓት የመዘርጋት ኋላፊነት ስላለበት ቼክን የተመለከተው መመሪያ ተሻሽሎ እነደወጣ ይጠቅሳል። ከዚህ በተጨማሪ ግን በዋናነት የቼክን ህጋዊ የመገበያያ ሰነድነት እና ተቀባይነት ያለው፣ እምነት የሚጣልበት ሰነድ ሆኖ እንዲቀጥል ማስቻል ለመመሪያው መሻሻል ምክንያት ነው።
በተሻሻለው መመሪያ መሰረትም በቀድሞው መመሪያ ውስጥ ያልተካተቱ ለምሳሌ የቼክ ሂሳብ ለመክፈት የሚያስፈልጉ ነገሮች ምን ምን እንደሆኑ ከመዘርዘር አልፎ ቢያንስ በትንሹ የቼክ ሂሳብ የሚከፍተው ሰው የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያለው እንዲሆን ይጠበቃል በማለት አስቀምጧል። ከዚህ በፊትም የግብር መለያ ቁጥር ሳያመጡ የቼክ ሂሳብ የከፈቱ ሰዎችም መመሪያው በስራ ከዋለበት ስድስት ወራት ውስጥ ማቅረብ እንዳለባቸው ይገልጻል። መመሪያው በሌሎች ነጥቦች ላይም ዝርዝር ነጥቦችን የያዘ በመሆኑ ይህንኑ መመሪያ በማጣቀስ የተሻሻሉትን የቀድሞውን መመሪያ ድንጋጌዎች እንዲሁም አዲስ የተጨመሩ ነጥቦችን መመልከት ይቻላል።
በአጠቃላይ ግን ለዚህ ሁሉ ክርክር መፍትሄ የሚሆነው የንግድ ሕጉ ማሻሻያ ከተግባራዊው የባንኮች አሰራር፣ ከፍርድ ቤት ክርክር መነሻዎች እንዲሁም ከሌሎች አገሮች ልምድና ተሞክሮ በመነሳት ሰፊ ዳሰሳ በማድረግ ህጉ ምሉዕ እንዲሀን እንዲሁም በቼክ ላይ ያለው ተአማኒነት እንዲሰፋ የሚያደርግ የህግ ድንጋጌ ማውጣት ነው።
በአጠቃላይ ባንኮች የቼክን ክፍያ አልፈጽምም ሊሉ ከሚችሉበት ምክንያት ውስጥ አንዱ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ (Stop payment Order) በአውጪው ሲሰጥ ነው። አውጪውም መጀመሪያ ለባንኮች የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ሲሰጥ ባንኮቹ ለዚሁ ትዕዛዝ ምክንያት የቼኩ መሰረቅ ወይም መጥፋት መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል። በሌላ በኩል ባንኮች የቼክ አውጪ ግለሰቦቸ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ ሲሰጥ የተከፋዩ መብትም በዚህ ምክንያት እንዳይጣበብ መጠንቀቅ ይገባቸዋል። የቼክ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ (Stop payment order) በህጉ አግባብ የተሰጠ መሆኑ ከተረጋገጠ ባንኮች ደንበኞቻቸውን ከሂሳባቸው ላይ ያለአግባብ ወጪ እንዳይሆንባቸውና የደንበኞቻቸውን ተአማኒነት ለማግኘት በከፍተኛ ሁኔታ ጠቀሜታው የጎላ ነው። በመሆኑም ባንኮች የቼክ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝ የቼክ አውጪውንም ሆነ የተከፋዩን መብት የሚነካ መሆኑን በመገንዘብ ለደንበኞች ጥቅም ለማስከበር በህጉ አግባብ የቼክ የክፍያ ይቁም ትዕዛዝን መተግበር ተገቢ ነው።
BY: GEZU AYELE MENGISTU On ABYSSINIA Law
