ar
Feedback
UNION FELLOWSHIP©✝

UNION FELLOWSHIP©✝

الذهاب إلى القناة على Telegram

#we deal about the strength and weakness of our fellowship #we advertise what programmes we have and had in the week. #we address you an information about such things whole over Ethiopia. #PRAYER IS THE ONLY MEANS OF RECEIVING SPIRITUAL POWER!!!!! @UACSFF

إظهار المزيد
553
المشتركون
+124 ساعات
+17 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
😍ቤተሰብ+ ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ እንደምን ከረማችሁ ይኸው ዛሬም አለን እርሱ አንድዪ መድሃኒያለም በሀሳባችን ላይ አስቦበት በውጥናችን ላይ ወጥኖበት ይኸው ጅረት ከሆነው ጊዜ በላይ እርሱ ሮጦልን ሙት በሆነች አለም ላይ ቃለ ህይወት እያሰማልን በልጁ በሆነ እምነት መንግስተ ሰማያትን አዋረሰን ክብር ለማይነጥፈው ግርማው ይሁን 🙏 😍ቤተሰብ+ ትላንት ትንሽ ህመም ቢጤ ከጀለኝ እና ከራስጌዪ ላይ ጋደም አልኩ 😱 አረ አትደንግጡ በጎ ነኝ አሁን ጠላታችሁ ይደንግጥ እናም እናም አንድ ባልንጀራዬ ሊጎበኘኝ በቅ ብሎ የሆድ የሆዳችንን እያወጋን ስለ ቀደምት አማኞች እያወራን ብዙ አመሸን ከውስጣችን የነበረው የአፍላ እውነት ትኩስ እንፋሎቱ አላፊ አግዳሚውን እየለበለበ በአቅራቢያችን የነበሩ ቤተሰቦቼን ጭምር ነደፈ ግና ከመጀመሪያችን ለወዳጄ መሸበት እና ሸንጎው ያለ ምንም አድማ በታኝ በሰላማዊ መልኩ ተበተነ ወዳጄም ተሰናብቶኝ ሲሄድ አንድ ከዚህ ቀደም ያነበበው ትንሽ ፅሁፍ አጋራኝ እናም ለእናንተ አቀረብ እና ታድያ የእንግዳ ፅሁፍ ስለሆነ እንግዳ ክብር ነው በርትታችሁ #share አድርጉ ጌታን ያልተቀበሉ ‹‹ጴንጤዎች›› (አሌክስ አብርሃም) እነዛ በድንጋይ ስንወግራቸው ‹‹ጌታ ይቅር ይበላችሁ›› ብለው የሚያልፉ በትህትናቸው የማረኩን ጴንጤዎች የት ሄደው ...ነው እርስ በእርስ ያውም በተራ ነገር አይናቸው በቁጣ ደም ለብሶ በፌስቡክና ዩቲዩብ የሚዘላለፉ ‹ጴንጤዎች› እንደአሸን የፈሉት? እነዛ በጊታር ብቻ ሲዘምሩ የቤተሰብ ቁጣ ተደብቀን በአጥራቸው ተንጠራረተን በአሮጌ ማምለኪያ ቤቶቻቸው ሽንቁር አጨንቁረን በጉጉት የምናያቸው፣ በጨረፍታ የሰማነው መዝሙራቸው ምላሳችን ላይ ተጣብቆብን የሚቀር ዘማሪዎች የት ሂደው ነው …. ልብስ ብቻ ቀይረው በየሰርግና ድግስ ቤቱ ያውም ክፍያ ተከራክረው በሰው መዝሙር የሚውረገረጉ መዝሙር ቸብቻቢ ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት? በስንት ፆሎትና ለቅሶ መዝሙር ተቀብለው የሚዘምሩ የቆዩ ዘማሪዎች የት ሂደው ነው ‹‹ክርስትና ሰጠን በሚል ነፃነት ስም›› የሰው መዝሙር እየዘመሩ ያውም ክሬዲት ሳይሰጡ እንደራሳቸው ስራ በዩቲዩብ ሳንቲም የሚለቅሙ ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት? እነዛ ሲገኝ በፈረስ ሲታጣም በእግራቸው በባዶ ሆዳቸው በየጠገጠሩ እየኳተኑ አቧራ ለብሰው የሚናገሩት ወንጌል የሚሊየኖችን ልብ የማረከ ወንጌላውያን የት ሂደው ነው…ውድ ሱፍ ለብሰው ውድ እህል ጎርሰው በፈርስት ክላስ በረራ ኤሮፕና አሜሪካ እየተዘባነኑ …እንኳን ልብን ልብስን የማያስቀይር ዝባዝንኬ ሲያወሩ የሚውሉ ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት ? እነዛ ለወንጌል እየተጠሉ እንኳን ቃሉ ሂወታቸው ላይ እየተነበበ የሚያስደንቃቸው እና የሚያስከብራቸው አገልጋይና ምእመኖች የት ሂደው ነው … በየሶሻል ሚዲያው በሳምት አስር ጊዜ ልብስ እየቀየሩ ፣ከተነሱት ፎቶ ጋር የሚለጥፉትን ጥቅስ በእነሱ ምክንያት ህዝብ የተፀየፈው ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት ? ድፍር ብለው ‹‹ብርሃንና ጨለማ ህብረት የላቸውም እግዚአብሔርን በማያከብር ነገር አትቀላቀሉ ›› የሚሉ ቆራጥ ጴንጤዎች የት ሂደው ነው እንኳን አማኝ እግዚአብሔርን የማያምኑ የሚፀየፉት ዘረኝነቱም ፣ ፖለቲካውም ፣ርግማኑም ፣ምርቃቱም ላይ ከመቀላቀል አልፈው ፊታውራሪ የሚሆኑ ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት ? እነዛ የሁሉም አማኝ ተስፋ ስለሆነው የዘላለም ህይዎት ሲናገሩ ‹ምነው ዛሬውኑ ሙቸ ወደጌታ በሄድኩ› የሚያስብሉ ሰባኪዎች የት ሂደው ነው …. ውድ ልብስ መልበስ ፣ውድ መኪና መንዳት …ቆንጆ ሴት እና ቆንጆ ወንድ ማግባት…ውድ ቪላ ቤት መኖር የበረከት መጨረሻ አስመስለው የሚያወሩ ‹‹ጴንጤዎች ›› የበዙት የት ሂደው ነው እነዛ ወንድምና እህቶቻቸውን በመከራ ይሁን በችግር የሚቀበሉ ደጋግ ክርስቲያኖች ….እንደዚህ በራሱ በእግዚአብሔር ስም እግዚአብሄርን ጭምር ወደዛ ገፍትረው እራሳቸውን ብቻ የሚቀበሉ ‹‹ጌታን ያልተቀበሉ ጴንጤዎች ›› የበዙት ?????? ጌታን ያልተቀበሉ ‹‹ጴንጤዎች›› እነዛ በድንጋይ ስንወግራቸው ‹‹ጌታ ይቅር ይበላችሁ›› ብለው የሚያልፉ በትህትናቸው የማረኩን ጴንጤዎች የት ሄደው ...ነው እርስ በእርስ ያውም በተራ ነገር አይናቸው በቁጣ ደም ለብሶ በፌስቡክና ዩቲዩብ የሚዘላለፉ ‹ጴንጤዎች› እንደአሸን የፈሉት? እነዛ በጊታር ብቻ ሲዘምሩ የቤተሰብ ቁጣ ተደብቀን በአጥራቸው ተንጠራረተን በአሮጌ ማምለኪያ ቤቶቻቸው ሽንቁር አጨንቁረን በጉጉት የምናያቸው፣ በጨረፍታ የሰማነው መዝሙራቸው ምላሳችን ላይ ተጣብቆብን የሚቀር ዘማሪዎች የት ሂደው ነው …. ልብስ ብቻ ቀይረው በየሰርግና ድግስ ቤቱ ያውም ክፍያ ተከራክረው በሰው መዝሙር የሚውረገረጉ መዝሙር ቸብቻቢ ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት? በስንት ፆሎትና ለቅሶ መዝሙር ተቀብለው የሚዘምሩ የቆዩ ዘማሪዎች የት ሂደው ነው ‹‹ክርስትና ሰጠን በሚል ነፃነት ስም›› የሰው መዝሙር እየዘመሩ ያውም ክሬዲት ሳይሰጡ እንደራሳቸው ስራ በዩቲዩብ ሳንቲም የሚለቅሙ ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት? እነዛ ሲገኝ በፈረስ ሲታጣም በእግራቸው በባዶ ሆዳቸው በየጠገጠሩ እየኳተኑ አቧራ ለብሰው የሚናገሩት ወንጌል የሚሊየኖችን ልብ የማረከ ወንጌላውያን የት ሂደው ነው…ውድ ሱፍ ለብሰው ውድ እህል ጎርሰው በፈርስት ክላስ በረራ ኤሮፕና አሜሪካ እየተዘባነኑ …እንኳን ልብን ልብስን የማያስቀይር ዝባዝንኬ ሲያወሩ የሚውሉ ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት ? እነዛ ለወንጌል እየተጠሉ እንኳን ቃሉ ሂወታቸው ላይ እየተነበበ የሚያስደንቃቸው እና የሚያስከብራቸው አገልጋይና ምእመኖች የት ሂደው ነው … በየሶሻል ሚዲያው በሳምት አስር ጊዜ ልብስ እየቀየሩ ፣ከተነሱት ፎቶ ጋር የሚለጥፉትን ጥቅስ በእነሱ ምክንያት ህዝብ የተፀየፈው ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት ? ድፍር ብለው ‹‹ብርሃንና ጨለማ ህብረት የላቸውም እግዚአብሔርን በማያከብር ነገር አትቀላቀሉ ›› የሚሉ ቆራጥ ጴንጤዎች የት ሂደው ነው እንኳን አማኝ እግዚአብሔርን የማያምኑ የሚፀየፉት ዘረኝነቱም ፣ ፖለቲካውም ፣ርግማኑም ፣ምርቃቱም ላይ ከመቀላቀል አልፈው ፊታውራሪ የሚሆኑ ‹‹ጴንጤዎች›› የበዙት ? እነዛ የሁሉም አማኝ ተስፋ ስለሆነው የዘላለም ህይዎት ሲናገሩ ‹ምነው ዛሬውኑ ሙቸ ወደጌታ በሄድኩ› የሚያስብሉ ሰባኪዎች የት ሂደው ነው …. ውድ ልብስ መልበስ ፣ውድ መኪና መንዳት …ቆንጆ ሴት እና ቆንጆ ወንድ ማግባት…ውድ ቪላ ቤት መኖር የበረከት መጨረሻ አስመስለው የሚያወሩ ‹‹ጴንጤዎች ›› የበዙት የት ሂደው ነው እነዛ ወንድምና እህቶቻቸውን በመከራ ይሁን በችግር የሚቀበሉ ደጋግ ክርስቲያኖች ….እንደዚህ በራሱ በእግዚአብሔር ስም እግዚአብሄርን ጭምር ወደዛ ገፍትረው እራሳቸውን ብቻ የሚቀበሉ ‹‹ጌታን ያልተቀበሉ ጴንጤዎች ›› የበዙት ??????

😢ቤተሰብ + እንደምን ከረማቹ ዛሬ ከወትሮው ለየት ያለ የደበኩትን ሚስጥር ነው ማወጋችሁ💔 ከሰሞኑን ልቤን ተስፋ መቁረጥ ቢጤ ከጀለው እናም ዝም ብሎ ትርጉም የሌለው ህይወት አሸተትኩ ከንቱነት ቤቱን ሰራብኝ😭 ዝም ብሎ መሮር ሰለቸኝ😞 እናም በዝህ ሀሳብ አእምሮዪ ሲወጠር መኖር ስለደከመኝ መሞት አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ተረዳው ከዛም ስልኬን ከፍቼ የአሟሟት ዘዴዎችን ከታወቁ የሞት አማካሪዎች ብሎም ልምዱን ካካበቱ እውቅ ሟቾች አያሌ ልምዶችን ቀሰምኩ ግን አንዳቸውም የሚያስገርም ሞት አልሞቱም በዝህ እየበገንኩ እያለ አንድ መፅሐፍ ላይ ያነበብኩት ድንቅ አሟሟት በልጭ አለልኝ በአግራሞትም ከኪሴ ያቺ ቃላት በምሬት የተሰደዱባትን ሀዘንተኛ ብእሬን በማውጣት እንደ ማንኛውም ተስፍ የቆረጠ ሰው እንዲህ ብዪ ከአውላላው ማስታወሻዪ እንደኑዛዜ ከተብኩ 🤔በቃ ብንሮጥ ይሻላል ? በደንብ ይሮጣል...በደንብ ነዋ የመጀመሪያው የማራቶን ሯጭ # ፊዲፒዲስ ይባላል። #ግሪካዊ ነው። በ 490 አ.አ አካባቢ #ግሪክ ከ #ፐርሺያ (ኢራን) ጋር ከፍተኛ ጦርነት ላይ ነበሩ። የጦርነት ስፍራው #ማራቶን ይባላል። እልህ አስጨራሽ #ጦርነት ካደረጉ ብኃላ #ግሪካውያን አሸነፉ። ይህን ግዜ ወታደሩ #ፊዲፒዲስ ደስታውን #ብቻውን ሀሴት ማረግ አቃተው። ስለዚህ #በጭንቀት የምስራች ይጠብቁ ለነበሩ የአቴና ኑዋሪዎች ይህን #የምስራች ሊያበስር ወሰነ! ከጦርነቱ ስፍራው ከ #ማራቶን እስከ #አቴንስ 42 ኪ.ሜ የሚያህል ርቀት ፣ ያለ አንዳች ማቋረጥ ሮጠ። ወደ አቴንስ ከተማ በር ሲደርስ እግሩ #በደም ተጨማልቆ ፣ ሰውነቱ በላብ ተጠምቆ ነበር። #ፊዲፒዲስ "አሸንፈናል እንኳን ደስ አላችሁ" ብሎ ለህዝቡ አበሰረ። #ግሪክ በደስታ ብዛት ፈነደቀች። #ፊዲፒዲስ ግን #የምስራቹን ካበሰረ ብኃላ በድካም ብዛት ፣ ተዝለፍልፎ ወደቀና ፣ በዚያው ህይወቱ አለፈች። ። ይህ አሳዛኝ ፣ እውነተኛ ታሪክ ፣ ስለ ምድራዊ የ # ሀገር ፍቅር የተፈፀመ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ፣ ከ 2000 አመት በፊት #የደም ላብ አልቦት ፣ በኢየሩሳሌም #ሴቶች ፊት ስላንተ #ራቁቱን ተሰቅሎ ፣ #በፍቅር አንድ ትልቅ # ጦርነትን በቀራንዮ ስላሸነፈው #ኢየሱስ የምስራች ሰምተሀልን?። ጌታ ኢየሱስ እስከሞትና እስከ ዘላለም ድረስ ይወድሃል ብታምንበት የዘላለም ሕይወት ይሰጥሃል ። ስለ አንተ(ቺ) በአብ ፊት ያማልዳል። ሮሜ8:34 ከሰማህ.. ይህን የምስራች # በጭንቀት ፣ # በፍርሀት ፣ # በተስፋ_መቁረጥ ውስጥ ላሉት ልታበስር ፣ እንዲሁም አንተ ያገኘኸውን #ሀሴት ለሌሎች #ልታካፍል እየሮጥክ ነው?? ወይስ ቁጭ ብለሀል??. #ፊዲፒዲስ እኮ የሞተው #ደስታውን ከሌሎች ጋር #ለመጋራት ሲል ነው። #ወንጌል ለምድራዊ ፣ ጊዜያዊ #ደስታ አይደለም የሚያስሮጠን ፣ #ዘላለማዊ ደስታ ወንድሞቻችን ያገኙ ዘንድ ነው። ወንድሜ ለራስህ #ደስታ መሮጡን #ግታና ለሌሎች #ደስታ #ሩጥ ግዜ የለም። #ከሞቱ አይቀር እንዲህ የከበረ እየሮጡ መሞት ነው አዎ በወንጌል መንገድ ላይ ለክርስቶስ መሞት ታሪኩ ከአንድ ሳምንት ዎይታ እና ለቅሶ ያለፈ በበጉ ሰርግ ያከብራል አዎ ድንገት። ድንገት ከአጠገቤ የነበረው የውሀ ኮዳ ከ ጠረፔዬ ላይ ዱብ ሲል ከገባውበት የሀሳብ ፍሰት ከ ብእሬም መሪር ለቅሶ ነቃው✍ አዎ በቃ ብንሮጥ ይሻላል 🏃 😍ቤተሰብ + ለዛሬ በዚህ ይብቃን ምህረት እና ቸርነት ይብዛላችሁ 😍 አደራ #share እንዳይረሳ

Repost from Theophilus Terefe
#Prayer «...ትጸልያላችሁ?» ለነገ ሕይወታችሁ ትጸልያላችሁ? ትጸልያላችሁ? ራሳችሁን ትልቅ እናትና አባት አድርጋችሁ አስባችሁ፣ ቀጣይ “Generation” እንደምትሰሩ አስባችሁ ለራሳችሁ ትጸልያላችሁ? ነገ ስለሚገጥማችሁ ሕይወት፣ ስለቤታችሁ ትጸልያላችሁ? ስለምትሠሩት ሥራ ትጸልያላችሁ? ስለምታገለግሉት ስለምትመሩት ሕዝብ፣ ስለምትመሩት መስሪያ ቤት፣ ስለምትመሩት አከባቢ፣ ስለምትመሩት ሀገር ትጸልያላችሁ? እሱ ነው ነገ ላይ አቅም 'ሚሆንላችሁ። ሌሎች አቅም አተው ሲንገዳገዱ፤ አቅም ሆኖ 'ሚያቆማችሁ ዛሬ 'ምትጸልዩት፣ ዛሬ 'ምታነቡት ቃል፣ ዛሬ በቤቱ 'ምታሳልት ጊዜና እርሱን በመፈለግ 'ምትጨርሱት ዕድሜአችሁ ወሳኝ ነው። ከ2014 ዓ/ም ማሕደር። https://t.me/Theophilus_Terefe

Repost from Theophilus Terefe
#በእምነት_ብቻ በመዝሙር 32 ዳዊት ከእግዚአብሔር ስለ ተቀበለው ነጻ የሆነ ይቅርታ ሐሴትን ያደርጋል። ኃጢአትን አድርጎ ስለነበረ፥ ኃጢአቱን ለእግዚአብሔር ይናዘዛል፤ እግዚአብሔርም በታላቅነቱ ኃጢአቱ
#በእምነት_ብቻ በመዝሙር 32 ዳዊት ከእግዚአብሔር ስለ ተቀበለው ነጻ የሆነ ይቅርታ ሐሴትን ያደርጋል። ኃጢአትን አድርጎ ስለነበረ፥ ኃጢአቱን ለእግዚአብሔር ይናዘዛል፤ እግዚአብሔርም በታላቅነቱ ኃጢአቱን ይቅር ይለዋል። በመዝሙር 32 ዳዊት የተቀበለው ምሕረት ፈልጎ ያገኘው ነገር እንዳልነበር ጳውሎስ ተገንዝቦ ነበር። (ሮሜ 4፥6-8) በዚህ መዝሙር ዳዊት ያደረገው ነገር ኃጢአቱን ለእግዚአብሔር መናዘዝና በእግዚአብሔር ምሕረት መደገፍ ነበር። እግዚአብሔር በነጻ ይቅር አለው። እግዚአብሔር ኃጢአትን ይቅር እንደሚልና ሰዎችን ጻድቅ እንደሚል ይህ ግልጽ የሆነ ተጨማሪ ማረጋገጫ ነው። መልካም ሥራን ስለሠሩ ወይም ኃጢአትን መሥራት ስላቆሙ ሳይሆን በእግዚአብሔር ስለታመኑ ብቻ ነው። (መዝ 32፥9) https://t.me/Theophilus_Terefe

ለ2015 ዓ.ም የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ለወሰዱ ተማሪዎች በሙሉ የነገው ፕሮግራም መግቢያ በነጻ ተደርጓል። ይህ እድል እንዳያመልጣችሁ!! በብዙ ውጣውረድና ዋጋ መክፈል አዲስ የሥራ ፈጠራ ሃሳብን አ
+1
ለ2015 ዓ.ም የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ለወሰዱ ተማሪዎች በሙሉ የነገው ፕሮግራም መግቢያ በነጻ ተደርጓል። ይህ እድል እንዳያመልጣችሁ!! በብዙ ውጣውረድና ዋጋ መክፈል አዲስ የሥራ ፈጠራ ሃሳብን አንግበው እውን እስከማድረግ ተጉዘው ለስኬት የበቁ ሥራ ፈጣሪዎች የተጋበዙበት "የብርሃን መንገድ 5" መሰናዶ እነሆ ደረሰ። ነገ ዕለተ እሁድ ህዳር 02/2016 ዓ.ም በሃዋሳ ሳውዝ ስታር ሆቴል ከቀኑ በ09:00 ሰዓት ሁላችሁም ተጋብዛችኋል! መግቢያ ትኬቱን በእለቱ መግቢያ በር ላይም ያገኙታል። ለ2015 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መግቢያ በነጻ!

Ye ahunochu ena ye kedimo asitebabarwoch ye anidnet gize melikam gize neber silagegnewachu des bilognal berituln Geta eyesus yiredachuhal tebarekulgn❤️😘😍 UNION FELLOWSHIP

photo content
+5

photo content
+9

😍ቤተሰብ+ ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ እንደምን ቆያቹ ዛሬም ትንሽ በህይወት እንመሰጥ 🫥 ዛሬ ትንሽ ለየት ያለ እንግዳ ነገር ከልቤ በረሀ ላይ ሲንቆረቆር በማስተዋል ሳደምጠው ትንሽ ከፍኝ እናም መከፋቴን ባህሪዪ እንደ ወራጅ ውሀ ሲደፈርስ መልኬ የሀዘን ደመና ☁️ ሲከበው አንድ መተንፈሻ ጓዴን ያችን ተማኝ ብዕር ከማህደሩ አውጥቼ ከትዝብት ቀለም እየነከርኩ እዚህ ግባ በማይባል ብጣሽ ወረቀት ላይ የብእሬን እንባ በሀቅ ከተብኩ ምን አትሉኝም ? 😢 ኢየሱስ ናፎቆን በፍዘቴ ወስጥ ዛሬ ኢየሱስ ናፈቀኝ 😢 🩸ኢየሱስን ከፀሎት ስፍራዪ ከሚፈሰው የእንባ ፈሳሽ ላይ ብፈልገው አጣውት ያገኘውት የነገ መሻቴን ሆነ 🩸 ኢየሱስን በዛሬ ቀኔ ላይ መስቀሉን እያየው ሁሌ የማለቅሰው ከእልፍኝ ጓዳዪ እኔ የምንበረከከው ነበረ ለፍቅሩ ነበረ ለደሙ ነበረ ዛሬ እንኳን በዛሬ ነገ ባለየውት የመኖር ተስፍ ላይ ኢየሱስ ከህይወት መንገድ ላይ እንግዳ ሆኖ ሳይ የእውነት ከፍኝ 🩸የልቤ ጨኸት ንዋይ ለመቆለል ዝና ለማስጨመር እውቀት ለመደረብ ራስን ለማሞገስ መሆኑን አደመጥኩ እንደው ምፈልገው ውበቴን ጌታዪን ከኋላ ታሪኬ አራግፌ ጥዬ የማይረባኝን የማይጠቅመኝ ስለቃቅም ቆየሁ 🩸 እንደው የሚገርመው ቤቴን ብትፈትዪ ከሸልፉ ከአናቱ የተደረደረው መፅሀፍት አርእስቱ ይገርማል "አምስቱ የህይወት መንገዶች " "ሰላማዊ ህይወት በደሀ ሀገራት" " መንገድህን በዝና " በሚሉ እና ተመሳሳይ ይዘት ባላቸው መፅሐፍ ተሞልቷል ስልኬንም ብከፍቱ ከ YouTube Instagram ላይ ታትሬ ያየውት "ትችላለህ " "ማንንም ሳትሰማ ተጎዝ " የሚሉ መልእቶች ነው ይብላኝ ለእኔ ይሄን ረስቻለው “ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ ዮሐንስ 14፥6 🩸ከእልፍኜ መፍረስ ባንኜ ስነሳ አደባባዪን ቤተክርስቲያንን ሳይ እልፍኛቸው የፈረሰባቸው እየሱስ ካሸተቱ የቆዪ በቁስ ቀውስ ውስጥ ያሉ ከመዳን ወንጌል ፈቀቅ ያሉ አዳራሽ ጥቅጠቃ የተያያዙ የሀይልን መንፈስ አግፋፍተው አፈንጋጭ ልምምድ የዘፈቁ አያሌ የኔ ቢጤዎችን ሳይ ይልቁን አዘንኩኝ 🩸ለካ የዘመኔ ጉባኤ እልፋኙ ፈርሶ ነው ግራ የተጋባው ወዳጆቼ ከትውልድ ልብ መሰንጠቅ ይልቅ የአዳራሽ ግንብ መሰንጠቅ የሚያስጨንቀን ለካ እልፍኛችን ፈርሶ ነው ሀጥያት ካፈነው ትውልድ ድምፅ በላይ የታፈነ ድምፅማጉያ ሚረብሽ ለካ እልፍኛችን ፈርሶ ነው ቤታችን አላፊ አግዳሚ የሚፈነጭበት ሀይ ባይ መካሪ አተን በደጀ ሰላሙ ሸመታ የተያያዝው 🩸ለካ እልፍኝ ሲፈርስ መስቀል የፍሲካ ሰሞኑን ስብከት ይሆናል ለካ እልፍኝ ሲፈርስ የክርስቶስ ፍቅር የአዲስ ክርስቲያን መነካት ብቻ ይሆናል ለካ እልፍኝ ሲፈርስ ፈውስ እና ትንቢት ደግሞም መንፈሳዊ ዜማ በቤቱ እንግዳ ይሆናሉ ስለዚህ ኢየሱስ ናፈቀኝ አዎ ኢየሱስ ናፈቀኝ ይሄ ባይገልፀው አለወትሮዪ በእንባ ረጥቤ ቃላትን ከቃላት አጋጨው የነብሴን መጨነቅ በብእሬ እንባ በትዝብቴ ቀለም በግጥም ለወረቀቴ እንዲህ ብዪ አወጋው፦ 😢ኢየሱስ ናፍቆን አገልጋዩ መጥቶ : ህዝቡ ተኮልኩሏል አዳራሹ ጠቦ : ግማሹ ውጭ ቆሟል ስብከት ተጀመረ:ሰባኪው አበደ በጩህት ሆይሆይታ:ጉባኤው ነጎደ የገባው አሜን በል:ተነስተህ ተቀበል በርበሬውና ሽሮ:አይወደድም በል እምነት ሆኖ ጩህት:ላንቃ ተተርትሮ ዝም ያለ አላመነም:ወድያ ተገፍትሮ በአቋራጭ መንገድ:እግዜርን ለመቅደም ቃሉን ንቆ ትንቢት:ነብያት ሲታደን ኢየሱስ ናፍቆን:ቃሉ እጅግ ተርበን ደጀ ሰላም መጣን:ከቶ እሱን አጣን ስብከት ተቀይሮ:ሲሆን ቡራቡሬ ቁስላችን ታኮ:ጠገብን በወሬ ጥርመሳው ኮንፈረንስ:እንዳሻን አብዝተን የመኸሩ ጊዜ: አደራ እንዳያልፈን:: 🩸በመጨረሻ የናፍቆቴን ፅሁፍ ልቋጨው ስሞክር አንድ የጌታዪ ባሪያ የጴጥሮስ ንግግር ትዝ አለኝ “ስምዖን ጴጥሮስ፦ ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤” ዮሐንስ 6፥68 አዎ በትክክል እንዲህ እንላለን ጌታችን የደምህ መአዛ ከእልፍኛችን ያውድ አዎ መድሀኒያለም ምንም እንኳን ብዙ ጊዜ በልጅነታችን ተስፍ ብንቆርጥ አንተ ዛሬም በአባትነትህ ተስፍ አልቆረጥክም ዛሬም በቤታችን መትጋት ላቃተን ከአንተ ዘንድ ተስፍ አለ ከወደቅንበት አንሳን በሀሳባችን ላይ አንተ ጌታችን አስብበት በውጥናችን ላይ ወጥንበት ልጆችህን በመጨረሻም ዘመን የመንፈስህ ሀይል ጓብኘን ቃለ ህይወት አስማልን የእውነትን መንገድ አሳየን የቃልህን አብርሆት አብራልን ከሁሉ በላይ በሰማያት ያለፍከውን አንተን ብሎም በእውነት ወንጌልን ያለመሸቀጥ የኖሩትን የቅዱሳንን የአባቶቻችን የሰመአታትን ፈለግ እንድንከተል ፀጋ ይደግፈን በኢየሱስ ስም አሜን🙏

Zetseat chori❤️❤️❤️ ✅UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff @uacsff join shere👆👆👆👆👆

Zetseat chori❤️❤️❤️ ✅UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff @uacsff join shere👆👆👆👆👆👆

Zare tiru ye amiliko gize neberen tebareku Zetseat chori❤️❤️❤️❤️ ✅UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff @uacsff join shere👆👆👆👆👆👆

😍ሰላም ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ ቤተሰብ + እንደምን ቆያቹ በጣም እንደተጠፍፍን ይገባኛል ብዕሬ ከማንቀላፍት አልፍ እራሱዎን ስታብኝ ነበር አረ አትደንግጡ 😂 ተነስታለች 🤔ለማንኛውም አንድ የትዝብት ፅሁፍ ከሀሳብ ዎሻ ውስጥ በቀለም ዝማሬ በምናብ ፏፏቴ በእይታ ጅረት በእውነት ጋራ ላይ በሀቅ ዋርካ ስር በማንበብ ህይወትን እንቀልም በራቁትነት አለም የተራቆተ ትውልድ ••• የዚህች አለም ነገር እጅጉን ይገርማል። ይህች እርቃኗን የቀረች አለም እድሜ ለስልጡን ነን ላሉ ሀገራት እርቃን ሆነው ራቁቷን አስቀሯት። እኔ የገረመኝ ግን ስልጡን ባዮች በጮሁ ቁጥር አለም ሁሉ ያለማስተዋል አብሮ ሲጮህ መኖሩ ነው። ሀብታም ሲናገር ደሃ ያለ ውስጣዊ ፍላጎቱ ሲያጨበጭብ እንመለከታለን። ያለው ካመጣ የሌለው ሳያማርጥ ከነግሳንግሱ ሲቀበል እናስተውላለን። ዛሬ ዛሬ እርቃንነት የአለማችን ታላቁ ስልጣኔ እየሆነ መጥቷል። መጥቀናል አድገናል ሰልጥነናል(ሰይጥነናል) ባዮች የአለም መሪ ሀገራት በተለይ ለሴቶች ከእግር በላይ ልብስን ከፍ ማድረግንን እና መገላለጥን የዘመናዊነት መለኪያው ካደረጉ ሰነበቱ። ዳሌን እና ባትን እንዲሁም ከፍ ካለ ሀፍረተ ስጋን ማሳየት የበለጠና የተሻለ ስልጣኔ እንደሆነ ከመከሩ ቆዩ። ሙሉ መልበስ ሙድ የለውም አይን አይገባም ብለው አጣጣሉ። ወደ እግር  ዝቅ ያለ ልብስ የተሸፋፈነ ገላ የኋላ ቀርነት ምልክት ነው ከጊዜው ጋር ለመራመድ ልብስን ከላይም ዝቅ ከታችም ከፍ አስፈላጊ እየሆነ መጥቷል። (ወይ ጉድ ጊዜም ሴሰኛ ዝሙተኛ ሆነ እንዴ?) ••• በጥባጭ ካለ ማን ጥሩ ይጠጣል እንዲሉ ሰልጥነናል የሚሉ ምእራባዊያን ለሰው ልጅ ጥሩ ስብእናና የባህርይ ምጥቀት አዋጩን መንገድ መርጦ ከመከተል ይልቅ የአጥፍቶ መጥፋት ዘመቻቸውን በማጋጋል ርካሽ ባህሎቻቸውን ልቅ ስነምግባሮቻቸውን ለአለም ለማዳረስ ቅርጠው ተነስተዋል። (ቆዩ እኮ እየተሳካላቸውም ነው) ፈጥኖ የገባው ሲቀር የተጃጃለው የራሱን ምርጥ እምነት ባህልና አምላክ የወደደ እሴት ትቶ የነ ስልጡን ሰይጣናዊ እሴት ያለማገራገር ተቀብሏል። እየተቀበለም ነው። (እስኪ ኢንተርኔት ቤት ጎራ ይበሉ ለአቅመ ዝሙት ያልደረሰን ታዳጊ የከፈተውን የድህረገፅ አይነት ይመልከቱ) በሌላ ቅንፍ(እስኪ ወደ ትልቅ ትምህርት ተቋማት ይግቡና እድሉን ካገኙ ሞባይላቸው ላይ የተጫኑ ፊልሞችና ዘፈኖች ይመልከቱ። ተማሪዎቻችንም ይመልከቱ ሞባይል ላይ ካለው ልቅ ስነምግባር ጋር ልዩነቱ የጠበበ ነው)። ••• የእርቃንነት ጉዳይ በዋናነኛነት ዛሬ በአለም ላይ እጅጉን አሳሳቢ ከሆኑት ነገሮች መካከል ይጠቀሳል። በውበት ስም(የሴት ልጅ ውበትን ማድነቅ የጤንነት ምልክት ነው የምትለዋን መርዘኛ አባባልን የፈጠረ ምን ያህል ሊቅ ነው። ራቁት ገላን በአደባባይ ማሳየት በተለይ በወጣትነት የአፍላ(የእሳት) ስሜት ላይ ቤንዚን የማርከፍከፍ ያክል ፈታኝ ከሆኑት መካከል አንዱ ነው። ••• ስልጡኑዎ የቤተክርስቲያን ወጣት የምትገዛውን ልብስ ተመልከቱማ... 🤔አሁን አሁን ስታዘብ በትምህርት ተቋማት በተለይ የሴት እህቶቻችን የደንብ ልብስ (UNIFORM) ለእኔ ብቻ ነው ከላይ ካለው ሀሳብ ጋር የተገናኘብኝ እጄን ከአፌ እያስጫነኝ እየመጣ ያለ ጉዳይ ዎነኛ ባንድራ አራጋቢ የሆኑት ክርስቲያን ወጣቶች መሆናቸው ነው በትምህርት ተቋማት ይሄ ጉዳይ የአፍላ ተማሪዎች ፈተና ከመሆን አልፎ አእማድ የእውቀት ከያኒያን መምህራንንም ደንቀፍ እያደረገ እንደሆነ ሀገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው ሰለዚህ በፌሎሽፕ ብሎም በቤተክርስቲያን የምናገለግል እህቶች እንደው ግድ የለም አለባበሳችንን ከለበስነው ፀጋ አንፃር ብንቃኘው ባይ ነኝ ለብዙ ተማሪዎች እና የቤተክርስቲያን ወጣቶች ምሳሌነት ያለው አለባበስ ብንለብስ ለእኛም ጥቅም ለቤተክርስቲያንም ክብር ነው💯 ‼️ ይሄን ስል ለፊሎሽፕ + ለቤተክርስቲያንም ኩራት የሆናችሁ ምግባረሰናይ ሴት ወጣት እህቶቻችን አያሌዎች እንዳላቹ የማይካድ እውነት ነው‼️ ሀሳቤን ስጨርስ ከላይ በርእሱ እንዳልኩት ‼️በተራቆተች አለም የተዎበውን እየሱስን በምግባራችን እንመስክር‼️                

photo content

Beteseb zarem barikot alegn tebarekubet maledaye nw👏❤️🫡beka simut 😍😘😍😘👏👏

✨ልዩ የወጣቶች ትምህርታዊ ኮንፈረንስ✨ 📌 “ተፅዕኖ ፈጣሪ ትውልድ”📌 ከጥቅምት 1-4 ሀሙስ እና አርብ ከ10:00-1:30 ቅዳሜ ጠዋት ከ3:00-6:00 እና ከሰዓት 10:00-1:30 እሁድ ጠዋት
✨ልዩ የወጣቶች ትምህርታዊ ኮንፈረንስ✨ 📌 “ተፅዕኖ ፈጣሪ ትውልድ”📌 ከጥቅምት 1-4 ሀሙስ እና አርብ ከ10:00-1:30 ቅዳሜ ጠዋት ከ3:00-6:00 እና ከሰዓት 10:00-1:30 እሁድ ጠዋት ከ3:00 ጀምሮ በወጣቶች አገልግሎት የተዘጋጀ 👉 We kindly invite everyone And invite all your friends HGC YOUTH MINISTRY, 2023

✨ልዩ የወጣቶች ትምህርታዊ ኮንፈረንስ✨ 📌 “ተፅዕኖ ፈጣሪ ትውልድ”📌 ከጥቅምት 1-4 ሀሙስ እና አርብ ከ10:00-1:30 ቅዳሜ ጠዋት ከ3:00-6:00 እና ከሰዓት 10:00-1:30 እሁድ ጠዋት
✨ልዩ የወጣቶች ትምህርታዊ ኮንፈረንስ✨ 📌 “ተፅዕኖ ፈጣሪ ትውልድ”📌 ከጥቅምት 1-4 ሀሙስ እና አርብ ከ10:00-1:30 ቅዳሜ ጠዋት ከ3:00-6:00 እና ከሰዓት 10:00-1:30 እሁድ ጠዋት ከ3:00 ጀምሮ በወጣቶች አገልግሎት የተዘጋጀ 👉 We kindly invite everyone And invite all your friends HGC YOUTH MINISTRY, 2023

😍ቤተሰብ + 😍ሰላም ሰላም ፀጋ እና ምህረት ይብዛላችሁ ቤተሰብ + እንደምን ከረማችሁ ስለ ሁሉ ጌታ ይመስገን ደግሞ በልባችን ያለ ግን ደግሞ ድምፅ የሌለው አንድ ሚስጥር ልንገራችሁ 🥹 በጣም ተና
+1
😍ቤተሰብ + 😍ሰላም ሰላም ፀጋ እና ምህረት ይብዛላችሁ ቤተሰብ + እንደምን ከረማችሁ ስለ ሁሉ ጌታ ይመስገን  ደግሞ  በልባችን ያለ ግን ደግሞ ድምፅ የሌለው  አንድ ሚስጥር ልንገራችሁ  🥹 በጣም ተናፍቃችዃል☺️ 😎በመጠርጠር ፀጋዪ ስጠረጥር የሁላችሁም ልብ ውስጥ ያለ እውነት ነው 🤔 በጠቆረ ሰማይ የታጀበው ልክ እንደ ጎበዝ አለቃ ድምፅ በሚያስተጋባ ነጎድጓድ ብሎም እንደ ድሮ ፎቶ አንሺ አንፖል ብልጭ ብሎ የሰውን ቀልብ አስከትሎ ድርግም በሚለው መብረቅ የተገመደው የክረምት ጊዜ ፍጥረቱን በእግዜሩ ፈሳሽ አርሶ በበጋ ንዳድ የከሰለውን መሬት አጥግቦ ሙቀትን አስናፍቆ ነገን አሳይቶ በተስፍ ታሽጎ በፍቅር ተቋጥሮ በእምነት ተጭኖ ይኸው በሰላም ተሸኘ ይኼ ገለፃ ሀዋሳ ለነበርን አይሰራም ምክንያቱም ክረምቱ ፀሀያማ ነበር😂 ለማንኛውም በናፍቆት ባብር ተሳፍሮ እያነጎደ ያለውን የህበረታችንን የ2016 የአገልግሎት ዘመን ከጥቂት ቀናት በኋላ በ wellcome መርሀ ግብር ፌርማታው ላይ አድርሰን እናወርደዋለን እስከዛ ባብሩ ፍጥነት ስለሚፈልግ ናፍቆታችሁ እንዲበረታ ባብሩም እንዲፈጥን ቀኑ መቼ አንደሆነ አልነግራችሁም ዛሬ የተከሰትኩበት  አላማ ጊቢ ውስጥ የገብ አዳዲስ ብሎም ነባር ተማሪዎችን  ወደ እዚህ የ fellowship official telegram channel link share በማድረግ እድትጋብዟቸው መረጃ  በፍጥነት እንዲደርሳቸው እንድታረጉ ለማሳሰብ ብሎም በክረምቱ ትንሽ ያቀላፍችውን ብዕሬን በናፍቆት ፅሁፍ ቀስቅሼ ላነቃት አስቤ ነው 😁 የ wellcome ቀን መረጃ በሚቀጥሉት ቀናት ይዤ እከሰታለው እስከዛ ደረስ ግን አደራ 👇👇 ‼️ባብሩ ከፌርማታው እንዲደርስ በብዙ መናፈቃችሁን ቀጥሉ የባብሩንም ፍጥነት ጨምሩ   🥹 ቸር ሰንብቱ ቤተሰብ+ 🥹 😍UNION FELLOWSHIP @uacsff @uacsff

😍ቤተሰብ + 😍ሰላም ሰላም ፀጋ እና ምህረት ይብዛላችሁ 😍ቤተሰብ + እንደምን ከረማችሁ ስለ ሁሉ ጌታ ይመስገን ደግሞ በልባችን ያለ ድምፅ የሌለው አንድ ሚስጥር ልንገራችሁ 🥹 በጣም ተናፍቃችዃል
+1
😍ቤተሰብ + 😍ሰላም ሰላም ፀጋ እና ምህረት ይብዛላችሁ 😍ቤተሰብ + እንደምን ከረማችሁ ስለ ሁሉ ጌታ ይመስገን ደግሞ በልባችን ያለ ድምፅ የሌለው አንድ ሚስጥር ልንገራችሁ 🥹 በጣም ተናፍቃችዃል☺️ 😎በመጠርጠር ፀጋዪ ስጠረጥር የሁላችሁም ልብ ውስጥ ያለ እውነት ነው😎 🤔 በጠቆረ ሰማይ የታጀበው ልክ እንደ ጎበዝ አለቃ ድምፅ በሚያስተጋባ ነጎድጓድ ብሎም እንደ ድሮ ፎቶ አንሺ አንፖል ብለጭ ብሎ የሰውን ቀልብ አስከትሎ ድርግም በሚለው መብረቅ የተገመደው የክረምት ጊዜ ፍጥረቱን በእግዜሩ ፈሳሽ አርሶ በበጋ ንዳድ የከሰለውን መሬት አጥግቦ መቀትን አስናፍቆ ነገን አስቀርፆ በተስፍ አሰንቆ በፍቅር ታሽጎ በእምነት ተቋጥሮ ይኸው በሰላም አለፈ ይኼ ገለፃ ሀዋሳ ለነበርን አይሰራም ምክንያቱም ክረምተ ፀሀያማ ነበር😂 ለማንኛውም በናፍቆት ባብር ተሳፍሮ እያነጎደ ያለውን የህበረታችንን የ2016 የአገልግሎት ዘመን ከጥቂት ቀናት በኋላ በ wellcome መርሀ ግብር ፌርማታው ላይ እድርሰን እናወርደዋለን እስከዛ ባብሩ ፍጥነት ስለሚፈልግ ናፍቆታችሁ እንዲበረታ ባብሩም እንዲፈጥን የ wellcome ቀን አልነግራችሁም ዛሬ የተከሰትኩበት አንድም አላማ ጊቢ ውስጥ የገብ አዳዲስ ብሎም ነባር ተማሪዎችን ወደ እዚህ የ fellowship official telegram channel link share በማድረግ እድትጋብዟቸው መረጃ በፍጥነት እንዲደርሳቸው እንድታረጉ ለማሳሰብ በሎም በክረምቱ ትንሽ ያቀላፍችውን በእሬን በናፍቆት ፅሁፍ ቀስቅሼ ላነቃት አስቤ ነው 😁 የ wellcome ቀን መረጃ በሚቀጥሉት ይዤ እከሰታለው እስከዛ ደረስ ግን አደራ ‼️ባብሩ ከፌርማታው እንዲደርስ በብዙ መናፈቃችሁን ቀጥሉ የባብሩንም ፍጥነት ጨምሩ‼️ 🥹 ቸር ስንብቱ ቤተሰብ +

ሕይወትህ በእግዚኣብሔር እጅ ስትሆን እርሱ ለሚያስፈልግህ ሁሉ ኃላፊነት ይወስዳል። ዋና ዋናዎቹን ኣሟልቶ አነስ አነስ ያለውን ኃላፊነት ላንተ አይተውም። ለሚያስፈልግህ ሁሉ አንድ ቁልፍ ሰጥቶሃል፤ ኢየ
ሕይወትህ በእግዚኣብሔር እጅ ስትሆን እርሱ ለሚያስፈልግህ ሁሉ ኃላፊነት ይወስዳል። ዋና ዋናዎቹን ኣሟልቶ አነስ አነስ ያለውን ኃላፊነት ላንተ አይተውም። ለሚያስፈልግህ ሁሉ አንድ ቁልፍ ሰጥቶሃል፤ ኢየሱስ ክርስቶስ። በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያስፈልግህን ሁሉ ይሞላ ዘንድ የእግዚኣብሔር ፈቃድ ነው። ሲሰጥህና ሲሞላህም የጠየቅኸውን ያህል ብቻ ሳይሆን የባለጠግነቱን ያህል ነው። ምንም የማይጎድልበት ባለጠጋው አምላክህ ኢየሱስ ክርስቶስን ያዝና የሚያስፈልግህን በረከት ሁሉ ወስደህ ሞሞላት ትሻለህ? #tesfa #hope Follow Tesfa on: Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads