ar
Feedback
STAKE COMPUTER™️

STAKE COMPUTER™️

الذهاب إلى القناة على Telegram

💻 Brand new laptops 💻Dubai used laptops 💻Europe used laptops 💻Gaming laptops Accessories importer whole sale and retail seller ⚠️ADDRESS-ETHIOPIA ADDIS ABABA,MEGENANGA,ZEFEMESH GRAND MALL 3rd floor no.

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام STAKE COMPUTER™️

تُعد قناة STAKE COMPUTER™️ (@stakecomputer) في القطاع اللغوي الإنكليزية لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 10 714 مشتركاً، محتلاً المرتبة 11 434 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 3 107 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 10 714 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 09 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -190، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -4، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 1.79‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 0.64‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 192 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 69 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.
  • الاهتمامات الموضوعية: يركز المحتوى على مواضيع رئيسية مثل processor, intel, ssd, battery, megenagna.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
💻 Brand new laptops 💻Dubai used laptops 💻Europe used laptops 💻Gaming laptops Accessories importer whole sale and retail seller ⚠️ADDRESS-ETHIOPIA ADDIS ABABA,MEGENANGA,ZEFEMESH GRAND MALL 3rd floo...

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 10 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

10 714
المشتركون
-424 ساعات
-357 أيام
-19030 أيام
أرشيف المشاركات
​​🔥 ከቤቱ በታች ያለው ድብቅ መቃብር ቤት 📖 👇 ሰናይት እና ሰሚራ 🌹 ክፍል 3⃣ ✍ ደራሲ ጥላሁን ተስፋዬ . . . እሄን ግዜ በልሁ "እዚህ ቤት ሰራተኛች ሲገቡ እንጂ ሲወጡ አይቼ አላውቅም" ያለኝ ነገር ተትዬ መሰወር ጋር ተገናኝቶ በመላ ሰውነቴ ትኩሳት ከፍርሀት ጋር ለቀቀብኝ ፓሊሶቹ ስራቸውን አገባደው ለምሄድ ሲሰናዱ አየሁና እየተጣደፍኩ ወደ በልሁ ጋር ሄጄ እኔ ይችን ቀን እዚህ ቤት ከማድር ወጥቼ መንገድ ላይ ብሞት ይሻለኛል ትለው "እናትሽንስ ታናሽ ወንድምሽንስ አታዝኝላቸውም ባክሽ ተይ አታድርጊው " አለኝ ክንዴን ጨበጥ አርጎ ።እሄውልሽ ሰንዬ እኔን ምን እንዳሉኝ ልንገርሽ አንድ ስተት ብትፈፅም በነዚህ ላይ እንደፈረድክ ቁጠረው ብለው ያሉበትን ቦታ እንደሚያውቁ ቀያቸው ድረስ ሄደው ያነሱትን የቤተሰቦቼን ፎቶ ነው አምጥተው ያሳዩኝ ታናሽ እህቴ አድጋ ውሃ ለመቅዳት መብቃቷን እንኳን ያየሁት ተነ እንስራዋ አንስተው ባሳዩኝ ፎቶ ነው ሰንዬ ያንችንም ማወቃቸው አይቀርም ተይ ይቅርብሽ ቀን እስኪያወጣን እንጠብቅ መሞት ካለብንም ቤተሰቦቻችን ታይነኩ ብቻችንን እንሙት " ሲለኝ ምን እንደሆን እንጃ ተላይ እስከታች ሲወረኝ ተስማኝ አይኖቼ በእንባ እንደተሞሉ ፓሊሶቹ ግቢውን ለቀው ወጡ... የፍርሀት ፣ የመገፋት እና የመበደል ስሜት መላ አካላቴን አላወሰው ተከትለሻቸው እሩጪ እሩጪ አምልጪ እራስሽን አድኚ የሚል ስሜት ወተወተኝ በር በሩን ስመልከት ሆዱ ነገረው መሰል በልሁ ተንደርድሮ በሩን ጠረቀመው እንኳን እዛ ቤት ተመልሼ ልገባ ዞሬ ማየት አስፈራኝ በሀገሬ ውስጥ ከሰው ጋር የምኖር አልመስልሽ አለኝ ተዛ ግቢ ውጪ ሰላም ሰው ሳቅ ደስታ በጥቅሉ የተለመደ የሰው ኑሮ መኖሩን ውስጤ አልቀበል አለኝ አርቀው የወረወሩት የማይፈለግ ጥቅም አልባ እቃ የሆንኩ መስሎ ተሰማኝ የሚያስብልኝ ወገን ዘመድ ቤተሰብ የለለኝ ከሰው እንዳልተፈጠርኩ መኖሬም መሞቴም በሰው ፍቃድ የሆነ ሳልሞት ደራሽ ብሞት ወቃሽም አልቃሽም የሌለኝ ተስፋ ቢስ ሰው አልባ መሆኔ ሲታወቀኝ ለዚህ የዳረገኝን ድህነቴን ጠላሁት ። መፈጠሬን ረገምኩት። ተንሰቀሰቅሁ። በልሁ ሊያባብለኝ ሞከረና ለቅሶዬ ብሶቱን ፈንቅሎ አወጣው መሰል ይንሰቀሰቅ ጀመር ። ወደ ቤት ተመልሼ ለመግባት እግሬ አልላወሲ ቲለኝ እዛው ቁጭ እንዳልሁ በሉሁ ወሃ "እንኪ ፊትሽን ታጠቢና ግቢ ደሞ እትዬ እዚህ ጋር ተቀምጠሽ ታዩሽ ጥሩ አይመጣም ሰንዬ " እሺ እስከመቼ በልሁ እስከመቼ ነው ታለ ወንጀላችን እንደ ወንጀለኛ ታስረን የምንኖረው? "እንጃ ሰንዬ " እንጃ....እንጃ አልከኝ በልሁ "ታድያ ምን ልበል ሰንዬ " የህል ክፉ አጃ የሳር ክፉ ሙጃ የነገር ክፉ እንጃ "አለ ያ ገር ሰው እባክሽ ተነሽ ሰንዬ እዚሁ ቁጭ ብለሽ እትዬ እንዳይመጡ"የሉም አልኩህ እኮ። "ፓሊሶቹ ያልደረሱበት መሸ መሸሸገያ ቢኖራቸው እንጂ ወየት ይሄዳሉ ሰንዬ?"ፈራሁ በልሁ እኔ እዛ ቤት ተመልሼ አልገባም። ለምኖ ወደ ቤት አስገባኝና ጠጋ ብሎ " በርታ በይ "ብሎኝ ወጣ ቀኑ ደንገዝገዝ ብሏል እቤት ውስጥ መቀመጥ ስለፈራሁ ሳሎኑ ደጃፍ ላይ ተቀምጬ በልሁን በቅርብ ርቀት እያየሁት ትንሽ እንደቆየሁ ትከሻዬን ከበደኝ ደሞ ተጠሎት ቤቱ ውስጥ የሆነ ድምጥ የሰማሁ መሰለኝና ልቤ በላይ በላይ መምታቷን አባሰችው ብድግ አልኩና ወደ በልሁ ተጠግቼ ተቤት ውስጥ ድምጥ ሰማሁ አልኩት "ስለፈራሽ ነው ሂጂ ሰንዬ እዛው ሁኚ" አለኝ ተመለስኩ ተመቀመጤ በፊት ወደ ቤቱ ውስጥ አየት ታረግ እትዬ ፀጉራቸው ተንጨብርሮ ጭራቅ እንደመሰሉ ሳሎኑ መሀል ላይ ተገትረው አፈጠጡብኝ ።ተይህ ቡሀላማ ምኑን ላውጋችሁ ..እንዳልጮህ ፍርሀቱ አፌን አሰረኝ ፣እንዳልሮጥ ድንጋጤው ጉልበቴን ከዳኝ ትንሽ ቆይታ ልቤም ተወችኝ..እራሴን መሆን ተስኖኝ ተዝለፍልፌ መሬት እንደደረስኩ እትዬ "አንቺ ምን ሆነሻል" አሉና አምባረቁብኝ ። ተንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው ሰመመን ውስጥ ሆኜ ምድር ምድሪቱን ትመለከት በልሁ ተወደ ጀርባዬ እየሮጠ መጣና ..."እይይ እቺ ሚስኪን ልጅ እንዲሁ እትዬ ክፉ እንዳይገጥማቸው ብላ ትትጨነቅ ነው የዋለችው አይዞሽ እትዬ መለኛ ናቸው መላ አያጡም ክፉ አይነካቸውም ብላት አልሰማኝ አለች ወይ ለርሶ ያላት ፍቅር እትዬ እንዲሁ ትታለቅስ ነው የዋለችው "በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተደምሮ "አለ ያ ገር ሰው ልጅቱ ትትታይም ድንጉጥ ነገር ነች የፖሊሶቹ መምጣት የርሶ መጥፋት ጭራሽ ድንብርብሯን አወጣው አሁን ድንገት ስታዬት ደንግጣ ነው ሰላም ትሆናለች እትዬ አይጨነቁ" "ቆይ እሷ ምን ለጉማትና ነው አንተ አስረጂ የሆንከው?ምን ሆነሻል እያልኩሽ እኮ ነው!? አሉ አሁንም እየጮሁ ግንባሬን በጣታቸው በመግፋት ታቀረቀርኩበት ቀና እያረጉኝ። በልሁ እኔን ለማዳን የባጥ የቆጡን ቲቀባጥር ግዜ ስላገኘሁ ተድንጋጤዬ ተመልሼ ነብስ ዘርቼ ትለነበር ...እትዬ ሁሉንም ነገር እሱ ተናግሮታል በቃ አንድ ነገር የሆኑ መስሎኝ ደንግጬ ነው አልኩ አፌን እሬት እሬት እያለኝ ፍታቸውን ላለማየት ያይኔን ቆብ እንደከደንኩ ። "በይ ተነሽና ወደ ክፍልሽ ገብተሽ አረፍ በይ " ክፍሌ እንደገባሁ ሙሉ በሙሉ እራሴን አረጋግቼ ስለተፈጠረው ነገር አሰላስል ጀመር ።እዛ ጠሎት ቤት ውስጥ አንድ ሚስጥር እንዳለ ልቤ ጠረጠረ ።እዚህ ቤት ተተቀጠርኩ ጀምሮ ያላጠዳሁት የቤቱ ክፍል የለም ጠሎት ቤቱን ግን ላጥዳሎት ብዬ ብዙ ግዜ ብጠይቅም አንድም ቀን እንዳጠዳው ፈቅደውል አያውቁም ። ብዙ ግዜ ደግሞ ልጠልይ ብለው ገብተው ቶሎ አይወጡም። አንዳንዴ ደግሞ ድንገት ስልካቸው ቲጠራ መጣሁ ይሉና ስልኩን ተዘጉ ቡሀላ ቆየት ብለው የሚገቡት እዛው ጠሎት ቤት እንጂ ሌላ ቦታ አይሄድም። ተዚህ በፊት ልብ ታልላቸው በዋዛ ያለፍኳቸው አጠራጣሪ ሁኔታዋች ሁሉ በየተራ በጭንቅላቴ መሰግሰግ ቲጀምሩ የዛን ጠሎት ቤት ሚስጥር ለማወቅ ወገቤን አጥብቄ ተነሳሁ ። ተክፍሌ ውስጥ አድፍጬ እትዬ እስቲተኙ መጠባበቅ እንደጀመርሁ ...ተመተኛታቸው በፊት ወደ ክፍሌ ቲመጡ ኮቴ ሰማሁ የተኛሁ መስዬ ተጠቀለልሁ ።ክፍሌን በርግደው ገቡና "ሰናይት አንቺ ሰናይት "ብለው ቲጣሩ ድምጤን አጥፍቼ ዝም አልኳቸው ተመልሰው ቲወጡ ግን "በይ ተኚ ነገ እናወራለን ተዛ ዘበኝኛ ጋር ምን ስትይ እንደገጠምሽ ቆይ "በሬ ከደነበረ ደሀ ካመረረ ሀገር ተሸበረ" አለ ገብረ ማርያም "የናንተ አንድ መሆን ምቾቴን ነስቶኛል ቆይ እማረገውን እኔ ነኝ የማውቀው" እያሉ ቱያጉረመርሙ ሰማሁና በድንጋጤ በተኛሁበት ደርቄ ቀረሁ። ምን ሊያደርጉ አስበው ይሆን ፈጣሪዬ እኔ ወይስ በልሁን ነው ሁለታችንንም ሊያጠፉን ነው ተመሞቴ በፊት ዛሬ የዚህን ጠሎት ቤት ጉድ ተመልክቼ ያኔ ሁሉም ነገር ይለይለታል እትዬ እንኳን ምን እንዳሰቡ በጆሮዬ ሰማሁ እኔና እርሶ ተንግዲህ እዚህ ቤት ውስጥ አይጥና ድመት ነን አልሁና እራሴን ለመከላከል የሚጠቅሙኝን ነገሮች አበጅቼ ጠሎት ቤት ለመግባት የትዬ ክፍል መብራት እስቲጠፋ መጠባበቅ ጀመርሁ.... 👉እንዲቀጥል Like ያድርጉ ➤ SHARE & JOIN @Yefker_Hayl @Yefker_Hayl @Yefker_Hayl @yefker_Hayl

​​🏘 ከመኖሪያ ቤቱ ስር ያለው ድብቅ መቃብር ቤት 📖 👇 ሰናይት እና ሰሚራ 🌹 ክፍል 2⃣ ✍ ደራሲ : ጥላሁን ተስፋዬ . . . ሀሎ...ሀሎ...ሀሎ ማን ልበል... ድምጥ የለም። እትዬ በጭንቀት ጆሮዬ ላይ ወደ ለጠፍኩት ስልክ ጠጋ አሉና የደዋዩን ድምጥ ለመስማት ሞከሩ ...ሀሎ .....ማን ልበል ሀሎ.... አሁንም ድምጥ የለም እትዬ ተፊቴ ቆመው እንድዘጋው በምልክት አዘዙኝ ። እንደዘጋሁት ስልኩን በሁለት እጃቸው ወደ ላይ አነሱና ተመሬት ደባለቁት። ብትንትን አለ ቆሌዬ እንደተገፈፈ ቁጢጥ ብዩ ስብርባሪውን ትለቃቅም " ወድያ ወዲህ እየተንቆራጠጡ... "ወይኔ አለቀልኝ ! እነዚህ አውሬዎች! እቤት መኖሬን ሊያረጋግጡ ነው የደወሉት! ወይ ውርዴት! ፣ወይኔ ልጆቼ እሄን ጉድ አያሰማችሁ ፣እሄን ጉድ አያሳያችሁ አሁን ይመጣሉ እዛው ከባሌ ጋር ሊደባልቁኝ። ሽንቴ መጣ ሽንቴ መጣ " የታለ ሽንት ቤቱ" ...አሉና ወደ ሽንት ቤት ሮጠው ገቡ።ያ ሁሉ ደስታና ሳቅ የሞላበት ቤት በየቀኑ አመት በአል የነበረበት ቤት ሁሉ ነገሩ እንዲህ እንደጥዋት ጤዛ ረግፎ ጋሼ ታስረው እትዬ በጭንቀት እና በፍርሀት ተውጠው እንዲህ መሆናቸው አስደመመኝ የሳቸውን ሁኔታ ታሰላስል የኔ ድሀዋ እናቴ እምዬ በዛች በጭስ በጠቆረች ጎጆ ቤታችን ውስጥ ቂጣም ይሁን ቆሎ ቤት ያፈራውን ቀምሳ ፈጣሪዋን አመስግና የምትተኛው የሰላም እንቅልፍ ውል አለብኝ...ኧረ ደስታ የለለው ሀብትስ ጦስን እቴ ባንተ መንገድ ታልሆነ ሀብት አትስጠኝ ፈጣሪዬ። ትንሽ ቆይተው ተሽንት ቤት እንደተመለሱ " ሂጂ እስቲ አንቺ ... ለበልሁ ማንም ቢመጣ እና እኔን ቢጠይቅ እቤት የለችም በል ብለኊለች በይው" አሉኝና ወይ ጣጣ ሽንቴ መጣ አሉና አሁንም ወደ ሽንት ቤት ሮጡ።በሁኔታቸው ግራ እንደተጋባሁ በልሁ ጋር ትሄድ ...በልሁ ያችን ትንሽ ራድዬኑን ከፍቶ ተሷ ድምጥ በላይ እየጮኸ ያንጎራጉራል... ቆም ብዬ አደመጥኩት.. ወይ አንቺ ኢትዬጲያ ወይ ሀገሬ ሆይ ሌባም እንደ ንጉስ ይከበራል ወይ?። ወይ አንቺ ኢትዬጲያ ወይ አራዳ ሆይ ሀገር እንደ ዳቦ ይቆረሳል ወይ? እባክህ በርታልን አንድ አርገን አብይ። ምንድን ነው እምትለው ጃል "ተይኝማ ሰንዬ እቺ ትንሽ ራድዬን ምን የማታሰማኝ ጉድ እለ!"ለማንኛውም እትዬ እንዲህ ብለውሀል አልኩና መልክቱን ነገርኩት" ምነው ሰንዬ እትዬም የጋሼ እጣ ይደርስብኛል ብለው ፈርተዋል እንዴ? አይ ጋሼ እንደው ተዚህ ተተንደላቀቀ የፈረንጅ ኑሮ ወጥተው ያን እስር ቤት እንዴት ይለምዱት ይሆን ?" ""ሲሳይ ያለቀበት አንበጣ ተድንጋይ ላይ ያርፋል" አለ ያገሬ ሰው"እሱስ ልክ ብለሀል በልሁ አፈር አይንካኝ እንዳላሉ ውይ ጉድ ያ ሁሉ ክብር ያ ሁሉ ግርማ ሞገስ እንዲህ ይቅለል "ውሸታምና ስንቅ እያደር ይቀላል" አለች እምዬ። በል መልክቱን እንዳትረሳ አልኩትና ወደ ቤት ስመለስ እትዬ እቤት ውስጥ የሉም ።ተሽንት ቤት አልወጡ እንደሁ ብዬ ትንሽ ጠበቅሁ አልወጡም ።ወደ ሽንት ቤት ሄድኩ የሉም ተላይም ተታች ሁሉም ክፍል ውስጥ ብፈልግ የሉም ።ግራ ቲገባኝ አናት ላይ ወዳለው መናፈሻ ወጣሁ።አንድ እጃቸውን አፋቸው ላይ አንድ እጃቸውን ደሞ ሆዳቸው ላይ እንደጫኑ ቆመው ሞዶ ማዶውን ያያሉ ተላይ ወደ ታች እራሳቸውን እንዳይፈጠፍጡ ሰጋሁና ጠጋ ብዬ ቆም እንዳልሁ.. አንድ የፓሊስ መኪና እየከነፈች ስትመጣ እኩል እየናት።እትዬ ተመደንገጣቸው የተነሳ ፊታቸው ባንድ ግዜ ጨው እንደመሰለ ወደ እኔ ዞሩና የለችም በሉ የለችም በሉ እኔ ፀሎት ቤት ገብቼ እደበቃለሁ አሉና እየተደነባበሩ ቁልቁል ወረዱ ተከትያቸው ወረድኩ ፀሎት ቤት ሲገቡ እኔ ወደ በልሁ ሄድኩ። ወድያው መኪናዋ በር ላይ ደረሰች በሩ በሀይል ተንኳኳ... በልሁ ፈራ ተባ እያለ በሩን ቲከፍተው አንድ አማላይ ግርማ ሞገስ የተላበሰሰ ፓሊስ "ጤና ይስጥልኝ" አለና ወደ ውስጥ ዘለቀ ሶስት አምሳያዋቹ ተከተሉት ሁለት አምሳያዋቹ ደሞ ሳይገቡ እዛው ደጅ ላይ ቆመው ሰፈሩን መቃኘት ጀመሩ። "የቤቱ ባለቤት ይኖራሉ?" " ማንም የለም ጌታዬ" አልኩኝ ቀድሜ በልሁ ዝም ብሎ ቲያፈጥ። "አንቺ ምንድን ነሽ ለቤቱ?" "የቤት ሰራተኛ ነኝ ጌታው" "ማንበብ ትችያለሽ?" "አማርኛ ተሆነ " እንቺ ቤቱን ለመፈተሽ ከፍርድ ቤት የተሰጠ ማዘዣ ነው እዚህ ቀሪው ላይ ስምሽን ፃፊ ወይ ፈርሚ፣ አለኝ ፊቱ ሳይፈግ። እትዬ ዛሬስ አብቅቶሎታል አልኩ በሆዴ ወረቀቱን እየተቀበልኩ። ወድያው ሁለቱ ተከታትለው ወደ ቤት ሲገቡ ሁለቱ ደሞ ወደ ግቢው ጓሮ ዘመቱ። ጨነቀኝ "ወይ እትዬ ዛሬስ ማምለጫም የላቸው በልሁ".. "ዝም በይ ሰንዬ እኔ ደስ! ነው ያለኝ ።ምነው ተዚህም በላይ ጠንከር ብለው በተንቀሳቀሱና ቀኝ ገዢዎችን ከየተደበቁበት ለቃቅመው ነፃ ባወጡን።" "ነገር ከግቡ ጋሻ ከንግቡ"አለች እምዬ በልሁ ደሞ ምኑን ከምኑ አሳስበህ ከቀኝ ግዛት ጋር አቆራኘኸው እኔ ሀገሬ በቀኝ ግዛት እንዳልተያዘች ነው ሲነገር ያደመጥኩ። " ተይኝማ ሰንዬ "እሳት ቢዳፈን የጠፋ ይመስላል!" አለ ያገር ሰው" አንቺ ምኑን አይተሽ ስንት አመት የተዳፈነ ፍም ይዘን ነው የኖርነው" እሄውልሽ አባቴ ስለሀገሩ በኩራት ሲያወጋ ድሮ ምን ይለኝ ነበር መሰለሽ ተዚሁ ተጎረቤቶቻችን እንኳን ብንጀምር ... ኬንያ ፣ ሱዳን እና ሱማልያ በእንግሊዝ...ጁቡቲ በፈረንሳይ... ኤርትርያ ደሞ በጥልያን ቀኝ ተገዝተዋል። ባለኩሩ ህዝቧ የኔና ያንተ ሀገር ኢትዬጲያን ግን በቀኝ ግዛት ሳናስገዛ ነው ለናንተ ያስረከብነው ይለኝ ነበር ። እኔ ግን አሁን አሁን ሳስበው ለብዙ አመት በራሳችን ወገኖች በቀኝ የተገዛን ትውልዶች የሆንን ያክል እየተሰማኝ ነው እውነቴን ነው ሰንዬ ውቅያኖስ አቋርጠው ወንዝ ተሻግረው የሰው ሀገር በቀኝ ግዛት የያዙትስ ተዚህ የከፋ ምን ያደርጉን ነበር ከዚህ የባሰ ምን ይዘርፉን ነበር ሰንዬ?" እሱስ ልክ ነህ እኔ ምልህ በልሁ ...ፖሊሶቹ ፈትሸው እንደጨረሱ መውጣት እየፈለኩ ፈርቼ መቀመጤን አስረድቻቸው ጨርቄን ማቄን ታልል አሁኑኑ ተዚህ ቤት ውልቅ ልል ወስኛለሁ። "አረ ተይ! ሰንዬ አረ ተይ! አሁንም እዛው ነሽ "እፀድቅ ብዬ ባዝላት ተንጠልጥላ ቀረች" አለ ያ ገር ሰው"በልሁ ደሞ አወቅሁ ብለህ ተረቱን ታበዛዋለህ እውነትም የዛችን ልጅ ልብስ እና ጫማ ማዳበሪያ ውስጥ ታየህ ወዲህ ተለክፈሀል መሰል: አሁን እሄ ተረት ተኔ ውሳኔ ጋር ምን ያገናኘዋል አልኩት በሽቄ። "ሰንዬ እኔ ላንቺ አዝኜ እንጂ ሀሳብሽን መች ጠላሁትና ቢሆንልኝ አብሬሽ ውልቅ ብል ደስ ባለኝ የነዚህ ሰወች እጅ ብዙ እና ረጅም ነው እንዲህ ባደርግ እኔን ባያገኙ ዱላቸው ቤተሰቦቼ ላይ እንደሚያርፍ ስለማውቅ እንጂ!" ደነገጥኩ ቤተሰብ? እነሱን ደሞ የት ያውቋቸዋል? አልኩት። "የተዳፈነ ፍም ያልኩሽ እሄን በደልም አይደል እሄውልሽ...."ብሎ ተመቀጠሉ በፊት ቆይ በልሁ በምዬ ሞት ትመለስ ታወጋኛለህ ሰዎቹ ገብተው ቀሩኮ ምን ላይ እንደደረሱ ተመልክቼ ልምጣ ብየው ወደ ቤት ትገባ ቤቱን እብድ የዋለበት አስመስለውታል ያልተነሳ እቃ የለም የትዬ ጠሎት ቤትም በሩ ተከፍቷል እትዬን ወዴት አስቀመጣቸው ይሆን ግራ ተጋባሁ።ወደ በልሁ ሮጬ ተመለስኩና እትዬ ጠሎት ቤት የሉም አልኩት እሱ ተኔ በላይ ደንግጦ ደርቆ ቀረ "አንድ ጥግ አስቀምጠዋቸው እንዳይሆን ሂጂ እስቲ በደንብ አጣሪ" አለኝ። ገብቼ ምንም ታይቀረኝ ፈልኳቸው የሉም ምን ውስጥ ገቡ? 👉ቀጣዩ ክፍል እንዲለቀቅ Like👍 ያድርጉ ♥️Share & join

​​​​ጉርሻ እንደጎረሱ ተግቢ ውጪ የመሂና ክላክስ ሰሙና ተነምግባቸው ተነስተው የመስኮቱን መጋረጃ በመግለጥ ወደ ግቢው ከተም በሪ ሲያጮልቁ ድንገት አጠገባቸው ያለው የቤት ስልክ ጮኊባቸው በስልኩ ደንግጠው ሰሀኑ ከነምግቡ ከእጃቸው ላይ ወደቀ ተንደርድረው አጠገቤ ደረሱ። ተፋጠጥን ቃል ማውጣት ተሳናቸው መሰል በአንገት ምልክት ስልኩን እንዳነሳው አዘዙኝ አነሳሁ ...ሀሎ...ሀሎ.. 👉እንዲቀጥል 250Like👍 ያድርጉ.. ♥️Share ለወዳጅዎ ❤️የፍቅር 🌺 🌺 ሀይል ❤️

🏬 ከትልቁ ቤቱ ስር ያለው ድብቅ መቃብር ቤት 📖 👇 ሰናይት እና ሰሚራ 📚 ክፍል 1⃣ ✍ደራሲ : ጥላሁን ተስፋዬ . . ‼️Notice : በታሪኩ ላይ የፊደል ስህተት የለውም...ሰናይት የምትናገረው የገጠራማ ክፍሉን የአናጋገር ዘይቤ የተከተለ ስለሆነ..የተዋቀረውም በዚሁ ዘይቤ ነው ስለሆነም የፊደል ስህተት እንዳልሆነ ከወዲሁ እንድትገነዘቡ ነው። 👉ሌላው attach ያደረግነው ማጀቢያ ፎቶ ከታሪኩ ጋር ህብረት የሚፈጥር በመሆኑ እንጂ ታሪኩ ላይ ያለው ትክክለኛው ቤት አይደለም።.. መልካም ንባብ👇👇 . . ሰናይት እባላለሁይ ትውልዴ እዚሁ ሸዋ አንድ የገጠር ቀበሌ ውስጥ ነው። እትዬ ቤት በቤት ሰራተይነት ከተቀጠርኩ 5 አመት አልፎያል ነገር ግን አንድም ቀን ቤተሰቦቼየን እንድጠይቅም ከግቢ እንድወጣም ተፈቅዶልይ አያውቅም ። የመጀመሪያ ቀን አንድ ደላላ ወደ እትዬ ቤት ሲያመጣይ ወደ ውጪም ወደ ሹፌሩም በማያሳይ ድፍንፍን ያለ መሂና ነበርና ከሰው ጋር አብሬ መኖሬን እይ የት እንዳለሁ አላውቅም ነበር.. ያለሁት አዲስ አበባ መሆኑን የነገረይ እይሁ ቤት ውስጥ በዘበይነት ተቀጥሮ የሚሰራው በልሁ ነበር። ሆኖም የትዬ ቤት ምቾትና የተንደላቀቀ ኑሮ ሌላውን አለም ያስረሳልይ።እንኳን አምስት አመት አምስት ወር የሆነይ ያክል ተሰምቶይ አያውቅም። ተቅርብ ግዜ ወዲህ ግን የትዬ ቤት የአንድ ቀን ሂወት እንደ አመት የረዘመ ሆኗልይ። እትዬ ሁለት ልዦች ቢኖራቸውም ቅሉ ሀገር ውስጥ አይኖሩም ባለቤታቸው የደለበ ስልጣን የነበራቸው ቲሆን ምህንያቱ ባይገባይም ከ ወራት በፊት እቤት መዋል ዥመሩ።ለእረፍት ነው እንዳይባል አርፈው አያውቁም በፊት ያልነበረባቸውን ባህሪይ ሲጋራውን በላይ በላይ እየማጉ ግቢ ውስጥ ወዲህ ወዲያ እየተንቆራጠጡ ስልክ ቲደውሉና ቲያወሩ ነው የሚውሉት.. አቤት የስልክ መአት!ቲላቸው ደግሞ ቀንም ማታም እቤቱ ማማ ላይ ያለው መናፈሻ ላይ ይወጡና እሚጠብቁት ሰው ያለ ይመስል አንገታቸውን ወዲህ ወድያ እያመላለሱ ሰፈር መንደሩን ሲቃኙ ይውላሉ ለምሳም አይገቡ። እትዬም ፀባያቸው ተለዋውጧልይ፣ ያ ሳቂታ ፊታቸው ጠቁሯል።በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ አንድ ቀን በጥዋት ፓሊሶይ ድንገት ግቢውን ወረሩት ወድያው ምንም ሳያወሩ ጋሼን እያንከወከው ወሰዷቸው ያኔ የትዬ ጭንቅት ወደ እብደቱ ታይጠጋ አልቀረም። እንቅልፍ እሚባል ነገር ከኧእምሮቸው ተነ ጭራሹ ጠፋ ቀን እና ሌት መቆሚያ መቀመጫ አሳጡይ..ተሳቸው ጭንቀት እና ፍርሀት ጋር አብሬ መጨነቅና መፍራት ሰለቸይ ያንን ቤት መልቀቅ ፈለኩይ ታድያ ቤቱን ለመልቀቅ ማሰቤን ለእትዬ ተመናገሬ በፊት ለዘበኛው ለበልሁ ላማኽረው አሰብሁና አንድ ቀን ወደ ማደሪያው ጠጋ ብዬ የመልቀቅ ሀሳቤን አወጋሁት። በድንጋጤ ጋደም ታለበት በርግጎ ተነሳ።ምነው ምን አስደነገጠህ? ትለው... "ይቅርብሽ የኔ እህት እኔ ልምከርሽ ይቅርብሽ እኔ ተወጣትነቴ ዥምሮ ለብዙ አመት እይህ ቤት በዘበኝነት አገልግያለሁ ።ግን የይህ ቤት ሰራተኞች ቲገቡ እንዢ ቲወጡ ተመልኽቼ አላውቅም " ምን ማለትህ ነው ?በቃ እሄው ነው ትለዚህ ቤት ሚስጥር ታወቁ ቡሀላ መፈናፈን እህህህም! አለ በልሁ ። ምናልህ? እልሁት። "አበቃሁ!" አለ። ስንት ሰራተኛ ገብቷልይ? እስታሁን?ትለው " ኧረ ተዤም ጣቶች የላቁ ናቸው አለኝ ደነገጥሁ ታድያ ቲወጡ ታላየህ የት ገቡ? "እንዣ እሱ የኔም የእድሜ ይፍታ ጥያቄ ነው ብቻ ይቅርብሽ እሄውልሽ አንዳንዶቹ እንዲህ እንደ አንቺ መውጣት እንደፈለጉ መጥተው ያማኽሩኛል ከቀናት ቡሀላ ወጡ ቲባል እንዢ ቲወጡ አይቼ አላውቅም እሄው እንደምታይኝ ቀንም ሌትም ከበር ላይ አልነቃነቅ!"እንዲህ ቲለኝ በጣም ነበር የደነገጥኹት ቀጠለና "ቆይ አንቺ ምን ሆነሽ ነው? የድሀ አምላክ ፈጣሪ እስቲፈታሽ ቁጭ እማትይ!? "አለኝ። እኔ ወድጄ አልነበረም ለመውጣት የወሰንሁት የትዬ ፀባይ እና ሁኔታ ባንድ ግዜ ተሰው ወደ አውሬነት በመቀየሩ እንዢ በየእለቱ ቀን እና ሌት ድንገት ይነሱና ያዙኝ ፣የፀሎት ቤቱን በር ከፈቱት እንዴ? ፀጉሬን ቆረጡት፣ ታልጋው ጋር አሰሩይ፣ ሁሉንም በር ምን ከፈተው? ሆኗልይ ወሬያቸው ምንም ታይፈጠር... ጋሼ ከታሰሩ ቡሀላ የትዬ ነገረ ስራቸው ሁሉ ያስፈራል ያስጨንቃል.. አሁን ለታ ለስንት አመት ግድግዳው ላይ የተሰቀለው ሰአት የለመደውን ቆጠራ ቀጥሏል ቃ....ቃ......ቃ.... ቃ ይላል ወድያው እትየ ተፈዘዙበት አለም ተመለሱና " እሄ የግድግዳ ሰአት ድምፁ ሊያሳብደኝ ነው አውርጄ ሳልከሰክሰው አውርጂና አጥፊልኝ! አሉኝ የጆሮዬ ታንቡር እስቲላቀቅ እያምባረቁብኝ።የታዘዝኩትን ፈፀምኩ ። "እሄውልሽ እህት አለም ሰንዬ" ወዬ በልሁ... "ወጣም ወረደም እንደወንድምነቴ የምመክርሽ አሰናብቱኝ የሚል ቃል ታፍሽ እንዳይወጣ ነው" እኔ እንጃ በልሁ እኔ በጣም ከብዶኛል የሳቸው ሁኔታ የቤቱ ጭር ማለት ብቻ... "ደሞ ቤቱ ምን ሆኖ ነው ጭር ያለው ጋሼ ስለታሰሩ ማለትሽ ነው?" ኧረ ምን የጋሼ መታሰር እትዬ ምን ያህል ሚድያ መከታተል ይወዱ እንደነበረ ታውቃለህ?እንዲያ በተለቀቀ ዘፈን ሁሉ ተነስቼ ካልጨፈርኩ እንዳላሉ ሌላው ቢቀር አንተን እንኳን ስንቴ ነው ና ያገርህ ዘፈን መጣ እያሉ በስክስታ ሲንጡህ የከረሙት አሁን ድምጡንም ምስሉንም ላይናቸው ጠሉት እንደው ይገርማል እኮ ቁጭ ብለን በሰላም ፕሮግራም እየተከታተልን ብቻ ዜና እንደጀመረ ድንገት ልውጥውጥ አሉልህና ጆሮአቸውን በሁለት እጃቸው ግጥም አርገው "የዚህን ቴሌቪዥን ድምጥ መስማት ጨርቄን ሊያስጥለኝ ነው ተነሽ አጠፋፊና ነቃቅለሽ እዛው ካርቶኑ ውስጥ አስገቢልኝ ፡ ቲሉኝ ደነገጥኩ... እንዴ እትዬ የምሮን ነው ስላቸው አፈጠጡብኝ እንዳሉት አደረኩ ታድያ እስተመቼ በዚህ ሁኔታ ዘልቀዋለሁ "አሁንም እደግመዋለሁ ሰንዬ ምንም ይሁን ምን አርፈሽ መቀመጡ ነው ላንቺ ሚበጀው..እስካሁን እምልሽን ካላመንሽኝ አንድ ነገር ልንገርሽ ...ልጅቱ እዚህ ቤት ተቀጥራ ስትሰራ እንዳንችው ትቀርበኝ ነበር ድህነትን መልክ ቢያሸንፈው በሷ በተሸነፈ ነበር ምን ዋጋ አለው ልትወጣ እንደሆነ መጥታ ስትነግረኝ ተይ ይቅርብሽ አልኳት በጄ አላለችም። ልቀቁኝ ልሂድ አለቻቸው ። ከአንድ ቀን ቡሀላ ለቀቀች ተባልኩ ተሶስት ቀን ቡሀላ ለትዬ ሶኬት ላበጅ ወደ ትልቁ ቤት ገባሁ እትዬ ሰው ሊሸኙ ወጣ እንዳሉ ምን እንደመራኝ እንጃ ዘው ብዬ ተልጅቱ ማደርያ ስዘልቅ አንድ አፉ የታሰረ ነጭ ማዳበርያ ጥግ ላይ ቆሞ ተመለከትኩ ጠጋ ብዬ ቋጦሮውን ትፈታው ወጣች የተባለችው ልጅ ልብስ እና ጫማ ነው ። ጠላትሽ ክው ይበል ክው ብዬ ቀረሁ እሄው እስተዛሬ አእምሮዬም ጤነኛ አይመስለኝም" ሲለኝ ። በድንጋጤ ይሁን በፍርሀት ካጠገቡ ተፈናጥሬ ምንም መልስ ሳልሰጠው ወደ ቤት ስመለስ " አደራ ሰንዬ ያወጋነው በኔና ባንቺ ይቅር " አለኝ አንጀቴ ተንሰፈሰፈ እራሴን መሆን ተሳነኝ ሰውነቴ እየተንቀጠቀጠ ወደ ዋናው ቤት ስዘልቅ ሊነጋጋ ሲል እንቅልፍ የጣላቸው እትዬ አሁንም አልተነሱም ወደ ክፍሌ ገብቼ አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩና ከዚህ ቤት የምጠፋበትን መንገድ ማስላት ጀመርኩ። አረፋፍደው የተነሱት እትዬ ፊታቸው የተዝረከረከ ማድቤት መስሏል። ተጣጥበው እስቲወጡ ቁርስ አቀረብኩ ከመተጣጠቢያ ቤት ሲወጡ ወደ ቤት መግቢያውን ዋናውን በር ከውስጥ ቆለፉና ቁርሳቸውን ከጠረጴዛው አንስተው በጃቸው እንደያዙ ፈንጠር በሏ እተቀመጠችው ሶፋ ላይ ተቀመጡ። ሁለት

​​ ┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹✿🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄ 💜 ማፍቀር ሀጢአት አይደልም ⇨ ነገር ግን በፍቅር ስም በሰው ስሜት ላይ መጫወት ትልቅ ሀጢአት ነው ።  ┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹✿🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄ ❤️♡ ከተብቃቃህ ትንሹ ብዙ ነው ⇨ ከተስገበገብክ ብዙው ትንሽ ነው ⇨ ከወደድክ ሩቁ ቅርብ ነው ⇨ ከጠላህ ቅርቡ ሩቅ ነው ።   ┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹✿🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄ ♥️😍ካንቺ የበለጡ ቆንጆዎች እንዳሉ አውቃለሁ ... ⇨ ነገር ግን የወደድኩሽ በአይኔ ሳይሆን በልቤ ነው ✍•┈┈•••┈┈•🌹•┈┈•••┈┈• ❤️የሚወድህ ሰው ለራሱ ማድረግየማይችለውን ነገርአንተን ስለሚወድህናስለምያፈቅርህ ብቻለአንተ ግን ያደርገዋል ••┈┈• ♡ ••┈┈•••┈┈•  ┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹✿🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄ 🌹ሁለት ከባባድ ጀግኖች ትግስትና ጊዜ ናችዉ  ┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹✿🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄   ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈ ⚜የመፈጠራችን ዋና ዓላማ ሌሎችን ለመርዳት ነው፤ መርዳት ካልቻልን ግን ቢያንስ አንጉዳቸው። ┈┈┈◦◎ ◎◦┈┈┈ ┈┈┈••✦✿✦••┈┈┈ ⚜ጨለማን ጨለማ አይገልጠውም፣ ብርሃን እንጂ፤ ጥላቻንም ጥላቻ አይፍቀውም፣ ጥላቻን ማጥፋት የሚችለው ፍቅር ብቻ ነው። 🎈በፍቅር ሀይል ተዘጋጅቶ የቀረበ🎈

​​​​┄┉✽̶🌺✿ምኞትና❤️ፍቅር✿🌺̶̥✽̶┉┄        ▬▬❁ ክፍል አስራ ስምንት❁▬▬         የመጨረሻዉ ክፍል          ✍...ረድኤት ይበልጥ ግራ ተጋባች፡፡ እንደምንም ስልኩን አወራችና ከጨረሰች ቡኃላ ..."ኤዲ ከወለደችማ ቢኒ አያገባኝም ማለት ነዉ?" እያለች ታስብ ጀመር፡፡ "አዎ ቢኒ አያገባኝም፡፡ እኔ ደግሞ በጣም አፈቅረዋለሁ፡፡ እሱን ማጣት አልፈልግም፡፡" እያለች ብቻዋን ታወራ ጀመር፡፡ረድኤት በጣም ተጨንቃለች፡፡ የፍርሃቷ ተጋሪ፤ የደስታዋ አጋፋሪ እማማ በለጡ ናቸዉ፡፡ ስልኳን አነሳችና ወደ እናቷ ደወለች፡፡ ከወዲያኛዉ መስመር ስልኩ መጥራት ጀምሮ ብዙም ሳይቆይ እናቷ ስልኩን አነሱና... ..."ሄሎ ረዲዬ" አሉ እማማ በለጡ ..."ሄሎ እማዬ ሰላም ነሽ" የሆነ ነገር እንደሆነች ድምፅዋ ያሳብቃል፡፡ እማማ በለጡ ወዲያዉ ነዉ የገባቸዉ፡፡ ..."ደህና ነኝ ልጄ ... ምን ሆንሽብኝ የኔ ልጅ?" ብለዉ ጠየቋት፡፡ ልጄን ምን አግኝቶብኝ ነዉ ብለዉ እየፈሩ ..." አይ እማዬ ምንም!" ረድኤት እምባ እየተናነቃት ነዉ፡፡ ለእናቷ ልትነግር ነበር የደወለችዉ፡፡ ግን...እንዴትና ምን ብላ ትንገራቸዉ፡፡ ..."አመመሽ እንዴ ረዲ?" አሉ እማማ በለጡ፡፡ ..."ኧረ ከህመም በላይ ነዉ እማዬ" አለች፡፡ አዎ ቢኒያምን ማጣት ለሷ ከህመምም በላይ ህመም፤ ከስቃይ በላይ ስቃይ ነዉ፡፡ ምክንያቱም በጣም ታፈቅረዋለች፡፡ረድኤት ንግግሯ ለለቅሶም እየጋበዛት ነበር፡፡ እምባ ይተናነቃታል፡፡ ..."የኔ ልጅ ምን ሆንሽብኝ?" ..."ኤዲ እርጉዝ ነች እማ " ስትላቸዉ እማማ በለጡ ማመን አቃታቸዉ ልጃቸዉ አምርራ እንደነገረቻቸዉ ስላወቁ... ..."እልልል እልልልልልልልል..." ሲሉ ረድኤት እልልታቸዉን አቋረጠቻቸዉና... ..."እማዬ እኔንኮ መተዉ አይቀርም፡፡ አንቺ እልል ትያለሻ?" ብላ እናቷ ላይ ጮኸችባቸው፡፡ ..."አያግባሻ! ኤዲ ትዉለድ እንጂ ላንቺም ፈጣሪ ያለልሽ ይመጣልሻል!፡፡ ደግሞ የኔ ልጅ ላንቺም እኮ ተቀናቃኝ የሌለው ባል ቢሆን ነው ሚሻልሽ ቢኒያም አንቺን ማግባት የነበረበት ልጅ ስላጣ ነበር፡፡..." ብለዉ ንግግራቸዉን ሊቀጥሉ ሲሉ ረድኤት አቋረጠቻቸዉና ..."እንዴ እማዬ...እኔኮ ቢኒን አጥቼ መኖር አልችልም፡፡ አፈቅረዋለሁ... ከማለቷ ስልኳ በቂ ሂሳብ ስላልነበረዉ ዘጋባት፡፡የኤዲን ማርገዝ ስሰሙ እማማ በለጡና አባባ ሀብታሙ ከኤዲ እና ከቢኒ በላይ ተደስተዋል ፈጣሪ ይመስገን ኤዲ መውለድ ከቻለችማ ልጄ በእነሱ መሀል ገብታ ይሄን የመሰለ ፍቅር እንድታቀዘቅዘው አልፈልግም። ብለው ወሰኑ እማማ በለጡ ...ቢኒና ኤዲ ደስታቸዉ ይበልጥ ጎልብቷል፤ ፍቅራቸዉ ከስከዛሬዉ በላይ ፋፍቷል፡፡ ቢኒ ለኤዲ ያለዉ እንክብካቤ በጣም ጨምሯል፡፡ ለኤዲና ለቢኒ ዛሬ ልዩ ቀናቸው ናት፡፡ ኤዲ ከሆነ ያህል ቆይ በኋላ ቢኒን ስታየው እንደመተከዝ፤ ሀሳብ ዉስጥ ገብቶ እንደመፍዘዝ ብሏል፡፡ እንዲህ እንዲሆን ያደረገዉ ደግሞ የረድኤት ጉዳይ አሳስቦት ነዉ፡፡ ' አሁን ረድኤትን ምንድነው የምላት?እማማ በለጡንና አባባንስ ምን ልላቸው ነው? እያለ በውስጡ ይጨነቃል?' 'ቃሌስ' እያለ በሃሳብ ተጉዟል፡፡ አይኖቹ መጀመሪያ ካረፉበት እይታ ጨረራቸዉን አልነቀሉም፡፡የሚያያቸዉ ነገሮች ይበልጥ የእየፈዘዙ የረድኤት ጉዳይ እንደገና እያወዛ ሄዷል፡፡ ከተጓዘበት አለም የመለሰችዉ ኤዲ ናት፡፡ ..."ምን ሆንክ የኔ ፍቅር?" አለችዉ፡፡ 'የኔ ፍቅር' የምትለዋን ብቻ ነዉ የሰማት ..."ወዬ ኤዲዬ" አላት እንደመደንገጥ እያለ... "እ..." ፡፡ እሷም ጥያቄዋን እንዳልሰማት ስላወቀች ..."ምን ሆነክብኝ ነዉ እንደዚህ የምታስበዉ?" አለችና ጥያቄዋን ደገመችለት፡፡ እንዳለፈዉ ጊዜ ሊደብቃት አልፈለገም፡፡ ሁሉንም ነገር ከኤዲ ጋር ተነጋግሮ መወሰን እንዳለበት አምኗል፡፡ ..."ምን... የረድኤት ጉዳይ ትንሽ አሳስቦኝ ነዉ" አላት ፈራ ተባ እያለ ..."የረዲ ጉዳይ ምን? የሷ ጉዳይ ምን ያስጨንቀሃል?" ብላ እየጠየቀችዉ ወደሱ ቀረብ አለችና ከጎኑ ቁጭ አለች፡፡ ..."ኤዲዬ ... አሁን እንዴት ብዬ ነዉ መጋባት እንደማንችል የምነግራት?" አላት፡፡ ..."የኔ ፍቅር ረዲንማ ማግባት አለብህ" አለችዉ፡፡ ..."ለልጅ ብዬ አልነበር የማገባት ያዉ አሁን ደግሞ ዉዷ ሚስቴ በሆዷ ያብራኬን ክፋይ ይዛልኛለች!" ."አየህ ውዴ...(በትኩረት እየተመለከተችዉ ነበር) መጀመሪያም ተሳስተን እንደነበር አሁን ነዉ የገባኝ" አለችዉ፡፡ ..."እንዴት ዉዴ? ምንድን ነዉ የተሳሳትነዉ?" አላት እሱም ወደሷ ዞወር እያለ፡፡ ኤዲ ደግሞ ይበልጥ ወደሱ እየተጠጋች እጆቿን ትከሻዉ ላይ ጣል እያረገች... ..."መጀመሪያም እሄን ያህል ዓመት ታግሰን በችኮላ መወሰን አልነበረብንም ትንሽ መታገስ ነበረብን" አለችው፡፡ ...መጥፎ እንዳልሆንክ አዉቃለሁ፤ ስለ ጥሩነትህ የማወራልህ፤ ስለ መልካምነትህ የምመሰክርልህ ሚስትህ ነኝ ስለዚህ ረዲን አግባት!!!! እሺ ፍቅሬ....!!!" አለችዉ፡፡ በቃ የኔ ፍቅር ሁሉንም ነገር ነገ እናወራለን ብሏት ዛሬ የደስታችን ቀን ናት በቃ አሁን እንተኛ አላትና ተኙ፡፡ ..." ረድኤት እንቅልፍ እንቢ ብሏት ስትገላበጥ ተነስታ ቁጭ ስትል ምንም እንቅልፍ በዓይኗ ሳይዞር ሊነጋ ነው፡፡ሊነጋጋ አከባቢ አንድ ነገር አሰበች፡፡ለምን?የሰው ትዳር ውስጥ ገብቼ ፍቅራቸውን ለምን?አቀዘቅዘዋለው ግን ለምን?ለኔ ያለውን ፈጣሪ ልክ እንደ ቢኒ ዓይነት አፍቃሪ እንዲሰጠኝ መለመን ስችል፡፡  እያለች ብዙ አሰበች መንጋቱ አይቀርምና ነጋ ልክ እንደነጋ ብዙም ሳትቆይ ረድኤት ለቢኒያም ደወለች፡፡ ስልኩን አንስቶ ረድኤትን ማዋራት ጀመረ ..."ሄሎ ረዲ...." ..."ቢኒ ሰላም ነው"አለችው፡፡ ..."ደህና ነኝ..."ማታ እኔና ፈቲ ስላንቺ" ብሎ ሳይጨርስ" ረዲ... "ሄውልህ ቢኒ ምንም እንኳን ባንተ ፍቅር ብከንፍም ግን ያ እንደዛ ምትሳሱለትን የሞቀ ፍቅር በመሃላችሁ ገብቼ ማቀዝቀዝ በጭራሽ አልፈልግም እኔ ባንተና በኤዲ ፍቅር በጣም ነው የምቀናው ባይሆን ለኔም እንዳንተ አይነት ባል ፈጣሪ እንዲሰጠኝ ለምኑልኝ"አለችው፡፡ ..."ረዲ ምንም ሆነሻል ቤቲስ እነ እማማ ና አባባስ ምን ይሉኛል፡፡አላት ..."አይ ቢኒ አታስብ ለእማዬም ለአባዬም እኔ አስረዳቸዋለው እዚህ ጊቢ ውስጥ ከአንዱ ጋር ፍቅር ይዞኛል ብዬ እነግራቸዋለው፡፡ ደሞ እነሱም የሚፈልጉት እሄንኑ ነው በጣም ነው ደስ ሚላቸው አታስብ አለችውና ኤዲን ሰላም በልልኝ ብላ ስልኩ ዘጋችው። ቀናት በቀናት ወራት በወራት እየተተኩ የኤዲ መውለጃ ጊዜም ደረሰ ኤዲም ቆንጂዬ በጣም የሚያምር ልጅ ወለደች<< በፀሎት>> አለው ስሙን ቢኒ። ቢኒና ኤዲ በጣም ደስተኞች ናቸው። ከ 4 አመት ቡኃላ... ...ረድኤት ተመርቃ ምን የመሰለ ለአይን እንኳን የሚያሳሳ ባል አግብታ በፍቅር ኑሮዋን ጀምራለች።   ፈጣር ሁሌም ከምትወዱት አይለያቹ።                                         ተፈፀመ ምኞትና❤ፍቅር የተሰኘው የፍቅር ታሪክ ዛሬ በዚህ መልኩ ተጠናቀቀ በሌላ ታሪክ እስክንገናኝ መልካም ጊዜ ይሁንላቹ። 📚ታሪኩ የወደዳችሁት ና ሌላ 📚ታሪክ እንድንጀምር የምትፈልጉlike 👍 አድርጉልን፡፡ ♥️ተ♥️ፈ♥️ፀ♥️መ♥️      ✽̶🌺✿❁🌺🌺❁✿🌺̶̥✽̶ 💚የ❣ፍቅር 💛❣ሀይል❤️

​​​​┄┉✽̶🌺✿ምኞትና❤️ፍቅር✿🌺̶̥✽̶┉┄          ▬▬❁ ክፍል አስራ ሰባት❁▬▬ ፡ ....ከሶስት ወር ቡሃላ... ፡       ✍...ቢኒና ኤዲ አብረዉ በደስታ እየኖሩ ነዉ፡፡ ቢኒ ከረድኤትም ጋር አላቆሙም ይደዋወላሉ፡፡ ረድኤት ስትደዉል ቢኒን ብቻ ሳይሆን ኤዲንም ታዋራታለች፡፡ ሲያወሩና ሲጫወቱ በአንድ ወንድ ላይ የሚሻሙ ተቀናቃኞች ሳይሆኑ ምርጥ ጓደኛሞች ይመስላሉ፡፡ ይጫወታሉ፤ ይቀላለዳሉ፡፡ ረድኤት ከቢኒ ይልቅ ኤዲ ጋር ለረጅም ሰዓት ታወራለች፡፡ እንደዉም አንዴ እየቀለደች ቁም ነገር አስመስላ..."ኤዲዬ የወደፊት ባሌን ተንከባከቢልኝ እሺ!" አለቻት፡፡ ሁለቱም ያለማቋረጥ ለረጅም ሰዓታት ተሳሳቁ፡፡ ሂሂሂሂ...ክክክ....እሺ እንከባከብልሻለው በይ እንግዲህ በርትተሽ ተማሪ።አለቻት እሺ እደውልልሻለው ኤዲዬ ደህና ሁኝ ብላ ረዲ ስልኩን ዘጋችው። ...ቢኒያም ከስራ መጥቶ ወደ ቤቱ ሲገባ ኤዲ ቤት የለችም፡፡ "ኤዲ...ኤዲዬ!" እያለ ተጣራ ምናልባት ወደ ጓዳ ዉስጥ እንደሆነች ብሎ ኤዲ ግን የለችም ነበር፡፡ ወደ ዉጭ ወጣና እማማ በለጡን ተጣራና... ..."ኤዲ የት ሄዳ ነዉ?" አላቸዉ፡፡ እማማ በለጡም ..."እ...ሐኪም ቤት ሄዳ ነዉ፡፡" አሉት፡፡ ቢኒ ድንግጥ አለ፡፡ ..."መቼ? ምን ሆና? ምን አገኛት? እና አትከተሏትም ነበር ወይም አደዉሉልኝ?" እያለ ጥያቄ በጥያቄ ላይ እየደራረበ እማማ በለጡን የጠየቃቸዉን ጥያቄ የመመለሻ አፍታ አሳጣቸዉ፡፡ ይሄን ከማለቱ ወዲያዉ የግቢዉ በር ተከፈተና ኤዲ መጣች፡፡ በጣም አምሮባት፤ ከደስታ ብዛት ፊቷ ላይ ፀሐይ የወጣች እስኪመስል ድረስ አብርታለች፡፡ በረዶ የሚመስሉት ነጫጭ ጥርሶቿ ይፍለቀለቃሉ፡፡ ቢኒያም እንዳያት በጣም ደስ አለዉ፡፡ አሟት ነበር የመሰለዉ እሷ ግን እንደጨረቃ ፈክታ፤ ከፀሐይ አብርታ ብቅ አለች፡፡ ገና የነጋ መሰለዉ፡፡ ለሱ ንጋቱ ኤዲ ነች፡፡ ያለ ኤዲ ሁሌም ጨለማ ነዉ የሚሆንበት፡፡ ወደነሱ ቀረበችና..."ቢኒ ና ወደ ቤት እንግባ" ብላዉ እጁን ይዛ ሳበችዉ፡፡ ሰላምታ እንኳን አልሰጠቻቸዉም ነበር፡፡ ደስታ አስክሯታል፡፡ ቢኒም ምንም አልተናገረም ዝም እንዳለ ተከተላት፡፡ እማማ በለጡ ..."ኤዲዬ ደህና መጣሽ?" ፊቷን ሳታዞር ወደ ቤቷ እያመራች "አዎ እማማ" አለቻቸዉ፡፡ ዉስጧ የሆነ ነገር አለ፡፡ ለቢኒያም እስከምትነግረዉ ቸኩላለች፡፡ ቤት ከገቡ ቡኋላ እየተፍለቀለቀች በደንብ ሳቀች፡፡ ..."ኤዲዬ ምን ተገኝቶ ነዉ? ሆስፒታል አይደለም እንዴ የሄድሽዉ" አላት ቢኒ ..."አዎ ሆስፒታል ነበር የሄድኩት" አለችዉ ..."ምንሽን አሞሽ ነዉ?" ..."ሆዴን" ..."ወይኔ በፈጣሪ እንዴት አደረገሽ የኔ ፍቅር" ብሎ እጆቹን ሆዷ ላይ አድርጎ አይን አይኗን ያያታል፡፡ ኤዲ አሁንም ጥርስ በጥርስ እንደሆነች ናት፡፡ የምትስቀዉ እሱን ላለማስጨነቅ እንደሆነ አድርጎ ነዉ ያሰበዉ - ቢኒ፡፡ ..."የኔ ፍቅር" አለችዉ ድምፅዋን ለስለስ አድርጋ ..."ወዬ የኔ ቆንጆ" ..."የሆነ ነገር ልንገርህ?" ..."አዎ ንገሪኝ ፍቅሬ...ምንድን ነዉ እሱ?" እያለ ይመለከታታል፡፡ ..."የ ሶስት ወር እርጉዝ ነኝ!" አለችዉ፡፡ ቢኒ የሰማዉን ማመን አቃተዉ፡፡ አራት አመት እምቢ ብሏት እንዴት አሁን?? ..."እዉነትሽን ነዉ ኤዲዬ? ለማረጋገጥ ያክል ጠየቃት፡፡ ኤዲ ለአዎንታ እራሷን ነቀነቀች፡፡ ቢኒ ምድር ጠበበችዉ፡፡ ኤዲን እቅፍፍፍ አደረጋት፡፡ ሰዉነቷ ላይ ጥምጥም ብሎባት ይስማት ጀመር፤ ግንባሯን...፤ አይኗን...፤ ጉንጯን...፤ አፍንጫዋን...፤ ከንፈሯን...የቀረዉ የለም፡፡ በየመሃሉ እየጮኸ 'ፈጣሪ ሆይ ተመስገን' ይላል።ኤዲም ትፈለቀለቃለች፡፡ ደስታ ቢገድል ኑሮ ከቢኒ ቀድማ ትሞት ነበር፡፡ ከምንም በላይ ያስደሰታት መፀነሷ ሳይሆን ቢኒያም እንደዚህ ሲደሰት ማየቷ ነዉ፡፡ በርግጥ የደስታዉ ምንጭ ማርገዟ ቢሆንም...፡፡ቢኒ አሁንም እየጮኸ ጌታዉን ማመስገኑን አላቋረጠም፡፡ 'ጌታ ሆይ አመሰግንሀለው' እያለ ላንቃዉ እስኪበጠስ ድረስ ይጮሃል፡፡ እንደገና ቀጥ ብሎ ፈቲን በመሳም ያጣድፋታል፡፡ ደስታቸዉ እንደቀጠለ ነዉ፡፡... . ...ኤዲና ቢኒ ከዚያ ሁሉ ፈንጠዝያ ቡኃላ አብረዉ ቁጭ ብለዉ ራት እየበሉ ረዲ ደወለች፡፡ ቢኒም ስልኩን በኤዲ ሊያስነሳዉ አለና ..."ሆ ሆ ነገሩ እናንተ ወሬ ከጀመራችሁ ስለማታበቁ እኔ ካዋራኃት በኃላ እሰጥሻለሁ" ብሏት ስልኩን አንስቶት ረድኤትን ማወራት ጀመረ፡፡ እያወሩ እያለ ኤዲ አላስወራም አለችዉ፡፡ በትክክል እንዳያወራ ታጎርሰዋለች፡፡ በመሃል ትስመዋለች ቅብጥ ቅብጥብጥ አለችበትና ረበሸችዉ፡፡ ቢኒም "ዉይ እንቺ እስኪ አዉሪያት" ብሎ ስልኩን ሰጣት፡፡ ... ኤዲና ረዲ ማዉራት ጀመሩ፡፡ ..."ረዲዬ ራት እየበላን ነዉ፡፡ እንብላ አለቻት ኤዲዬ የተባረከ ይሁን ብሉ እሄ ቢኒ ሽሮ እንኳን መስራት አይችልም ስትላት ሁለቱም ተሳሳቁ በተለይ የኤዲ ሳቅ ከስከዛሬዉ ለየት ያለ ነበር፡፡ ፍንድቅድቅ አለች፡፡ ..."ደግሞ ለሽሮ ሌላም አስተምረዋለሁ" አለቻት ረዲ ለፈቲ ..."ሌላ ሌላዉንማ እኔ አስተምሬዋለሁ" ብትላት በሳቁ ላይ ቢኒም ተሳትፎ ነበር ከት ብለዉ ሳቁ፡፡ ሃሃሃሃ ሂሂሂ ኪኪኪኪ ... ..."ሆ" አለች ረዲ ..."ራትሽን የምትበይዉ ምላስ ነዉ እንዴ ወሬ ለቆብሻልሳ" ..."እረ እሱን ተይዉና ...ይልቅ የምወልዳት ልጅ ሴት ከሆነች ያንቺ ሞክሼ ነዉ የማረጋት ረድኤት ...እላታለሁ፤ ወንድ ከሆነ ግን ቢኒ ነው ስም የሚያወጣለት፡፡" ስትላት ረድኤት ደነገጠች፡፡ ..."ኤዲዬ አረገዝሽ እንዴ?" ..."ዉይ ረዲዬ በደስታ ብዛትኮ የነገርኩሽ መስሎኝ ነዉ፡፡ አርግዣለሁ፡፡ ዛሬ ሆስፒታል ሂጄ የሶስት ወር እርጉዝ ነሽ አሉኝ" አለቻት፡፡ ረድኤት... አስተማሪ የፍቅር ታሪክ📒       በፍቅር ሀይል ተዘጋጅቶ የቀረበ              ታርኩ ቶሎ እንዲቀጥል ካነበባቹ በኋላ like👍 ሳታደርጉ አትለፉ::     ክፍል_18 የመጨረሻው ክፍል ነገ የሚለቀቅ ይሆናል...       ✽̶🌺✿❁🌺🌺❁✿🌺̶̥✽̶ የፍቅር ሀይል

🌈ይችን ፁፍ የሆነ ሰው #የፌስቡክ ግድግዳ ላይ ተሰቅላ አነበብኳትና በጣም #ገረመችኝ❗️ " #ፌስቡክ ና #ትራስ " አንድ ናቸው፡፡ . -✨ሁለቱንም #ጭንቅላት ያለውም #የሌለውም ይጠቀማቸዋል፡፡ 🌤 #መልካም_ቀን☀️ @Yene_Ethiopia @Yene_ethiopia

​​​​┄┉✽̶🌺✿ምኞትና❤️ፍቅር✿🌺̶̥✽̶┉┄             ▬▬❁ ክፍል አስራ ስድስት❁▬▬         ✍እቃዎቹን አዘገጃጅቶ ከጨረሰ ቡሃላ ወደ ስራ ሊወጣ ሲል "ኤዲዬ ልሄድ ነዉ" አላት፡፡ ...."ቆይ የኔ ፍቅር በር ድረስ ልሸኝህ" አለችዉና ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደሱ መጣች፡፡ ተያይዘዉ አብረዉ ሲወጡ አባባ ሀብታሙ በጧቱ ከቤታቸዉ በር ስር ተቀምጠዉ ነበርና አገኟቸዉ፡፡ ..."ደህና አደራችሁ የኔ ልጆች እንዴት አደራችሁ?" አሏቸዉ፡፡ ሰላምታዉን ከመለሱላቸዉ ቡኃላ... አባባ ሀብታሙም ..."ኤዲ አንቺም ፈቅደሻል አሉ፡፡ እሁን ቢኒያምን ልትድሪዉ ነዉ ለረድኤት" ብለዉ ጠየቋት፡፡ የአባባ ሀብታሙ ንግግር ልቧን ለሁለት ስንጥቅ ነበር ያደረጋት፡፡ እንደምንም እራሷን ካረጋጋች ቡኃላ ፈገግ ለማለት እየሞከረች... "አዎ አባባ ፈቅጀለታለሁ፡፡" ብላ መልሷን አሳጠረች፡፡ ደስታዋ ነበር ኤዲ፡፡ በጣም ነበር የደነገጠችዉ፤ ዉስጧ ተሸበረ፡፡ ቢኒ የኤዲን እንዲህ መሆን ከሁኔታዋ ሲረዳ ..."በቃ አባባ ስራ ስለረፈደ ስመለስ እናወራለን፡፡" አላቸዉ፡፡ ..."ደግ እንግዲህ...." አሉና አባባ ወደ ቤታቸዉ ገቡ፡፡ ..."ኤዲዬ ወደ ቤት ግቢና አረፍ በይ እደዉልልሻለሁ" አላትና ግንባሯን ሳም አድርጓት ከግቢዉ ወጣ፡፡ ኤዲ እንደምንም ብላ ቤቷ ገባች፡፡ የሰማችዉን ማመን አቅቷታል ሀሙስ ማለት ከሁለት ቀን ቡሃላ ነዉ፡፡ "እና ከሁለት ቀን ቡሃላ ረድኤት ቢኒን ልትጋራኝ ነዉ ማለት ነዉ" ስትል አስበች፡፡ ብዙም ሳትቆይ ከባድ ራስ ምታት አመማት፡፡ በጣም አመማት፡፡ ቁርሷን ሰርታ መብላት ሁሉ አልቻለችም፡፡ አቃታት፡፡ ተንቀሳቃሽ ስልኳን አነሳችና ወደ ቢኒያም ደወለች፡፡ ..."ሄሎ ኤዲዬ እደዉላለሁ ብዬ ቆየሁ እንዴ?" አላት ቢኒ ..."በጣም አሞኛል ቢኒ ናልኝ፡፡ ቶሎ በል" አለችዉና ስልኳን ዘጋችዉ፡፡ እየተንቀጠቀጠች ነበር ያወራችዉ፡፡ እንደምንም ብላ ቀስ ብላ ተኛች፡፡ ወዲያዉ እማማ በለጡና ረድኤት እየተሯሯጡ መጡና "ኤዲ ምን ሁነሽ ነዉ?" ብለዉ አይን አይኗን አይዋት፡፡ ኤዲ ራሷን በሻርብ ግጥም አድርጋ አስራዉ ነበር፡፡፡ እማማ በለጡ ኤዲን ግንባሯን እያሻሹ "ትኩሳትም የለሽ ምን ሁነሽ ነዉ ኢዲዬ" ብለዉ ጠየቋት፡፡ኤዲም ..."ትንሽ ራሴን አሞኝ ነዉ" አለቻቸዉ፡፡ ..."እኔኮ ቢኒያም ሲደዉልልኝ ምን አጋጠመሽ ብዬ ነበር፡፡ለራስ ምታት ነው ውይ ፈጣሪ ይመስገን" ብለዉ ፈጣሪን አመሰገኑ፡፡ ቢኒ ለእማማ በለጡ ደዉሎ ሲነግራቸዉ በጣም የተጎዳችና ድንገታዊ አደጋ የደረሰባት አስመስሎ ነበር፡፡ እማማ በለጡና ረዲ ከኤዲ አጠገብ ሳይነሱ ወዲያዉ ላብ በላብ ሆኖ እያለከለከ ቢኒ ብቅ አለ፡፡ ..."ኤዲዬ ምን ሆንሽብኝ? ምን አግኝቶሽ ነዉ?" በጣም አመመሽ?" እያለ ከተኛችበት ቀና እያደረገ በጥያቄ አጣደፋት፡፡ ..."የኔ ፍቅር መጣህልኝ!" አለችዉና ከተኛችበት ራሷ ቀጥ ብላ እቅፍ አደረገችዉ፡፡ ..."ቢኒ..." አለችዉ፡፡ ቢኒም ..."ወዬ የኔ ማር!" አላት፡፡ እማማ በለጡና ረድኤት አጠገባቸዉ እንደተቀመጡ ነበር፡፡ ለነሱ ብዙም ቦታ ሳትሰጣቸዉ ቢኒያምን ወደራሷ ሳብ አደረገችዉና... ..."ከነገ ወዲያ ሀሙስ ቀለበት አትሰሩ፡፡" አለችዉ፡፡ ለማሜ ድንገታዊ ጥያቄ ነበር፡፡ ወዲያዉ መልስ መስጠት ያለበት ጉዳይ ነዉ፡፡ ይሄን ጥያቄ ስትጠይቀዉ የህመሟ ምክንያት የጧቱ የአባባ ሀብታሙ ወሬ እንደሆነ ገምቷል፡፡ አባባ ሀብታሙን እናትና ልጅ ባንድ ሌሊት አሳምነዋቸዉ እርሳቸዉም ልጃቸዉ እንዳትጎዳ፤ እንደገና ዩንቨርሲቲም ገብታ እንዳትበላሽ፤ በበፊት ባህሪዋ እንድትቀጥል ሲሉ ለቢኒ ለመዳር ቆርጠዋል፡፡ ....ቢኒ ... እማማ በለጡንና ረድኤትን ዞር ብሎ እያፈራረቀ ከተመለከተ ቡኃላ እንደገና ወደ ፈቲ ዞር ብሎ ሲመለከት፡፡...ሁሉም ተፋጠዋል፡፡ ኤዲ ቢኒን የጠየቀችዉ ጥያቄ ባሏን ብቻ ሳይሆን ረድኤትን ልቧን ቀጥ፤ የእማማ በለጡን አይን ፍጥጥ አድርጓቸዋል፡፡ ኤዲ በድንገት ባሏን ማጣት አልፈለገችም፡፡ ለዚያም ነዉ ይሄን ጥያቄ እነሱ ፊት ያፈረጠችዉ።ቢኒ ምን እንደሚመልስ ግራገባው፡፡ 'እሺ ቀለበት አናስርም' ብሎ አያስደስታት ረድኤትና እናቷ አጠገቡ ናቸዉ፡፡ ሊያዋርዳቸዉና ክብራቸዉን ዝቅ እንደማድረግ ሆኖ ተሰማዉ፡፡ 'አይ አይሆንም ማግባት አለብኝ' እንዳይል ደግሞ ኤዲን ማሳዘንና መጉዳት አልፈለገም፡፡ ዝም ብሎ በማሳዘን አይነት ስሜት እየተቅለሰለሰ ኤዲን ያያታል፡፡ ኤዲም ታየዋለች፡፡ እነሱም (ረድኤትና እማማ በለጡ) ያዩታል፡፡ ሁሉም ይተያያሉ፡፡ ቢኒ ምን ይመልስ፡፡ ዉድ ሚስቱ ኤዲ እንደተጨነቀ ስለተረዳች አይኑን በተመስጦ እያየች... ..."የኔ ፍቅር እኔ'ኮ አታግባት አላልኩህም (ዘወር ብላ እናትና ልጅንም አየቻቸዉ እንደገና ቢኒን እየተመለከተች) ቢኒ ... ታገባታለህ፡፡ ረድኤት ትወድሃለች፡፡ አንተም እንደዚያዉ በተለይ ደግሞ ልጅ መዉለድ አለብህ፡፡ እኔ ልሰጥህ ያልቻልኩትን ነገር እሷ ትሰጣሃለች፡፡ስለዚህ ትጋባላችሁ፡፡ ግን ትንሽ አቆዩት እባክ" ብላ ረድኤትንም በተማፅኖ ተመለከተቻት፡፡ ..."እሺ ኤዲዬ እናቆየዋለን" አለና ቢኒ ወደ ረድኤት ዘወር ብሎ ..."መቼ ነዉ ግቢ የምትገቢዉ ረዲ?" ብሎ ጠየቃት፡፡ የረድኤት መልስ አጭር ነበር "እሁድ" ብላዉ በረዥሙ ተነፈሰች፡፡ እህህህ አተነፋፈሷ ለሁሉም ይሰማ ነበር፡፡ ቢኒያምም ወደ እማማ በለጡ ዘወር አለና.... ..."እማማ ረዲ ወደ ትምህርቷ ትሂድና ለእረፍት ስትመጣ ቀለበት እናስራለን፡፡ እስከዚያ ኤዲም ትረጋጋ" አላቸዉ፡፡ከረጅም ፀጥታ በኃላ ቢኒያም ወደ ረድኤት ዘወር አለና ..."አይሻልም ረዲ?" ብሎ ጠየቃት፡፡ ረድኤትም በአዎንታ ራሷን ወደ ታችና ወደ ላይ ነቀነቀች፡፡ እማማ በለጡ ቀጠል አደረጉና "መቼ ይሆን እረፍትሽ?" ብለዉ ረድኤትን አተኩረዉ እያይዋት ጠየቋት ..."የካቲት ዉስጥ ነዉ የሚሆነዉ" አለቻቸዉ፡፡ ..."የዛሬ አምስት ወር መሆኑ ነዉ?" አሉ እማማ፡፡ ኤዲ ይሄን ስሰማ የአምስት ወር ጊዜ መሰጠቷ አስደስቷት ከሌሎቹ ቀደም ብላ ..."አዎ እማማ" አለቻቸዉ፡፡ በዚሁ ተስማሙና የካቲት ላይ የዛሬ አምስት ወር ቢኒ ለረድኤት ቀለበት እንደሚያስርላት ተወሰነ፡፡ አስተማሪ የፍቅር ታሪክ📒       በፍቅር ሀይልተዘጋጅቶ የቀረበ               ታርኩ ቶሎ እንዲቀጥል ካነበባቹ በኋላ like👍 ሳታደርጉ አትለፉ::     ክፍል_16 ይቀጥላል ...         ┄┉✽̶🌺✿❁🌺🌺❁✿🌺̶̥✽̶┉┄

​​🌸"በህይወት ጎዳና አንድ እርምጃ ወደፊት ስትራመድ🚶‍♂ ብዙ መንገድ ወደ ሁዋላ ሊመልሱህ የሚችሉ ፈተናዎች እንደሚገጥሙህ አምነህ ተቀበል፡፡ 🌸ለምታገኘው ነገር ብቻ ሳይሆን ላጣኸውም ነገር አመስግን፡፡ ምናልባት ስለማያስፈልግህ ይሆናል ከመንገድህ ዞር የተደረገው፡፡" 🌹 #መልካም_ቀን 🌹 🌷🌸የፍቅር ❖❖❖❖ሀይል🌸🌷

​​​​┄┉✽̶🌺✿ምኞትና❤️ፍቅር✿🌺̶̥✽̶┉┄             ▬▬❁ ክፍል አስራ አምስት❁▬▬        ✍...አባባ ሀብታሙ ባለቤታቸዉ ላይ እንዳፈጠጡ ነዉ፡፡ መልስ ይፈልጋሉ፡፡ ልጃቸዉን በሚስጥር ልትድራት እንደ ሆነ ነገር ነዉ የገመቱት፡፡ "ከማን ጋር ነዉ ሴራ የምታሴረዉ?" ጥያቄያቸዉን ለማማ በለጡ ደገሙላቸዉ፡፡ እማማ በለጡና ረድኤት ይተያያሉ፡፡ አባባ ሀብታሙ ደግሞ ባለቤታቸዉ ና ልጃቸዉ ላይ አይን አይናቸዉን እያፈራረቁ ተመለከቷቸዉ፡፡ እማማ በለጡ በረዥሙ ትንፋሻቸዉን እህህህህ ብለዉ ካወጡ ቡኃላ ይሄዉልህ ሀብታሙ ብለዉ ለማስረዳት ሊሞክሩ ሲሉ "ማንን ነዉ የምታገባዉ? እ!" ብለዉ መልሱን ለመስማት ጓጉ... እማማ በለጡም ቀስ አሉና... "ረድኤት እንግዲህ ደርሳለች፡፡ ህፃን ልጅ የምትባል ልጅ አይደለችም፡፡ ለማፍቀርም ለመፈቀርም፤ ለማግባትም ለመዉለድም ደርሳለች፡፡" ...የጋሽ ሀብታሙን አይን አይን እያዩ ነበር የሚያወሩት "አይደለም እንዴ ሀብታሙ?" ብለዉ የረድኤትን መድረስ ለማረጋገጥ ባለቤታቸዉን አባባ ሀብታሙን ጠየቁ፡፡ ..."አዎ ደርሳለች ግን...ለማን ነዉ የምትድሪያት? ማንን ነዉ የምታገባዉ?" ብለዉ ጠየቁ የምታገባዉን ሰዉ ይበልጥ ለማወቅ እየጓጉ፡፡ "...እኔ አይደለሁም የምድራት፡፡ ልጄ ረዲ የምታገባዉን ሰዉ ራሷ መርጣለች" አሉ እማማ በለጡ ረድኤትን እንደ ማቀፍ እያረጉ፡፡ ረድኤት አባቷን ለማየት ተሳናት፡፡ ..."አትፍሪ የኔ ልጅ ንገሪኝ ማንን ነዉ የመረጥሽዉ? እኔምኮ አባትሽ ነኝ ለናትሽ ብቻ ነዉ እንዴ የምትነግሪያት" አሉ አባባ ሀብታሙ፡፡ ረድኤት ደፈር ብላ እንድትነግራቸዉ እየገፋፏት፡፡ ረድኤትም አባቷን በፍርሃት ቀጥ ብላ እያየች "አባዬ... ቢኒያምን ነዉ!" አለቻቸዉ፡፡ ይሄ አባቷን ድፍረቷ ሳይሆን አሰተዳደጓ ነዉ፡፡ ምንም ነገር አጥብቀዉ ከጠየቋት አትዋሽም፡፡ እማማ በለጡም ስሙን ከረድኤት አፍ ነጠቅ አደረጉና "አዎዎ ቢኒያም ነዉ፡፡ የኤዲን ባል" ..."ምን?በስመአብ" ብለዉ ከተቀመጡበት ብድግ እንደገና ቁጭ አሉና....፡፡አይሆንም?አታደርጉትም። ...ኤዲና ቢኒ አንድ ላይ ተኝተዉ እየተንሾካሾኩ ያወራሉ፡፡ ኤዲም ንዴቷን እረስተዋለች፡፡ ከምንም በላይ ደግሞ ረድኤትን በጣም ወዳታለች፡፡ ምክንያቷ ደግሞ ከሜሴጁ ላይ ረድኤት ለኤዲ እጅግ በጣም አሳቢ እንደሆነች ነዉ የተረዳችዉ፡፡ "ለኤዲ አንተ ቀድመህ ንገራት"..."ኤዲ ትፍቀድ እንጂ" ... ይሄ የረድኤት ንግግር ዉስጧ ገብቷል፡፡ እኔ የማልፈቅድ ከሆነኮ ረድኤት ቢኒያምን አታገባዉም ማለት ነዉ እያለች ታስባለች፡፡ እንደ እዉነቱም ረድኤት ለኤዲ ታዝንላታለች፤ ታከብራታለች፡፡ ፍቅር ሆኖባት እንጂ የኤዲን ባል ልትቀናቀናት አትፈልግም ነበር፡፡ ..."የኔ ፍቅር እማማ በለጡ ሁሉንም ነግረዉኛል" አለችዉ ቢኒያምን፡፡ ቢኒም እቅፉን ይበልጥ እያስተካከለ ..."ምን ነገሩሽ የኔ ቆንጆ!" ብሎ ጠየቃት፡፡ ..."ረድኤትም በጣም እንደምትወድህና ልታገባህ እንደምትፈልግ እና ሌላም ብዙ..." ብላ በቁጭት አይነት ወሬዋን አቋረጠችዉ፡፡ ትንፋሿ ይጋረፍ ነበር፡፡ ቢኒያም በዚሁ ርዕስ ወሬ ከቀጠሉ ወደ ማኩረፍ እንደምትሄድ ስለተረዳ ወሬ ለመቀየር ያክል... ..."ኤዲዬ ..." አላት ..."ወዬ ቢኒ" ..."ስትተኚ ይበልጥ የምታምሪዉ ለምንድን ነዉ? በጣም ዉብብ ሆነሻልኮ" አላት፡፡ ጉንጯን እንደመሳም እያረገ ነበር፡፡ ኤዲም ... ..."እሺ የኔ ፍቅር እንቅልፍ ሲወስደኝ ደግሞ ይበልጥ ስለሚያምርብኝ ልተኛ" አለችዉና እሷም ሳም አድርጋዉ ራሷን ከእቅፉ አዉጥታ ጀርባዋን ሰጥታዉ ተኛች፡፡ ...ኤዲና ቢኒ ሰሞኑን በረድኤት ጉዳይ የተነሳ አልተኙም  ቢኒ  በለሊቱ ተነስቶ ወደ ስራ ለመሄድ ወደ ስራ ይዟቸዉ የሚሄደዉን እቃዎች እያዘጋጀ ነጋ፡፡ አስተማሪ የፍቅር ታሪክ📒       በፍቅር ሀይል ተዘጋጅቶ የቀረበ               ታርኩ ቶሎ እንዲቀጥል ካነበባቹ በኋላ like👍 ሳታደርጉ አትለፉ::     ክፍል_16 ይቀጥላል ...         ┄┉✽̶🌺✿❁🌺🌺❁✿🌺̶̥✽̶┉┄

​​​​┄┉✽̶🌺✿ምኞትና❤️ፍቅር✿🌺̶̥✽̶┉┄             ▬▬▬❁ ክፍል አስራ አራት❁▬▬▬          ✍"ኤዲ ስፈልግሽ ነበር...ስራ አለሽ እንዴ?" አሏት፡፡ ..."አይ ስራ የለኝም፡፡ ለምን ፈለጉኝ እማማ" አለቻቸዉ ፊቷን ሳታዞር በቆመችበት፡፡ ..."የሆነ የምነግርሽ ነበረኝ" አሉ እማማ በለጡ፡፡ ኤዲ እማማ በለጡን ማስቀየም አልፈለገችም ነበርና ወደ እሳቸዉ ጠጋ እያለች ..."ምንድን ነዉ እሱ እማማ" አለቻቸዉ፡፡ ... ቢኒ እንዴት አድርጎ ይንገራት?፡፡ ጭንቅ ብሎታል፡፡ ኤዲ እንደዚህ የምትሆን፣ እሱ በማግባቱ፣ ልጅ ለዉለድ እርምጃዎችን መሄዱ ደስተኛ ካልሆነች "አላገባም" እያለ ያስባል፡፡ "ጥፋተኛ ነኝ" እያለም ራሱን ይወቅሳል፡፡ እርግጥ ነዉ የመጀመሪያዉ መልዕክት የተላከ ቀን ለኤዲ መንገር ነበረበት፡፡ ለሷ ባለመንገሩ ዛሬ ሁኔታዎች እሱ እንደጠበቃቸዉ ሊሄዱ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ኤዲን ደስ የማይላት ከሆነ አያገባምም ልጅም አይወልድም፡፡ ይሄ የቢኒ የመጨረሻ ዉሳኔ ነበር፡፡ ወስኗል፡፡ . ...እማማ በለጡ ምንም ሳያስቀሩ ለኤዲ ነግረዋታል፡፡ ረድኤት ቢኒያምን በህልሟ እንደምታዬዉ፤ በቅዥቷ እንደምጠራዉ፤ በጣም እንደምታፈቅረዉና ልታገባዉ እንደምትፈልግ ሁሉንም ብጥርጥር አድርገዉ ኤዲ ጆሮ ላይ አድርሰዋል፡፡ በመጨረሻም ኤዲ ተነስታ ወደ ቤቷ ልትገባ ስትል፡፡ እማማ በለጡ "እንዲጋቡ ትፈቅጃለሽን?" ብለዉ ጠየቋት፡፡ ኤዲም..."ቢኒኮ ሁለት ሴት የማስታዳደር አቅም የለዉም!" አለቻቸዉ፡፡ እማማ በለጡም ..."የኔ ልጅ አንቺ ፍቀጂላቸዉ እንጂ ለኑሮው ችግር የለዉም፡፡ አንቺ የምትኖሪበት ቤት የራስሽ ይሆናል፡፡ ይሄንኛዉ ደግሞ የረዲ (በእጃቸዉ እየጠቆሟት) በዚያ ላይ እሷ ተመርቃ ስራ ትይዛለች፡፡ ደግሞም እኛ ያለን ሁሉ የቢኒያም ይሆናል፡፡ ለሀብትማ አትጨነቂ ፈጣሪ አለ፡፡ አይዞሽ" አሏት፡፡ የማስተዳደር አቅም የለዉም ማለቷ በጊዜዉ ተናዳ ስለነበርና እዉነታዉም ይሄ ስለሆነ ለማሳወቅ ብላ እንጂ ቢኒ ረድኤትን እንዳያገባ እያሸሸች አልነበረም፡፡..."እማማ በለጡ እሱ ከፈለገና ፍቃደኛ ከሆነ እኔኮ መከልከል አልችልም፡፡ፈጣሪ ፈቅዶለት የለ?" አለቻቸዉ፡፡... "አይይ የኔ ልጅ ብዙ ወንዶች ፈጣሪ ፈቅዶልናል፡፡ ለሚስቶቻችን ፍትሃዊ እንሆናለን እያሉ ነዉ የመጀመሪያ ሚስቶቻቸዉን የሚጎዱት፡፡" ስለ አባባ ሀብታሙ ማለታቸዉ ነበር፡፡ ኤዲ ታሪኩን ስለማታዉቅ ነዉ እንጂ..."አዎ ልክ ነዎት! እማማ እኔ ግን ቢኒያም እንደነዚያ አይነት ወንዶች እንደማይሆን ስለማዉቅ ረድኤትን ቢያገባት ደስስ ይለኛል እንጂ ቅር አይለኝም፡፡" አለቻቸዉ፡፡ እማማ በለጡ ደስ አላቸዉ፡፡ ልጃቸዉን ሁለተኛ ሁና እንድታገባ ሳያናዳቸዉ ለጥሩ ወንድ እንደሚድሯት ሲያስቡ ዉስጣቸዉን ደስታ ተሰማቸዉ፡፡ ...ቢኒ የኤዲ ዉጭ መቆየት አሳስቦት ወደ ዉጭ ሲወጣ ኤዲ ከእማማ በለጡ ጋር ቁጭ ብላ ተመለከታት፡፡ በዉስጡ "እየነገሯት ተመልሶ ወደ ቤቱ ገባ . ኤዲ እና እማማ በለጡ ተለያዩና ሁለቱም ወደ የቤታቸዉ ገቡ፡፡ ወደ ቤቷ ስገባ ቢኒ እንደተቀመጠ ነዉ፡፡ "የኔ ፍቅር ነገ ስራ አለብህ አይደል? ለምን ገብተህ አተኛም?" አለችዉ፡፡ የቅድሙ ቁጣ እንደጠፋ ስላዬ እሱም ዘና ብሎ "የኔ ቆንጆ እንዴት ዉድ ሚስቴን ትቼ እተኛለሁ!" አለና ከተቀመጠበት ተነስቶ እቅቅፍ አደረጋት፡፡ ...እማማ በለጡ ወደ ቤት ሲገቡ አባባ ሀብታሙና ልጃቸዉ ረድኤት ቁጭ ብለዉ እያወሩ አገኟቸዉ፡፡ ወደ ወሬዉ ለመቀላቀል ያክል "አባትና ልጅ ምን እያወጋችሁ ነዉ?" ብለዉ "ኧረ ኧረረ እህህ.." ብለዉ ከረድኤት አጠገብ ቁጭ አሉ፡፡ አባባ ሀብታሙም ..."ወደ ትምህርቴ ልገባ ነዉ፡፡ ግቡ ተብለናል ትላለች" አሉ፡፡ እማማ በለጡ የጀመሩት ሳይቋጭ ወደ ዩንቨርስቲ ልትገባ መሆኑን ሲያዉቁ ..."መቼ ነዉ ወደ ዩንቨርስቲ የምትገቢዉ የኔ ልጅ?" ብለዉ ጠየቋት፡፡ ረድኤትምም ... " የሳምንቱ መጨረሻ ላይ እሁድ እሄዳለሁ" ስትላቸዉ እማማ በለጡ ደንገጥ አሉና..."እንግዲያዉስ ከመሄድሽ በፊት በዚህ ሳምንት ዉስጥ ቀለበት ማሰር አለብሽ!" አሉ፡፡አባትና ልጅ ሁለቱም ድንግጥ ብለዉ "እ..." አሉ፡፡ የረድኤት አደነጋገጥ እንዴት... አስተማሪ የፍቅር ታሪክ📒       በፍቅር ሀይል ተዘጋጅቶ የቀረበ               ታርኩ ቶሎ እንዲቀጥል ካነበባቹ በኋላ like👍 ሳታደርጉ አትለፉ::     ክፍል_15 ይቀጥላል ...         ┄┉✽̶🌺✿❁🌺🌺❁✿🌺̶̥✽̶┉┄

​​​​┄┉✽̶🌺✿ምኞትና❤️ፍቅር✿🌺̶̥✽̶┉┄             ▬▬▬❁ ክፍል አስራ ሶስት❁▬▬▬ ✍አባባ ሁኔታዋን ሲያይዋት ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ይታይባታል፡፡ እሷ ግን እንደምንም እየታገለች ፈገግ ለማለት ትሞክራለች፡፡ ምክንያቱም ልጃቸዉን ለባሏ ልትጠይቃቸዉ ነዉና፡፡ ከረጅም ዝምታና ፀጥታ ቡኃላ አባባ ተንፈስ አሉና "ባልሽ ቢኒያም ግን በጣም ጎበዝ ነዉ አደነቅኩት" አሏት፡፡ እሷም ለምን? እንዴት? በምን ምክንያት አደነቁት? ብላ አልጠየቀቻቸዉም፡፡ ቢኒ የሚደነቅ ጥሩ ሰዉ እንደሆነ ታዉቃለችና፡፡ አንድ ነገር ግን እርግጠኛ እየሆነች ነዉ፡፡ የረድኤት ቤተሰቦች ቢኒያም ረድኤትን ለትዳር ቢጠይቅ እምቢ እንደማይሉና በደስታ እንደሚድሩት ከአባባ ሀብታሙ ሁኔታ መረዳት ችላለች፡፡ የረድኤት ቤተሰቦች ቢኒያምን ይወዱታል፡፡ ደስ አላት፡፡ ባሏን እሷዉ ልድረዉ ነዉ፡፡...ቢኒ ከስራ እንደመጣ ጊዜ ማባከን አልፈለገችም፡፡ "ቢኒ ለረድኤት ቤተሰቦች ሽማግሌ መላክ አለብህ" አለችዉ፡፡ ..."እንዴ ፈጠንሽሳ?" አላት ቢኒ ..."አዎ ፍቅሬ ሌላ የኔን ቢጤ ደሃ ካገባህኮ እኔን መፍታትህ አይቀርም፡፡ እኔ ደግሞ አንተ እንድትፈታኝ አልፈልግም፡፡ ሁሌም በፍቅርህ መኖር እፈልጋለሁ" አለችዉ እየተቅለሰለሰች፡፡ ይሄን ከማለቷ ብዙም ሳይቆዩ የቢኒያም ስልክ መልዕክት (ሜሴጅ) ገባ "ጢጢጥ ጢጢጥ" ሜሴጁ ሲገባ የቢኒ ስልክ ያሰማዉ ድምፅ ነበር፡፡ ቢኒ ስልኩን አነሳና የላኪዉን ስም ሲያይ በማማ በለጡ ስልክ ነዉ የተላከዉ "ረድኤት መሆን አለባት" አለ በዉስጡ፡፡ ኤዲ እያየችዉ ነበር፡፡ ደንገጥ ብሎ ስታየዉ ፊቷ ክስም ይላል፡፡ እንደገና ፈገግ ሲል እሷም አብራ ትፈካለች፡፡ ኤዲ ሁሌም ቢሆን በቢኒያም ደስታ ደስ ይላታል፡፡ "የኔ ፍቅር ምንድን ነዉ መልዕክቱ?" አለችዉ....ኤዲ ቢኒ ፈገግ ስላለበት ጉዳይ ለማወቅ ጓጓች፡፡ ቢኒ አሁንም እንደፈገገ ነዉ፡፡ " ንገረኛ ዉዴ?" አለችዉ፡፡ በአይኖቿ እየተማጸነች፡፡ ቢኒያም ሊነግራት ነበር ነገር ግን ከረድኤት ጋር ከዚህ በፊት እንደተደዋወሉና በስልኩ መልዕክት እንደላከችለት ቀድሞ ለኤዲ አልነገራትም ነበር፡፡ ትቆጣ ይሆን እንዴ? ፈራ፡፡ ከሷ መደበቅ ስላልፈለገና ኤዲ ብትቆጣም ብታኮርፍም ልትንሽ ሰዓታቶች እንደሆነ ስላወቀ ስልኩን ለኤዲ አቀበላት፡፡ አንብቢዉና የባልሽን ጉድ ተመልከቺ ይመስላል አሰጣጡ፡፡ ኤዲም ስልኩን ተቀበለችውና የላኪዉን አድራሻ ስታይ እማማ በለጡ ይላል፡፡ "የኔ ፍቅር እማማ ደግሞ ምን ብለዉ ልከዉልህ ነዉ?" ብላ ጠየቀችዉ፡፡ "ኤዲዬ ስልኩ እጂሽ ላይ አይደል? አንብቢዉ" አላት ..."ቢኒ ለእማዬ ነግሬያታለሁኝ ኤዲ ፍቃደኛ ትሁን እንጂ ..."ኤዲ ፊቷ እየተቀየረ ነበር፡፡ ቀጥ ብላ ቢኒያምን ተመለከተችዉ ትኩር ብላ አየችዉ፡፡ ቢኒያም የኤዲን የቁጣ አይኖች መቋቋም አልቻለምና ጎንበስ አለ፡፡ኤዲ እንደገና ወደ መልዕክቱ ትኩረቷን አደረገች፡፡ ማንበብ ቀጠለች... "...አንተ እንድታገባኝ ፍቃደኛ እንደምትሆን ነግራኛለች፡፡ ግን ደግሞ እሷ ራሷ እማዬ ለኤዲ እነግራታለሁኝ ብላለች፡፡ ቢኒ ፕሊስ እማዬ ለኤዲ ከመንገሯ በፊት አንተ ቀድመህ ንገራት፡፡" ይላል መልዕክቱ፡፡ ፊቲ ሁለት ልብ ሁናለች፡፡ ደስተኛም ግን ደግሞ የብቸኝነት ስሜት የተሰማት ባዶ እንደሆነች አድርጋ እራሷን አሰበች፡፡ ከዉስጧ ደስታ ይበልጥ ንዴቷ ፊቷ ላይ ገንፈሎ ወጣና "ቢኒ እኔን ሳትነግረኝ ከረዲ ጋር ጀምረህ ነበራ?" ብላ ጠየቀችዉ፡፡ "የኔ ፍቅር እኔ ላንተ ድብቅ ነኝ ማለት ነዉ?" ኤዲ ምን እንደምትናገር ሁሉ አቅቷታል፡፡ እምባ እየተናነቃት የምታወራዉ ሁሉ ይቆራረጣል፡፡ቢኒ የዚህን ያህል ትቆጣለች፤ እንደዚህ ትሆናለች ብሎ አላሰበም ነበር... ..."እንደሱኮ አይደለም ኤዲዬ..."እያለ ወደሷ ጠጋ አለ ..."አትጠጋኝ! ደግሞ ምንም ነገር አትንገረኝ!" አለችዉ፡፡ በሂወቱ ኤዲ እንዲህ ስታመር አይቷት አያዉቅም፡፡ ዛሬ በጣም ተለይታበታለች፡፡ ለማባባል እንኳ በሚያስቸግር ሁኔታ፡፡ ኤዲን እንዲህ እንድትሆን ያደረጋት ሁለተኛ ማግባቱ አይደለም፡፡ ይሄንን ደግሞ እራሷ ፈቅዳለታለች፡፡ እሷዉ ሴት መርጣ ልትድረዉም ተዘጋጅታ ጨርሳ ነበር፡፡ ነገር ግን... ገና ሳያገባ እንዲህ ሚደብቃት፤ ለሱ እየለፋችለት፤ ሁሉንም ነገር ለሱ እየሆነችለት እሱ ግን ልቧን መስበሩ በጣም አዘነችበት፡፡ ...ቢኒ ምን እንደሚያወራ አፉ ተያያዘበት፡፡ ተንተባተበ፡፡ ጥፋተኛ እንደሆነ አዉቆታል፡፡ ኤዲ ጎንበስ ብላ ነበር ቀና ብላ ቢኒያምን ስትመለከተዉ እሱም የመለማመጥ አይነት አንገቱን ሰብሮ አይኖቹን አቁለጨለጨ፡፡ ..."ቢኒ ... እኔ እንደፈቀድኩና መጋባት እንደምትችሉ ፃፍላት" አለችዉ፡፡ ..."ኤዲዬ መጀመሪያ ስለነበረዉ ነገር ላንቺ ልንገርሽ" ..."የኔ ፍቅር በፈጣሪ!? አሁን ምንም ነገር ለመስማት ዝግጁ አይደለሁም!" ..."እይዉልሽ ማሬ...." ብሎ ወሬ ሲጀምር ኤዲ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደ ዉጭ ወጣች፡፡ ከመዉጣቷ እማማ በለጡን ዉጭ ላይ አገኘቻቸዉ፡፡ ሰላምታ ቀድማ አልሰጠቻቸዉም፡፡ እማማ በለጡም ኤዲን ሲያይዋት "ደህና ነሽ ኤዲ" አሏት፡፡ ኤዲም ለሰላምታቸዉ መልስ ሰጠችና ከማንም ጋር ምንም ማዉራት ስላልፈለገች ተመልሳ ወደ ቤት ልትገባ ስትል... አስተማሪ የፍቅር ታሪክ📒       በፍቅር ሀይል ተዘጋጅቶ የቀረበ               ታርኩ ቶሎ እንዲቀጥል ካነበባቹ በኋላ like👍 ሳታደርጉ አትለፉ::     ክፍል_14 ይቀጥላል ...         ┄┉✽̶🌺✿❁🌺🌺❁✿🌺̶̥✽̶┉┄

​​​​┄┉✽̶🌺✿ምኞትና❤️ፍቅር✿🌺̶̥✽̶┉┄             ▬▬▬❁ ክፍል አስራ ሁለት❁▬▬▬ ✍...."እንዴት?... ለምን?... ማለቴ ...በምን ምክንያት ሞተች?" እየተንተባተበች ነበር የጠየቀቻቸዉ፡፡ ...."ይሄዉልሽ ልጄ አባትሽና ሚስቱ በጣም ነበር የሚዋደዱት፡፡ ፍቅራቸዉ እጅግ ያስቀና ነበር፡፡ ግን ምን ይደረግ ልጅ መዉለድ አልቻለችም፡፡ ከዚያ አባትሽ ሀብታም ስለነበር ሁለተኛ እኔን አገባኝና አንቺን ወለድኩለት፡፡ ከመጀመሪያ ሚስቱ ጋር የነበረዉ ፍቅር ቀነሰ፡፡ ዉሎዉ፤ አዳሩ ከእኔና ካንቺ ልጁ ጋር ሆነ፡፡ የመጀመሪያ ሚስቱን ፈታት እንዴ? እስከሚባል ድረስ ረሳት፡፡ እሷም በፍቅር ተጎዳች፡፡ እኔ በመዉለዴ ቅናት አብሰከሰካት፤ ብቸኝነት አጠቃት ይሄን ሰበብ አድርጎ ነዉ መሰለኝ በጣም ታመመች፡፡ ብዙም ሳትቆይ ሞተች፡፡አባትሽም ከሞተች ቡኃላ ነበር የመሞቷ ስበብ እሱ መሆኑን ያወቀዉ፡፡" በሀዘን ተዉጠዉ ነበር የሚነግሯት በፈጣሪ" አለች ረድኤት "እንዴት እስከዛሬ ሳላዉቅ ግን ማሚ?ይሄን ያክል ድብቅ ነሽ ማለት ነው...ጊዜዉ እየነጎደ ነዉ፡፡ ረድኤትም የዩንቨርሲቲ መግቢያዋ ቀርቧል፡፡ ቀናቶች ናቸዉ የቀሩት፡፡የቢኒ ጉዳይ አልተቋጨም፡፡ አሁንም ቢሆን እሱን ከማሰብ ስለሱ ከማለም አልቦዘነችም፡፡ ከጭንቅላቷ ጋር አብሮ የተሰራ ይመስል ሁሌም ስሙን ትደጋግማለች፡፡ ልቧ ላይ ግን ላይለቅ፤ ላይገፈፍ ታትሟል፡፡... ኤዲና ቢኒ እያወሩ ነዉ፡፡ በባለፈዉ ምሽት ሁለተኛ ማግባት እንዳለበት ተስማምተዋል፡፡ኤዲ የሆነ ነገር አስባለች ግን ደግሞ ለቢኒያም መንገር ፈራች፡፡ከስንት ፍርሃትና ትግል ቡኃላ ..."ቢኒ" አለችዉ ..."ወይዬ ፍቅሬ🌺" አላት፡፡ አቤት አጠራር ፤ አቤት ፍቅር ..."ለምን እኔ እራሴ አልድርህም" ..."እንደዉም ከአንቺ ጋር የምትስማማዋን አምጭልኝ" አላት፡፡ እየቀለደ ነበር፡፡ ..."ቢኒ አትቀልዳ...ከምሬኮ ነዉ፡፡ እኔዉ ልዳርህ ፍቅሬ" አለችዉ፡፡ ቢኒያም ግራ ገባዉ፡፡ በዉስጡ "ይቺ ልጅ ከምሯ ነዉ እንዴ?" እያለ ..."ማንን ነዉ የምትድሪልኝ?" ብሎ ጠየቃት፡፡ ኤዲም ፈራ ተባ እያለች..." በጣም ቆንጅዬ ልጅ ናት በዚያ ላይ ስርዓቷ ጥግ ድረስ ነዉ፡፡ እንደዉም ላንተ የምትሆንህ እሷ ናት፡፡"ቢኒ ተደናገጠ፡፡ ነገሩ እሱ ብቻ ሳይሆን ንግግራቸዉን የሚሰማ ሰዉ ቢኖር ይደነግጣል፡፡እንዴት ተቀናቀኟን እሱዋለዉ ትመርጣለች፡፡ በዚያ ላይ ቆንጆ ብላ እያሞገሰች፤ ስለ ፀባይዋ እየመሰከረች፡፡ ..."ማን ናት እሷ😘 ኤዲዬ" ..."ረድኤት!" አለችዉ፡፡ በጣም ከመደንገጡ የተነሳ ምላሱ ተሳሰረበት የሚናገረዉ ጠፋዉ፡፡ ..."እዉነትሽን ነዉ?" አላት፡፡ በመጠራጠር አይነት ስሜት..."አዎ! ደሞኮ በጣም ምርጥ ልጅ ናት ፍቅሬ" አለችዉ፡፡ በዉስጡ 'አንቺ ሳታዉቂ መጀመራችንን አታዉቂ?" አሞግሻት' እያለ ..."እሷስ እሺ የምትል ይመስልሻል?" አላት ወሬያቸዉ ቀጥሏ ረድኤት ተክዛ በሃሳብ ተዉጣ ቁጭ ብላለች፡፡ ዛሬም መንታ መንገድ ላይ ነች፡፡ ቢኒን ልተወዉ ወይስ እንደምንም ብዬ ላግባዉ፡፡ እማማ በለጡ የረድኤትን በሀሳብ መዋጥ ተመለከቱና ጠጋ ብለዉ "ልጄ ምን ሁነሽብኝ ነዉ? ሰሞኑን ሁኔታሽ ልክ አይደለም" አሏት ረዲም "ምንም አልሆንኩምመ እማዬ" ብላ መለሰችላቸዉ፡፡"የሆነ ነገርማ ደብቀሽኛል፡፡ በፊትኮ እንዲህ አልነበርሽም የኔ ልጅ" እንደ መንቃት እያለች ተንጠራራችና ወገቧን ነቅነቅ አድርጋ"ያዉ እማዬ አሁንስ እንደ በፊቱ ሆንኩልሽ?" አለቻቸዉ፡፡ እማማ በለጡ ጣታቸዉን አገጫቸዉ ላይ ጣል አድርገዉ ..."የኔ ልጅ በህልምሽ ቢኒያም፣ ቢኒ የምትይዉ ማንን ነዉ?"..."ምን?... ማ እኔ?... ኧረ እኔ አላልኩም እማዬ" አለች፡፡ ተደናግጣ ነበር፡፡ እማማ በለጡም ቀስ እያሉ ሊያዉጣጧት ፈልገዉ ..."አንድ ቀን'ኮ ብቻ አይደለም፡፡ ብዙ ጊዜ ነዉ የምትይዉ" አሏት ..."እኔንጃ እማዬ ግን..." ..."ግን ምን የኔ ልጅ?" ይበልጥ ለማወቅ ጓጉተዋል ..."ቢኒያም የሚባል ልጅ ሳልወድ አልቀርም!" ..."ምን?" አሉ እማማ በለጡ ያላወቁ በመምሰል "የኤዲን ባል ቢኒያምን ነዋ?" ..."አይ..." ብላ ንግግሯን ሳጨርስ ረዲ ..."አዎ እሱኑ ነዉ፡፡ አትዋሺኝ የኔ ልጅ፡፡ ባለፈዉም እንዳማረብሽ ሲነግርሽ ሰምቻለሁ፡፡ ለመሆኑ ኤዲ ታዉቃለች?"ብለወ ጠየቋት፡፡ ረድኤት እናቷን ፈራቻቸዉ፡፡ ንግግራቸዉ ወደ ቁጣ እየተቀየረ ይመስላል፡፡ ..."አይ አታዉቅም" አለች ..."የኔ ልጅ!" አሉ እማማ "ባለፈዉ ያባትሽ ሚስት በእኔ ምክንያት እንደሞተች ነግሬሻለኃ?" ..."አዎ እማዬ ነግረሽኛል" ..."ስለዚህ የኔ ልጅ ኤዲም ባንቺ ምክንያት መጎዳት የለባትም፡፡ አንቺና ቢኒያም እንደሆናችሁ ሳጨርሱ አቀሩም፡፡ እኔ ለቢኒያም የምድርሽ የእናንተን መስማማት አይቼ ሳይሆን የኤዲን ፍቃደኝነት ጠይቄ ነዉ!"አሉት፡፡ ረድኤት ደስም አላት ግራ ተጋባችም፡፡ ቢኒያምን ልታገባዉ ነዉ ግን ደግሞ ኤዲ ባትፈቅድስ ..."እና ለኤዲ  ልትነግሪያት ነዉ እማዬ?" ..."አዎ ቀስ ብዬ እነግራታለሁ፡፡ አንቺ አታስቢ የኔ ልጅ" ብለዋት ከተቀመጡበት ተነስተዉ ወደ ዉስጥ ገቡ፡፡ አባባ ሀብታሙ ከዘራቸዉን ይዘዉ ዉጭ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ እንደ አጋጣሚ ኤዲ ከቤት ስትወጣ ፊት ለፊት አየቻቸዉና "አባባ ሀብታሙ ሰላም ኖት" አለቻቸዉ፡፡ እርሳቸዉም "ደህና ነኝ ፈጣሪ ይመስገን ሰላም ነሽ ወይ ኤዲ" ብለዉ መለሱላት፡፡ ከዚያም አጠገባቸዉ ቀረበችና ስለ ረዲ አንዳንድ ነገር ለማወቅ "አባባ ረዲን አትድሯትም እንዴ እድሜዋኮ እየሄደ ነዉ፡፡"አለቻቸዉ፡፡አባባ ሀብታሙም የሷን ጥያቄ ወደ ጎን አሉና "አንቺና ቢኒያም ከተጋባችሁ ምን ያህል ጊዜ ሆናችሁ?" ብለዉ ጠየቋት፡፡ኤዲ ይሄን ጥያቄ ከመለሰች ቡኋላ ቀጣዩ ጥያቄ ምን እንደሚሆን አዉቃለች፡፡ ለጥያቄያቸዉ መልስ መስጠት ስላለባት ብቻ "አራተኛ አመታችንን ይዘናል" አለቻችዉ፡፡"ታዲያ ልጃችሁን ቤተሰቦችሽ ዘንድ አርጋችሁት ነዉ?" ብለዉ ጠየቋት፡፡ ..."አይይ አባባ..." አለቻቸዉ በረጅሙ የብሶት ትንፋሽ እየተነፈሰች፡፡ ተራርቀዉ መቀመጣቸዉ እንጂ ትንፋሿ እንደ በርሃ ወበቅ ይጋረፋል፡፡ ..."ምን ነዉ? የኔ ልጅ?" አሏት ጭንቀቷን ሲያዩ ..."አይ ምንም" አለችና አቀረቀረች ኤዲ፡፡ አባባ የሆነ ነገር እንዳለ ጠረጠሩ፡፡እሳቸዉም የልጅ ፍቅር ስላላቸዉ ጭንቀቷ ይገባቸዋል፡፡ "ልጅ አልወለድኩም አባባ..." አለቻቸዉ፡፡ አስተማሪ የፍቅር ታሪክ📒       በፍቅር ሀይል ተዘጋጅቶ የቀረበ              ታርኩ ቶሎ እንዲቀጥል ካነበባቹ በኋላ like👍 ሳታደርጉ አትለፉ::     ክፍል_13 ይቀጥላል ...         ┄┉✽̶🌺✿❁🌺🌺❁✿🌺̶̥✽̶┉┄

​​​​​✿┈┈🌹┈••✦🌹✦••┈🌹┈┈✿ ፨ "ወሲብ የፍቅር መግለጫ ባይሆንም የፍቅር ማጣፈጫ ነው" የሚለው አባባልስ በናንተ ዘንድ ትክክል ነው ወይስ አይደለም...? ✅ትክክል ❌አይደለም Share and join ❤️ 🌸 @Yefker\_Hayl @Yefker\_Hayl 🌸

​​​​┄┉✽̶🌺✿ምኞትና❤️ፍቅር✿🌺̶̥✽̶┉┄             ▬▬▬❁ ክፍል አስራ አንድ❁▬▬▬ ✍... እማማ ሚረዱ፤ ኮሽታ ሰምተዉ የሚነቁ በአሁኑ አባባል አራዳ የሚባሉ ሴት ናቸዉ፡፡ እስከዛሬም ልጃቸዉን አላጤኗትም እንጂ ቅዠት ከመስማታቸዉ ቀድመዉ ያዉቁባት ነበር፡፡ ይሄዉ አሁን ደግሞ ስሙ ቢላቸዉ በራቸዉ ስር መጥቶ ቢኒያም ልጃቸዉን ረድኤትን እያዋራት ነዉ፡፡ ..... "ቢኒ ምን ብዬ እንደምነግርህ አላዉቅም፡፡ ግን... ትቸዋለሁ፡፡ ምክንያቱም አንተን ላገኝህ አልችልም፡፡ ኤዲንም ላሳዝናት አልፈልግም፡፡" አለችዉ ረዲ ቢኒም....."ረዲ እሱን ላወራሽ አልነበረም፡፡ በጣም እንዳማረብሽ ልነግርሽ ነበር አመጣጤ! በይ ደህና ዋይ" ብሏት መልሷን ሳይሰማ ጥሏት ሄደ፡፡ ረድኤት በህይወቷ እንደዚች ሰዓት የተደሰተችበት ቀን የለም፡፡ ደስታ ቢገል ኑሮ ቢኒ "በጣም እንዳማረብሽ ልነግርሽ ነበር አመጣጤ" ካላት በኃላ ትንፋሿ ፀጥ ብሎ ትሞት ነበር፡፡ ከበር እስከሚወጣ በአይኗ ከሸኘችዉ ቡኃላ ከተቀመጠችበት ተነስታ መስተዋት ፍለጋ እየሮጠች ስገባ እናቷ የመስኮቱን መስተዋት ከፍተዉ እንደማፅዳት እያደረጉ ነበር፡፡ ደነገጠች፡፡"እማዬ ስናወራ ሰምታን ይሆን እንዴ?" ብላ አሰበች፡፡ የእናቷ ነገር ደስታዋን እንዳያከስምባት ቶሎ ብላ ወደ መኝታ ክፍሏ መስተዋቱ ፊት ተገተረች፡፡ 'እዉነትም ቆንጆ ነኝ!" ስትል ለራሷ አሰበች፡፡ረዲን በጣም ብዙ ወንዶች ግማሹ ለትዳር፣ ግማሹ ለአዳር፣ ሌላዉ ደግሞ ለፍቅር ጓደኝነት ሲጠይቋት አላማና ኢላማ ያላት ስነ-ስርዓት ያላት ልጅ ስለነበረች ሁሉንም ገፍታ አባራቸዋለች፡፡ ለቁጥር የሚያዳግቱ ብዙ ወንዶች ለዉበቷ ቋምጠዉላታል፤ በጣም ዉብ ነች፡፡ብዙ ሰዎች የቁንጅናዋን ልክ ለመናገር ቃላት ደርድረዋል፡፡ እሷ ... ግን ለጊዜያዊ ስሜት የምትረታ የዋዛ አልነበረችምና አሻፈረኝ ብላለች፡፡ የቢኒ አንዷ ቃል ግን ዉስጧ ገብቷል፡፡ ልትተወዉ የነበረችዉን ሴት እንደገና የልቧን ፍም ጭሮባታል፡፡ "ቢኒንማ አልተወዉም!!" የረዲኤት ዉሳኔ ነበር፡፡ ... ኤዲ ከእንቅልፏ እንደነቃች በባሏ እጅ የተከሸነዉን ጣፋጭ ቁርስ ማጣጣም ይዛለች፡፡ ቁርሷን በልታ ሳጨርስ ተኝታበት ወደነበረዉ አልጋ ዘወር ስትል ከትራሷ ስር ብጣሽ ወረቀት አየች፡፡ አነሳችዉና ስትገልጠዉ "የኔ ፍቅር አፈቅርሻለሁ፡፡ ፈጣሪ ይጠብቅሽ!" የሚል ፅሁፍ አነበበች፡፡ ደስታ ልቧን ፈነቀለዉ፡፡ ቢኒ እዉነትም ፍቅር ነዉ፡፡ ቁርስ ሰርቶ አካሏን ከመጠገኑም በላይ 'አፈቅርሻለሁ' ብሎ የመንፈስ ምግብ ሰጣት፡፡ ባዲስ ንጋት ከቁርስ ጋር ፍቅር መገባት፡፡ኤዲ አዳሯን እንቅልፍ ማጣቷን ሁሉ እረሳችዉ፡፡ በደስታ ተፍነከነከች፤ በሀሴት ጮቤ እረገጠች፡፡ በዚህ ልዩ ጧት፤ በዚህ ልዩ ቀን የጧቷን ፀሐይ ልትሻማ ከቤቷ ወጥታ ለፀሐይ ጀርባዋን ሰጥታ ቁጭ አለች፡፡ ...... ረድኤት ቆንጆ መባሏ ሳያንስ ሌላ ዉበት፤ ሌላ ድምቀት ተላብሳ፤ ንጋቷን በፍቅር አድሳ እሷም እንደ ኤዲ የፀሐይን ሙቀት ልትኮመኩም ወጣች፡፡ ከመዉጣቷ ኤዲን ስላየቻት ወደሷ ሄደች፡፡ ረድኤት ላይ ዉበት ጎልቷል፤ ኤዲ ላይ ደግሞ ደስታ ነግሷል፡፡ ሁለቱም ለጨለማ ድምቀት እንደሆነችዉ ጨረቃ ደምቀዋል፡፡ ሰላምታ ከተለዋወጡ ቡኃላ ኤዲ፡ ረዲን... ..... "ዛሬ ወደየት ልትሄጂ ነዉ ባክሽ ተሽቀርቅረሻልሳ" አለቻት ረድኤትም ..... "ኤዲዬ አንቺምኮ አምሮብሻል ምን ተገኝቶ ነዉ?" ....."እኔማ የዉበቴም የድምቀቴም ምክንያት ባሌ ነዉ፡፡......" ብላ ስለ ቁርሱ፤ ስለ ወረቀቱ ምንም ሳታስቀር ለረዲ ነገረቻት፡፡ ኤዲና ረድኤት በደንብ ተግባብተዋል፡፡ ብዙ ሚስጥሮችን አብረዉ እየተጋሩ ነዉ፡፡ ረዲ ለኤዲ 'ባልሽን ልቀማሽ ነዉ ተዘጋጂ!" የሚለዉ ሲቀር፡፡ .....ኤዲም "አንቺስ የዚህ ዉበት ምንጭ ማን ይሆን ረዲ?" አለቻት፡፡ ባልሽ ቢኒያም ነዉ አትላት ነገር... እ እ እያለች ስትደናገጥ የረድኤት አባት ከቤት ዉስጥ ወጡና "እንዴት አደርሽ ኤደን" ብለዉ ጨዋታቸዉን አቋረጧቸዉ፡፡ ...... "ደህና አደሩ አባባ" ብላ መለሰችላቸዉ፡፡ አባባ  ትንሽ ቀለድለድ ካደረጉ ቡኃላ ... "ኤዲ" አሏት፡፡ ..."አቤት አባባ" አለቻችዉ፡፡ ..."ኧረ እቺን ጓደኛሽን ምከሪያት እስኪ" ..."ማንን? ረድኤትን?" ስትላቸዉ ..."መቼም በለጡን ምከሪያት አልልሽ የኔ ልጅ" ሲሉ ሁሉም ተሳሳቁ፡፡ አባባ ቀልዳቸዉና ምራቸዉ አያስታዉቅም፡፡ ቁም ነገር እያወሩ በመሃል ይቀልዳሉ፡፡ በቀልዱም መሃል ያመራሉ፡፡ ሁሌም ፀባያቸዉ እንዲህ ነዉ፡፡ ቀጠል አደረጉና.... ..."ባል እየተንጋጋ ይመጣል እሷ ግን አሻፈረኝ አለች፡፡ ሁሌም ልማር ነዉ የምትለዉ፡፡ አግብቶስ ትምህርት የከለከላል እንዴ የኔ ልጅ?" ብለዉ ጠየቋት ኤዲን፡፡ ረድኤት አንዴ ኤዲን፤ አንዴ አባቷን እያየች የሚሉትን ትሰማለች፡፡ ..."አይ አይከለከልም፡፡ እንደዉም ሴት ልጅ በጊዜ ስታገባ ነዉ ጥሩዉ" አለቻቸዉ ..."ተባረኪ የኔ ልጅ" አሏት ደስ ብሏቸዉ "...እንደዉም እንደ ቢኒያም አይነት ባል ፈልጊማ ኤዲ፡፡ ሳልጠይቃት ነዉ የምድራት" ሲሉ ሁሉም ተሳሳቁ፡፡ ረዲ "እሱ እራሱ ቢኒ በመጣ"አለች በዉስጧ፡፡ ..... ጨዋታዉ እንደቀጠለ ነዉ፡፡ እማማ በለጡም አራተኛ ተጨምረዉ ወሬዉን አድምቀዉታል፡፡ . ቢኒ በንግግሩ ኤዲን እንዳስደሰታት አዉቋል፡፡ ይበልጥ ወደ እሱ እንድትቀርብ ያደረገዉም ዘዴ ነዉ፡፡ ከኤዲ ጋር በተነጋገሩት መሰረት ሁለተኛ ማግባት እንዳለበት ወስነዋል፡፡ ሌላ ሴት ፍለጋ መኳተን አልፈለገም፡፡ እዚሁ እፊቱ በሱ ፍቅር የተራበችዉን ረድኤትን ሊያገባት ነዉ፡፡"ግን... በምን መልኩ? አባቷስ እሺ ብለዉ ይድሩልኝ ይሆን?" እያ ያስብ ጀመር፡፡... . ......"ረዲዬ..." አሏት እማማ በለጡ ልጃቸዉን ..."ወይዬ እማዬ...." ቤት አብረዉ ቁጭ ብለዉ ነበር፡፡ አባባ ስለሌሉ ረድኤትን የሚያዋርባት ምቹ ጊዜ አግኝተዋል እማማ በለጡ፡፡ ... "አባትሽ ሁለት ሚስት እንደነበረዉ ታዉቂያለሽ?" ረድኤትም "ኧረ እማዬ አላዉቅም፡፡" አለች መልሱን ለማሳጠር ያክል፡፡ ምክንያቱም ወደ እሷ ቀስ እያሉ እንደሚመጡ አላጣችዉም፡፡ .... "ይሄዉልሽ የኔ ልጅ! አባትሽ መጀመሪያ ሌላ ሚስት ነበረችዉ..." "ካንቺ በፊት?" ብላ ሊቀጥሉት የነበረዉን ወሬ አቋረጠቻቸዉ፡፡ በዚያም ላይ ደንግጣለች፡፡ረድኤት እስካሁን ድረስ እናቷ የአባቷ ሁለተኛ ሚስት እንደነበረች አታዉቅምና፡፡ ...."አዎ ከኔ በፊት ሌላ ሚስት ነበረችዉ" ...."እና ምን ሆነች ማሚ? ፈቷት ነዉ ወይስ...?" ...."አይ አልፈታትም ነበር፡፡ ሙታ ነዉ ፈጣሪ ነብሷን ይማራትና" አሉ ...."እንዴት?... ለምን?... ማለቴ ...በምን ምክንያት ሞተች?"... አስተማሪ የፍቅር ታሪክ📒       በፍቅር ሀይል ተዘጋጅቶ የቀረበ ታርኩ ቶሎ እንዲቀጥል ካነበባቹ በኋላ like♥️ ሳታደርጉ አትለፉ::     ክፍል_12 ይቀጥላል ...         ┄┉✽̶🌺✿❁🌺🌺❁✿🌺̶̥✽̶┉┄

​​​​♥️♥️ያለህበት/ሽበት የፍቅር ግኑኝነት ጤናማ እንዳልሆነ የሚያሳዩ ምልክቶች♦️ ★፠★፠★♥️፠♥️★፠★፠★፠ 1♥️. ካሁን ይልቅ ያለፈውን መልካም ጊዜ ብቻ እያስታወስን መኖር ስንጀምር። 2♥️.የፍቅር ግንኙነት ከደስታ ይልቅ የሀዘናችን ምንጭ መሆን ሲጀምር። 3♥️. የፍቅር ጓደኛህ/ሽ እንድትለወጥ/ጪ ሲጠብቅ/ስትጠብቅ። 4♥️. የፍቅር ግንኙነቱ የስነልቦና ጉዳትን ሲያስከትልብህ/ሽ። 5♥️. ካሁን ቀደም ተነጋግራችሁ የፈታችሁት ችግር ደግሞ ደጋግሞ ሲከሰት። 6♥️. የፍቅር ጓደኛህ/ሽ ለግንኙነቱ መዳበር ጥረት ማድረግ ሲተው/ስትተው። 7♥️. በመካከላችሁ መሰረታዊ የሆነ የእምነት እና የእሴት ልዩነት ሲኖር። 8♥️. አንዳችሁ ለሌላኛችሁ ያላችሁ የፍቅር ክብር ደራጃው ሲለያይ። 🌹━━━✦◉●••┈❀┈┈••●◉✦━━━ 🌹 ❣ 🌸🌺🌸🌺🌸 ❣ 💞የፍቅር ሀይል♥️ ┈┈••◉❖◉●••┈❀┈┈••◉❖◉●••┈┈

​​​​💔!!!​ትክክለኛ አፍቃሪ!!!💔 🧥ውበትሽን አይቶ የተመኘሽ እና ከውበትሽ ጀርባ ያለውን ማንነትሽን አውቆ 💞ያፈቀረሽ💞 ሰው የተለያዩ ናቸው። ለምን እነደዚህ አልከኝ እንዳትይኝ ? ❣እኛ ወንዶች የፈለግነውን እስክናገኝ ሴትን ንግስት ማድረግ እናውቅበታለን ። ያፈቀረ ግን ንግስቱን ንግስቴ ብሎ ለመጥራት እንኳን ቃል አጥሮት ይንተባተባል፤ ውበትሽን ለመግለፅ እንኴን አንደበት የለውም፤ ነገር ግን በውስጣዊ ማንነትሽ እሱነቱን አጥቶ ሌት ከቀን አንቺን በምናቡ ሲያወጣና ሲያወርድ ውበትሽን ለመግለፅ ሲቸገር ፣ የአንቺን ህይወት በማድመቅ የራሱን ሲያፈዝ፣ 💞ከሰው በላይ የነበረው ማንነቱን መቀመቅ ሲያወርድ........ያኔ ላንቺ ያንስብሻል። እናም ፍቅርሽን ገላሽን ለተመኘው ትሰጪና ደግመሽ ብትፈጠሪ እንኴን የማታገኝውን ንፁህ አፍቃሪሽን ልብ አንኮታኩተሽ ጥለሽ ትሰብሪዋለሽ ። እሱም ለዘለዓም ልቡ ታሞበት እንደማቀቀ ፍቅሩን ተቀምቶ አዝኖ አፈር ይሆናል። ❣ አንቺ ሳታውቂ ራስሽን የሰጠሽው ግን አውቆ ይተውሻል። 💝በቃላት ድርደራ በስጦታ ጋጋታ በአፉ ንግስት ያስመሰለሽ.......ያሻውን ፈጽሞ ሲያበቃ ከጥፍሩ ቆሻሻ እንኴን ሳይቆጥርሽ ይርቅሻል ። ለዚህ ነው የተመኘሽ እና ያፈቀረሽ የተለያዩ ናቸው የምልሽ። ምርጫው ግን ያንቺ ነው። ♥️ፈጣሪ ለሁሉም ሰው የሚመኘውን ሳይሆን በልቡ የሚያፈቅረውን ይስጠው !!! 📨ሼር and ላይክ💌