ar
Feedback
Vision Academy Grade 6

Vision Academy Grade 6

قناة بسيطة
486
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

ማሳሰቢያ ለተማሪዎችና ለወላጆች! ከት/ት ቢሮ በተሰጠን መመሪያ መሠረት የ2013 ዓ/ም የትምህርት ዘመን እስከ ሀምሌ 20/ 2013 ዓ/ም እንድናጠቃልል በተቀመጠልን የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ለትማሪዎችም እንደገለጽነው ከ1ኛ - 4ኛ ክፍል በሁለቱም ፈረቃ የሚማሩ ተማሪዎች የ4ኛው ሩብ ዓመት ምዘና፦ ዐርብ ሐምሌ 09 እና ቅዳሜ ሐምሌ 10/ 2013 ዓ/ም ይወስዳሉ፡፡

ለተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ ከአዲስ አበባ ት/ቢሮ በተላለፈው መመሪያ መሰረት የትምህርት ካላንደር ክለሳ ተደርጓል። ክለሳውን ተከትሎ የተሻለ አፈጻጸም እንዲኖረን የት/ቤታችን ማኔጅመንት የሚከተለውን የፈረቃ ማሻሻያ ማድረጉን እንገልጻለን። ✅ ከ9-11ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ከሰኞ ሰኔ 28/2013 ዓ.ም ጀምሮ በፈረቃ ሲሰጥ የነበረው ትምህርት ቀርቶ ሙሉ ሳምንቱን ከሰኞ - ቅዳሜ የሚሰጥ ይሆናል። ✅ ከአፀደ ህፃናት እስከ 7ኛ ክፍል ድረስ የሚማሩ ተማሪዎች የፈረቃ ትምህርቱ በነበረበት ይቀጥላል። ስለሆነም ወላጆች በዚህ መሰረት ልጆቻችሁን እንድትልኩ እናሳስባለን። የት/ቤቱ አስተዳዳር!

ለቪዥን ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ:: የ3ኛ ሩብ አመት የመምህር-ወላጅ የምክክር ቀን የሚካሄደውና ሪፖርት ካርድ የሚሰጠው ቅዳሜ በ26/10/13 ዓ.ም መሆኑን በድጋሚ እያስታወስን ልጆቻችሁ በሚማሩበት ካምፓስ በመሄድ ከጠዋቱ 2፡30-6፡30 ባለው ሰዓት በመገኘት ውጤታቸውን እንድትወስዱ እናሳስባችኋለን። የት/ቤቱ አስተዳደር!

ለቪዥን ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ:: የ3ኛ ሩብ አመት የመምህር-ወላጅ የምክክር ቀን የሚካሄደው ቅዳሜ በ 26/10/13 ዓ.ም ሲሆን፣ ከመጪው ሰኞ ሰኔ 21/10/2013 ዓ.ም ጀምሮ የፈረቃ ለውጥ የሚደረግበት ሳምንት መሆኑን እያሳወቅን ለቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት ልጆቻችሁን በተገቢው ፈረቃ እንድትልኩ ማሳሰብ እንወዳለን፡፡ የት/ቤቱ አስተዳደር!

ውድ ተማሪዎችና ወላጆች! መጪው ሰኞ ሰኔ 14/2013 ዓ.ም ምርጫ የሚካሄድበት ቀን ስለሆነ ትምህርት አይኖረንም። የሚቀጥለው ሳምንት ትምህርት በነበረው ፈረቃ የሚቀጥል ሲሆን፥ የፈረቃ ለውጥ የሚደረገው ከሰኔ 21/2013 ጀምሮ መሆኑን እንገልጻለን። የትምህርት ቤቱ አስተዳደር!

ከKG - 12ኛ ለሚማሩ ተማሪዎችና ወላጆች የ3ኛው ተርም ማጠቃለያ ፈተና ከሰኔ 7 እስከ ሰኔ 12 ባሉት ቀናት የሚጠናቀቀው በጠዋቱ ክ/ጊዜ መሆኑን አውቃችሁ ከ6፡30 ጀምሮ ልጆቻችሁን እንድትወስዱ እያሳሰብን፣ ሰኞ ሰኔ 14/2013 የዐራተኛው ሩብ ዓመት ትምህርት የሚጀመር መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን። መልካም ውጤት ለልጆቻችን እንመኛለን! የትምህርት ቤቱ አስተዳደር!

photo content

ከKG - 12ኛ ለሚማሩ ተማሪዎችና ወላጆች የ3ኛው ተርም ማጠቃለያ ፈተና ከሰኔ 7 እስከ ሰኔ 12 የሚሰጥ መሆኑን አውቃችሁ ወላጆች ልጆች ቤት በሚሆኑበት ቀናት አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ክትትላችሁና እገዛችሁ እንዳይለያቸው እናሳስባለን፡፡ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር!

ውድ ተማሪዎችና ወላጆች! ከመጪው ሰኞ ግንቦት 30/2013 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣይ ሁለት ሳምንት የፈረቃ ለውጥ የሚደረግ ስለሆነ ልጆቻችሁን በተገቢው ፈረቃ ወደ ት/ቤት እንድትልኩ እናሳስባለን።

ውድ ወላጆችና ተማሪዎች፥ ከት/ቤቱ የሚላኩ አጠቃላይ መረጃዎችን ለማግኘት የሚያስችልዎት ቻናል- Vision Academy https://t.me/joinchat/Fm01fl0TN-w0MmRk የሚለው ነው። እስካሁን ካልተቀላቀሉ ከት/ቤቱ የሚላኩ መሰረታዊ መረጃዎች እንዳያመልጥዎት ማስፈንጠሪያውን በመጫንእንድትቀላቀሉ በአክብሮት እናሳስባለን ።

ውድ ወላጆች የ4ኛው ሩብ ዓመት የትምህርት አገልግሎት ክፍያ እስከ ሰኔ 5/2013 መሆኑን አውቃችሁ የመክፈያ እስሊፕ ባንክ የተቀመጠ በመሆኑ እንድትከፍሉ ልናሳስባችሁ እንወዳለን። የትምህርት ቤቱ አስተዳደር!

ውድ ወላጆችና ተማሪዎች፥ ከት/ቤቱ አጠቃላይ መረጃዎችን ለማግኘት የሚያስችልዎት ቻናል- Vision Academy https://t.me/joinchat/Fm01fl0TN-w0MmRk የሚለው ነው። ማስፈንጠሪያውን በመጫንእንድትቀላቀሉ በአክብሮት እናሳስባለን ።

ውድ ወላጆች! ከመጪው ሰኞ ግንቦት 16/2013 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣይ ሁለት ሳምንት የፈረቃ ለውጥ የሚደረግ ስለሆነ ልጆቻችሁን በተገቢው ፈረቃ ወደ ት/ቤት እንድትልኩ እናሳስባለን።

ውድ ወላጆች ከት/ቤቱ አጠቃላይ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት ልጅዎ ከሚማርበት ክፍል ቻናል በተጨማረ በአማራጭነት ከተዘጋጁት ቻናሎች መጀመሪያ ላይ የሚገኘውን "Vision Academy" የሚለውን ቻናል በመፈለግ ወይም ቀጥሎ ያለዉን ማስፈንጠርያ https://t.me/joinchat/Fm01fl0TN-w0MmRk በመጠቀም እንድትቀላቀሉ በአክብሮት እናሳስባለን ።

ውድ ወላጆች ከት/ቤቱ አጠቃላይ መረጃዎችን በየጊዜው ለማግኘት ልጅዎ የምማርበት ክፍል ቻናል በተጨማረ በ አማራጭነት ከተዘጋጅት ቻናሎች ቀዳም የሆነዉና "Vision Academy" የሚለውን ቻናል በመፈለግ ወይም ቀጥሎ ያለዉን ማስፈንጠርያ https://t.me/joinchat/Fm01fl0TN-w0MmRk በመጠቀም እንድትቀላቀሉ በአክብሮት እናሳስባለን ።

ማሳ ሰቢያ፡በፈተና ቀናት ተማሪዎች ሙሉ ቀን ት/ቤት ስለሚውሉ ምሳ ይዘው መምጣት ይኖርባቸዋል።
ማሳ ሰቢያ፡በፈተና ቀናት ተማሪዎች ሙሉ ቀን ት/ቤት ስለሚውሉ ምሳ ይዘው መምጣት ይኖርባቸዋል።

ውድ የእስልምና እምነት ተከታይ ወላጆች ኢድሙባረክ እንኳን አደረሳችሁ እያልን ሐሙስ፤ ግንቦት 05፤ 2013 ዓ.ም በዓል በመሆኑ ምክንያት ት/ቤት ዝግ እንደሚሆን እያሳሰብን፣ ነገ ረቡዕ፤ ግንቦት 04፤ 2013 ዓ.ም መደበኛ የመማር ማስተማር ህደት የሚቀጥል መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን። ት/ቤቱ

ቀን:29/08/13 ዓ.ም የፈረቃ ለውጥ መረጃ ዛሬ አርብ ሚያዝያ 29 2013 ዓ.ም ትምህርት ቤት የመጡ ተማሪዎች ለቀጣይ ሁለት ሳምንታት ማክሰኞ፣ሐሙስ፣ቅዳሜ የሚማሩ ሲሆን ነገ ቅዳሜ ሚያዝያ 30/2013 ዓ.ም ትምህርት ቤት የሚመጡ ተማሪዎች ለቀጣይ ሁለት ሳምንታት የሰኞ፣ረቡዕ፣አርብ ፈረቃ ይሆናሉ። በዚህ መሰረት ወላጆች ልጆችን በፈረቃቸው እንዲልኩ እናሳስባለን።ያለፈረቃቸው የሚመጡ ተማሪዎች አይስተናገዱም።

Welcome to the new channel for grade 3!You will receive messages from the school through this channel. Thank you!