486
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
ውድ የቪዥን አካዳሚ ወላጆች
ዐርብ ታኅሳስ 5/2016 ዓ.ም ከ2:30-9:00 የ1ኛ ተርም ውጤት የሚሰጥበትና ስለ ልጅዎ የትምህርትና የስነ ምግባር ሁኔታ ውይይት የሚደረግበት ዕለት ስለሆነ በሰዓቱ ልጅዎ በሚማርበት/በምትማርበት ግቢ ተገኝተው ልጅዎን በተመለከተ በውይይቱ እንዲሳተፉ በአክብሮት ጠርተኖታል።
የት/ቤቱ አስተዳደር
📩ዉድ ወላጆች📨
ከወላጆች በቀረበልን ጥያቄ መሰረት ከት/ት ሰአት በኋላ በሣምንት ለ3 ቀናት ፍላጐት ላላቸው ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ለመስጠት ዝግጅታችንን አጠናቀን ሰኞ ፣ ታህሳስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ኘሮግራሙ ይጀምራል፡፡
📌የማጠናከሪያ ት/ት የሚሠጠው በሣምንት ለ3 ቀናት (ሰኞ ፣ እሮብ እና አርብ) 🕰 ከ9፡15-10፡15 ይሆናል፡፡
📌በዚህም መሰረት ልጅዎ እንዲታገዝ የሚፈልጉ ከሆነ በማስመዝገብ ት/ት ማሰጀመር የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ት/ቤቱ
World HIV/AIDS Day is celebrated in our School with the theme 'Let Communities Lead'
📩ውድ ወላጆች📨
📌ሰኞ ህዳር 17/2016 ዓ.ም ለ ተማሪዎች የፈተና ግብረ መልስ የሚሠጥ ሲሆን ተማሪዎች እስከ 6:00 የሚቆዩ መሆኑን በድጋሚ ልናሳስባችሁ እንወዳለን።
📌ማክሰኞ ህዳር 18/2016 ዓ.ም መምህራኖች በመማር ማስተማር ዙርያ ስለጠና ስለሚኖራቸው ተማሪዎች እቤታቸው ይቆያሉ።
📌 ረቡዕ ህዳር 19/2016 ዓ.ም የ2ኛ ሩብ ዓመት ትምህርት ይጀመራል።
ት/ቤቱ!
ውድ ወላጆች
👉ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል የሂሳብ
መፅሐፍ፤
👉ከ4ኛ ክፍል ውጪ ከ1ኛ እስከ 8ኛ እንግሊዝኛ መፅሐፍ፤
👉 የ6ኛ ክፍል ግብረ ገብ እና አፋን ኦሮሞ፤
👉 የ7ኛ ክፍል ዜግነት ትምህርት(citizenship) መፅሐፍ
ስለመጣ ዋናው ግቢ በመምጣት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ት/ቤቱ!
ውድ ወላጆች
ነገ ቅዳሜ ህዳር 15/2016 ዓ.ም የማጠናከሪያ ትምህርት(ለ 6ኛ እና 8ኛ ክፍል) የማይኖር መሆኑን እናሳውቃለን።
ት/ቤቱ
ውድ ወላጆች
የ2ኛ ሩብ ዓመት የትምህርት አገልግሎት ክፍያ እንድትከፍሉ ባሳሰብናችሁ መሠረት ክፍያውን የፈፀማችሁትን ወላጆች እያመሰገንን፣ ያልከፈላችሁ ወላጆች የመጨረሻው የመክፈያ ቀን ህዳር 15 /2016ዓ.ም መሆኑን ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡
ለክፍያ ስትመጡ
የልጅዎ መታወቂያ ላይ ያለውን መለያ ቁጥር በመያዝ በተመቻችሁ የአቢሲኒያ ባንክ ቅርንጫፎች በመሄድ
በአካውንት ቁጥር 5208599 ገቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡
የቪዥን አካዳሚ አስተዳደር
📩ውድ የተከበራችሁ ወላጆች፣📨
📌የ1ኛው ሩብ ዓመት የመጨረሻ ፈተና ከሰኞ፣ ህዳር 10 ፣ 2016 እስከ ዓርብ፣ ህዳር 14 ፣ 2016 በተላከዉ ፕሮግራም መሰረት የሚሰጥ ይሆናል።
📌ልጅዎን እቤት ውስጥ ለማገዝ የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ ይበሉ።
📌መልመጃ 1፣ 2፣ ፈተናዎችን፣ ማስታወሻዎችን፣ የመማሪያ መጽሃፎችን እና ሌሎች ግብአቶችን በመጠቀም በ1ኛዉ ሩብ ዓመት የተማሩትን በማንበብ ለፈተና ይዘጋጁ፡፡
📌ተማሪዎች በቤት ውስጥ የመለማመጃ ፈተናዎችን እና የጥያቄ እና መልስ ክፍለ ጊዜዎችን በመጠቀም ከቤተሰቦቻቸው ጋር ያንብቡ፡፡
📌ተማሪዎች ጊዜያቸውን በተሳካ ሁኔታ ለመጠቀም በቤት ውስጥ ስልኮችን፣ ኮምፒዩተሮችንና ቲቪን ከማየት እንዲቆጠቡ ያድርጉ ።
👉 በፈተና ቀናቶች ተማሪዎች እስከ 6:00 ስዓት የሚቆዩ ይሆናል።
👉ሰኞ ህዳር 17/ 2016 ዓ.ም የፈተና ግብረ መልስ ለተማሪዎች ይሰጣል። በእለቱ ተማሪዎች እስከ 6:00 ሰዓት ት/ቤት ይቆያሉ።
👉ማክሰኞ ህዳር 18 / 2016 ዓ.ም የ 2ኛ ሩብ አመት ትምህርት ይጀመራል።
በዝግጅታቸው ወቅት ልጅዎን በማገዝ ለተሻለ ውጤት እንስራ።
ስለ ምንገዜውም ትብብርዎ እናመሠግናለን!!
ትምህርት ቤቱ.
__
ውድ ወላጆች
👉ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል የሂሳብ
መፅሐፍ እና
👉የ4ኛ ክፍል እንግሊዝኛ መፅሐፍ
ስለመጣ ዋናው ግቢ በመምጣት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ት/ቤቱ!
ውድ የቪዥን አካዳሚ ወላጆች
የትምህርት አገልግሎት ክፍያን ጊዜ ማሣወቅን ይመለከታል፣
የክፍያ ጊዜ
-የመጀመሪያ ሩብ አመት (1st quarter) ክፍያ በተማሪዎች ምዝገባ ወቅት የተሰበሰበ ሲሆን፡-
1. የ2ኛ ሩብ ዓመት (2nd quarter) ክፍያ ከጥቅምት 30 - ህዳር 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ይጠናቀቃል።
2. የ3ኛ ሩብ ዓመት (3rd quarter) ክፍያ ከጥር 30 - የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ሲሆን
3. የ4ኛ ሩብ ዓመት (4th quarter)
ክፍያ ከሚያዝያ 2- ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ብቻ ይሆናል።
የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ከላይ በተገለፀው መሠረት እንዲከፈል እያሣሠብን በጊዜ ገደብ ካልተፈፀመ ከዚህ በታች በተዘረዘረው ሁኔታ ቅጣት ተጨምሮ ይከፈላል፡፡
የቅጣት ክፍያ ዝርዝር
-ከክፍያ ማጠናቀቂያ የጊዜ ገደብ በኋላ የመጀመሪያ ቀን ቅጣት ብር 50.00 (ሃምሳ )
-በሁለተኛው ቀን ጀምሮ እስከ ሳምንት መጨረሻ ድረስ በየቀኑ ብር10.00(አስር) እየተጨመረ ይከፈላል፡፡ በዚህ መሠረት ብር 60፣ 70፣ 80፣ 90፣ 100 እና 110 ብር
ቀጥሎ ባለው ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ በየቀኑ ብር 20.00 (ሃያ) ብር እየተጨመረ ይከፈላል ይኸውም በአኃዝ ሲገለጽ ብር 130፣ 150፣ 170፣ 190፣ 210፣ 230 እና 250 ይሆናል፡፡
ከዚህ ቀጥሎ ባለው በየቀኑ ብር 30.00 (ሰላሳ) እየተጨመረ ይከፈላል፡፡ይህ ማለት ብር 280፣ 310፣ 340፣ 370፣ 400፣ 430 እና 460 ብር ሆኖ በመጨረሻው ከ4ኛ ሳምንት በኋላ በየቀኑ ብር 40.00(አርባ)እየተጨመረ ማለትም 500፣ 540፣ 580 ወዘተ እያለ ክፍያ እስከ ሚጠናቀቅ ድረስ የሚከፈል ሲሆን ይህም በመደበኛው የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ጋር ተደምሮ ይከፈላል፡፡
-የትምህርት ቤት ክፍያ ከወሩ ካለፈ በተቋሙ የወላጅ ተማሪ መመሪያ መሠረት አገልግሎት የሚቋረጥ ይሆናል፡፡
እንደተለመደው ወላጆች ደረሰኙን ለማግኘት ወደ ትምህርት ቤት መምጣት ሳያስፈልጋቸው ከአፀደ ሕፃናት እስከ 8ኛ ክፍል ላሉት ተማሪዎች ከመምህር ወላጅ ግንኙነት ማኑዋል (Communication book) ጋር አያይዘን መላክ የምንችል ሲሆን ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ላሉት ተማሪዎች በእጃቸው የሚላክ ሆኖ ወላጆች ተከታትለው እንዲቀበሉ እናሳስባለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር!
Congratulations 🎉 to all Parents, Students, and the community of our school!!
