cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Abu_Oubeida~channel

من أحب أن لا ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم {ابن الجوذي رحمه الله /التذكرة(٥٥)

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
8 665
المشتركون
-424 ساعات
+2607 أيام
+84930 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ጌታዬ ሆይ ሚስኪን አድርገኝ!! ~~ መልእክተኛው አለይሂ ሶላቱ ወስሰላም፡እንዲህ አሉ፦ ጌታዬ ሆይ! ሚስኪን አድርገህ አኑረኝ፤ሚስኪን አድርገህም ግደለኝ፤በእለተ ትንሳኤ ቀንም ከመሳኪን ስብስቦች ጋር አድርገህ ሰብስበኝ። 📚ሶሐሐሁ_ል አልባኒ ፊ ተስሒሒ_ል አት'ቲርሚዚ፡(2352) አቡ ዑበይዳ t.me/AbuOubeida
إظهار الكل...
Abu_Oubeida~channel

من أحب أن لا ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم {ابن الجوذي رحمه الله /التذكرة(٥٥)

👍 16
ቀጥተ ስርጭት የተፍሲር ደርስ ሡረቱ አንነምል አንቀፅ 41 ላይነዉ በሸይክ አወል ቢን አሕመድ https://t.me/SheihkAbuAmarAwolIbnuAhmed?livestream=f41651bd2e91af6d69
إظهار الكل...
قناة دروس فضيلة الشيخ أبو عمار أول بن أحمد الخميسي

الْقَنَاةُ الرَّسْمِّيةُ لِفَضِيلِةِ الْشَّيْخِ أَولِ بْنِ أَحْمَدَ الْخميسي -حَـفِظَهُ اللّه تَعَالَى

=>አላህ ይዘንላቸውና ቀታዳ እንዲህ ይላሉ፦ ቁርአን በሽታችሁንም ይሁን መድሃኒቱን ይጠቁማችኋል። *በሽታው=ወንጀል ሲሆን *መድሃኒቱ ደግሞ=ካሳለፉት ወንጅል አላህን ይቅርታ መጠየቅ ነው። 📚ሹዓቡ_ል ኢማን 9/347 አቡ ዑበይዳ t.me/AbuOubeida
إظهار الكل...
Abu_Oubeida~channel

من أحب أن لا ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم {ابن الجوذي رحمه الله /التذكرة(٥٥)

👍 16
Add a comment
ጭፍራው ቅርቃር ውስጥ ገብቷል ~ ቅልጥ እንደ ቅቤ - ፍርስ እንደ ሸክላ ሁሉ ነገር እርቃን - እነ ሳይሞቅ ፈላ! ይሄ ሰካራም ጭፍራ ብዙ እንደማይራመድ በጣም እርግጠኛ ነበርኩ። በዚህ ፍጥነት ድንብርብሩ ሲወጣ፣ ጉዱ ሲዝረከረክ ማየት ግን የጠበቅኩት አልነበረም። የዛሬን ሁለት ዓመት መሰለኝ ወራቤ ላይ አንድ ወንድም ዐብዱልሐሚድ ለተሞ አንድ መንሀጅ ላይ ሁለት አመት ታግሶ መቆየት አይችልም ጠብቁ ሲል ሰምቼው ነበር። ምናልባት የሆነ ያክል ተጋኖ ይሆን? አላውቅም። ንግግሩ ግን በውስጡ የሆነ እውነት አዝሏል። አሁን ላይ አንዳንድ ነገሮች ጫፋቸው እየዘለቀ ነው። እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል እንዲሉ ይሄው እየጠራ መጣ። በየጊዜው እየወጡ ካሉ በርካታ የቪዲዮ እና የፎቶ ማስረጃዎች ውስጥ ለጊዜው አንድ ማሳያ ልጥቀስ፦ ጠሃ ኸዲር የዚህ የተንቀዠቀዠ ጭፍራ አጫፋሪ መሆኑ ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። ሶሻል ሚዲያ ላይ እየዘለቀ ሁለት ሶስት መስመር ስድብ መፃፍን ቁም ነገር ያደረገ በተግባር ግን በተለያየ ቦታ የተለያየ ፊት የሚጠቀም ሰው ነው። * ሳዑዲ ውስጥ ጤነኛ ያልሆኑ ሰዎች ዘንድ ቁጭ ብሎ ለአመታት ይማራል። እዚህ ደግሞ እነ እከሌ ከእነ እከሌ ጋር ተቀመጡ እያለ ፎቶ ይለጥፋል። የሳዑዲ ኤምባሲ ሲጋብዛቸው ራሱም ጭፍራዎቹም ከነዚያው ከሚያወግዛቸው አካላት ጋር አንድ ላይ ይጣዳሉ። በተለያዩ ቦታዎች የተለያየ ፊት ማሳየትን ተክኖበታል። * መሻይኾች ዘንድ ሌላ ሰው ነው። ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ደግሞ ሌላ። * ሳዑዲ ውስጥ ሌላ ሰው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ሌላ። * እንደ ባህሩና ሑሴን ያሉ ተናካሽ ጓዶቹ ጋር ሲሆን ሌላ ነው። አቃቂር እያወጡ፣ ቅጥፈት እየለጠፉ የሚናከሱ አውሬዎች ናቸው። እያደናነቀ የሚያስተዋውቃቸው የሀረር አካባቢ ጭፍራዎቹ ደግሞ እሱ በሚስላቸው 'ሙስተዋ' ላይ አይደሉም። ያያያዝኩት ቪዲዮ ለዚህ አንድ ምስክር ነው። በቪዲዮው ላይ የጠሀ ጭፍራ የሆኑት (የነበሩት ብለው ይሻል ይሆን?) እነ ኢልያስ ዐባስ እና አሕመድ ሙሐመድ (ጭሮ?) ከነ ዶክተር ጀይላን ጋር ተቀማምጠው የአንድነት መግለጫ ያወጡበት ጉባዔ ነው። ቪዲዮው ላይ ከሰፈረው ቃል ቀንጨብ ላድርግ፦ 1- የዶክተር ጀይላን ንግግር፦ "በሀረር ዑለማኦች መካከል ልዩነት እንደሌለ እንዲሁም በዑለማኦቹ መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚጥሩ አካላት በዑለማእ ስም የሚነግዱ እንደሆኑ፤ እኛ ሁላችንም አንድ እና የተሰማማን እንደሆንን፤ በመካከላችን ልዩነት እንደሌለ የሀረር እና የኢትዮጵያ መሻይኽ ጉባኤ ገልጿል።" 2- የኢልያስ ዐባስ ንግግር፦ "እኛ እንደ አሕመድ ሱኣላ እና እንደ ዶክተር ጀይላን ካሉ ታላላቅ ዑለማኦች ጋር ነን። ድሮም፣ አሁንም በመካከላችን ልዩነት የለም። እስከ ዘላለም ከነሱ አንለይም።" 3- የአሕመድ ሙሐመድ ንግግር:- "እኛ አሁን ከዑለማኦቻችን ጋር ነን። እነሱን ከሚሳደቡ አካላት ድሮም አሁንም የጠራን ነን። ፈፅሞ ከነሱ (እነሱን ከሚሳደቡ) ጋር አንሆንም።" ልብ በሉ! ጠሀ ኸዲር እነዚህን ሁለቱን ሰዎች (ማለትም ኢልያስ ዐባስ እና አሕመድ ሙሐመድ) ሞቅ አድርጎ ያወድሳል። ያሰራጭላቸዋልም፡፡ ለምሳሌ ያክል በቅርቡ እንዲህ ሲል ፅፏል:- "أشد على أيديكم يا أبطال شرق هرر فضيلة الشيخ Sheek Iliyaas Abbaas وفضيلة الشيخ Shekh Ahmade Muhammed زادكم الله قوة إلى قوتكم فقد أقضت جهودكم المضاجع وألهبت المشاعر وأسهرت وهزت ولن يهنأ منهم أحد مهما كان بعدما التهبت الأحشاء واضطرمت!" እነዚህ የጠሀ ጀግኖች ግን፡ 1ኛ፦ ከነ ዶክተር ጀይላን ጋር እንደሆኑ ድሮም፣ አሁንም በመካከላቸው ልዩነት እንደሌለ ገልፀዋል። እስከ ዘላለም ከነሱ እንደማይለዩም አስረግጠው ተናግረዋል። 2ኛ:- እነሱን (እነ ዶክተር ጀይላንን) ከሚሳደቡ አካላት ድሮም አሁንም የጠራን ነን። ፈፅሞ እነሱን ከሚሳደቡ ጋር አንሆንም ማለታቸውን ያዙ። እዚህ ላይ ቁጥር አንድ ተጠቃሹ ጠሀ ኸዲር ነው። አሞሌው አልሰራም። ከዚህ በኋላ ያለው ምርጫ ሁለት ነው። 1ኛው ምርጫ፦ ወይ እንደ ግለቱ እያዩ ሲያሻቸው "እኛ ድሮም ጀምሮ መንሀጅ ገብቶናል፣ ለ 20፣ ለ30 አመታት ሰለፊያን (የነሱን ቨርዥን) ስናስተምር ነው የኖርነው፣ ከኢኽዋን የጠራን ነን፣ ..." እያሉ መሞገት፤ ሲላቸው ደግሞ ከነዚያው ኢኽዋን ከሚሏቸው ሰዎች "ድሮም አሁንም አንድ ነን፣ ዘላለም አንለያይም" እያሉ የጋራ መግለጫ እያወጡ መቀጠል ነው። በተለያየ መመዘኛ እየመዘኑ፣ የተለያየ ፊት እያሳዩ መሄድ ለጠሀ ከባድ አይመስለኝም። ይሄ ግን የሰለፊ መገለጫ አይደለም። ሸይኽ ሙቅቢል እንዲህ ይላሉ፦ فالحزبي مستعد أن يكون له خمسة أوجه. والنبي ﷺ يقول: إن من شر الناس ذا الوجهين الذي يأتي هـولاء بوجه وهؤلاء بوجه. أما السني فإنه متمسك بدينه سواء رضي فلان أو لم يرضَ بخلاف الحزبيين. "ቡድንተኛ ሰው አምስት ፊት ሊኖረው ዝግጁ ነው። ነብዩ ﷺ 'ከክፉ ሰዎች ውስጥ የሆነው ባለ ሁለት ፊት ነው። ያ እነዚያ ዘንድ በአንድ ፊት፣ ሌሎቹን ደግሞ በሌላ ፊት የሚቀርበው።' ሱኒይ የሆነ ሰው ግን እከሌ ቢወድም ሆነ ቢጠላ ዲኑን አጥብቆ የሚይዝ ነው። ከቡድንተኞች በተለየ።" [ቱሕፈቱል ሙጂብ፡ 290] 2ኛው ምርጫ፦ ከነዚህ ሲያወድሳቸው ከነበሩ አካላት መለያየቱን ማወጅ ነው። ከሙብተዲዕ ጋር የሚቀማመጡ፣ ህብረት የሚፈጥሩ፣ ሰለፊችን የሚገፉ፣ ለሙብተዲዕ የሚከላከሉ ሙብተዲዎች ናቸው የሚል መግለጫ ማውጣት። ሰውየው ተቃራኒ ነገሮችን የማስተናገድ ልምድ ቢኖረውም ይሄኛው ግን ለመሸፈን የሚመች አይደለም። "ግመል ሰርቆ አጎንብሶ" የማይሆን ነገር ነው። ስለዚህ መለያየትን ከማወጅ ውጭ ምርጫ አይኖርም። ካ'ህያ ቆዳ የተሰራ ቤት ይበታተናል ጅብ የጮኸ 'ለት! የነዚህ ሰዎች ጉድ ይሄ ብቻ አይደለም። አለ ገና! ستُبْدي لكَ الأيّامُ ما كنتَ جاهلاً - ويأتِيكَ بالأخبارِ مَن لم تُزَوِّدِ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

👍 27
Add a comment
06:07
Video unavailableShow in Telegram
የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
👍 1
Add a comment
ሸይጅ መሀመድ ወሌ ( ሀጂ ወሌ) https://t.me/AbuHafsaYimam
إظهار الكل...
🌏Abu Hafsua (አቡ ሐፍሷ)

አስተያየት ጥቆማ ካለዎት!! /t.me/Abu_hafsua_imam_Bot «رَبَّنَا تَقَبَّلْ مِنَّا إِنَّكَ أَنتَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ»

👍 1
إظهار الكل...
قناة دروس فضيلة الشيخ أبو عمار أول بن أحمد الخميسي

الْقَنَاةُ الرَّسْمِّيةُ لِفَضِيلِةِ الْشَّيْخِ أَولِ بْنِ أَحْمَدَ الْخميسي -حَـفِظَهُ اللّه تَعَالَى

👍 2
ትምህርታችን በትኩረት ይሁን። ~~ ስትማሩ ከልባችሁ ሁናችሁ በዘርፉ ላይ ብቁ እስከምትሆኑ ድረስ ተማሩ። ለምሳሌ፦እየተማራችሁ ያላችሁት በ"ዐቂዳ"ዘርፍ ላይ ከሆነ በደንብ እስከሚገባችሁ ድረስና ለሰው መጥቀም እስከምትችሉበት ድረስ በደንብ አትኩራችሁ ተማሩ።የ"ነሕው"ዘርፍ ላይም ከሆነ እየተማራችሁ ያላችሁት ልክ እንደዚሁ።ዒልሙል_ኸጥ"የኪታባ"ትምህርም ይሁን በ"ሐዲስ" በያዛችሁት ዘርፍ ላይ በነካነካ ሳይሆን ብቁ እስከምትሆኑ ድረስ ትኩረት ሰጥታችሁ ተማሩ።በየትኛው የትምህርት ደረጃችሁ መጠቀምና መጥቀም እንደምትችሉ አታውቁም።ምናልባትም የሆነ ቦታ ላይ በአንድ የትምህርት ዘርፍ ላይ ብትፈለጉ፡ሰውንም ጠቅማችሁ ለራሳችሁም ታተርፋላችሁ። ነገራቶችን ሁሉ የሚያገራው አላህ ነውና አላህ ሁሉን ነገር ያግራልን። አቡ ዑበይዳ t.me/AbuOubeida
إظهار الكل...
Abu_Oubeida~channel

من أحب أن لا ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم {ابن الجوذي رحمه الله /التذكرة(٥٥)

👍 36
Photo unavailableShow in Telegram
ያ"ጨለማ ተወግዶ በተራው ይሄ ብርሃን መምጣቱ"ይሄ የፀሀይ ጮራ ፈንጥቆ"ብቅ ማለቱ ለአስተዋዮች ሌላ እድል ነው። አቡ ዑበይዳ t.me/AbuOubeida
إظهار الكل...
👍 39
የአላህ መልእክተኛ አለይሂ ሶላቱ ወስሰላም እንዲህ አሉ፦ ከእናንተ፡የውሎው ምግብ ያለው ሁኖ፡ በቤተሰቦቹ ውስጥ ሰላም ሆኖ ያነጋ፣በሰውነቱ ጤነኛ የሆነ፡ልክ"ዱኒያ"ለርሱ እንደተጠቀለለችለት ነው። *ጌታዬ የላቀ የሆነ ምስጋና ይገባህ። አቡ ዑበይዳ t.me/AbuOubeida
إظهار الكل...
Abu_Oubeida~channel

من أحب أن لا ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم {ابن الجوذي رحمه الله /التذكرة(٥٥)

👍 14