cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Aduliz Chronicle

Aduliz Chronicle, a digital magazine based in Addis Ababa develops and presents inspiring business-related and other stories from across Ethiopia and all around the world in English, Amharic, Afaan Oromo, Tigrinya, and other local languages.

إظهار المزيد
Ethiopia10 831Amharic8 924الفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
193
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ዜና እረፍት🕯 ድምፃዊ አሊ ቢራ ከዚህ አለም በሞት ተለየ! እዉቁ እና ተወዳጁ የኦሮምኛ ሙዚቃ አቀንቃኝ ድምፃዊ አሊ ቢራ ከዚህ አለም በሞት መለየቱን የኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ባወጣዉ የሀዘን መግለጫ አስታዉቋል። ከ50 ዓመታት በላይ በሚዚቃው ኢንዱስትሪው የቆየው ድምጻዊ ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ኢትዮመረጃ በአርቲስቱ ህልፈተ ህይወት የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል። @EthioipaNews @Adulichronicle
إظهار الكل...
Photos from South Africa
إظهار الكل...
ሰበር ዜና የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ዘላቂ ግጭት የማቆም ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገለሸ በደቡብ አፍሪካ ሲያደርግ የነበረውን የሰላም ንግግር ውጤት ዛሬ ይፋ ተደርጓል። የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ የፌደራል መንግሥት እና የህወሓት የሰላም ንግግር ይዘት ይፋ አድርገዋል። በዚህም በዘላቂነት ግጭት ለማቆምና አገልግሎቶችን ለማስጀመር ከስምምነት መደረሱን አስታውቀዋል። Source: አል አይን @ Adulizchronicle
إظهار الكل...
#እንድታውቁት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የፌስቡክ ገጹ (ከ2.1 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያለው) ከቁጥጥሩ ውጭ መሆኑን አስታውቋል። አየር መንገዱ ፤ ደንበኞች እንዲሁም የገጹ ተከታታዮች በፌስቡክ ገጹ የሚተላለፉ ማንኛውም መልዕክቶች የአየር መንገዱ አለመሆኑን ገልጿል፡፡ ችግሩን ለመፍታት በአሁኑ ሰዓት ከሜታ ኩባንያ ጋር እየሰራ መሆኑን አስታውቋል። Source:@tikvahethiopia @Adulizchronicle
إظهار الكل...
በአዲስ አበባ ታግዶ የቆየው የመታወቂያ እድሳት በተያዘው ጥቅምት ወር መጨረሻ እንደሚጀመር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ዋና ስራ አስኪያጅ ጥራቱ በየነ ገልፀዋል። አቶ ጥራቱ በየነ ለኢዜአ የሰጡት ቃል፦ - በመታወቂያ አሰጣጥና እድሳት ዙሪያ ለተስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች ዘላቂ እልባት በመስጠት ችግሩን ለመፍታት አገልግሎቱ በጊዜያዊነት እንዲቆም ተደርጎ ነበር። - በብልሹ ተግባሩ ላይ ተሳታፊ የነበሩ አመራሮችና ሰራተኞችን በመለየት ተጠያቂ የማድረግ ስራ ተከናውኗል። - በሁሉም ክፍለ ከተሞች በተለይም ችግሩ ጎልቶ በታየባቸው 37 ወረዳዎች በተደረገ ክትትል 90 አመራሮችና ባለሙያዎችን ተጠያቂ ተደርጓል። - ታግዶ የቆየው #የመታወቂያ_እድሳት ህጋዊ አሰራሩን ተከትሎ በተያዘው ጥቅምት ወር መጨረሻ ይጀመራል። ከዚህ ጎን ለጎን የከተማዋ ነዋሪዎች የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ እንዲሆንኑአሰራሩን የማዘመን ስራ ይቀጥላል ነው የተባለው፡፡ - በአሁኑ ወቅት የራሳቸው መለያና ምሥጥራዊነት ያላቸው መታወቂያ ለመስጠት የሚያገለግሉ ወረቀቶች በመታተም ላይ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይ ለነዋሪው የመስጠት ተግባር ይከናወናል ብለዋል። #ኢዜአ
إظهار الكل...
#Kenya #Ethiopia የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የመጀመሪያ የአፍሪካ ሀገር ጉዟቸውን ወደ #ኢትዮጵያ እንደሚያደርጉ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል። ነገ በአዲስ አበባ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚታደሙ የተነገረላቸው ሩቶ ፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ይመክራሉ። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ምርጫ ማሸነፋቸው በIEBC በተገለፀበት ዕለት ከዓለም ሀገራት መሪዎች ሁሉ በቅድሚያ የ " እንኳን ደስ አልዎት " መልዕክት ያስተላለፉላቸው መሪ እንደነበሩ ይታወሳል። @tikvahethiopia @Adulizchronicle
إظهار الكل...
ህወሓት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር እንዲደራደር የቀረበለትን ጥሪ ተቀበለ! ህወሓት የአፍሪካ ህብረት በደቡብ አፍሪካ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር እንዲደራደር ያቀረበለትን ጥሪ መቀበሉን አስታውቋል፡፡የኢትዮጵያ መንግስትም በዛሬው እለት ባወጣው መግለጫ በአፍሪካ ህብረት በኩል ከህወሓት ጋር እንዲደራደር የቀረበለትን ጥሪ መቀበሉን አስታውቋል፡፡ የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በትዊተር ገጻቸው ህወሓት የተደራዳሪ ቡድን ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመላክ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል፡፡በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃመት ለቀረበላቸው የድርድር ጥሪ ምስጋና ያቀረቡት ቃል አቀባዩ ህወሓት በደቡብ አፍሪካ በታቀደው ድርድር ይሳተፋል ብለዋል፡፡ ግጭት ማቆም የድርድሩ አጀንዳ መሆኑን ወቅ ጠቃሚ ይሆን ነበር ያሉት ቃል አቀባዩ ግልጽ እንዲሆኑልን የምንፈልጋቸው ነጥቦች አሉ ብለዋል፡፡በድርደሩ እንደ ታዛቢ፣ ተሳታፊ እና ዋስትና ሰጭ የሚጋበዙ ተጨማሪ አካላት ስለመኖራቸው እንዲሁም የአለምአቀፉ ማህበረሰብ ስለሚኖረው ሚና ማብራሪያ እንደሚገልግ አቶ ጌታቸው ረዳ ጠቅሰዋል፡፡ከዚህ በተጨማሪም የተደራዳሪ ቡድኑ የጸህንነት ጉዳይ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ Via Alain @EthioipaNews @Adulizchronicle
إظهار الكل...
አዲስ አበባ የሚዘጉ መንገዶች‼️ ሰኞ መስከረም 16 ቀን 2015 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ የሚካሄደውን የደመራ የመለኮስ ስነ-ስርአት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ፦ •  ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም  ከኤድናሞል በአትላሳ ወደ ካዛንቺስ የሚወስደው መንገድ  ኡራኤል አደባባይ • ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አጎና ሲኒማ • ከጎፋ በአዲሱ መንገድ ወደ  ለገሃር  ለሚመጡ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን መስቀለኛ ላይ • ከቡልጋሪያ በሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሃር የሚሄዱ ጠማማ ፎቅ አካባቢ •  ከሳር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ እንዲሁም ከጦር ኃይሎች በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወደ ለገሃር  የሚወስደው ሚክሲኮ አደባባይ • ከተከለ ሃይማኖት በጎማ ቁጠባ  ወደ ለገሃር ሰንጋተራ 40/60 ኮንደሚኒዬም አካባቢ • ከጌጃ ሰፈር ፣ በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎማ ቁጠባ • ከመርካቶ በተክለ ሃይማኖት ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሜትሮሎጂ በር ላይ • ከራስ ቴአትር በጎላ ሚካኤል ውስጥ ለውስጥ ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ • ከተክለ ሃይማኖት ጥቁር አንበሳ ኢሚግሬሽን ጥቁር አንበሳ ሼል • ከፒያሳ በቸርችር ጎዳና ለገሃር ቴዎድሮስ አደባባይ • በአሮጌው ቄራ ፍል ውሃ ንግድ ማተሚያ ቤት • ከካዛቺስ ወደ ሂልተን ካዛንቺስ ቶታል • ከአዋሬ በካዛንቺስ ወደ ፍል ውሃ የሚወስደው መንገድ የቀድሞ 6ኛ ፖሊስ መታጠፊያ ላይ ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል። ህብረተሰቡ ይህን አውቆ አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም መልዕክት አስተላልፏል። በተገለፁት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም ክልክል ነው ተብሏል። @Aduliazchronicle
إظهار الكل...