cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

azyrot አዚሮት

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
161
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
“ውሳኔዎቻችን በስሜት የሚወሰኑ ሳይሆን ዘላቂ ጥቅምን ያገናዘቡ ናቸው!” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ********************** በዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት የተጀመረው ማጥቃት አሸባሪውን ሕወሐት ከአማራና ከአፋር ክልሎች በማስወጣት የመጀመሪያውን ግብ አሳክቷል። መንግሥትም የመከላከያ ሠራዊቱ አሁን በያዛቸው አካባቢዎች ላይ እንዲቆይ ትእዛዝ ሰጥቷል፤ ይሄንን ውሳኔ የወሰንነው በስሜት ሳይሆን የሚያስገኘውን ዘላቂ ጥቅም ከግምት አስገብተን ነው። ኢትዮጵያን ዘላቂነት ባለድል የማያደርግ አካሄድ ሁሉ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለጠላቶቻችን ብርታትን የሚፈጥር፣ የሽብር ቡድኖች እድሜያቸውን የሚያረዝሙበትን ሰበብ እንዲያገኙ መፍቀድ ነው። አለፍ ሲልም በስሜት የሚወሰኑ ወታደራዊ ውሳኔዎች ሀገራችንን በተራዘመ ጦርነት አዙሪት ውስጥ እንድትዘፈቅ ያደርጋል። ኢትዮጵያን ለማዳከም የተከፈተው ዘመቻ መልከ ብዙ ነው። የሕልውና አደጋው በግልጽ ብቻ አይደለም በስውርም ይፈጸማል። ወታደራዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የመረጃ ጦርነቶች የሚካሄዱብን በተቀናጀና በረቀቀ መልኩ ነው። እኛ እየመከትን ያለነው ውጊያውን ብቻ ሳይሆን ዘመቻውን ጭምር ነው። የዘመቻው ግንባሮችም ብዙዎች ናቸው። አንዳንዶቹ ፊት ለፊት የሚፈጸሙ ሲሆን፣ አንዳንዶቹም በወጥመድ መልክ የሚከወኑ ናቸው። መንግሥት በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ህልውና ላይ የተከፈተውን ግልጽና ረቂቅ ዘመቻ ለመመከትና ለመቀልበስ ብሎም በዘላቂነት የኢትዮጵያን አሸናፊነት ለማረጋገጥ የነደፈው ዕቅድ ሁለገብና ሁሉንም ግንባሮች ለመመከት የሚያስችል ስልት ነው። በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ችግር መከሠት የጀመረው ለውጡን ተከትሎ መሆኑን ሕዝባችን ያውቃል። “እኔ ብቻ የማልገዛት ኢትዮጵያ መፍረስ አለባት” ብሎ የሚያምነው ሕወሐት ክልሉን ምሽግ አድርጎ ችግር መፍጠር የጀመረው በለውጡ መባቻ ነበር። መንግሥት ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት እንዳይፈጠር፣ የሕዝብ ሰላምና ደኅንነት እንዳይደፈርስና በኢኮኖሚው ላይ ከባድ ጫና እንዳይደርስ በማሰብ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ተሞክሮ ነበር። አሸባሪው ሕወሐት ግን ከጥፋት መንገድ በቀር ሰላማዊ መንገድ የማይታየው ሆነ። በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የተፈጠረውን ሰላም መነሻ በማድረግ፣ በሌሎች አካባቢዎች ያለውንም የሥጋት ደረጃ በመመርመር፣ ሠራዊታችንን ከኢትዮ ኤርትራ ድንበር ወደ ሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ለማንቀሳቀስ ስንሞክር፣ በትግራይ ሕዝብ ውስጥ መሽጎ የሚገኘው አሸባሪው የሕወሐት ቡድን፣ ሕጻናትን መንገድ ላይ እያስተኛ፣ አረጋውያንንም እንዲለምኑ እያደረገ፣ ሠራዊቱ ከትግራይ እንዳይወጣ ማድረጉ ይታወሳል። ይሄንን በሕዝብ ጥያቄ የተሸፈነ እኩይ ተግባር በአንድ በኩል እያከናወነ በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያን ለመውረር ከሚፈልጉ የውጭ ኃይሎች ጋር በምሥጢር ይደራደር ነበር። ኢትዮጵያን ለመውጋት ከውጭ ኃይሎች ጋር ያደረጉትን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ ሲሉ፣ በሕዝቡ ልመና በትግራይ የቆየውንና ሕዝቡን በደሙና በላቡ ሲያገለግል የኖረውን ሰሜን ዕዝን በግፍ መሣሪያውን ለመንጠቅ ዘግናኝ ጥቃት ሰነዘሩ። የሀገር የመጨረሻው ደጀን በሆነው የመከላከያ ሠራዊት ላይ የሚፈጸም ማንኛውም ጥቃት የሉዓላዊነትና የህልውና ጥቃት ነው። የአሸባሪው ሕወሐት ዋና ዓላማም የሰሜን ዕዝ የታጠቃቸውን ትጥቆችና ስንቆች በመንጠቅ ኢትዮጵያን ለመውረርና ለማፈራረስ ነበር። ይሄንንም ከውጭ ጠላቶቻችን ጋር መክሮና ተቀናጅቶ ያደረገው ነበር። የዛሬ ዓመት በጥቅምት መጨረሻ፣ የመከላከያ ሠራዊት በወሰደው አፋጣኝ የማጥቃት ርምጃ ጁንታው ተሸንፎ ወደ ተንቤን በረሐ ፈርጥጦ ነበር። በዚህ የህልውናና ሕግ የማስከበር ዘመቻ የተነጠቅናቸውን መሣሪዎያችና የተማረኩብንን የሠራዊት አባላት አስመልሰናል። ከሽብር ቡድኑ ከፍተኛ አመራሮች የተወሰኑ ወንጀለኞችን ለሕግ እንዲቀርቡ ማድረግ የቻልን ሲሆን አሻፈረኝ ያሉትም እርምጃ ተወስዶባቸዋል። ሠራዊታችን በትግራይ ሕዝብ ጥያቄ መሠረት ለስምንት ወራት በክልሉ ቆይቷል። በቆይታውም ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች እንዲቀላጠፉ መሥዋዕትነት ከፍሏል። መሠረተ ልማቶች እንደገና እንዲገነቡ፣ የሕዝብ አገልግሎቶች ሥራ እንዲጀምሩ፣ ሰብአዊ እርዳታዎች በተሻለ ሁኔታ ተደራሽ እንዲሆኑ የሚቻለውን ሁሉ አደርጓል። ይኼን በሚያደርግበት ወቅት ሠራዊታችን በሁለት በኩል ዋጋ ሲከፍል ነበር። አንደኛ በዚያ የነበረው ቆይታ በጠላት ፕሮፓጋንዳና የጠላትን ፕሮፓጋንዳ በሚያስተጋቡ የውጭ ሚዲያዎች ያለ ስሙ ስም ተሰጥቶታል። ሁለተኛ የፕሮፓጋንዳ ሰለባ በሆነው የክልሉ ማኅበረሰብ ከጀርባ ለመውጋት ተገደደ። ሠራዊታችን ደም ከፍሎ በሰጠው አገልግሎት የተረፈው ወቀሳና መጥፎ ስም ሆነ። ለሰብዓዊ ተግባራትና ለመልሶ ግንባታ ከ100 ቢልዮን ብር በላይ ማውጣታችን ከምን ሳይቆጠር አስተዳደሩና የጸጥታ ኃይሉ ባልዋለበት መወቀስ ጀመረ። የትግራይ ገበሬም በአንበጣ ምክንያት የተጓጎለበት የእርሻ ሥራ በጦርነቱ ምክንያት ዳግም ስለተጎዳበት ፋታ ማግኘት ያለበት ደረጃ ላይ ደረሰ። ይሄንን ከግምት ውስጥ በማስገባትም መንግሥት በሰብአዊነት ላይ የተመሠረተ የተኩስ አቁም ስምምነት አድርጎ የመከላከያ ሠራዊቱን ከትግራይ ክልል የማስወጣት ውሳኔ ሊተላለፍ ቻለ። አሸባሪው ሕወሐትና አንዳንድ ዓለም አቀፍ አጋሮቹ ግን ሠራዊታችን ለሰብአዊነት ብሎ ከትግራይ መውጣቱን እንደ መሸነፍ ሲቆጥሩት ተስተውለዋል። በስምንት ወራት መታከት ውስጥ የቆየው ሠራዊታችን ፋታ ሳያገኝ ማዳከም ስለተፈለገ፣ ከአምስት መቶ ዓመታት በፊት በቀረ የሕዝብ ማዕበል የጦር ስልት አሸባሪው ቡድን ዳግም የማጥቃት እርምጃውን ጀመረ። ይሄንን ወረራ ለመቀልበስ እንዲቻል፣ ለዝግጅት በቂ ጊዜ ወስደን፣ የአመራር ጥበብን፣ የተቀናጀ ዕቅድንና ቴክኖሎጂን በመጠቀም፣ የደረሰብንን ወረራ ስንከላከል ቆይተን የጥፋት እርምጃውን ቀልብሰነዋል። ጠላት ከወረራቸው አካባቢዎችም ተጠራርጎ ወጥቷል። መንግሥት ህልውና የማስከበር ዘመቻው ባለ ብዙ መልክ መሆኑን ዐውቆ ለሁሉም ግንባር የሚሆን በቂ ዝግጅት አድርጓል። ህልውናችንንና ሉዓላዊነታችንን የምናስከብርበት ሜዳ የጦር ሜዳው ብቻ አይደለም። ከወታደራዊ ዘመቻው ጋር አብረው ልንዘምትባቸው የሚገቡ ሌሎችም ሜዳዎች አሉ። መንግሥት የሚወስናቸው ውሳኔዎች ሁሉንም ግንባሮች መሠረት ያደረጉ እንጂ በተናጠል እይታ የታጠሩ አይደሉም። የመጀመሪያው ዕቅዳችን አሸባሪውን ቡድን ከአፋርና ከአማራ አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ ማጽዳት ነው። ይሄንንም መቶ በመቶ ሊባል በሚችል መልኩ አሳክተናል። ሠራዊታችንንም ስትራቴጂያዊ በሆኑ ቦታዎች እንዲሠፍር በማድረግ የጠላትን እንቅስቃሴ በአንክሮ እንዲከታተል አድርገናል። ይሄንን እንድንወስን ያደረጉን ብዙ ምክንያቶች አሉ። አንደኛ የግዛት አንድነታችንና ሉዓላዊነታችነን የሚያሠጋ ነገር ከገጠመን በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ ወደ ትግራይ ክልል ገብቶ የሀገርን ደኅንነት ለማስከበር የመከላከያ ሠራዊቱ ሕገ መንግሥታዊ መብት ብቻ ሳይሆን ግዴታም አለበት። በሌላም በኩል ሕወሐትና አፈ ቀላጤዎቹ መንግሥትንና ሠራዊቱን ለመክሰስ ወደ አዘጋጁት የሤራ ወጥመድ መግባት እንደሌለብን እናምናለን። በዚህ ወቅት የእኛ ወደ ክልሉ መግባት ከጥቅሙ ጉዳቱ ነው የሚያመዝነው። የትግራይ እናቶች ይሄንን ሁሉ ምስቅልቅል ያመጣባቸውንና ልጆቻቸውን ነጥቆ ያስጨረሰባቸውን አሸባሪ ኃይል መጠየቅ አለባቸው። ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ይሄንን አሸባሪ ከጫንቃው ላይ ያስወገደው በመራራ ትግሉ ነው። የትግራይ ሕዝብም እንደ ሌላው
إظهار الكل...
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ ሰራዊቱ ወደ ትግራይ ክልል እንዳይገባ በተወሰነው ውሳኔ ዙሪያ የሰጡት ማብራሪያ
إظهار الكل...
⬆️ የባይደን አስተዳደር ለኢትዮጵያ ተፈቅዶ የነበረውን የአግዋ ከቀረጥ ነጻ ተጠቃሚነት ሰርዟል! (አቶ ሙሼ ሰሙ በዚህ ዙርያ በጥሩ ሁኔታ የፃፉትን ያንብቡ) እ.ኤ.አ በ2020 ኢትዮጵያ ከቀረጥ ነጻ የጨርቃ ጨርቅና የቆዳ ውጤቶችን ወደ አሜሪካ በመላክ 238 ሚሊየን ዶላር አግኝታለች፡፡ ይህ ማለት ከአጠቃላይ የሀገራችን ኤክስፖርት ውስጥ 7% ገዳማ ሲሆን ወደ አሜሪካ ከምንልከው 525 ሚሊየን ዶላር ውስጥ 45.34 % ነው፡፡ በተቃራኒው አሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የምትልከው ምርት 868 ሚሊየን ዶላር የሚያወጣ ሲሆን የንግድ ሚዛኑ በ343 ሚሊየን ዶላር ለአሜሪካ ያጋደለ ነው አሜሪካንን ከማማረር በላይ ከስራ ለሚሰናበተው በ100 ሺ የሚቆጠረው ሰራተኛ የስራ እድል መፍጠርና ማዕቀቡ የሚያስከትለውን ጉዳት በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ለማካካስ የሚስችል አማራጭ እስክናገኝ ድረስ እቀባው በአጭር ጊዜ ሊደቅንብን የሚችለውን ፈታና እንዴት እንቋቋመው የሚለው ጥያቄ ዋነኛ መወያያችን መሆን አለበት፡፡ ለጊዜው ብዙ አማራጭ ያለን አይመስለኝም፡፡ ይህም ሆኖ፣ በመካከለኛ ጊዜ ሊሰሩ የሚችሉ አዳዲስ ገበያን የማፈላለግ፣ በረጅም ጊዜ ደግሞ የሚገነቡ የኤክሰፖርት አቅማችንን የማሳደግና በራስ አቅምና ምርት የመተማመን አማራጮች እስኪጎለብቱ ድረስ አንድ ሁለት ነገሮች ማመላከት ይቻላል፡፡ 1) የውጭ ምንዛሬ አቅርቦቱን መሰረታዊ ለሚባሉ አቅርቦቶች ብቻ ማዋልና ጊዚያዊ ፍላጎቶቻችንን በመግታት የውጭ ምንዛሪ ፍጆታን መቆጠብ፡፡ 2) ኢምባሲዎች፣ ቆንስላዎች፣ የተለያዩ የዲያስፖራ ኮሚኒቴዎችንና የኢትዮጵይ ተቆርቋሪ ማህበረሰቦችን በማስተባበር ከምንጊዜውም በላይ ገበያ የማፈላለጉን ስራ በስፋት፣ ተከታታይነት ባለው መንገድና በቁጭትና በተደራጀ መልኩ ማካሄድ፡፡ 3) የኤክሰፖርት ገበያው ላይ ያለውን ውስብስብ ችግር በጥናት ላይ ተመስርቶ መፍትሔ በመስጠትና በርካታ ዜጎች በኤክሰፖርት ስራ፣ በተለያየ አቅምና የምርት አቅርቦት ሥራ ላይ እንዲሰማሩ የሚያበረታቱ የብድር፣ የታክስ፣ የቦታ አቅርቦትና ሌሎች የድጋፍና የማበረታቻ መንገዶችን ለአጭር ጊዜ በገደብ ማመቻቸት ሲሆን ሌላውና መሰረታዊ ጉዳይ፤ እስካሁን 13 ሺ ከሚደርሱ ትውልደ ኢትዮጵያውያን 3 ሚሊየን ዶላር መሰባሰብ እንደተቻለ ተዘግቧል፡፡ ከአጠቃላይ የትውልደ ኢትዮጵያውያን ቁጥር አኳያ የፈቃደኞች ቁጥር ጥቂት ቢሆንም በነዚህ ጥቂት በጎ አሳቢ ዜጎች ተነሳሽነት ምክንያት ቀላል የማይባል ሀብት መሰብሰቡን መረዳት ይቻላል፡፡ አንዱ ችግሩ የማያቋርጥ የመዋጮ ጥያቄ መሆኑ ይመስለኛል (Donor Fatigue)። መንግስት ይህንን አሰራር በጊዜ ገደብ ወደ የሚመለስ የቦንድ ሽያጭ በማሳደግ የአንድ ዓመት የአጋዋ ኤክስፖርታችንን ያህል የውጭ ምንዛሪ በቀላሉ ማግኘት ይቻላል፡፡ በዘለቄታው የሚሰሩ ስራዎች መፍትሔ እስኪሰጡ ድርስ አንድ ሚሊየን ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በማስተባበር እያንዳንዳቸው በአማካይ 500 ዶላር የሚያወጣና በተለያየ የግዢና የክፍያ ስርዓት የሚሰበሰብና ተመላሽ የሚሆን ቦንድ ቢገዙ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ500 ሚሊየን ዶላር በላይ ከዲያስፖራ በመበደር (Revolving Fund) የእፎይታ ጊዜ ማግኝት ይቻላል፡፡ የእፎይታ ጊዜው በሚሰጠው ትንፋሽ ውስጥ ሆነን ከላይ የቀረቡትን አማራጭ ስራዎች ያለማሰለስና በንቃት ከተሰራ በራስ አቅም የችግሩን ውስብስብነት ከመቀነስ ባሻገር አደጋውን እስከ መቀልበስ የሚሻገር ዘላቂ ውጤት ማግኘት ይቻላል። @EliasMeseret
إظهار الكل...
ቢቢሲ ኒውስ አወር፦ የፌዴራል ኃይሎች ጥምረት በምዕራብ ትግራይ፣ የኤርትራ ሠራዊት በሰሜን ትግራይ አለ ብለውኛል። እንደዚያ ከሆነ ለምን እዚያ ላይ አላተኮራችሁም? አዲስ አበባ ለመገስገስ ምናልባት ጓጉታችሁ ይሆን? ጄነራል ጻድቃን፦ አይደለም። ከመነሻው ግልጽ መሆን ያለበት ነገር አለ። አዲስ አበባን የመቆጣጠር ፍላጎት አልነበረንም። እርግጥ ነው ጦርነቱን በተቻለ ፍጥነት የማጠናቀቅ ጉጉት ነበረን። በእኛ አስተሳሰብ ወደ ደቡብ ዘመቻ በማድረግ፣ በዚያውም የፖለቲካ ጥምረቱን በተቻለ ፍጥነት በማቀናጀት መንግሥት ሁሉን አቀፍ ለሆነ ንግግር እንዲቀመጥ እናስገድደዋለን ብለን ነበር።
إظهار الكل...
ጆ ባይደን ትናንት ምሽት ኢትዮጵያን፣ ማሊንና ጊኒን ከአጎዋ የቀረጥና ታሪፍ ነፃ መብት በይፋ ሰርዘዋል። ...ምን ነበር ያሉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፦ "የአድዋ ልጆች መኾናችንን ረስተው በአጎዋ ሊያስፈራሩን ሞከሩ!" ትክክል! "እኛ የነጻዋ ምድር ልጆች ኢትዮጵያውያን ነን፤ ነጻነታችንን በእርዳታ አንለውጥም!! በፍጹም!!"
إظهار الكل...
እንኳን ደስ አለህ ውድ አብርሃም… ትዳርህ ያማረ እንዲሆንና የምትመሰርተው ቤተሰብ ደስተኛ እንዲሆን ከወዲሁ ተመኝቻለሁ ዜናውን ያልሰማችሁ፣ አብርሃም ወልዴ ሊሞሸር እንደሆነ ገልጽዋል፡፡ ቤተሰብ ወዳጆቹ ለሰርግ ድጋፍ እናድርግልህ የሚሉትን ድጋፋቸውን በጦርነቱ ለተፈናቀሉ እንዲሰጡለት አሳውቋል፡፡ እነሆ ንግግሩን በራሱ ብዕር ስሙት… … በሃገራችን፡ “ሰርግና፡ ሞት፡ አንድ፡ ነው” ይባላል። በሞት፡ ሃዘንም፡ በጋብቻ፡ ሰርግም፡ እኩል፡ ቦታ፡ ይሰጣቸዋል። እኔ፡ ግን፡ ጋብቻ፡ ለሃገሬ፡ ከመስራት፡ እና፡ ከመሮጥ፡ የሚያሰናክለኝ፡ ብወልድ፡ ደግሞ፡ ፈሪ፡ ሆኜ፡ እንደ፡ ልቤ፡ እንዳልናገር፡ የሚያደርገኝ፡ ስለሚመስለኝ፡ ብቻ፡ ለዓመታት፡ ስሸሸው፡ ኖርያለሁ። አሁን፡ ግን፡ ግዜው፡ ሲገፋ ሃሳቤን፡ አስቀይሮኝ፡ ወደ፡ ትዳር፡ አለም፡ ልገባ፡ ነው። እድሜውን፡ ሙሉ፡ ስለ፡ ሃገርና፡ ስለ፡ ህዝብ፡ ብቻ፡ አስቦ፡ ለኖረ፡ ሰው፡ ምናልባት፡ ሃዘኑን፡ እንጂ፡ ሰርጉን፡ ብቻውን፡ ሊያደርገው፡ እንዴት፡ ይቻለው፡ ይሆን? ስለዚህም፡ እኔና፡ የህይወት-አጋሬ፡ የደስታችን፡ ተካፋይ፡ መሆን፡ ለምትሹ፡ ወዳጆቻችን፡ ሁሉ፡ በመንፈስ፡ ከእኛ፡ ጋር፡ እንደምትሆኑ፡ በፅኑ፡ ልብ፡ በማመን፡ የሰርጋችን፡ ጥሪ፡ በያላችሁበት፡ ይድረሳችሁ፡ እንላለን። ከቤተሰቦቻችንና፡ ከቅርብ፡ ጓደኞቻችን፡ አንስቶ፡ ለሰርጋችሁ፡ ምን፡ እናድርግላችሁ፡ እያላችሁ፡ የጠየቃችሁን፡ እና፡ ለማድረግም፡ ለምትሹ፡ ወዳጆቻችን፡ እና፡ አክባሪዎቻችን፡ ሁሉ፡ ለእኛ፡ ልታደርጉ፡ የምትፈልጉትን፡ ሁሉ፡ በጦርነቱ፡ ለተፈናቀሉና፡ ለተጎዱ፡ ወገኖቻችን፡ ድጋፍ፡ እንዲሆንልን፡ ስንል፡ የጎፈንድሚ፡ አካውንት፡ከፍተናልና፡ ድጋፋችሁን፡ እንድታሳዩንና፡ እንድትተባበሩን፡ ስንል፡ በኢትዮጽያዊ፡ እህታዊና፡ ወንድማዊ፡ ፍቅርና፡ አክብሮት፡ እንጠይቃችኋለን። ይህንንም፡ ፈለግ፡ ሌሎች፡ ሰርገኞች፡ ሁሉ፡ እንዲከተሉት፡ የእግዚአብሔር፡ ፍቃድ፡ ይሁን። ሰርግና፡ ሞት፡ አንድ፡ ነው። በደስታም፡ በሃዘንም፡ መረዳዳት፡ ኢትዮጵያዊው፡ ህይወታችን፡ ነው። ምንም፡ እንኴን፡ በአሁኑ፡ ሰዓት፡ ሃገራችን፡ ምጥ፡ ላይ፡ ብትሆንም፡ እንድነቷንና፡ ሰላሟን፡ ወልዳ፡ ዳግም፡ ታላቅነቷን፡ እንደምትጎናፀፍ፡ ጥርጥር፡ የለንም። ሰርጋችንም፡ የነገዪቱ፡ ኢትዮጵያችን፡ አንዱ፡ የተስፋና፡ የብሩህ፡ ቀን፡ ምልክት፡ እንዲሆንልን፡ እንመኛለን። አብርሃም፡ ወልዴ፡ እና፡ የህይወት፡ ጓደኛዬ፡፡ .. ለጦርነቱ ርዳታ ማሰባሰቢያ Gofundme ሊንኩን ከታች ያገኙታል - 👉 https://www.gofundme.com/f/wedding-announcement-charitable-donation?utm_campaign=p_lico+share-sheet&utm_medium=copy_link&utm_source=customer
إظهار الكل...
#NewsAlert የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ (ዩኤኢ) ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ጋር በተያያዘ ከኬንያ፣ #ኢትዮጵያ ፣ ታንዛኒያ እና ናይጄሪያ ወደ ሀገሯ የሚገቡ መንገደኞችን አገደች። እግዱ ከታህሳስ 16 ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ነው። እግዱ ወደ ተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ከመምጣታቸው 14 ቀናት በፊት በአራቱ ሀገራት የነበሩ ተጓዦችን እንዳይገቡ ማገድን የሚያካትት ነው። ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ወደ እነዚህ ሀገራት የሚደረገው በረራ በተያዘለት መርሃ ግብር ይቀጥላል ተብሏል። የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ዜጎችና የመጀመሪያ ደረጃ ዘመዶቻቸው (FDR) ፣ ወርቃማ ቪዛ (የረጅም ጊዜ የመኖሪያ ቪዛ) ያላቸው ፣ በእነዚህ ሀገራት መካከል ያሉ የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች እንዲሁም ኦፊሴላዊ ልዑካን ከአዲሱ የጉዞ ህግ / እገዳ ነፃ መሆናቸው ተናግሯል። ነገር ግን ከመነሳታቸውን ከ48 ሰዓት በፊት የኮቪድ-19 ምርመራ ተመርምረው ነፃ መሆናቸው የሚያረጋግጥ ውጤት ማቅረብ ፣ ኤርፖርት ላይ ፈጣን የPCR ምርመራ በስድስት ሰዓት ውስጥ ማድረግ እንዲሁም ዩኤኢ ሲደርሱ ኤርፖርት ላይ የPCR ምርመራ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ዜጎችና የመጀመሪያ ደረጃ ዘመዶቻቸው ፣የረጅም ጊዜ የመኖሪያ ቪዛ ያላቸው እና የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች የ10 ቀን ኳራንቲን እና ወደ ሀገር በገቡ በ9ኛው ቀን የPCR ምርመራ ማድረግ አለባቸው ተብሏል። የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ዜጎች ወደ አራቱ የአፍሪካ ሀገራት እንዳይጓዙ የተከለከሉ ሲሆን ክልከላው የሀገሪቱ የድንገተኛ ህክምና ጉዳዮች ፣ ይፋዊ ልዑካን እንዲሁም ከሶኮላርሺፕ ጋር በተያያዘ የሚጓዙትን አይጨምርም። ምንጭ፦ https://www.wam.ae/en/details/1395303005869 @tikvahethiopia
إظهار الكل...
ካለፉት መዘናጋቶች መማር ያስፈልጋል! 1) ሰራዊቱ ትግራይ ከገባ በኋላ ተረስቶ የትግሬ ወራሪ እንዲደራጅ እድል ተሰጠው። የመከላከያና ፖለቲካዊ አመራሩ ሌላ ጉዳይ ላይ ተጠመዱ። የትግሬ ወራሪ በየቦታው ኃይል አሰልጥኖ ሰራዊቱን እስከመምታት ደረሰ። 2) የምርጫ ወቅት ላይ ከፖለቲከኛው ባሻገር ወታደራዊ አመራሩም ጦርነቱን ረስቶ ጦርነቱ ሌላ አቅጣጫ ያዘ። በመዘናጋት የትግሬ ወራሪ ሰራዊቱን እንዲመታ እድል አገኘ። 3) የመንግስት ምስረታ ወቅት ትህነግ እድሉን ተጠቀመበት። ደሴና ኮምቦልቻን ለማጥቃት በርካታ ኃይል ይዞ መጣ። ከትግራይ ብቻ ሳይሆን አማራ ክልል ይኖር ከነበረው በሺህ የሚቆጠር ትግሬ መካከል አብዛኛውን አሰልጥኖ፣ ሌላውን ጀሌ አድርጎ ደሴና ኮምቦልቻን ብሎም ወሎን ወረረ። 4) አሁንም ከወረረው አብዛኛው ቦታ ወጣ ማለት ተሸነፈ ማለት አይደለም። በርካታ ኃይል እያሰለጠነ ይገኛል። ዛሬ ከመሸ ባወጣው መግለጫ ደግሞ እገጥማቸዋለሁ ብሏል። አሁንም የተወሰነ ቦታ ደረስ ስለተገፋ የተሸነፈ የሚመስለው ብዙ ነው። ነገር ግን አላማው ጥፋት እንደመሆኑ የአጥፍቶ መጥፋት ስራ ለመስራት የሚያንስ ኃይል አይደለም። ከአዲስ አበባ ስለራቀ፣ ካወደማቸውና ከዘረፋቸው ከተሞች ስለራቀ ተሸነፈ ማለት አይደለም። ካለፉት መዘናጋቶች መማር ያስፈልጋል። ከዚህም ባሻገር አሁን በያዛቸው የራያ አካባቢዎች በርካታ ሕዝብ ፈጅቷል። አውድሟል። ዘርፏል። አማራ ክልልን ሲወር የመጀመርያው የጭፍጨፋ ሰለባ የሆኑት የመሆኒ ሙስሊሞች ናቸው። ሰራዊቱ ከጋሸና ወዲህም "ቆይ" ተብሎ ነበር። ይሁንና ወደ ትግራይ አይገባም ወዘተ የሚባለው ሌላ አጀንዳ ነው። አሁን የተወረሩት የአማራ አካባቢዎችም ነፃ አልወጡም። በሌላ በኩል ደግሞ ባለፉት ጊዜያት አንደኛው መዘናጋት የውጭ ጫና በመስጋት ነው። ሰራዊቱ ትግራይ ውስጥ የተመታው የውጭ ጫና በመስጋት ወለም ዘለም ሲባል ነው። ጦርነት ጊዜ ይጠይቃል። ሌላም ሌላም ይጠይቃል። ፖለቲከኞቹ መግለጫ ሲሰጡ ግን ከማዘናጋት መቆጠብ አለባቸው። አንድ ሚሊዮን ዳያስፖራ መምጣትም ሆነ ሌሎች ጉዳዮች ትኩረታችን ከጦርነቱ ሊያነሱት አይገባም። በመዘናጋት ተደጋጋሚ ችግሮች ተፈጥረዋል። ከልክ በላይ ተጠቅተንባቸዋል። ከባለፉት መዘናጋቶች መማር ግድ ይላል። @GetachewShiferaw
إظهار الكل...
በተመድ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ስብሰባ ላይ ድምጸ ተዓቅቦ ካደረጉ የአፍሪካ ሀገራት ጋር ውይይት መጀመሩን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ገለጸ በቀጣይ በሚደረገው በብሄራዊ ውይይት ህወሓትን እንደማይመለከትም ተገልጿል። አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ኢትዮጵያ ግፊት ማድረጓ ይቀጥላል ተብሏል።
إظهار الكل...
ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ የተሰጠ መግለጫ ቁ.6 ታኅሣሥ 14 ቀን 2014 ዓም የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ ማምሻውን ባደረገው ስብሰባ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ አፈጻጸሙን ገምግሟል፡፡ በግምገማውም በግንባር ለተገኘው ድል የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጉልበታቸውን፣ ዕውቀታቸውን፣ ሞያቸውንና ገንዘባቸውን ለሀገራቸው ሳይሰስቱ በመስጠት የፈጸሙት የደጀንነት ገድል አኩሪ መሆኑን ተመልክቷል፡፡ ለዚህ የሕዝባችን ከፍተኛ አስተዋጽዖ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዙ ምስጋና ያቀርባል፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዙ የተገኙ ድሎቻችንን ዘላቂና አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ሲሆን፣ ለዚህም በማኅበረሰቡ፣በአስተዳደር አካላትና በጸጥታ አካላት መወሰድ የሚገባቸውን ተግባራት በመለየት የሚከተሉትን ትእዛዛት ሰጥቷል፡፡ 1. ከሕዝብ ችግር ለመጠቀም የሚፈልጉ አንዳንድ አካላት፣ ወደ ሀገር ቤት የሚመጣውን የዳያስፖራ ማኅበረሰብ ምክንያት አድርገው ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ለማድረግ መነሣሣታቸው ተደርሶበታል፡፡ ይህ ደግሞ ድኻውን የኀብረተሰብ ክፍል ስለሚጎዳ በእነዚህ ሕገ ወጥ አካላት ላይ መንግሥት አስፈላጊውን ቁጥጥርና ሕግ የማስከበር ተግባር እያከናወነ ነው፡፡ በመሆኑም በየአካባቢው በመሠረታዊ ፍጆታዎችና አገልግሎቶች ላይ ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የሌለው የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉና ያለ አግባብ በሚያከማቹ አካላት ላይ፣ የንግድ ቢሮዎችና የጸጥታ አካላት አስፈላጊውን ርምጃ እንዲወስዱ ታዝዘዋል፡፡ 2. ከአሸባሪው ሕወሐት ነጻ በወጡት አካባቢዎች አስተዳደርን መልሶ የማቋቋምና መሠረታዊ የኅብረተሰብ ችግሮችን በመፍታት ረገድ ያለው እንቅስቃሴ ወጥ በሆነ ሁኔታ እየተተገበረ አለመሆኑን ገምግሟል፡፡ በዚህም ምክንያት የጸጥታ ችግሮችና የወንጀል ተግባራት ነጻ የወጣውን ማኅበረሰብ እያማረሩት ነው፡፡ በመሆኑም የአማራ ክልል መንግሥት የየአካባቢውን አስተዳደር በአስቸኳይ በብቁ አመራሮች እንዲያደራጅ፤ መደበኛ የፖሊስ ኃይሎችም የተጠናከረ ሥራ እንዲጀምሩ እንዲያደርግ፣ እነዚህን ለማድረግ ባልተቻለባቸው ቦታዎች የሚንቀሳቀስ የመከላከያ ኃይል፣ ነጻ በወጡ አካባቢዎች የጸጥታ ችግር በሚፈጥሩ አካላት ላይ፣ ሕጋዊ ርምጃ እንዲወስድ ታዝዟል፡፡ 3. አሸባሪው ኃይል ተቆጣጥሯቸው በነበሩ አካባቢዎች፣ ባደራጃቸው ሕገ ወጥ መዋቅሮች አማካኝነት፤ የቀደመው አስተዳደር ይጠቀምባቸው የነበሩትን ማኅተሞች በመጠቀምና አዳዲስ ሕገ ወጥ ማኅተሞችን በመቅረጽ ሕገ ወጥ መታወቂያዎችን መስጠቱ፤ የተለያዩ ሕገ ወጥ ሰነዶችን ማዘጋጀቱ ተደርሶበታል፡፡ በመሆኑም በየአካባቢው የተቋቋሙ የመስተዳድር አካላትና የጸጥታ ኃይሎች አሸባሪው ሕወሐት ያስቀረጻቸውን ማኅተሞች፣ መታወቂያዎችና ሌሎች ሰነዶች እንዲያመክኑ ታዝዘዋል፡፡ 4. ነጻ በወጡ አካባቢዎች ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውሮችና ጠላት አንጠባጥቧቸው የሄዱ የጦር መሣሪያዎች በመኖራቸው ለሕዝብ ሰላምና ደኅንነት ሥጋት ሊሆኑ የሚችሉ አዝማሚያዎች መኖራቸው ተደርሶበታል፡፡ በመሆኑም የየአካባቢው ልዩ ኃይልና ፖሊስ በአስቸኳይ እነዚህ ጉዳዮች ሥርዓት እንዲያሲዙ ታዝዘዋል፡፡ እነዚህ ኃይሎች ባልተጠናከሩባቸው አካባቢዎችም የመከላከያ ኃይል አስፈላጊውን ርምጃ እንዲወስድ ትእዛዝ ተሰጥቷል፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ዕዝ
إظهار الكل...
የተዘረፈውን ንብረታችንን የፌደራል መንግሥት ሊከፍልና ሊክስ ነው? የተዘረፈው ንብረታችንን ማስመለስ እና/ወይም መካስ ግድ ነው። በአማራና በአፋር ክልልና ሕዝብ ንብረት የሚበለጽግ ወራሪ አይኖርም። በዘረፈው ንብረታችን ተደራጅቶ ድጋሜ እንዲወጋን የሚፈቅድ ውሳኔ በበደል ላይ በደል ነው። የዘረፈና የገደለ መያዝ መቀጣት አለበት። እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል። በመሆኑም በአማራና በአፋር ሕዝብ ንብረት የሚበለጽግ፤ በኢትዮጵያውያን ልጆች ሞትና ጉዳት ተደላድሎ የሚኖር ለዳግም ጥቃት የሚዘጋጅ ወራሪ እንዲኖር የሚፈቅድ ካለ እሱ ራሱ ዋና ጁንታ ነው። @Wubishet_Mulat
إظهار الكل...
መረጃ - ሁመራ (በረከት) ከትላንት ሌሊት ጀምሮ ከሱዳን ተነስቶ ወደ ጠረፍ ተጠግቶ ትንኮሳ የፈፀመው የወያኔ ጦር ያው የለመደውን ምሱን ቀመሰ!!! ጄኔራል ፍስሃ ማንጁስ እና ኮሎኔል ፀጋዬ አብረሃ (በምስሉ ላይ የሚታየውና በጁባ ሰላም አስከባሪ የነበረ ነው) ሱዳን ሃሸባ ውስጥ ሆነው ያሰማሩት የጁንታው የስደተኛ ጦር ተቀጥቅጦ ተመልሷል። 👉 በወገን በኩል ከመጠነኛ የመቁሰል አደጋ ውጪ ምንም ያላደረሰው ይህ የቀቢፀ ተስፋ ሙከራ የጁንታውን ከ150 በላይ ስደተኛ ታጣቂዎች ሙት በማድረግ በአጭር ተቀጭቷል። (ዝርዝር መረጃዎችን እንዳገኘሁ እመለሳለሁ) @wlkayi
إظهار الكل...
የአሜሪካ ሴናተሮች የሆኑት ካረን ባስ እና ክሪስ ቫን ሆለን ኢትዮጵያ ከአጎዋ እንድትሰረዝ የተያዘው እቅድ በድጋሜ እንዲጤን የፃፉት ደብዳቤ ይፋ ሆኗል! ደብዳቤው በትክክል እንዳስረዳው ኢትዮጵያ ከዚህ እድል ብትሰረዝ በቀዳሚነት የሚጎዳው ህዝብ ነው፣ በበርካታ አመታት ልፋት የተገኘን ልማት እና እድገት መጉዳቱ ጥያቄ የለውም። የውጭ ፖሊሲ አቅጣጫ በተንሸራተተ ቁጥር ለፍቶ አደር ህዝብን ከመንግስት ያልለዩ እርምጃዎች ሲወሰዱ እዚህም፣ እዛም ይታያል። ይህ አካሄድ እርምጃውን የሚወስዱ ያደጉ ሀገራት በሌሎች ታዳጊ ሀገራት የማደግ ህልም ላይ ያላቸውን የተንሸዋረረ እይታ ይፋ ከማረጉም በላይ አለም አቀፍ ግንኙነቶች ምን ያህል "might is right" በተባለ ያረጀ አስተሳሰብ እንደሚመሩ ማሳያ ነው። @EliasMeseret
إظهار الكل...
አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ በሽጉጥ በተመታበት ወቅት በቸልተኝነት እርዳታ እንዳያገኝ ባለማድረግ ወንጀል ላምሮት ከማል ጥፋተኛ ተባለች። የጥፋተኝነች ፍርዱን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የፀረሽብርና የህገመንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። ከሳሽ ዓቃቢህግ ተከሳሿ ከአንድ የኦነግ ሸኔ አባል ጋር ሜክሲኮ አካባቢ በመገናኘት መንግስትን ከስልጣን ለማውረድ ታዋቂ ሰዎችን ለማስገደል ማቀዳቸውንና ከነዚህ ታዋቂ ሰዎች መካከል አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ መሆኑን ግለሰቡ ገልጿላት አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ እንዲገደል ቦታ እንድታመቻች በተነጋገሩት መሰረት የግድያ ቦታ አመቻችታለች ብሎ ክስ አቅርቧባት የነበረ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ግን የተከሰሰችበት ወንጀል በቂ ማስረጃ አልቀረበም ሲል በነጻ አሰናብቷት ነበር። ዓቃቢህግ በውሳኔው ቅር በመሰኘት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ይግባኝ ያለ ሲሆን ይግባኙን የመረመረው የጠቅላይ ፍርድ ቤት የስር ፍ/ቤት ነጻ በማለት የሰጠውን ውሳኔን በመሻር አርቲስት ሀጫሉ በሽጉጥ በተከሳሽ ጥላሁን ያሚ ተመቶ ደም ሲፈሰው በቸልተኝነት እርዳታ እንዲያገኝ ባለማድረግ የወንጀል ህግ አንቀጽ 575 ንዑስ ቁ1 በመተላለፍ እንድትከላከል ትዛዝ ሰቶ ነበር። ይህን ትዕዛዝ ተከትሎ ለመደበኛ ፍርድ ቤት ተከሳሿ መከላከያ ማስረጃ የለኝም ዓቃቢህግ ባሰማው ማስረጃ ይፈረድብኝ ማለቷን ተከትሎ ፍ/ቤቱ ዛሬ በቸልተኝነት ሰውን ባለመርዳት በወንጀል ህግ አንቀጽ 575 ንዑስ ቁ1 በመተላለፍ የጥፋተኝነት ፍርድ ተሰቶባታል። ተከሳሿ 1 ገጽ ቅጣት ማቅለያ በጽሁፍ አቅርባለች። ፍ/ቤት የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት በይደር ቀጥሯል። ተከሳሽ ላምሮት ከማል የቅጣት ውሳኔ እስኪሰጥ እስከ ነገ ፖሊስ ጣቢያ እንድትቆይ ታዟል። ምንጭ፦ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ
إظهار الكل...
ወደ ሀገር ቤት ለሚመጡ ዳያስፖራዎች በቂ የደህንነት ጥበቃ እንደሚደረግላቸው ጥምር የፀጥታ ኃይሉ አስታወቀ! የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን ጥሪ ተከትሎ ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ያለምንም የፀጥታ ችግር መንቀሳቀስ እንዲችሉ በቂ የደህንነት ጥበቃ እንደሚደረግላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቋቋመው ጥምር የፀጥታ ኃይል አስታወቀ፡፡ ይህ የተገለፀው በዛሬው ዕለት ከሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ከሪፐብሊካን ጋርድ፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ፣ ከኦሮሚያ ክልል ፖሊስ እና ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት የተውጣጣው ጥምር የፀጥታ ኃይል ሀገራዊ የፀጥታ ሁኔታን በገመገመበትና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ባስቀመጠበት መድረክ ላይ ነው፡፡ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ቤት በሚመጡበት ጊዜ ያለምንም የሰላምና የፀጥታ ስጋት በፕሮግራማቸው መሰረት መንቀሳቀስ እንደሚችሉና ያለው የፀጥታ ሁኔታም አስተማማኝ መሆኑን ጥምር የፀጥታ ኃይሉ ገልጿል፡፡ጥምር የፀጥታ ኃይሉ በአጠቃላይ ያለውን ሀገራዊ የፀጥታ ሁኔታ ገምግሞ በቂ ዝግጅት አድርጎ ወደ ስምሪት መግባቱንም የፌደራል ፖሊስ አስታውቋል፡፡
إظهار الكل...
" ሰራዊቱ ባለበት እንዲቆይ ተወስኗል " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ መግለጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር ለገሰ፥ " በጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የተመራው 'ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት' በአሸባሪው ሃይል የተወረሩ አካባቢዎችን በማስለቀቅና ተልዕኮውን በማሳካት የመጀመሪያው ምዕራፍ ተጠናቋል" ሲሉ አሳውቀዋል። በዘመቻው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ታላቅ ጀብዱ የሰሩበትና በታሪክ ወርቃማ ሆኖ የሚጻፍ ስራ የሰሩበት ነው ያሉ ሲሆን የአማራና አፋር ክልል የፀጥታ ሃይሎችም የራሳቸውን ጥረት አድርገው አኩሪ ድርሻ ተወጥተዋል ሲሉ ተናግረዋል። "አሁን ላይ የጠላት መሻት፣ ፍላጎትና የማድረግ አቅም ክፉኛ ተመቷል ያሉት ሚኒስትሩ፥ "ይሁን እንጂ የጠላት ሃይል ፍላጎት ዳግም እንዳይቀሰቀስ መንግስት በቀጣይ በጥናት ላይ ተመስርቶ እርምጃ ይወስዳል" ብለዋል። የወገን ሃይል ጥንካሬውን ይዞ እንዲቀጥል ጠንካራ ስራ ይሰራል ሲሉ የተናገሩት ሚኒስትሩ ህብረተሰቡ እስከዛሬ ሲያደርግ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። ዶ/ር ለገሰ፥"ወራሪውን ሃይል በገባበት የደመሰሰው የመከላከያ ሰራዊትም ባለበት እንዲቆይ ተወስኗል" ሲሉ አሳውቀዋል። "ለዚህም ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል ካጋጠሙ ችግሮች መማር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ በተጠና መልኩ የፀጥታ ሃይሉ እርምጃ እንዲወስድ እንዲሁም በሽብር ቡድኑ ሴራና ወጥመድ ላለመግባት በማሰብ ነው ውሳኔው የተወሰነው" ሲሉ አስረድተዋል። በምዕራብ አማራ ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ መንግስት ወደፊት መረጃዎችን እንደሚሰጥ ጠቁመዋል። ሚኒስትሩ፥ "በኦሮሚያ ክልል በንጹሃን ላይ በአሸባሪው ሸኔ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን ለመከላከል መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል" ሲሉ ማስገንዘባቸውን ፋና ዘግቧል።
إظهار الكل...
ሁለተኛው የቴሌኮም አገልግሎት ፍቃድ ጨረታ ታገደ! የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከመስከረም 18/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለተኛ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ፍቃድ ለመስጠት የሚያስችለውን የጨረታ ፍላጎት ማሳወቂያ ሂደት ላልተወሰነ ጊዜ ማገዱን አስታወቀ፡፡በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት ካላቸው በርካታ አካላት የጨረታ ሂደቱ እንዲዘገይ ያቀረቡትን ጥያቄ መሠረት በማድረግ፣ ባለስልጣኑ የፍላጎት ማሳያ የጊዜ ገደቡን ለተወሰነ ጊዜ እንዲቋረጥ ማድረጉን አስታውቋል፡፡በመሆኑም የሁለተኛው የቴሌኮም ፈቃድ ጨረታ ሂደት መታገዱንና ዳግም ጨረታውን የመክፈት እንቅስቃሴ በቅርብ ጊዜ እንደሚቀጥል ገልጿል። Reporter
إظهار الكل...
የቀድሞ የኢቲቪ ባለስልጣን የነበረው ተሻለ አወቀ ለወራሪው ኃይል ሲታገል እንዲህ ተጎሳቁሎና አመድ መስሎ ተማርኳል!
إظهار الكل...
በአማራ ክልል የሰዓት እላፊ ገደብ ላይ ማሻሻያ ተደረገ። የአማራ ክልል መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃለፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ዛሬ በሰጡት መግለጫ የክልሉ የፀጥታ ኮማንድ ፖስት በክልሉ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ውይይት ካደረገ በኋላ በተጣለው የሰዓት እላፊ ገደብ ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ መወሰኑን ተናግረዋል። ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ ጠዋት 12 ሰዓት የተጣለው የሰዓት እላፊ ገደብ በክልሉ ያለው የጸጥታ ሁኔታ እየተሻሻለ በመምጣቱ የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴዎች እንዳይዳከሙ እና በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ዲያስፖራዎችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ማሻሻያ ተደርጓል ነው ያሉት። በዚህም መሠረት የሰዓት እላፊ ገደቡ ከምሽቱ 4 ሰዓት እስከ ንጋት 11 ሰዓት ድረስ ማሻሻያ መደረጉን አስታውቀዋል። ምንጭ፦ አሚኮ
إظهار الكل...
በአማራ ክልል የመንግሥት ተቋማት መደበኛ ሥራዎቻቸውን እንዲጀምሩ ውሳኔ መተላለፉን የክልሉ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ትናንት ተወያይቶ አቅጣጫዎችን ማስቀመጡን እና በተወሰኑ ጉዳዮች ዙሪያ ማሻሻያ ማድረጉን የክልሉ መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ተናግረዋል። የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በውይይቱ አሁን የተገኘውን አንፃራዊ ድል ከግምት ውስጥ በማስገባት ተቋማት መደበኛ ሥራዎቻቸውን እንዲጀምሩ እና በየደረጃው ከሚገኙ ሠራተኞቻቸው ጋር በመወያየት እቅዳቸውን አሻሽለው እንዲጀምሩ ወስኗል። የተፈናቀሉ የመንግሥት ሠራተኞች ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ፣ የኅልውና ዘመቻውን ለመደገፍ የወጡ የመንግሥት ሠራተኞች ተመልሰው ከመደበኛ ሥራቸው ጎን የኅልውና ዘመቻውን እንዲደግፉም ውሳኔ ተላልፏል።በክተት ጥሪው የክልሉ መንግሥት ተቋማት መደበኛ ሥራዎቻቸውን አቁመው ወደ ኅልውና ዘመቻው እንዲዞሩ እና በጀታቸውም ለዚሁ ዓላማ እንዲውል አስገዳጅ ውሳኔ ተወስኖ ነበር።ከቀበሌ እስከ ዞን የፈረሱ ተቋማትን አደራጅቶ ወደ ሥራ የማስገባቱ ሥራ እየተጠናቀቀ ነውም ተብሏል።ብዛኛው አካባቢዎች ከሽብር ቡድኑ ነጻ መሆናቸውን ተከትሎ የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ገልጿል።
إظهار الكل...
ገንዘብ ሚኒስቴር የተጨማሪ በጀት ጥያቄ ለፓርላማ ሊያቀርብ ነው! የገንዘብ ሚኒስቴር፤ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ የደረሰውን ጉዳት መልሶ ለመገንባት የሚያስችል እና ዜጎች ለማቋቋም የሚውል አዲስ በጀት ሊያጸድቅ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በተዘጋጀው “የአዲስ ወግ” መርሃ ግብር ላይ መስሪያ ቤታቸው በጦርነት ምክንያት የተጎዳውን ኢኮኖሚ ለማካካስ ብሎም መልሶ ለመገንባት ተጨማሪ በጀት እንደሚጠይቅ ተናግረዋል፡፡ [Alain]
إظهار الكل...
አሜሪካ የምትወስደው የአጎአ እድል ስረዛ የቻይናን ኢኮኖሚያዊ ይዞታ የሚያጠናክር ነው ተባለ! ቻይና በምስራቅ አፍሪካ ላይ ያላትን ኢኮኖሚያዊ ይዞታ የሚያጠናክር መሆኑን በመጠቆም የአሜሪካ መንግስት ኢትዮጵያን ከአጎአ ፕሮግራም ለመሰረዝ የደረሰበትን ውሳኔ በደጋሜ እንዲያጤን የአሜሪካ ሴኔት አባሏ ክሪስ ቫን ሆለን እና የኮንግረስ አባሏ ካረን ባስ በድጋሚ ጠየቁ። የአሜሪካ ዉሳኔ ከአጎአ ተጠቃሚ የሆኑ ሴቶችና ወጣቶችን ከመጉዳት ባለፈ ቻይና በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የሚኖራትን ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚያሳድግ በመሆኑ አስተዳደሩ ዉሳኔዉን መቀልበስ እንደሚገባው የአሜሪካ የህግ አዉጪ አካል አባላቶቹ ለፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በጻፉት ደብዳቤ ገልጸዋል። ኢትዮጵያን ከአጎአ እድል መሰረዝ እየተካሄደ ላለው ጦርነት መቋጨትም ምንም ሚና አይኖረውም ያሉት የኮንግረስና ሲኔት አባላቱ የኢትዮጵያ የውስጥ ችግር በተዋጊ ኃይሎቹ መፈታት ያለበት በመሆኑ የባይደን አስተዳደር መሰል ጫናዎችን ማቆም አለበት ብለዋል። ካረን ባስ ባለፈው ሳምንትም ተመሳሳይ ይዘት ያለው ጥያቄ አቅርበው ነበር። ክሪስ ቫን ሆለን እና ካረን ባስ የሕወሓት ኃይል ከአማራና አፋር ክልሎች ለመውጣት የወሰደው እርምጃ በድርድር አማካኝነት የተኩስ አቁም ላይ ለመድረስ የሚያስችል በመሆኑ ከአጎአ የማስወጣት ውሳኔው ሰፊ ጊዜ ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።የህግ አውጪ አባላቱ በጦርነቱ የተሳተፉ ሁሉም አካላት ጦርነቱን በጊዜ እንዲቋጩትም ጥሪ አቅርበዋል።
إظهار الكل...
በካሜሩኑ የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያን የሚወክሉ 25 ተጫዋቾችን ዝርዝር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ አህጉራዊ ውድድር መመለሱ ይታወቃል።ዋልያዎቹ በ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ አንድ ከአስተናጋጇ ካሜሩን፣ ኬፕ ቨርዴ እና ቡርኪና ፋሶ ጋር መደልደላቸው ይታወሳል። በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ የተመረጡት ተጫዋቾች ዝርዝር፦ ግብ ጠባቂዎች፤ ፋሲል ገ/ሚካኤል ተ/ማርያም ሻንቆ ጀማል ጣሰው ተከላካዮች፤ አስቻለው ታመነ ያሬድ ባየ ምኞት ደበበ መናፍ አዎል አስራት ቱንጆ ሱሊማን ሃሚድ ረመዳን የሱፍ ደስታ ዮሃንስ አማካዮች፤ አማኑኤል ዮሃንስ ጋቶች ፖኖም ፍፁም አለሙ ፍሬው ሰሎሞን በዛብህ መለዩ መሱድ ሙሃመድ ሽመልስ በቀለ አጥቂዎች፤ ሽመክት ጉግሳ ሙጅብ ቃሲም መስፍን ታፈሰ ዳዋ ሁቴሳ አቡበከር ናስር ጌታነህ ከበደ አማኑኤል ገ/ሚካኤል ሆነው ተመርጠዋል።
إظهار الكل...
በካማሺ በጸረ-ሠላም ኃይሎች ታፍነው የነበሩ 62 ሰዎች የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን ወደ ማህበረሰቡ ተቀላቀሉ! በካማሺ ዞን በካማሺ ከተማ ሄና ቀበሌ ሁሩንጉ ጎጥ በጸረ-ሠላም ኃይሎች ታፍነው የነበሩ 62 ሰዎች የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት አሰሳና ኦፕሬሽን ከጠላት እጅ ወጥተው ወደ ማህበረሰቡ መቀላቀላቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ የአሰሳና የኦፕሬሸን ስራውን የመሩት የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ምስጋና እንጂፋታ እንደገለጹት÷ ለሃገርና ለወገን ደንታ የሌላቸው የአሻባሪው ህወሃት ተላላኪዎች ማህበረሰቡን በማታለል፣ በማስገደድና በማፈን ላልተገባ ዓላማ እያሰለፏቸው ነው፡፡የታፈኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን የጸጥታ ኃይሉ ከፀረ-ሰላም ሀይሎች እጅ ለማስለቀቅ ለተደረገው ትግል አመስግነው፥ ንጹሃንን ከጠላት የመነጠል ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል። በተደረገው አሰሳና ኦፕሬሽን 62 ሰዎችን ከጠላት እጅ በማስለቀቅ ወደ ማዕከል እንዲገቡ መደረጉን ጠቅሰው፥ ቀሪ በየአካባቢው በግዳጅ የታፈኑ ሰዎች በሠላማዊ መንገድ ወደ መንግሥት እንዲመጡ መንግስትም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደረግላቸው መገለፁን ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳይ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡m
إظهار الكل...
ህወሓት ለአፍሪካ ህብረት በፃፈው ደብዳቤ ላይ አቦ ሳንጆ የኢትዮጵያ መንግስት ጠበቃ እንጅ የሰላም አደራደሪ አይደለም አለ። ህወሓት ለአፍሪካ ህብረት በፃፈው ደብዳቤ ላይ የኢትዮጵያ መንግስት ሁሉንም አቀፍ ምክክር ይደረጋል አለን እንጅ ህወሓት መከታቱን የሚያሳይ ፍንጭ አለገኘንም አለ። በዚህም መሰረት ህወሓት በአፍሪካ የተመድ የሰለም አባት ተብለው የተሰየሙትን የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት አቦ ሳንጆ የኢትዮጵያ መንግስት ጠበቃ እንጅ የሰላም አደራዳሪ አይደለም ብሏል። በደብዳቤው ላይ የአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ መንግሥት ጦሩን ወደ ትግራይ ከማስገባት በተጨማሪ የአየር ድብደባ እንዲያቆም ግፊት ማድረግ አለበት ሲል ጠይቋል። ሱሌማን አብደላ
إظهار الكل...
ኢትዮ ቴሌኮም ያልተገደበ ፕሪምየም ጥቅል አገልግሎት ላይ እስከ 34% የሚደርስ ቅናሽ አደረገ። ወርሃዊ ያልተገደበ ዳታ 1,510 ብር የነበረው አሁን 999 ብር ሆኗል። ሳምንታዊ ያልተገደበ ዳታ 440 ብር የነበረው 300 ብር ሆኗል። ወርሃዊ ያልተገደበ የድምፅ ጥሪ 1,510 ብር የነበረው 999 ብር ሆኗል፣ ወርሃዊ ያልተገደበ የድምፅ እና ጥሪ በጋራ 2,545 የነበረው አሁን 1,700 ብር ሆኗል። ወርሃዊ ያልተገደበ ፕሪሚየም ፕላስ 3,530 የነበረው አሁን 2,330 ብር ሆኗል። በተጨማሪም በቴሌብር እነዚህን አገልግሎቶች ሲገዙ ተጨማሪ 10% ቅናሽ ያገኛሉ።
إظهار الكل...
ቅልጥም ሰባሪው የአጥንት ሐኪም በ Esleman Abay የአሜሪካና ስፔን ዜግነት ያለው ግለሰብ አዲስ አበባ ገባ። ከአስር ቀን በፊት። ዶ/ር ልዊስ አርዞላ ስሙ ነው። "የአጥንት ስፔሻሊስት ነኝ" ይላል። ፈቃድ አልጠየቀም፤ የለውምም። ከህክምና ተቋማት ብርቱ ጉዳይ እንዳለበት ግን ርግጥ ነው። በአዲስ አበባ ኮሪያ ሆስፒታል፤ ጥቁር አንበሳና ሚኒልክ ሆስፒታሎች እየተዘዋወረ ነው። "ነፃ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ነው" ይላቸዋል። ከግለሰቡ ጉዳይ በላይ የበረታ ስራቸው ላይ የተጠመዱ ሰዎችም በዙሪያው ነበሩ። ግለሰቡ ልብ ሊላቸው አይችልም። እነሱ ንሥሮች ስለነበሩ። ሀገር ዉስጥ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ክትትል እየተደረገበት ቆዬ። በመጨረሻም ከዬ ሆስፒታሎቹ ሰባስቦ ለ BBC እና CNN ሊያደርስ ተዘጋጀ። በቁጥጥር ስር ዋለ። የያዘው መረጃ፣ ዳታ እና ግብአቶች አብረው ገቢ ተደረጉ። በትላንትናው ዕለት ማለትም ሀገር ውስጥ በገባ በ 10ኛ ቀኑ በታህሳስ 12/2014 ከኢትዮጵያ ዲፖርት ተደርጎ እንዲወጣ ተደረገ። ግለሰቡ የአጥንት ስፔሻሊስት መስሎ የገባ የ CIA ቅልጥም ሰባሪ ነበር ግልባጭ፦ U.S. Embassy Addis Ababa ለኤምባሲው መረጃ ሞኒተሪንግ ለሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን
إظهار الكل...
"ሀገራዊ ምክክር የሚደረገው የሀገሪቷን የህግ የበላይነት አክብረው ከሚንቀሳቀሱ ሀይሎች ጋር ብቻ ነው። ሰላም ለኢትዮጵያ የፅናት ሽልማቷ ነው፤ ወያኔ በኢትዮጵያ ላይ ከፈፀመው ጥቃት በምንም አይነት የሚያመልጥበት የውሸት ሰበብ የለውም፤ ወያኔ #በውድም_በግድም ትቁን እንዲፈታ ይደረጋል የህግ የበላይነትም ይረጋገጣል፣ ለሰራውም ጥፋት ህግ ፊት ይጠየቃል።" ..... [ አምባሳደር ታዬ የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት የትላንትናውን ምሽት ስብሰባ ካተጠናቀቀ በኋላ የተናገሩት ]
إظهار الكل...
አርቲስት ዘለቀ ገሠሠ በዛሬው ዕለት ከደረሰበት የመኪና አደጋ በሕይወት ተረፈ አርቲስት ዘለቀ ገሠሠ በዛሬው ዕለት ከደረሰበት የመኪና አደጋ በሕይወት መትረፉን አስታወቀ። አርቲስቱ በጠዋት ወደ ሥራ ሲሄድ ቦሌ ማተሚያ ቤት አካባቢ የሸገር አውቶቡስ መንገድ ስቶ የእርሱን መኪና እና ሌሎች ስድስት ተሽከርካሪዎችን በመግጨት እና በማገጫጨት አደጋ አድርሷል። በአደጋውም የአንዲት እግረኛ እናት ሕይወት ወዲያው ሲያልፍ ሌላ አንዲት ግለሰብም ከባድ ጉዳት ደረሶባት ወደ ሕክምና ተወስዳለች። አርቲስት ዘለቀ ገሠሠ በተሽከርካሪው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ቢደርስበትም ሕይወቱ በመትረፉ ፈጣሪን አመስግኗል። ምንጊዜም አሽከርካሪዎች ፍጥነት ቀንሰው እንዲያሽከረክሩም ለኢቲቪ አስተያየቱን ሰጥቷል። ዛሬ ጠዋት ከመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ቶታል አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉን የትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ማስታወቁ ይታወሳል። EBC and AL ain
إظهار الكل...