cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

GA Accountancy & Tax Consultant Firm

የምንሰጣቸው አገልግሎቶች -የሂሳብ ስራ-prepare Financial statement -የግብር እና የታክስ- As'smnt of Taxation -የንግድ ዕቅድ-Business Proposal -ስልጠና- አዲስ ለሚደራጅ ድርጅት, በቡድን እና በግል.. -IFRS -ለአስመጪና ላኪ-Import and export *ገዛኸኝ አበራ የተፈቀደለት የሂሳብ አዋቂና አማካሪ 0926066262 @GezahegnAbera

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدلم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
171
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

የአሜሪካ ዶላር የባንክ እና የጥቁር ገበያ ምንዛሬ ልዩነት እንደገና በከፍተኛ ደረጃ እየሰፋ ነው ©ዋዜማ መንግስት ከወራት በፊት በወሰድኩት የገንዘብ ፖሊሲ እርምጃ በተወሰነ መልኩ ተቆጣጥሬዋለሁ ያለው የአሜሪካ ዶላር የባንኮች ወይንም ይፋዊ የምንዛሬ ዋጋ እና የትይዩ (በተለምዶ የጥቁር ገበያ)  የምንዛሬ ዋጋ ልዩነት ተመልሶ ከፍተኛ ጭማሬ እያሳየ ነው። በሁለቱ ገበያዎች መካከል ያለው የምንዛሬ ዋጋ ልዩነት ወደ 17 ብር ተጠግቷል።ዕሮብ መጋቢት 28 ቀን 2014 አ.ም በነበረ ዋጋም አንድ የአሜሪካ ዶላር በባንክ 51 ብር ከ06 ሳንቲም የሚመነዘር ሲሆን በትይዩው ገበያ ደግሞ አንድን የአሜሪካ ዶላር ከ68 ብር ጀምሮ ይሸጠዋል። በሌላ በኩል የውጭ ምንዛሬውን (ዶላር) ለመግዛት በባንኮች እና ትይዩ ገበያ ያለው ልዩነት 18 ብር እንደሆነም ተረድተናል።  መስከረም ወር በፊት ይሄው ልዩነት 20 ብር በመጠጋቱ ሳቢያ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ብድር በሀገር አቀፍ ደረጃ ታግዶ እንዲቆይና ሌሎች ገንዘብ ነክ እርምጃዎችን በመወሰዱ እንዲሁም ሌሎች የመንግስት ተቋማት የቤት ሽያጭ ለጊዜው እንዲቆም ማድረጋቸው በመጠኑም ቢሆን በሁለቱ ገበያዎች መካከል ያለውን የምንዛሬ ተመን ልዩነት አጥቦት ቆይቷል። ለበርካታ ጊዜያትም የአሜሪካ ዶላርና የብር የባንክ እና የትይዩ ገበያ የምንዛሬ ልዩነት ዘጠኝ እና አስር ብር ገደማ ቆሞ ነበር። ይሄም ልዩነት ሰፊ የሚባል ቢሆንም መንግስት ልቆጣጠረው የምችለው ልዩነት ነው በሚል ትቶት ነበር።  ባለፈው ሳምንት ጥቂት ቀናት ውስጥ ብቻም የጥቁር ገበያው ዋጋ እስከ ሶስት ብር ጭማሬን አሳይቷል። ይህም በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ያለው የመንግስት መጠባበቂያ የውጭ ምንዛሬ ክምችት 1.6 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር መሆኑን ማዕከላዊ ባንኩ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ የታየ ሊሆን እንደሚችል ባለሙያዎች አስተያየታቸውን ለዋዜማ ራዲዮ ሰጥተዋል። የመጠባበቂያ የውጭ ምንዛሬ ክምችቱ ከአንድ  ወር ብዙም ፈቅ ለማይል ጊዜ የገቢ እቃዎች ነው የሚበቃው መባሉም የትይዩ ገበያውን ዋጋም ሳያንረው እንዳልቀረም ነው ባለሙያዎች የሚገምቱት። ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ለሶስት ወራት የገቢ ምርቶችን ሊሸፍን የሚችል የመጠባበቂያ የውጭ ምንዛሬ የነበራት ቢሆንም አሁን ያለው ክምችትም እየተፈጠረ ላለው እጥረት ማሳያ ነው ተብሏል። በሌላ በኩል የበጀት አመቱ የስድስት ወራት የሸቀጦች የወጪ ንግድ ገቢ ወደ ሁለት ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ቢሆንም የገቢ ምርቶች የጠየቀው የውጭ ምንዛሬ ግን ከእጥፍ በላይ መጨመሩ የፈጠረው እጥረትም የጥቁር ገበያው ዋጋ መልሶ እንዲጨምር እንዲያሰፋ ምክንያት መሆኑም ተገልጿል። በንግድ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ አንድ ግለሰብ ባለፉት ሳምንታት ኢትዮጵያ በተለያዩ የአሜሪካ ህጎች የማዕቀብ ሰለባ ትሆናለች የሚሉ መረጃዎች መናፈሳቸውም የጥቁር ገበያ ፍላጎትን ማናሩን እንዳስተዋሉ ገልጸውልናል። 
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
" የነዳጅ ዋጋ ኢትዮጵያን በ1 ወር ውስጥ ብቻ 10 ቢሊዮን ብር አክስሯታል‼️ 🗣 ታደሰ ሃይለማርያም በሩሲያ እና በዩክሬን ጦርነት ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ የጨመረው የነዳጅ ዋጋ በ1 ወር ውስጥ ብቻ ኢትዮጵያን 10 ቢሊዮን ብር እንዳከሰራት ተገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት ፤ የነዳጅ ዋጋ በበርሜል ይሸጥበት ከነበረው 60 እና 70 ዶላር ወደ 140 ዶላር ማሻቀቡ፣ ኢትዮጵያ 10 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ወጪ እንዳስወጣት ወይም እንዳከሰራት አመልክቷል። የድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ኃይለ ማርያም ለሪፖተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፤ እንደ ሌሎቹ አገሮች ሁሉ የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ኢትዮጵያንም ዋጋ እያስከፈላት ነው ብለዋል። በአንድ ወር ብቻ 10 ቢሊዮ ብር እንድታጣ ምክንያት መሆኑ እና ይህም ትልቅ ጉዳት መሆኑን ገልፀዋል። "በወርኃዊ የነዳጅ ወጪዋም ወደ 250 ሚሊዮ ዶላር ከፍ እንዲል አስገድዷል" ያሉት አቶ ታደሰ ይህም መንግሥት ይህንን ልዩነት በመሸፈን በዓለም ዝቅተኛ በተባለ ዋጋ ነዳጅ እየተሸጠ የሚገኝ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል ብለዋል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ መጨመር የበለፀጉ አገሮችን ጭምር እየፈተነ የሚገኝ ሲሆን እንደ ፈረንሣይ ያሉ አገሮች በነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ በማድረግ ህብረተሰቡ ነዳጅን ቆጥቦ እንዲጠቀም ሁሉ ማወጃቸውን አቶ ታደሰ አስታውሰው በኢትዮጵያ ነዳጅ ጭማሪ ባይደረግም ህብረተሰቡ በቁጠባ የመጠቀም ባህሉን ማዳበር አለበት ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ አሁን ነዳጅ በምታስገባበት ዋጋ መሠረት ለገበያ ቢቀርብ የአንድ ሌትር የቤንዚን ዋጋ 76 ብር መሸጥ የነበረበት መሆኑንም የአቶ ታደሰ ገልፃ የሚያስረዳ ሲሆን አሁን ላይ ግን የአንድ ሌትር ቤንዚን ዋጋ 31 ብር ከ74 ሳንቲም እየተሸጠ ይገኛል። ©ሪፖርተር t.me/GAAccountancyandTaxation
إظهار الكل...
አቶ አብነት በሼህ መሀመድ አላሙዲን አዲስ የ13 ሚሊየን ብር ክስ ቀረበባቸው ©ዋዜማ የረጅም ዘመን የሚድሮክ ኩባንያዎች አንዱ አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ አብነት ገብረመስቀል 13 ሚሊየን ብር ደሞዝ ያለአግባብ ወስደዋል በሚል በሼህ መሀመድ አላሙዲን ክስ ቀርቦባቸው ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ።  የዋዜማ ሪፖርተር እንደዘገበችው አቶ አብነት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ ከውል ውጪ ያሉ ጉዳዩች ችሎት ቀርበው በቀረበባቸው ክስ ዙሪያ ምላሽ ሰጥተዋል።  በተከሰሱበት መዝገብ የምስክርነት ቃላቸውን የሰጡት አቶ አብነት ገ/ መስቀል  ከከሳሽ ጋር ዝምድና ወይም ፀብ እንዳላቸው በችሎት ተጠይቀው ዝምድና እንደሌላቸው ገልፀው አሁን ላይ ግን የተከሰተ ፀብ አለ ሲሉ አስመዝግበዋል። በህገ ወጥ መንገድ ደሞዜን እንደወሰድኩ ተደርጎ ለተመሰረተብኝ ክስ ምስክርነት ለመስጠት ነው የመጣሁት ያሉት አቶ አብነት 13 ሚሊዩን ብር የአንድ አመት  ደሞዝ እንዲከፈለኝ ለሂሳብ ክፍል ደብዳቤ ፅፌ ባስገባሁት መሰረት ደሞዜ  ነው የተከፈለኝ ሲሉ ለችሎቱ ተናግረዋል ።  “ለብዙ አመታት ደሞዝ ሳይከፈለኝ ነበር የምሰራው”  ያሉት አቶ አብነት “ደሞዜ ስንት እንደሆነ የምናውቀው እኔ እና ሼክ መሀመድ አላሙዲን ነን”  “ሜድሮክ በ 1993 ስራ ሲጀምር እኔ እና አንተ ደሞዝ አንነጋገርም ደሞዝህን እራስህን ወስን ያሉኝ ሼክ አላሙዲን ናቸው። በዚህ መሰረት የራሴን ደሞዝ የወሰንኩት እራሴ ነኝ”  ብለዋል።  ስለደሞዙ ክፍያ ስምምነት በወረቀት ላይ የተፃፈ የሰነድ ስምምነት ስለመኖሩ የተጠየቁት አቶ አብነት ከ40 ዓመታት ባልንጀራቸው ጋር ስምምነቱ በቃል እንደነበርና እርሳቸውን ሼህ አላሙዲን ብቻ የሚያውቁት ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። “የደሞዝ ክፍያውን መጠን የወሰንኩት አስተዳድራቸው የነበሩ 10 ኩባንያዎች የሚሰሩትን ስራ ታሳቢ በማድረግ ነበር። ለረጅም ጊዜ ድርጅቶቹ ስኬታማ እንዲሆኑ ያለደሞዝ በነፃ ሳገለግልም ነበር”  ብለዋል አቶ አብነት። ለ27 ዓመታት የሚድሮክ አማካሪ የነበሩትና አሁንም ድርጅቱን እያገለገሉ ያሉት አቶ ተክሌ ዳኘው በጉዳዩ ላይ ምስክር ሆነው የቀረቡ ሲሆን አቶ አብነት ባቀረቡትና ሚሊየን ብር እንዲከፈላቸው የሚጠይቀውን ደብዳቤ ለምን ይከፈላቸው ብለው እንደፈረሙ ተጠይቀዋል። አቶ ተክሌ ደብዳቤውን የፈረሙት አቶ አብነትን በማመን እንደሆነ ለችሎቱ ተናግረዋል።  አቶ ዳኘው ደብዳቤውን እንዲፈርሙ ከሌላ አካል ፈቃድ አግኝተው እንደሆነ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ አብነትን በማመን ብቻ ክፍያውን እንዳፀደቁ መስክረዋል። በጠበቆቻቸው አማካይነት መጥሪያ እንዲደርሳቸው የተደረገው ሼህ መሀመድ አላሙዲን በችሎቱ አልቀረቡም።   ችሎቱ ጉዳዩን ተመንክቶ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ በመስጠት ተጠናቋል።
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
ዘመን ባንክ የማስተር ካርድ የክፍያ ሲስተምን መተግበር የሚያስችለውን ስምምነት አደረገ! ዘመን ባንክ ኤም ፒ ጂ ኤስ የተባለ የማስተር ካርድ ሲስተምን በማስጀመር ክፍያዎችን በቀጥታ መክፈል የሚያስችል ቴክኖሎጂን አስተዋውቋል።ይህንን ቴክኖሎጂ ያስተዋወቀው ከማስተር ካርድ ጋር በመሆን ነው።ይህ የክፍያ ሲስተም ለአየር መንገድ እንዲሁም ለሆቴሎች ቅድሚያ አገልግሎት ክፍያ መፈጸም የሚያስችል ነው ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪም የኦንላየን ግብይቶችን በቀጥታ መክፈል የሚያስችል ነው።ይህ የክፍያ ሲስተም በኢትዮጵያ ብርም መገበያየት የሚያስችልና የቀጥታ ክፍያ ንክኪን የሚቀንስ ነው።ኢኮሜርስ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ የመጣ ከመሆኑ አንጻር እንዲህ አይነት ቴክኖሎጂ ግብይቱን በአንድ ቦታ በመጨረስ እንዲቀላጠፍ ያደርጋል። [FBC]
إظهار الكل...
አዲስ አበባ በአፍሪካ ለኑሮ ውዷ ከተማ በመሆን በቀዳሚነት ተቀመጠች ሰኞ መጋቢት 19 ቀን 2014 (አዲስ ማለዳ) አዲስ አበባ በአፍሪካ ከሚገኙና ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ካለባቸው 15 ከተሞች መካከል በቀዳሚነት መቀመጧን ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ የተባለ ድህረገጽ ይዞት በወጣው መረጃ አስታውቋል። ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ የኑሮ ውድነት ደረጃውን በአገራቱ ያለውን የምግብ፣ አልባሳት፣ መዝናኛ፣ የጤና አጠባበቅና መሰል መሠረታዊ ፍላጎቶች አማካይ ወጪዎችን በማነፃፀር ማውጣቱን አስታውቋል። በዚህም ድህረገጹ ባወጣው አሃዛዊ የኑሮ ውድነት መለኪያ ነጥብ መሰረት አዲስ አበባ በ58 ነጥብ 92 በአንደኛ ደረጃ ተቀምጣለች። በኹለተኛ እና በሦስተኛ ደረጃ የተቀመጡት የኮትዲቯሯ አቢጃን እና የዚምባቡዌዋ ሀራሬ ከተሞች ሲሆኑ 55 ነጥብ 73 እና 52 ነጥብ 33 በቅድመ ተከተል የኑሮ ውድነት መለኪያ ነጥብ ተሰጥቷቸዋል። በዝርዝሩ የኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ በ38 ነጥብ 51 እንዲሁም፤ የሞሮኮ ዋና ከተማ ራባት 37 ነጥብ 95 የኑሮ ውድነት ነጥብ በመያዝ በ14ተኛ እና በ15ተኛነት ተቀምጠዋል።
إظهار الكل...
ልማት ባንክ አዲስ ያዘጋጀውን የመዋቅር ማሻሻያ መተግበር አልቻለም ባንኩ ተግባራዊ ሊያደርግ ያስጠናው አዲስ መዋቅር ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር በአንድ ላይ ታጭቆ ይመራ የነበረው የተለያየ የኢንቨስትመንትን ዘርፍ በአይነት በመክፈል በዳይሮክቶሬት ደረጃ የሚያዋቅር እና ለደንበኞችም የተቀላጠፈ እና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላልም የተባለለት ነው። ለአብነት ያህልም በግብርና ኮርፖሬት ፋይናንሲንግ ስር የሰብል ምርት ዳይሮክቶሬት፤ የሆልቲካልቸራል እና የደን ልማት ዳይሮክቶሬት፤ የቁም እንስሳት እርባታ ዳይሮክቶሬት ሌሎች የግብርና ስራዎችንም ያካተተ ዳይሮክቶሬት እንዲቋቋም መዋቅሩ ተጠንቶ ተጠናቋል። ይኸው አደረጃጀት በኢንደስትሪያል ፋይናንስ ኮርፖሬት ስርም የጨርቃ ጨርቅ እና ሌዘር፤ የምግብ እና ምግብ ነክ ፕሮሰሲንግ፤ የኬሚካል እና ፋርማቲኩላር ዳይሮክቶሬት አና ሌሎችም በዚሁ ስር እንዲዋቀሩ እንደሚደረግ ዋዜማ ያገኘችው የባንኩ የጥናት ሰነድ ያመለክታል። ይህ አዲስ መዋቅር የሚቋቋሙት ዳይሬክቶሬቶች ለዘርፉ እውቀት ባላቸው ባለሙያዎች እንዲመራ በማስቻል ከዚህ ቀደም ባንኩ ያጋጥመው የነበረው የፕሮጀክቶች መበላሸት እና የብድር አለመመለስ ችግርን የሚፈታ መፍትሄ ይዞ እንደሚመጣም ተስፋ ተጥሎበታል ይህንን መዋቅርም ተግባራዊ ለማድረግ እንዲቻል የባንኩ ሰራተኞች ከ4 ወር በፊት በፈተና እንዲወዳደሩ በማድረግ የስራ ምደባ ለማውጣት ሙከራ ቢደረግምዋ ግልፅ ባልሆነ ምክንያት ሂደቱ መቋረጡን ሰራተኞቹ ያስረዳሉ። ባንኩ በፍጥነት ያስጠናውን የመዋቅር ጥናት ተግባራዊ እንዲያደርግ ለማስገደድም ሰራተኞቹ የጋራ ፊርማ በማሰባሰብ ለባንኩ የአመራር ቦርድ ማስገባታቸውንም ዋዜማ ከምንጮቿ አረጋግጣለች። የባንኩ የስራ አመራር በጉዳዩ ላይ አስተያየት ካለው በሚል ከሁለት ሳምንት በፊት ላቀረብነው ጥያቄ እስካሁን ምላሽ አላገኘንም።  https://bit.ly/3JSGCQs
إظهار الكل...
ልማት ባንክ አዲስ ያዘጋጀውን የመዋቅር ማሻሻያ መተግበር አልቻለም - Wazemaradio

ዋዜማ ራዲዮ- የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በዓመቱ መጀመሪያ እተገብረዋለሁ ያለውን ተግባራዊ ማድረግ አልቻለም፣ በዚህም ሳቢያ የባንኩ ሰራተኛች ቅሬታ ማሰማት መጀመራቸውን ዋዜማ ሰምታለች። ባንኩ ተግባራዊ ሊያደርግ ያስጠናው አዲስ መዋቅር ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር በአንድ ላይ ታጭቆ ይመራ የነበረው የተለያየ የኢንቨስትመንትን ዘርፍ በአይነት በመክፈል በዳይሮክቶሬት ደረጃ የሚያዋቅር እና ለደንበኞችም የተቀላጠፈ እና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላልም የተባለለት ነው። ለአብነት [&hellip

Photo unavailableShow in Telegram
10 ከፍተኛ ሰንዴ አምራች አገራት የሩስያ እና ዩክሬንን ጦርነት ተከትሎ ዓለም ጦሱ እንደሚተርፋትና እንደማይቀርላት ያጣችው አይመስልም። ይህም በአዳጊ አገራት እንደሚከፋ ከወዲሁ ብዙዎች ሥጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ይልቁንም የስንዴ ዕጥረት መከሰቱ አይቀሬ ነው ተብሏል። የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተለያዩ የዓለም አገራትን ድጋፍ የሚፈልጉ እንደ ኢትዮጵያ ላሉ አገራ ይህ በእጅጉ አሳሳቢ ዜና መሆኑ እሙን ነው። https://bit.ly/3us1dEz
إظهار الكل...
የኢትዮጵያ መንግስት አምርሮ የሚቃወመው ኤች አር6600 ረቂቅ ህግ ይዘት ምንድነው? አል ዓይን የአሜሪካ ኮንግረስ ኤችአር 6600 ረቂቅ ህግ በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት ለማምጣት እንደሚያስችል ይገልጻል የአሜሪካ ኮንግረስ በግጭት ውስጥ ባለችው ኢትዮጵያ ሰላም፤መረጋጋትና የዲሞክራሲ ጥረቶች ይደግፋል ያለውን “የኢትዮጵያ መረጋጋት፣ሰላም እና ዲሞክራሲ አክት” (ኤች አር6600) የተሰኘ ረቂቅ ህግ አቅርቧል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ይህ ረቂቅ ህግ በአሜሪካ ኮንግረስ እንዳይጸድቅ ተቃውሞ እያሰማ ይገኛል፡፡ ረቂቅ ህጉ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የእርስ በእርስ ጦርነት እና ሌሎች ግጭቶችን፤ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን፣ የጦር ወንጀሎችን፣በሰብአዊነት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችን፤ የዘርማጥፋትን እና ሌሎች ግፎችን ለማስቆም ሁሉንም የዲፕሎማሲያዊ፣የልማት እና የግህ መሳሪያዎች ይጠቀማል ይላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ህጉ በኢትዮጵያ ውስጥ የሰብአዊ መብት ጥሰት፤ የጦር ወንጀል፣ ዘር ማጥፋትን እና ሌሎች ግፎችን የፈጸሙ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ ጥረት ያደርጋል፡፡ በረቂቅ ህጉ መሰረት፤ በኢትዮጵያ ከአመት ባለይ ባስቆጠረው ግጭት ተሳታፊ የሆኑት የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግስት እና የትግራይ ኃይሎችን ጨምሮ ሌሎች ተሳታፊዎች ማእቀብ እንደሚጣልባቸው ይገልጿል፡፡ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከተለያዩ የአሜሪካ መስሪያ ቤቶች ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ የሚጠየቁበትን እና ግጭት ቆሞ እርቅ የሚወርድበት ስትራቴጂ እንደሚቀርጽ በረቂቅ ህጉ ተጠቅሷል፡፡ በረቂቅ ህጉ የተቀመጠውን ስትራቴጂ ለማሳካት፤ መፈጸም ያለባቸውን 10 ነጥቦች ዘርዝሯል፡፡ መፈጸም አለባቸው ተብሎው ከተዘረዘሩት ነጥቦች መካከል ከአፍሪካ ህብርት፣ከአውሮፓ ህብረት፤ከተመድ እና ከሌሎች ቀጣናዊ ተቋማት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማጠናከር፣ ያለገደብ ሰብአዊ እርዳታ ማድረስ፣ ቀውስ ሊያባብስ የሚችል የውጭ እርዳታ ማራቅና መለየት፣ የአሜሪካ ኢምባሲ ሰራተኞችን ደህንነት ማስጠበቅ፣የጥላቻ ንግግር መዋጋት፣ግጭቱን ለመፍታት ሁሉንም ብሄሮች ያካተተ ውይይት ማድረግ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ ይህ ህግ ከጸደቀ ከ180 ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ እና ከ180 ቀናት በኋላ በወንጀል ተጠያቂ የማድረግ ሂደትን ሪፖርት ለሚመለከተው የኮንግረስ ኮሚቴ ያቀርባል፡፡ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ግጭቱን በሰላም እንዲፈታ በሚደረጉ ጥረቶች ላይ እክል በሚፈጥር፤ የእርበእርስ ግጭቱ እና ሌሎች ግጭቶች እንዲስፋፉ ተባባሪ የሆነ፣የዘር ማጥፋትና የሰብአዊ መብት ጥሰት በፈጸመ፣ ሰብአዊ እርዳታ እንዳይደርስ ባደረገ እና በኢትዮጵያ ውስጥ በአፍሪካ ህበረት፣ በተመድ እና በሰብአዊ እርዳታ ሰጭ ሰራተኛ ላይ ጥቃት የፈጸመ አካል ላይ ማእቀብ እንዲጥሉ በረቂቅ ህጉ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በግጭቱ ውስጥ በማወቅ የተሳተፋ፤ በግጭቱ ለተሳተፈ ማንኛውም አካል እርዳታ ያደረገ አካል ማእቀብ ይጣልበታል፡፡ በረቂቅ ህጉ ላይ ማእቀብ የሚጣልበት ሰው በአሜሪካ የሚኖር ከሆነ ንብረቱ እና የሚያደርገው ግብይት ሊታገድ ይችላል፡፡ ማእቀቡ ቪዛ የማገድ፣የመሰረዝ እና ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ማድረግን ያካትታል፡፡ ሌላው በረቂቅ ህጉ የተካተተው ብዙዎችን ያሳተፋ ማእቀብ ወይም መልቲ ላተራል ማእቀብ ነው፡፡ በአሜሪካ የጦር መሳሪያ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ መሳሪያዎች ሁሉ ወደ ኢትዮጵያ እና ወደ ኤርትራ የሚደረግ ሽያጭ ፍቃድ እንደማይሰጥ ረቂቅ ህጉ ጠቅሷል፡፡ በረቂቅ ህጉ፣የኢትዮጵያ መንግስት ከእርበእርስ ግጭቱ ጋር የተገናኘ ወታደራዊ ዘመቻውን ካላቆመ፣ አካታች ውይይት ለማድረግ ካልተንቀሳቀሰ እና ሰብአዊ እርዳታ ያለገደብ የሚደርስበትን እድል ካልፈጠረ፣ ለኢትዮጵያ መንግስት የሚደረገው የጸጥታ ድጋፍ ይታገዳል፡፡ የአሜሪካ መንግስት በረቂቅ ህጉ፤ ለኢትዮጵያ የሚደረገውን አለም አቀፍ የገንዘብ ድጋፍ ውስን እንዲሆን ለማድረግ ትሰራለች፡፡ የአሜሪካው ገንዘብ ሚኒስትር በሁሉም አለምአቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ያሉትን ተወካዮች መጠቀም፤ ተቋማቱ ለኢትዮጵያ እና ለኤርትራ የሚያደርጉትን ብድር፣ ብድር ማራዘም እና ማንኛውንም ቴክኒካዊ ድጋፍ ማድረግን እንዲቃወሙ ያደርጋል፡፡ በረቂቁ እንደተጠቀሰው ከሆነ አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ማለት አይ አም ኤፍን፣ የአውሮፓ ባንክን፣የአፍሪካ ልማት ባንክን፣ባንክ ኦፍ ዴቨሎፕመንት ኤንድ ኮኦፐሬሽን ኢን ሚድል ኢስት ኤንድ ኖርዝ አፍሪካን ጨምሮ ከ10 በላይ አበዳሪ ተቋማትን ነው፡፡  በረቂቅ ህጉ መሰረት፣አሜሪካ ከሌሎች ለጋሽ ሀገራት ጋር በመሆን በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብትን ለማሻሻል እና ሰላምን ለማምጣት የሚያስችል የብድር ስትራቴጅ ያዘጋጃል፡፡ ይህ ረቂቅ አዋጅ ከጸደቀ ከ180 ቀናት በኋላ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ህወሓት፣ የታጠቁ ተቃዋሚዎች ወይም ተባባሪ ኃይሎች፣ በሰብአዊ መብት ጥሰት፣በጦር ወንጅል፣በዘርማጥፋት እና በሌሎች ኢትዮጵያ ውስጥ በተፈጸሙ ግፎች፣ ሰላማዊ ሰዎች ላይ እና በሲቪል በመሰረት ልማቶች ላይ በደረሰው ጥቃት ያላቸውን ተሳትፎ በመለየት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሚመለከተው ኮንግረስ ኮሚቴ ያቀርባል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሚኒስቴሩ ከአሜሪካ የውጭ ገዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ቱርክ፣ሩሲያ፣አረብ ኤምሬትስ፣ግብጽ፣ኢራን፣ሱዳን እና ቻይና በኢትዮጵያ በግጭት ውስጥ ላለ ማንኛውም አካል ያደረጉትን የገንዘብ እና የመሳሪያ ድጋፍ በመለየት ለኮንግሩ እንደሚያቀርብ ረቂቁ ላይ ተመልክቷል፡፡ ሪቂቅ ህጉ በግጭቱ ያላቸው ሚና ይለያል ያላቸው ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ወይም ሌሎች አካላት ያስቀመጡባቸው የውጭ የገንዘብ ተቋማት እና ሆነብለው ጦር መሳሪያ ግዥ ወይም ዝውውር እንዲፈጸም ያመቻቹ የገንዘብ ተቋማት ተለይተው ይቀርባሉ፡፡ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍት በትናንትናው እለት በሰጡት መግለጫ ረቂቅ ህጉ “በአሜሪካ አስተዳደር በኩል በአሁኑ ሰአት የሚፈለግ አለመሆኑን” ተረድተናል ብለዋል፡፡ አስተዳደሩ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ገንቢ በሆነ መልኩ የመስራት ፍላጎት ቢኖረውም ኮንግረሱ የህግ አውጭ አካል ስለሆነ አንዱ በአንዱ ላይ ሚያሳድረው ተጽእኖ ወሳኝ አይደለም ብለዋል አምባሳደር ዲና፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ባለፈው ሳምንት “በመላው አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ ወገኖች በአሜሪካ ምክር ቤቶች በኢትዮጵያ ላይ ለማሳለፍ የታቀዱት እጅግ አደገኛ ረቂቅ ህጎች እንዳይጸድቁ ከፍተኛ ዘመቻ እንዲያደርጉ” ጠይቀዋል፡፡ አንድ አመት ከሰባት ወር የሞላው በኢትዮጵያ ተቀሰቀሰው ግጭት፤ በሰላም እንዲፈታ አሜሪካ እና የአፍሪካ ህብረት ጥረቶች ጀምረዋል፡፡ በግጭቱ በትግራይ፣በአፋር እና በአማራ ክልሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወታቸውን ሲያጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ደግሞ ከቀያቸው በመፈናቀል ኑሯቸው እንዲመሰቃቀል ሆኗል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ በቅርቡ ባካሄደው ስብሰባ በኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት ለመፍታት ማንኛውንም የሰላም አማራጭ እንደሚከተል አስታውቆ ነበር፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ሚኒስቴር በትናንትናው እለት በሰጠው መግለጫ መንግስት የሰብአዊ እርዳታ በአግባቡ ወደ ትግራይ እንዲደርስ ለማስቻል የተኩስ አቁም ማወጁን ይፋ አድርጓል፡፡ የመንግስትን መግለጫ ተከትሎ ህወሓት በዛሬው እለት ባወጣው መግለጫ ሰብአዊ እርዳታ በአግባቡ ወደ ትግራይ የሚገባበት ሁኔታ ከተፈጠረ ተኩስ ለማቆም ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቋል፡፡
إظهار الكل...
የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከአንድ የኔዘርላንድ ትምህርት ተቋም ጋር በመተባበር ያስጠናው ጥናት ብሄራዊ ባንክ ለአነስተኛ ይዞታ ላላቸው አርሶ አደሮች የብድር ዋስትና እንዲሰጥ ምክረ ሃሳብ ማቅረቡን ሪፖርተር አስነብቧል። በአገሪቱ በ221 ወረዳዎች ላይ የተደረገው ጥናት፣ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ከባንኮች የገንዘብ ብድር ቢያገኙ፣ ብድራቸውን መመለስ እንደሚችሉ ደምድሟል። ሆኖም አበዳሪዎች አምነት እንዲኖራቸው፣ ብሄራዊ ባንክ የብድር ዋስትና እንዲሰጥ ጥናቱ ሃሳብ አቅርቧል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በቅርቡ ባንኮች ለአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ብድር ለመስጠት እንዲዘጋጁ ማሳሰባቸው ይታወሳል።
إظهار الكل...
ዋዜማ :በኢትዮጵያ 21 የታሸገ የማዕድን ውሃ አምራች ፋብሪካዎች ሥራ እንዳቆሙ ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። ውሃ አምራች ፋብሪካዎች ሥራ ለማቆማቸው፣ የጥሬ ዕቃዎች ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ መጨመር፣ ሕጋዊ የሽያጭ ደረሰኞችን አለመጠቀም፣ መንግሥት በታሸገ ውሃ ላይ የሚጥለው ኤክሳይስ ታክስ እና ውሃ አምራች ፋብሪካዎች ቅድሚያ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት አለማግኘታቸው በምክንያትነት ተጠቅሰዋል። አሁን ምርት ያቆሙትን ጨምሮ በመላ አገሪቱ ያሉት የታሸገ የማዕድን ውሃ አምራች ፋብሪካዎች 134 ሲሆኑ፣ ምርት በማምረት ላይ ያሉት ሌሎች ፋብሪካዎችም በሙሉ አቅማቸው እያመረቱ እንዳልሆነ ዘገባው ገልጧል። የችርቻሮ ነጋዴዎች የታሸገ ውሃ ከፋብሪካ ዋጋው እስከ ሦስት እጥፍ ጨምረው እንደሚሸጡ ፋብሪካዎቹ ይናገራሉ።
إظهار الكل...