cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Tesfaab Teshome

ለአስተያየት @jtesfaab ላይ ይፃፋልኝ ለመቀላቀል @tfanos ይጫኑ። ቤተሰብ ስለሆንን አመሰግናለሁ ❤❤😍

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
1 874
المشتركون
+124 ساعات
+107 أيام
+8630 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

01:11
Video unavailableShow in Telegram
ደራሲና ጋዜጠኛ መለስ ዜናዊ
إظهار الكل...
23.24 MB
02:42
Video unavailableShow in Telegram
52.40 MB
3👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ዋርካው ወደቀ ጋሽ ነብይ በዘመናቸው መስራት ያለባቸውን ሰርቷል። ዘመናቸው አልባከነም። ሞታቸው የሚያጎድለው ለኛ ነው። ዋርካ ናቸው። ዛሬ ዋርካው ወድቋል
إظهار الكل...
😢 9👍 1👏 1
ምስጋና ለ አዳማ ባቡር ጣቢያ ሃላፊ ትላንት በባቡር ጉዞ የገጠመኝን ችግር ካጋራሁ በኋላ የአዳማ ባቡር ጣቢያ ሃላፊ ስልክ ደውሎልኝ ነበር። አቶ ሮባ ይባላል። በፍፁም ትህትና እና በሃላፊነት ስሜት አናግሮኛል። ለተፈጠረው ችግር ሃላፊነት ወስዶ ይቅርታ ጠይቋል። የችግሩን ሰበብ በዝርዝር አስረድቶኛል። በተጨማሪም ለተጉላሉ ሰዎች ገንዘባቸው እንደሚመለስ ቃል ገብቶልኛል። የችግሩ ሰበብ ከተለመደው በላይ ተጓዥ መኖሩ እንደሆነ ነግሮኛል። አዲሳባ ፥ ሞጆ ፥ አዳማ ፥ ሚኤሶ መጫን የሚገባቸው የሰው ኮታ አለ። በዚህ መሓል አዲሳባ ትኬት የቆረጡ አዲስ አበባ ላይ በመሳፈር ፈንታ ወደ አዳማ አቀኑ። አዳማ ደግሞ ከኮታ በላይ ትኬት ፈላጊ ነበር። በተለይ ድሬዳዋ ተማሪ ስለሚያስመርቅ ከፍተኛ ተጓዥ ነበር። ስለዚህ ሰዎች እንዲመለሱ ከማድረግ ይልቅ አዲስ አበባ ቲኬት ቆርጠው ነገር ግን ባልተሳፈሩ ሰዎች ቦታ የአዳማዎችን ለማስገባት ታሰበ። ችግሩ የተፈጠረው አዲሳባ ትኬት የቆረጡቱ ከአዳማ ሊሳፈሩ መጡ። የአዲስአበባዎቹን ከፍለዋልና መመለስ አይቻልም። ስለዚህ የተወሰነው መፍትሄ የአልጋ የከፈሉት በመደበኛው እንዲጓዙ ማድረግ ነው። ለአዳማ ተጓዧች መደበኛው ወንበር አልቋል ተብሎ ነበር። ነገር ግን ያለቀው የአዳማው ኮታ ነው። ስለዚህ ከሜኤሶ ኮታ ላይ እንዲቀነስ ተደረገ። ሚኤሶ ባቡር ጣቢያ የሚሸጠው ኮታ ላይ በመቀነስ አዳማ ላይ የተስተጓጎሉቱ እንዲቀመጡበት ተደርጓል። ይህ ማብራሪያ ከአዳማ ባቡር ጣቢያ ሃላፊ አቶ ሮባ የተነገረኝ ነው። እንግዲህ "ስህተት ተሰርቷል" ብዬ ወቀሳ ባቀረብኩበት መድረክ ለተሰጠኝ ማብራሪያ እና ለእረምት እርምጃው ማመስገን ይኖርብኛል። @Tfanos
إظهار الكل...
👍 6 3
"መፅሐፍቶች በ Pdf" የሚል የቴሌግራም ቻናል አለ። ዛሬ የቻናሉ ሊንክ ተልክልኝ አየሁት። የኔን ፅሁፎች ምንጭ ሳይጠቅስ አጋርቷል። የሌሎች ሰዎችንም ፅሁፍ በተመሳሳይ አጋርቷል። ከዚህ በፊት ያልኩትን ልድገም በጥቂት የታመነ በብዙ ይሾማል። ማንኛውንም ነገር የሚሰርቅ ሌባ ነው። መርፌ ወይም የሰው ሃሳብ ወይም ሰባራ ሳንቲም የሚሰርቅ ፥ የራሱ ያልሆነን የራስ አስመስሎ የሚያቀርብ ሰው ሌባ ነው። የሰው ፅሁፍ የራስ አስመስሎ ማቅረብ የባህሪ ብልሽት ጭምር ነው። አንደኛ ለሰው ስራ ተገቢውን እውቅና እና አክብሮት ነፋጊነት ነው። ሁለተኛ የማይገባን ጥቅም ፥ ዝና ወዘተ ፈላጊነት ነው። መርፌ የሚሰርቅ ተው ካልተባለ ነገ ባንክ ሊዘርፍ ይችላል። የሰው ፅሁፍ ሰርቆ በቴሌግራም የሚያጋራም ዛሬ ዝም ከተባለ ነገ የሰው መፅሐፍ ሰርቆ ከማሳተም አይመለሰም። የዛ ቻናል አድሚኖች ታረሙ።
إظهار الكل...
👍 12
በባቡር ጉዞ የገጠመኝ ተቋማዊ ማጭበርበር! * * * ከአዳማ ድሬዳዋ በባቡር ለመጓዝ ትኬት ለመቁረጥ ተሰለፍን። ለሰአታት ከተሰለፍን በኋላ መደበኛ ትኬት እንዳለቀ ነገሩን። "ምንድነው መፍትሄው?" አልን "ተጨማሪ ገንዘብ ከፍላችሁ አልጋ ያለውን ያዙ" አሉን። እንደተባልነው አደረግን። ከመደበኛው ክፍያ ለእጥፍ የቀረበ ክፍያ ከከፈልን በኋላ ወደ ባቡሩ ከገባን በኋላ የተቋሙ ስላቅ ተጀመረ። "ቦታ የለም" ተባልን። በዚህ ጉዳይ እየተጨቃጨቅን ባቡሩ ጉዞ ጀመረ። ያን ረጅም መንገድ ቆመን ልንጓዝ መሆኑ ነው። ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ "መደበኛ ወንበር ላይ ቦታ ስላለ እዛ ተቀመጡ" ተባልን። ቀድሞ ነገር መደበኛ ቦታ ላይ ወንበር የለም ተብለን ተጨማሪ ገንዘብ ከከፍልን በኋላ በመደበኛው መጓዝ አግባብ አልነበረም። "ተጨማሪ ክፍያችሁ ይመለሳል" ብለው አረጋጉን። ተጨማሪ የከፍልነውን ሰዎች ስማችንን ተቀበሉን። 27 ሰዎች ነን። "የሁላችሁም ብር ይመለሳል" አሉን። ድጋሚ አመንን። ድሬዳዋ ደርሰን ከባቡሩ ከወረድን በኋላ ግን ሁሉም ሰራተኞች "አይመለከተንም" አሉ። ይህ ተቋማዊ ማጭበርበር ነው። ትኬት ቦታ ላይ "መደበኛው ትኬት አልቋል" ያለን ፌደራል ፖሊስ ነው። በሌለ ቦታ አለአግባብ አስከፍለው ትኬት የቆረጡልን የድርጅቱ ሰራተኞች ናቸው። ገንዘብ ይመለሳል ካሉ በኋላ አያገባንም ያሉትም የተቋሙ ሰዎች ናቸው። ይህ ተቋማዊ ማጭበርበር ነው። @Tfanos
إظهار الكل...
👍 4😁 1😢 1
ስለ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም አንዳንድ ነገር * * * መስፍን ወልደማርያም ፕሮፌሰር ከመሆናቸው በፊት ለአንዲት ቀን ያህል መናኝ ሆነው ነበር። መስፍን አዳጊ ልጅ በነበረ ግዜ ከጓደኞቹ ጋር በአእምሯቸው መጠን ስለ ህይወት ተወያዩ። በመጨረሻም "መናኝ መሆን አለብን" ብለው ወሰኑ። መስፍንና 3 ጓደኞቹ በጋራ በመሆን በአቅራቢያቸው ወዳለ ጫካ አመሩ። "ዱር ቤቴ" ብለው ቀሪ ዘመናቸውን በጫካ ለመኖር በማሰብ ወደ ጥቅጥቁ ደን ገቡ። እስከ አመሻሽ በጫካው ከቆዩ በኋላ ከመሃከላቸው አንዱ "እናቴ ናፈቀችኝ" አለ። ሌሎችም "እኔም" አሉ። ያኔ እስከ ህይወት ፍፄሜ ሊቆዩበት የወሰኑበትን ጫካ ትተው ወደ ቤተሰቦቻቸው ተመለሱ። ፕሮፌሰር መስፍን ይችን አጋጣሚ "ቢያንስ ለአንድ ቀን መንኛለሁ" በማለት ይገልጿታል። የፕሮፌሰሩን "አገቱኒ ተምረን ወጣን" መፅሐፍ ለወጋችን ምስክር ጠርተን ጥቂት የልጅነት ገጠመኞችን እናክል። መስፍን "ልጅ ሳለሁ ተፃራሪ ባህሪዎች ነበሩኝ" ይላሉ። "ለልመና የተቀመጠ ሰው አለማመኑ አሳዛኝ ከሆነ አብሬው ተቀምጬ አለቅሳለሁ። ያኔ እናቴ ናት ከስፍራው የምታነሳኝ" ይሉናል። ይህን አይተን አዛኝና ሩህሩህ ብላቴና አድርገን ከደመደምን ስህተት እንሰራለን። ታዳጊው መስፍን ውሃ ቀድተው የሚመለሱ ሴቶችን ማሰሮ በመስበር ይደሰት ነበር። ተቃራኒ ብላቴና! መስፍን ገና ልጅ ሳለ ከአንድ እኩያው ተጣለ። ልጁ ጭራሮ ወረወረበት። ይሄኔ መስፍን ልጁን አሳደደው። ልጁ ሲሸሽ ወደቀ። የዛሬው ፕሮፌሰር የያኔው ታዳጊ መስፍን ወልደማርያም ልጁን በወደቀበት ወጋው! ፖሊሶች መስፍንን እጁን አስረው ወደ ማረሚያ ወሰዱት። "የልጅነት ቁጣዬን እና ሃይለኝነት በስፖርት እና በፀሎት ገራሁት" ይሉናል ፕሮፌሰሩ። በነገራችን ላይ፥ መስፍን መጀመሪያ ሰሞን ወደ ተማሪ ቤት የሚላከው በእግረ ሙቅ እየታሰረ ነበር። በሂደት የትምህርት ቤቱ አለቃ ሲሆን የተማሪቤት ስልጣኑን እየወደደው ሲሄድ ያለ እስር በፈቃዱ ትምህርት ቤት መሄድ ጀመረ። በታዳጊነቱ እናቱ ስትሞትበት በቀላሉ አምኖ መቀበል ተሳነው። ያኔ ሳምንቱን ሙሉ ለሊት 11 ሰአት መቃብር ስፍራ ያቀናና መቃብሩን ትኩር ብሎ ይመለከታል። "ምናልባት መቃብሩ ከተንቀሳቀሰ ቆፍሬ እናቴን አወጣታለሁ" ይል ነበር @Tfanos
إظهار الكل...
🥰 4🔥 2👏 2
የትላንቱ ጥፋት ዛሬ ሲደገም... * * * ረሃብ የ 40 ቀን እድላችን የሆነ ይመስል በየዘመኑ ይጎበኘናል። ዘመን አልፎ ዘመን ሲመጣ ገበሬው የሚጎርሰውን ያጣል ፥ ጎበዙ በመብል እጦት ይወድቃል ፥ እናት በረሃብ የተነሳ ትሞታለች ፥ ከሞት የተረፉቱ ያለ አሳዳጊ ይቀራሉ። አንዱ ሰቆቃ ቁስሉ ሳይሽር ሌላ ረሃብ ይከሰታል። ትላንት የተራቡቱ ደግመው ይራባሉ። "ታሪክ ራሱን ይደግማል" እንደሚባለው ሁሉ በኢትዮያ ውስጥ ረሃብ ራሱን ይደግማል። እዚህ ሐገር ራሱን የሚደግመው ረሃብ ብቻ አይደለም። ሹማምንት ለዜጎቻቸው ያላቸው ንቀት እና ግድ የለሽነትም በየዘመኑ ይገማል። የቀደመውን የሚመስል መንግስታዊ ንቀት ይከተላል። ንጉሱ በ66 ረሃብ ወቅት ለህዝቡ ችግር ተገቢውን ትኩረት አልሰጡም ነበር። ዛሬም ድረስ "ህዝብ ተርቦ ይደግሳሉ" ተብለው ይወቀሳሉ። አሳዛኙ ስላቅ ህዝብ ተርቦ ንጉሱ በቅንጦት ማሳለፋቸው አይደለም። አሳዛኙ ስላቅ ለህዝብ እናስባለን ያሉቱ ጃንሆይን ባወገዙበት መንገድ መራመዳቸው ነው። በ77 ዳግመኛ ረሃብ መጣ። ህዝብ የሚበላውን አጥቶ በጠኔ ይረግፍ ጀመር። ደርግ ወደ ስልጣን የወጣ ሰሞን "የ 66ቱን ረሃብ ለሚዲያ እንዳይቀርብ በማድግ ህዝብ በድላችኋል" በማለት እነ በአሉ ግርማን መርምሯቸው ነበር። ንጉሱ ህዝብ ተርቦ በድግስ መያዛቸውን አውግዞም ነበር። በተራው ግን በ 77 ህዝብ ተርቦ ደርግ ለአብዮቱ አስረኛ አመት መታሰቢያ ከፍተኛ ገንዘብ በጅቶ ድግስ ደገሰ። ገንዘቡን ለተራቡቱ ማድረግ እየቻለ ስልጣን የያዘበትን 10ኛ አመት ማክበር አስቀደመ። አመታት አለፉ። የሹማምንት ስላቅ እና ንቀት እየተደጋገመ ዘማናት ሄዱ። በዘመናችን ሚሊዮኖች ስራ አጥ ናቸው። ትምህርት ቤቶች በጦርነት ወድመዋል። መንገዶች ፈርሰዋል። የጤና ተቋማት ከአገልግሎት ውጭ ሆነዋል። ገበሬው መዳበሪያ አጥቷል። የመንግሥት ሰራተኞች ደሞዝ በአግባቡ እየተከፈላቸው አይደለም። የሚከፈላቸውም ኑሮውን እየተቋቋሙት አይደለም። ይህ ብቻ አይደለም። በትግራይ ፥ በወለጋ ፥ በአማራ ፥ በቤንሻንል ወዘተ ዜጎች ለረሃብ ተዳርገዋል። በዚህ ሁሉ መሃል ሹማምንቶቻችን በቤተመንግስት ግንባታ ፥ ከተማን በመብራት በማብለጭለጭ ስራ ተጠምደዋል። የትላንቱ ጥፋት ዛሬም ተደግሟል። @Tfanos @Tfanos
إظهار الكل...
7👍 5
02:35
Video unavailableShow in Telegram
50.10 MB
4
ሴትዪቱ ፀብ አፍቃሪ ናት። ያለነገር መኖር አትችልም። በየማለዳው ለባብሳ ጥል ፍለጋ ትወጣለች። ምናልባት የጠዋት ፀሎቷ "ያለ ፀብ አታውለኝ" ይሆናል። ሲመሽ ደግም "የእለት ነገሬን ያልነሳኸኝ አምላክ ለነገው ፀብም አደራ" እያለች ይሆናል ወደ መኝታዋ የምታቀናው እንደልማዷ ያላትን የክት ልብስ ለባብሳ ፀብ ፍለጋ ስትወጣ ያየቻት ጉረቤቷ " በማለዳ ወዴት ነው?" አለቻት። "ነገር ፍለጋ ወጣ ልበል ብዬ" "ነገር ምን ያደርግልሻል?" አለቻት ግራ የገባት ጎረቤት "በቃ! የፈለግኩትን ነገር እዚሁ አገኘሁት" ፀብ ነበር የፈለገችው። የፀብ አምላክ ፀሎቷን ሰምቷል ማለት ነው። አንዳንዱ ደግሞ ያለ ጠላት መኖር አይችልም። ጠላት ቢቸግረው የገዛ ወዳጁን ጠላት ያደርገዋል። ቀጥሎ ያጠቀዋል። ያጠቃውን ከጣለው "በቃ ጀግና ነኝ" ብሎ ይፎክራል። ጀግና መሆናቸው እንዲታወቅላቸው ይታትራሉ። መታተራቸው ግን ለገዛ ራሳቸው ጠላት ፍለጋ ነው። ጀግና የመሰኘት ረሀባቸውን የፈጠሩትን ጠላት በማጥቃት ያስታግሱታል @Tfanos
إظهار الكل...
4
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.