cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ፍቁረ እግዚእ ሚዲያ Fikure Egzi Media – FEM

በደ/ነ/ቅ/ዮሐንስ እና መ/ጎ/ቅ/ማርያም ቤተክርስቲያን የፍቁረ እግዚእ ሰንበት ት/ቤት ገጽ ነው https://www.facebook.com/Fikureegzi4 √ ዌብሳይታችን www.fikureegzi.com √ የዩቲዩብ ገጻችንን https://youtube.com/channel/UCXceln4wpQhIVS42O02kAWg ለሀሳብ አስተያየት ይህንን ይጠቀሙ!! @FikureEgzi04

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
7 423
المشتركون
+624 ساعات
+417 أيام
+15530 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ባሕረ ጥበባት ዲጂታል መጽሔት የተለያዩ መንፈሳዊ ርዕሰ ጉዳዮችን እየዳሰሰች እውቀትን የምታስጨብጠን ዲጂታል ባሕረ ጥበባት የእጅ መጽሔት የሰኔ ወር እትም ።          📲   ገጹን ጆይን ያድርጉ!        📱📱  ያውርዱ!       📖📖  ያንብቡ!        👨‍👧‍👦👨‍👦‍👦  ያጋሩ!
إظهار الكل...
ባህረ ጥበባት ሰኔ 2016 01.pdf2.58 MB
10🙏 2🥰 1👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
ቅዱስ ዮሐንስ ሆይ ሰላምታ ይገባሃል ፨ የኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጅ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤  ፨ አቡቀለምሲስ የተባልክ ክቡር ዮሐንስ  ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤  ፨ የሐዲስ ሥርዓት ሐዋርያ ዮሐንስ ሆይ!  በቤተ ምንዳድ ለደረሰብህ መከራ  ሰላምታ ይገባሀል፤  ፨ በትዕግስትህ የሮምንና ቁጣ ችለህ  የሞተውንም ያስነሳህ ዮሐንስ ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤ ፨ መከራን የምትታገስ ዮሐንስ ሆይ! እንዳንተ ያለ በምድር ላይ ማነው፤ ፨ ክብርን የተሞላህ ዮሐንስ ሆይ! ሰላምታ ለአንተ ይሁን እያልኩ በምስጋናና በእምቢልታ  የቤተክርስቲያን የጉባኤዋ መሪ እነሆ  አደንቅሀለሁ፤ ፨ በምስጋና እና በማህሌት የመላእክት ወዳጅ የሆንክ እውነተኛ  ዮሐንስ ሆይ! ሰላም ለአንተ ይሁን፤  ፨ ዮሐንስ ሆይ! ለሚልህ የመልክህ ደምግባት ምን ያምር፤ የስምህስ አጠራር ምን ይጣፍጥ፤ ፨ አራተኛውን ወንጌል የጻፍክ ዮሐንስ  ሆይ! ሰላምታ ይገባሀል፤ ኮል የተባለ  የምስጋናህ መዓዛ በሰው ሁሉ አፍንጫ  በጎ በጎ ሸተተ፤ ፨ ንስር የተሰኘህ ዮሐንስ ሆይ! ልዑል ከሆነ ከሰማይ ተዋሕዶ ቃል ሥጋ ሆነ፤ በእኛም አደረ እያልክ በረህ ና                             መልክአ ቅዱስ ዮሐንስ
إظهار الكل...
73🙏 5👍 4👏 3🥰 2
Photo unavailableShow in Telegram
የመንፈሳዊ ትምህርት ለመማር አስበዋል! 📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖       የፍቁረ እግዚእ ሰንበት ት/ቤት የክረምት  ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት   አዘጋጅቶ ይጠብቆታል። 👉 ትምህርቱ የሚሰጥበት   🗓 ሰኞ እስከ ዓርብ 🕰 ከምሽት12: 00 እስከ 2:00 ሰዓት ድረስ 👉 📅  ትምህርቱ የሚጀምረው ሰኔ 17 ቀን 2016 ዓ.ም 📝 ምዝገባው: -  በሰንበት ት/ቤቱ ቤተ መጽሐፍት እና በሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከቀኑ 9:00 እስከ ምሽቱ  2:00 ሰዓት ቅዳሜና እሁድ ከጠዋቱ 3: 00 እስከ ምሽቱ 2:00 ሰዓት ወይም  🌍  ከስር ያለውን የዌብሳይታችንን  ሊንክ በመጫን ባሉበት ቦታ ሆነው  መመዝገብ ይችላሉ። https://fikureegzi.com/Free_Registration          ትምህርቱ የሚሰጠው በነጻ ነው!! "አንተ ግን በተማርክበት እና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር" 2ጢሞ 3÷14
إظهار الكل...
13👏 2👍 1
በዛሬው እለት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ከ አዲስ አበባ ከንቲባ ክብርት አዳነች አበቤ ጋር በመሆን በኮሪደር ልማት ምክንያት በፈረሱ ቤቶች ምትክ በቤተ ክርስቲያኒቱ የሚገነባ ህንፃ የመሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ።
إظهار الكل...
👍 20
ቤተሰብ ይሁኑ ‼ ምእመናን ጋር ተደራሽነታችንን ለማስፋት ይረዳን ዘንድ አዲስ የተከፈተውን የዋትሳብ ገጻችንን ሊንኩን በመጫን ጆይ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ። Follow the Fikure Egzi Media  ፍቁረ እግዚእ ሚዲያ – FEM channel on WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VaZYuAsJkK7Gt4gNXs1C
إظهار الكل...
Fikure Egzi Media ፍቁረ እግዚእ ሚዲያ – FEM | WhatsApp Channel

Fikure Egzi Media ፍቁረ እግዚእ ሚዲያ – FEM WhatsApp Channel. በደ/ነ/ቅ/ዮሐንስ እና መ/ጎ/ቅ/ማርያም ቤተክርስቲያን የፍቁረ እግዚእ ሰንበት ት/ቤት የዋት ሳፕ ገጽ ነው

https://www.facebook.com/Fikureegzi4

√ ዌብሳይታችን www.fikureegzi.com √ የዩቲዩብ ገጻችንን

https://youtube.com/channel/UCXceln4wpQhIVS42O02kAWg

ለሀሳብ አስተያየት ይህንን ይጠቀሙ!! @FikureEgzi04. 11 followers

👏 6👍 4🥰 3
👏 12🥰 3🙏 2
የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ኘምልዓተ ጉባኤ መግለጫ እንደሚከተለው ይነበባል። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቅዱሳን አበው ሐዋርያት ትውፊት በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባውን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በርካታ አጀንዳዎችን በመቅረጽ ውይይት ሲያካሄድ ሰንብቷል፡፡ ምልዓተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት፣ ለመንፈሳዊ ዕድገትና ለምእመናን ደኅንነት ትኩረት በመስጠት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ በዚሁ መሠረት፡- 1.በቅድስት ቤተ ክርስቲያንና በሀገራችን መንግሥት መካከል ሊኖር ስለሚገባው መልካም የሥራ ግንኙነት በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሚመካከር የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ልዑክ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፤ 2.በመላው ሀገራችን በተፈጠሩ ግጭቶች፣ አለመግባባቶችና የሰላም ዕጦት በርካታ የሰው ሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት እንደቀጠለ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን በእጅጉ አሳዝኗል፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከግጭትና ከጥፋት ድርጊት ተቆጥበው የተፈጠረውን አለመግባባትና ግጭት በውይይትና በምክክር እንዲፈቱ እና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንኦት ጥሪውን ያቀርባል፤ 3.በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት ምክንያት ለፈረሱ የቤተ ክርስቲያናችን ይዞታዎች የከተማ አስተዳደሩ ምትክ ቦታ በመስጠትና ቤተ ክርስቲያናችን ወደ መልሶ ማልማት እንድትገባ ድጋፍ በማድረግ፤ በተለይም ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በፈረሰው የጽርሐ ምኒልክ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃ ምትክ በከተማ አስተዳደሩ ሙሉ ወጭ ተጨማሪ ምድር ቤትና የቦታ ስፋት ያለው B+G+4 ሕንፃ ገንብቶ ለማስረከብ ቃል በመግባትና የቤተ ክርስቲያናችን የበላይ ኃላፊ አባቶች በተገኙበት የመሠረት ድንጋይ እንዲጣል ማድርጋቸውን ቅዱስ ሲኖዶስ ከምስጋና ጋር የተቀበለው ሲሆን በተሰጠን ምትክ ቦታ ላይም የከተማው ፕላን በሚፈቅደው መሠረት የመልሶ ማልማት ሥራው እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 4.የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት አዋጅ መረዳት እንደሚቻለው ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ ሀገራዊ ችግሮችን በምክክርና በውይይት ለመፍታት የተቋቋመ መሆኑን ተረድተናል፡፡ ይሁን እንጅ ሀገረ መንግሥትን ከመመሥረት ጀምሮ በአስታራቂነትና በሰላም ግንባታ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ለሆነችው እናት ቤተ ክርስቲያን እስከአሁን ድረስ በይፋ የቀረበ የተሳትፎ ጥሪ ሳይኖር ኮሚሽኑ የተሳታፊ ልየታንና አጀንዳ መረጣ አጠናቆ ወደ ምክክር ትግበራ እየገባ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስን ቅር አሰኝቷል፡፡ በመሆኑም የቤተ ክርስቲያኒቱ ተሳትፎና አጀንዳ የማቅረብ መብቷ እንዲረጋገጥ ከኮሚሽኑ ጋር በመነጋገር ጉዳዩን ተከታትሎ ለፍጻሜ የሚያበቃ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡ 5.የብፁዓን አባቶች የዝውውርና የአህጉረ ስብከት ሥያሜን አስምልክቶ የቀረቡ ጥያቄዎችን ምልዐተ ጉበኤው ተመልክቶ ተገቢውን ውሳኔ አሳልፏል፤ 6.የሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በረቂቅ አዋጁ ሊሻሻሉ ይገባቸዋል ብሎ ያመነባቸውን የማሻሻያ ሐሳቦች በማዘጋጀት ለሚመለከተው መንግሥታዊ ተቋም እንዲላክና ረቂቅ አዋጁ ከመጽደቁ በፊት የተሰጡት የማሻሻያ ሐሳቦች በረቂቁ ስለመካተታቸው ክትትል የሚያደርግ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡ 7.በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ ተመሥርቶ አባታዊ ምክርና ተግሣጽ ማስተላለፍ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው መሆኑ ቢታወቅም በሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተፈጠሩ አለመግባባቶች የተከሰቱትን ወቅታዊ ችግሮች አስመልክቶ እየተላለፉ ያሉ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ መልእክቶችን ቅዱስ ሲኖዶስ የማይቀበላቸውና በጥብቅ የሚቃወማቸው መሆኑን እየገለጸ ወደፊት እንዲህ ዓይነት ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጸም ለማድረግ ይቻል ዘንድ ወጥ የሆነ የመግለጫ አሰጣጥና የትምህርተ ወንጌል ተልእኮ ሕገ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምልዐተ ጉበኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ 8.ግብረ ሰዶማዊነትና የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በሕገ ተፈጥሮም ሆነ በሰው ልጅ የሰብዓዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው፣ ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር መለኮታዊ ፈቃዱ በተገለጠባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ፈጽሞ የተከለከለ፣ በቀኖናተ ቤተ ክርስቲያን፣ በፍትሕ መንፈሳዊና በፍትሐ ብሔር ድንጋጌዎች፣ በሥነ ልቦና ደንቦች የተወገዘ፣ ሥነ አእምሮዊ ሚዛንን የሚያዛባ፣ ግለሰባዊ ማንነትን፣ ቤተሰባዊ ሕይወትን፣ ማኅበራዊ ትሥሥርን የሚጎዳ ተግባር በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ እያወገዘ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና የግብረ ሰዶማዊነትን ኃጢአት በተመለከተ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አቋም በሚገልጽ መልኩ ራሱን ችሎ ዓለም አቀፋዊ ይዘቱን ባገናዘበ ሁኔታ ዝርዝር መግለጫ እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ 9.በደቡብ የሀገራችን ክፍል የቤተ ክርስቲያኒቱን አብነት ትምህርት ከማስፋፋትና ከፍ ያለ መዐርግ ከመስጠት አንፃር የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት የዝጊቲ ደብረ ሰላም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን የአራቱ ጉባኤያት ማስመስከሪያ ትምህርት ቤት እንዲሆን በቀረበው ጥናት መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ ለምሥክር ጉባኤ ቤቱ ዕውቅና በመስጠት ወደ ትግበራ እንዲገባ ወስኗል፡፡ 10.ከሀገራችን ውጭ ባሉ አህጉረ ሰብከት መደበኛ አገልግሎት ለመስጠት የሚላኩ አገልጋዮች በክፍሉ ሊቀጳጳስ ሲጠየቅ በሙያ ብቃታቸው፣ በምግባራቸውና በመንፈሳዊነታቸው የተመሰከረላቸው አገልጋዮች ከሁሉም አህጉረ ስብከት በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አቅራቢነት በውድድር እየተለዩ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲላኩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 11.የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ የዐሥር ዓመት መሪ ዕቅድ በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲገባ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ በዚሁም መሠረት ለአፈጻጸሙ ያመች ዘንድ በባለሙያዎች ተዘጋጅቶ የቀረበውን መዋቅራዊ አደረጃጀት በማጽደቅ በሕገ ቤተ ክርስቲያኑና በቃለ ዓዋዲው ተካቶ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 12.በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተዘጋጅቶ የቀረበውን የ2017 ዓ.ም. ዓመታዊ በጀት በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ በአጠቃላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራ ላለፉት ተከታታይ ቀናት በመንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየትና ተገቢውን ውሳኔ በማስተላለፍ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት በጸሎት አጠናቅቋል፡፡ መሐሪና ሁሉን ቻይ የሆነ እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን፣ ፍቅሩንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ግንቦት ፳፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ኢትዮጵያ አዲስ አበባ
إظهار الكل...
👍 6👏 4 1
Photo unavailableShow in Telegram
👨‍🏫 ኑ በጋራ አንባቢ ትውልድ እንፍጠር 👨‍🏫 መጻሕፍትን የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር 📚📖 የአቡቀለምሲስ ቤተ መጻሕፍት የመጻሕፍት ክምችት ለማሳደግ 📚( አምስት መቶ) 500 📚 ከሕጻናት የተረት መጻሕፍት እስከ ትልልቆቹ መጻሕፍት ድረስ ይለግሱ 📚 እኔ ትውልድን በምግባር እና በሃይማኖት ለምትቀርጽ ሰንበት ት/ቤት አንድ መጻሕፍት እለግሳለሁ። 📗📇
إظهار الكل...
👍 7 3👏 2😢 2
Photo unavailableShow in Telegram
የመንፈሳዊ ትምህርት ለመማር አስበዋል! 📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖       የፍቁረ እግዚእ ሰንበት ት/ቤት የክረምት  ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት   አዘጋጅቶ ይጠብቆታል። 👉 ትምህርቱ የሚሰጥበት   🗓 ሰኞ እስከ ዓርብ 🕰 ከምሽት12: 00 እስከ 2:00 ሰዓት ድረስ 👉 📅  ትምህርቱ የሚጀምረው ሰኔ 17 ቀን 2016 ዓ.ም 📝 ምዝገባው: -  በሰንበት ት/ቤቱ ቤተ መጽሐፍት እና በሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከቀኑ 9:00 እስከ ምሽቱ  2:00 ሰዓት ቅዳሜና እሁድ ከጠዋቱ 3: 00 እስከ ምሽቱ 2:00 ሰዓት ወይም  🌍  ከስር ያለውን የዌብሳይታችንን  ሊንክ በመጫን ባሉበት ቦታ ሆነው  መመዝገብ ይችላሉ። https://fikureegzi.com/Free_Registration          ትምህርቱ የሚሰጠው በነጻ ነው!! "አንተ ግን በተማርክበት እና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር" 2ጢሞ 3÷14
إظهار الكل...
👍 9🥰 3👏 1