Harari Regional Health Bureau የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ
الذهاب إلى القناة على Telegram
This is official Telegram canal of Harari Regional Health Bureau. this page delivers News, Health related information and vacancy announcements on daily basis.
إظهار المزيد3 218
المشتركون
+224 ساعات
+107 أيام
+7530 أيام
أرشيف المشاركات
+5
በ2018 በጀት ዓመት የተመዘገቡ ተቋማዊ ስኬቶችን በማስቀጠል፣ የምግብ ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
(ሐረር፤ ነሐሴ 13ቀን 2018 ) — የሐረሪ ሕዝብ ክልላዊ መንግሥት ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎትና ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት፤ ከወረዳ የምግብና ጤና ነክ ተቋማት ተቆጣጣሪ አካላት ጋር በመሆን “ዛሬን በመቆጣጠር፤ ነገን እንጠብቅ!” በሚል መሪ ቃል ያካሄደውን የ2018 በጀት ዓመት የቁጥጥር ዘርፍ የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አጠናቋል።
መድረኩ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን፣ ያጋጠሙ ስትራቴጂካዊ ማነቆዎችን እና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ አቅጣጫዎችን በጥልቀት በመገምገም ረገድ ሚናው ከፍተኛ ነው።
የጤናና ጤና ነክ አገልግሎትና ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አህመድ ሱሌይማን እንደገለጹት፤ የግምገማ መድረኩ ዋና ዓላማ የላቀ አፈጻጸም በታየባቸው ስራዎች እውቅና በመስጠት ለቀጣይ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፃም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚሰራበት ነው ብለዋል።
አቶ አህመድ አክለውም፤ የጤናና ምግብ ጥራት ቁጥጥር ሥራ ተቋማዊ ጥረትን ብቻ ሳይሆን ሁለንተናዊ የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን የሚጠይቅ በመሆኑ ከማህበረሰቡ ጋር ጠንካራ ቅንጅት መፍጠር እንደሚገባ አሳስበዋል።
የእቅድ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ወ/ሪት ራኒያ መሐመድ በበኩላቸው፤ በክልል ደረጃ በምግብ፣ በጤና ግብዓቶችና ቁጥጥር በሚደረግባቸው ምርቶች ዙሪያ የታዩ ውጤቶች የሚበረታታ ነው ብለዋል።
ውስንነቶችን ለመሙላት ጠንካራ ተቋማዊ የቁጥጥር ሥርዓት በመዘርጋት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በቀጣይም ቢሮው አፈጻጸሞችን የመከታታል ስራዎችን አጠናክረው እንደሚሰራ ተናግሯል።
+8
የጤናው ዘርፍ ሀገር አቀፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በሀረሪ ክልል እየተሰጠ ይገኛል።
በአሚር ኑር ወረዳ ለአቅመ ደካማዎች ሙሉ የጤና ምርመራ አገልግሎት ቤት ለቤት ተሰጥቷል
የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢማን ዜይዳን እንደተናገሩት የጤናው ዘርፍ ሀገር አቀፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥን በማስመልከት በዛሬው እለት በአሚር ኑር እና አባድር ወረዳዎች ላይ ለአቅመ ደካማዎች ሳሚንቱን ሙሉ የህክምና ምርመራ እተሰጠ መሆኑን ተናግሯል ።
በተለይ ክልሉ ባለፉት ሶስት አመታት በተሰጠው የጤናው ዘርፍ ሀገር አቀፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ብዙ አቅመ ደካማዎችን ተጠቃሚ ያደረገ ነው ብለዋል።
በቀጣይ ቀናትም የሚሰጠው የጤና አገልግሎት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ምክትል ቢሮ ሀላፊዋ ጠቅሰዋል ።
+4
የግል ጤና ተቋማት የክረምት የጤናው ዘርፍ ሀገር አቀፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በማስመልከት ለክልሉ ጤና ቢሮ የመድሃኒት ድጋፍ አደረጉ።
የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን በክልሉ የሚገኙ የግሉ የጤናው ዘርፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በማስመልከት ላደረጉት ድጋፍ አመስግኗል።
የተደረገው የመድሃኒት ድጋፋም በክልሉ ለሚገኙ ጤና ተቋማት የሚከፋፋል መሆኑን በሪክብክቡ ወቅት ተገልጿል።
+5
ከሀረሪ ክልል ወባ በሽታ ወርሽኝን ለመከላከልና ብሎም ለማጥፋት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን ተናገሩ።
ቢሮው የክርምት ዝናብን ተከትሎ የሚከሰት የወባ ወረርሽን በሽታን ለመከላከል የተለያዩ የቅድመ መከላከል ስራዎችን እየሰራ መሆኑን አስታውቋል ።
የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን እንደተናገሩት የወባ በሽታ ወርሽኝን ለመከላከል እና ብሎም ለማጥፋት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎና ቅንጅት እንዲያደርግ አሳስበዋል ።
በክልሉ ኤረር ወረዳ የወባ በሽታ ወርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግሯል ።
በተለይ የማህበረሰብ ግንዛቤ ስራዎችን አጠናክሮ በመስራት የወባ ወሽታ ስርጭትን መቀነስ እንደሚገባ አሳስበዋል ።
የኤረር ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጫላ መሀመድ በበኩላቸው ሰሞኑን በወረዳው የተከሰተውን የወባ በሽታ ወረርሽኝ ለመከላከል ሁሉም የጤና ባለሞያዎች ርብርብ በማድረግ ጨምሮ የነበረው የወባ በሽታ እየቀነሰ መምጣቱን በመጥቀስ በአጭር ግዜ ውስጥ በሽታውን እንደሚቆጣጠሩ ገልጸዋል ።
+8
የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ በቡርቃ ቀበሌ ለአምስት መንታ ህፃናት እናትና ቤተሰቦቻቸው የሕክምናና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
ሐረር — የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን የተመራ የሕክምና ባለሙያዎች ቡድን በቡርቃ ቀበሌ ዑመርዲን መንደር በመገኘት ለአምስት መንታ ህፃናት እናት ለወይዘሮ በድሪያ አደም እና ለቤተሰቦቻቸው የተሟላ የጤና ክትትልና የአስፈላጊ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።
በጉብኝቱ ወቅት የሕክምና ቡድኑ የእናቲቱን የድህረ-ቀዶ ጥገና ማገገም ሁኔታ እና የህፃናቱን (ናኢፍ፣ አማር፣ ሙንዚር፣ አንሳር እና ናዚራ) የዕድገት ደረጃ በዝርዝር መገምገሙ ተገልጿል።
ከጤና ክትትሉ በተጨማሪ ቢሮው ለህፃናቱ የሚሆን ወተት (ፎርሙላ)፣ የህፃናት ዳይፐር እና የእናቶች ንፅህና መጠበቂያዎችን አበርክቷል። የቤተሰቡን የምግብ ዋስትና የሩዝ እና የምግብ ዘይት ድጋፍ ተደርጓል።
በተያያዘም ለቤተሰቡና ለአካባቢው ማህበረሰብ ስለ ጨቅላ ህፃናት አመጋገብ፣ ንፅህና አጠባበቅ እንዲሁም ተላላፊ በሽታዎችን ስለመከላከል የሚያስገነዝብ የምክር አገልግሎትና የጤና ትምህርት ተሰጥቷል።
የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ በገጠር ቀበሌዎች የሚገኙ እናቶችና ህፃናትን ጤና ይበልጥ ለማሻሻል የሚያደርገውን ተቋማዊ ድጋፍና መደበኛ የክትትል ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
+9
የሐረሪ ከልል ጤና ቢሮ አመራሮች እና ሰራተኞች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በማስመልከት በሰዓዳ ህፃናት ማሳደጊያ በመገኛት የቁሳቁስ ድጋፍና የጽዳት ዘመቻ አካሄዱ፡፡
የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን እንደተናገሩት የጤናው ዘርፍ ሀገር አቀፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ የጤና አገልግሎት ዘርፎች እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል ።
በተላይ የህፃናት ማሳደጊያ ላይ በመገኛት የቁሳቁስ ድጋፍ እንዲሁም የጽዳት ዘመቻ ማካሄድ አርአያ ሊሆን የሚችል ስራ ነው ብለዋል ።
የክልሉ ማህበረሰብም የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል ።
የቁሳቁስ ድጋፍና የጽዳት ዘመቻው ጎን ለጎን በማሳደጊያ ውስጥ ለሚገኙት ህጻናት የተለያዩ የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል ።
+9
የሐረሪ ከልል ጤና ቢሮ ሰራተኞች ደም ልገሳ ስነ ስርዓት አካሄዱ፡፡
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር
በማስመልከት በክልሉ ጤና ቢሮ ሰራተኞች የደም ልገሳ ስነ-ስርት አካሂደዋል፡፡
የክልሉ ጤና ቢሮ ሰራተኞች ደም በመለገስ የብዙ ሰዎች ህይወትን ለማዳን ምክንያት ከመሆን
በተጨማሪ ለጋሾች እና ለማህበረሰቡ በርካታ ጥቅሞችን ያስገኛል ብለዋል፡፡
በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰቱ የደም እጥረት ለመቀነስ ብሎም ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ህይወት ለመታደግ ማህበረሰቡ ደም የመለገስ ባህላቸውን ማሳደግ ይገባል።
የክልሉ ማህበረሰብም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር በማስመልከት ደም እነድግሱ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል።
+8
ለማህበረሰቡ የሚሰጠው የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ልጠናከር ይገባል፦ ዶ/ር አብዲ አሚን።
የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ማኔጅመንት አባላት በኤረር ወረዳ እየተሰጠ ያለውን የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝቷል።
የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን በክልሉ ኤረር ወረዳ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግሯል ።
በወረዳው የበልግ ዝናብን ተከትለው የወባ በሽታ ወረርሽኝ እየጨመረ መሆኑን የገለጹት ቢሮ ሀላፊው እንደ ወረዳ የወረርሽኝ መከላከል ቡድን ተቋቅሞ እስከ ጤና ኬላ ድረስ ወርደው በሽታውን የመከላከል ስራዎች ተጠናክሮ መሰራት እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በተለይ ከአምቡላንስ አገልግሎት አሰጣጥ ጋር የተያያዙ ውስንነቶችን ለመቅረፍ የወረዳው አመራሮች የክትትል ስራዎችን መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል ።
የኤረር ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጫላ መሀመድ በበኩላቸው በወረዳው እየጨመረ የመጣውን የወባ በሽታ ለመከላከል ቡድን በማቋቋም ከነገ ጀምሮ ወደ ስራ እንደሚገበ አስታውቀዋል ።
+3
የጤና ሚኒስቴር ከላስት ማይል ሄልዝ ጋር በጋራ 20 ሺህ የዐይን መነፅር ለሐረሪ ክልል ድጋፍ አደረገ፡፡
በድጋፍ የተሰጡ መነፅሮች በክልሉ የአይን ችግር ላለባቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሰጥ ነው።
ከላስት ማይል ሄልዝ ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶክተር ማህቶት ሌይኩን የአይን ችግር ላለባቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በነፃ የሚሰጡ 20ሺህ መነፅሮች ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
በቀጣይ ዙሮች ድገፋን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን ለተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነዋል።
በድጋፍ የተገኙ መነፅሮችም በክልሉ በተደረገ ምርመራ የአይን ቅርብ ርቀት እይታ ችግር ላለባቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡
በክልሉ ጤና ቢሮ የእናቶች ፣ህጻናት እና ጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ብዱን አስተባባሪ
አቶ ያሚና አብዲ በመጀመሪያ ዙር የመነጽር እደላውም በሰለጠኑ ጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያዎች ልየታ በማድረግ ድሬ ጠያራ ፣ሀኪምና፣ ኤረር እና ሶፊ ወረዳዎች መሰጠቱን ገልጸዋል።
በቀጣይ ዙሮች ሌሎች የቀሩ ወረዳዎች በጤና ኬላ እንዲሁም ጤና ጣቢናዎች ላይ እደላው እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
+7
የህፃናት ልብ ቀዶ ጥገና ህክምና አገልገሎት ለመስጠት
ቅድመ ዝግጅት ስራ ተከናወነ፦ ዶ/ር አብዲ አሚን።
በሐረሪ ክልል በሚሰጠው የህፃናት ልብ ቀዶ ጥገና ህክምና አገልገሎት 30 ለሚሆኑ ህሙማን አገልግሎት እንደሚሰጥ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።
በሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን በተፈጥሮና በተለያዩ አደጋዎች የተጎዱና ቀዶ ጥገና የሚያስፈልጋቸው ህፃናት ህክምና ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።
በተለይ ተወልደው የልብ ህመም ችግር ያለባቸው እና የህክምና ቀጠሮ ተሰጥቷቸው እየጠበቁ ለሚገኙ ህፃናት አገልግሎቱን ያገኛሉ ብለዋል።
የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በማስመልከት በክልሉ ህይወት ፋና ሆስፒታል የሚሰጠው ቀዶ ጥገና ህክምና ከታዝማ የውስጥ ደዌና የቀዶ ህክምና ልዩ ማዕከል በተውጣጡ ባለሞይዎች ጋር በጋራ እንደሆነም አስታውቋል ።
አገልግሎቱ ከዚህ ቀደም በክልሉ ያልተሰጠ እና ለመጀመሪያ ጊዜ ለክልሉ ማህበረሰብ መሰጠቱ ያለው ጠቀሜታ የጎላ ነው ብለዋል።
በቀጣይም መሰል አገልግሎቶች ለመስጠት እንደሚሰሩ አስገንዝበዋል።
እየተሰጠ ያለው የክረምት በጎ ጤና አገልግሎት አሰጣጥ በተለያዩ ጤና ዘርፍ እየተሰጠ በመሆኑ የክልሉ ማህበረሰብ በአገልግሎቱ መጠቀም እንዳለባቸው ቢሮ ሀላፊው ጥሪ አቅርበዋል ።
+9
በሐረሪ ክልል የችግኝ ተከላ ተካሄደ።
የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በማስመልከት የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ የችግኝ ተከላ አካሂዶል።
በችግኝ ተከላ መርሃግብሩ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊዎች ፣ የስራ ሃላፊዎች እና ሰራተኞች በነቂስ በመውጣት ችግኝ ተከላ አካሂደዋል።
"ተስፉ እንትከል" በሚል መሪ ቃል 800 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀንበር ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ ነው።
+9
በሐረሪ ክልል በጊዜያዊ ድንኳኖችና በሕዝብ በሚበዛባቸው ስፍራዎች ጭምር የሚሰጠው የነፃ ሕክምና አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ለሕብረተሰቡ የሚያቀርበውን ነፃ የሕክምና አገልግሎት በጤና ተቋማት ብቻ ሳይወሰን፣ በሕዝብ በሚበዛባቸው የገበያ ቦታዎችና በጊዜያዊ ድንኳኖች ጭምር ተዳራሽ በማድረግ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታወቀ።
የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን በነዚሁ በሕዝብ በሚበዛባቸው ስፍራዎችና በተለያዩ የማህበረሰብ ማዕከላት በተተከሉ የነፃ ሕክምና ድንኳኖች ተዘዋውረው አገልግሎቱን ጎብኝተዋል።
ኃላፊው በጉብኝታቸው ወቅት እንደገለጹት፣ አገልግሎቱን በጊዜያዊ ድንኳኖችና በተንቀሳቃሽ የሕክምና ቡድኖች አማካኝነት ወደ ሕብረተሰቡ መጠጋቱ፣ በተለይም ወደ ጤና ተቋማት ሄደው ለመታከም አቅሙና ጊዜው የሌላቸውን አቅመ-ደካሞችና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች በቅርበት ተጠቃሚ ለማድረግ አስችሏል።
በበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ የደም ግፊት፣ የስኳር፣ የዓይን ምርመራ፣ የሕፃናትና የእናቶች ጤና እንዲሁም የጠቅላላ ሕክምናና የምክር አገልግሎት በነፃ እየተሰጠ ይገኛል።
አገልግሎቱን በየአካባቢያቸው ያገኙ የክልሉ ነዋሪዎች፣ ሕክምናውን በቅርበትና ያለ ምንም ወጪ ማግኘታቸው ትልቅ እፎይታ እንደፈጠረላቸው ገልጸው ለጤና ቢሮውና ለበጎ ፈቃደኛ የሕክምና ባለሙያዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
+3
በክልሉ የሚገኙ የመንግስትና የግል ፋርማሲዎች ጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን መተግበሪያ እየተጠቀሙ መሆኑን የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።
የሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አብዲ አሚን እንደተናገሩት፣ በክልሉ የመድኃኒት ቁጥጥር እና የመድሃኒት አቅርቦት አሰራርን ለማሻሻል በዲጂታል የመድሃኒት መድሃኒት መመዝገብ፤ አቅርቦትን መቆጣጠር፤የመድሃኒት አያያዝ፤ግዜያቸዉ ያለፈባቸው እንዲሁም ለመግሃኒት ተጠቃሚ መድሃኒት እና ፈርማሲዎች አድራሻ እንድሀም የመድሃኒት ዋጋ አማራጮችን የሚያይበት መተገበሪያ አፕሊኬሽን ቢሮዉ መተግበር መጀመሩን ተናግረዋል ።
በዚህም መሰረት እስከ ዛሬድረስ በክልሉ የሚገኙ ፋርማሲዎች ጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን እንድተገብሩ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት 136 የመንግስት እና የግል ፋርማሲዎች ተመዝግበው ተግባራዊ ማድረጋቸውን ቢሮ ሀላፊው አሳውቀዋል ።
ከዚህም በተጨማሪ የቢሮ ሃላፊው ጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን ስርዓትን መተግበር የቁጥጥር ስርዓትን የሚያቃልል እና መድሀኒቶችን በቀላሉ ለመለየት እንዲሁም ግልፀኝነትን የሚጨምር መሆኑን ተጠቅሷል ።
በሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ጤናና ጤና ነክ ግብ/ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳሬክተር አቶ አህመድ ሱሌይማን በበኩላቸው ጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን ስርዓት ውስጥ ከ1600 በላይ የመድሀኒት አይነቶች ተመዝግቧል ብለዋል ።
በመሆም ማህበረሰቡ ጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን በቀላሉ ከቴሌ ብር ወይም ከplay store በማውረድ መድሀኒቶች ዬት ፋርማሲ እንደሚገኙ እና ዋጋውንም አወዳድረው መግዛት እንደሚገባቸው አሳስበዋል ።
