cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

ማኅቶት ማለት መብራት ነው ቶኔቶር ደግሞ የኢትዮጵያ የጥንት ስሟነው እናም ማኅቶተ ቶኔቶር ማለት የኢትዮጵያ መብራት ማለት ነው መብራቷ ደግሞ መካከሏን ገነት ዳሯን እሳት እያለች የምትጠብቃት የምትጸልይላት እምነቷ ቅድስት ተዋህዶ ጥንት የሌላት ጥንታዊት ዘመን የሌላት ዘመናዊት ናት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አስተምሮ ነው አስተያየት ካለዎት @mahtotetonetor2 @mahtotetonetor1

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
1 181
المشتركون
-124 ساعات
+67 أيام
+2130 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

#የትንሣኤው ሦስተኛ ቀን ቶማስ_ይባላል የትንሣኤ ሦስተኛው ዕለት ቶማስ ይባላል፡፡ ቶማስ ማለት ፀሐይ ማለት ሲሆን ፣ዲዲሞስ ማለት ደሞ መንታ ማለት ነው፡፡ ማመኑ በፀሐይ ፤መጠራጠሩ በመንታነት ይመሰላል፡፡ ቶማስ ሰዱቃዊ ነው ሰዱቃውያን ትንሣኤ ሙታን የለም ብለው ያምናሉ ቶማስም ሰዱቃዊ ስለሆነ ትንሣኤ ሙታንን የማይቀበል የማያምን ሰው ነበር፤ የጌታን ትንሣኤ ለመቀበል የተቸገረው አእምሮውን ገድሎት የነበረው ሰዱቃዊው ሀሳብ ስላልተለየው ነበር፡፡ ይሄ ብቻ ሳይሆን ጌታ አልዓዛርን ለማስነሣት ሐዋርያትን እንሂድ ሲላቸው "ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ለባልንጀሮቹ ለደቀ መዛሙርት። ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ እኛ ደግሞ እንሂድ አለ" ይላል ዮሐ 11፡16፡፡ የጌታችንን ከሞት መነሣት እርግጥ ሆኖ ሲያገኘው ግን የሞተው አእምሮው/ሀሳቡ ተነሥቷል ፤ "ጌታዬ አምላኬ" ብሎ ጠርቶ ሕያውነትን ተቀላቅሏል፡፡ "አንሥአኒ በትንሣኤከ፤ በትንሣኤህ አንሣኝ" እንዲል ቅዱስ ያሬድ ቶማስን በትንሣኤው አንሥቶታል፤ ስለዚህ የትንሣኤው 3ኛው ቀን ለቶማስ መታሰቢያ ሆኗል፡፡ ቶማስም ከ 3 ዓመት ትምህርት በኋላ ከጥርጥር ሞቱ ተነሥቷልና። ቶማስ ጠያቂ ነው፤ ያልገባውን ይጠይቃል፤ ማየት የፈለገውን ልየው ይላል፡፡ በዚህም ፍጥረታዊ ወይም ሳይንሳዊ ሰውን ይመስላል፤ ፍጥረታዊ ሰው ተነግሮት አያምንም፤ካልጨበጠ ካልዳሰሰ እውነትነቱን አይቀበልም ፦ " ለፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ነውና አይቀበለውም፤ በመንፈስም የሚመረመር ስለ ሆነ ሊያውቀው አይችልም።" እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ 1ኛ ቆሮ 2 : 14፡፡ ቶማስ የጌታችንን ድርጊቶች በጥርጣሬ ይመለከት የነበረ ሐዋርያ ነበር ፡፡ ለምሳሌ ጌታችን አልዓዛርን ለማስነሣት ሲሄድ ደስተኛ አለመሆኑን በሞት ስጋት ገልጾ ነበር፦ "ስለዚህ ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ለባልንጀሮቹ ለደቀ መዛሙርት። ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ እኛ ደግሞ እንሂድ አለ" በማለት እንደተጻፈ፡፡ ዮሐ 11 : 16፡፡ በሌላ ጊዜም ቶማስ መንገዱን የጠየቀው ለዚህ ነበር፤ ያ መንገድ ወዴትና የት የሚወስድ ነው? የሚል ጥያቄ በውስጡ ይመላለስ ስለ ነበረ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ እንደጻፈው፦ "ቶማስም። ጌታ ሆይ፥ ወደምትሄድበት አናውቅም፤ እንዴትስ መንገዱን እናውቃለን? አለው" ዮሐ 14 : 5፡፡ በዚህ ሁሉ ጥያቄውና ጥርጥሩ ግን ጌታችን አንድም ቀን ሰልችቶት ተቆጥቶት ወይም በጥርጣሬ አትከተለኝ ብሎት አያውቅም ፤ ድካማችንን የሚያውቅ የሚሸከምልን አምላክ ነውና፤ ዛሬም ምንም ያህል ኃጢአት ብንሠራ ተጸጽተን በንስሐ ከተከተልነው አትከተሉኝ አይለንም፤ ከየትኛውም ክህደት ከየትኛውም ሃይማኖት ብንመለስ ወደ እውነተኛው ሃይማኖት ከገባን በኀላ አልፈልጋችሁም፡ውጡልኝ አይልም፤ "ወደኔ የመጣውን ወደ ውጪ አላወጣውም "ብሎናልና፤ ዮሐ 13፡32፡፡ ጌታችን ከሞት ከተነሣ በኀላ ለሁሉም ሲገለጥ ለቶማስ ግን አንድ ሳምንት ሙሉ አልተገለጠለትም ነበር፤ ቶማስም ጌታን በአካል ያዩት ሐዋርያት ሲነግሩት፦ • የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ • ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ • እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም" ይላቸው ነበር። ዮሐ 20 : 25፡፡ ጌታችን ይህንን ያደረገበት ምክንያትም፦ 1. ቶማስ በውስጡ መንፈሳዊ ቅናት እንዲያድርበት፤ ሁሉም ስለ ትንሣኤው ሲናገር እየሰማ እንዲጓጓ ነው፤ ይህ መጎምጀት ወደ ፍጹም መንፈሳዊነት ይመራልና፤ እኛም ዛሬ ለመንፈሳዊ ነገር ስንጓጓና ስንቸኩል እግዚአብሔርን እናገኘዋለን፤ በውስጣቸው የሚቀጣጠለው ፍቅረ እግዚአብሔር እርሱን ራሱን ይጠራዋል፤ ቀድሞም ለሞት ያደረሰው ፍቅር ነውና፡፡ 2. ጌታችን የአንዲት ነፍስ ጉዳይ ጉዳዩ እንደሆነ ያጠይቃል፡፡ የተገለጠው ለቶማስ ሲል ነበር ለሱም ሲባልም አስቀድሞ በሌለበት የተገለጠበት ፦ • ዕለት • ሰዓት • ቦታ • በተዘጋ ደጅ መግባቱ • ሰላምታው (ሰላም ለሁላችሁ ይሁን) • ሁኔታው /መልኩ አልተቀየረም፡፡ ቶማስ ባለበት የተገለጠበትና ሳይኖር የተገለጠበት ልዩነት ቢኖረው በመጀመሪያ ቀንና በስምንተኛ ቀን መሆኑ ብቻ ነበር፡፡ ይህም የሚያሳየው ፦ • ለሰው ሁሉ ያለውን ክብር/ፍቅር/ግድ • ትንሣኤው እርግጥ መሆኑን • ፍጹም ቸርነቱን • መጀመሪያ ያዩትም መጨረሻ የሚያዩትም በአንድነት እንደሚወርሱት ያጠይቃል፡፡ የቶማስ የመጨረሻ እምነት፦ "ጌታዬ አምላኬም" ፤ዮሐ 20፡28፡፡ ይህ ቃል የመጨረሻው የእምነት ጥግ ቃል ነው፤ የምናምነው ይህን ነው ፤ የምንናገረው ይህን ነው፤ የምንሰብከው ይህንን ነው፤ ከዓለም የምንለየውም በዚህ ቃል ነው፡፡ ቶማስ ብዙ ቢጠይቅም፤ ቢጠራጠርም በመጨረሻ ግን "አምላኬ" ብሎ አመነ፤ ዛሬ "ኢየሱስን አምላክ " ብለው መጥራት የሚከብዳቸው ብዙዎች ናቸው፤ እኛ እንኳን የቶማስን ቃል የወንጌሉን ፍጥጥ ያለ እውነት ስንናገር ይጠሉናል፡፡ እግዚአብሔር ማስተዋሉን ያድላቸው!!! ቶማስ ጌትነቱን አምላክነቱን ያመነው በመዳሰስና በማየት ከሆነ እኛስ ሳናይ እንዴት እናምናለን እንዳንል ጌታችን " ኢየሱስም። ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው" በማለት ወሳኝ መልእክት አስቀምጦልናል፡፡ ዮሐ20 : 29፡፡ ወንጌላዊውም ታሪኩን ሲጠቀልለው፦ " ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል" በማለት ይህን አንብበን፤ ሰምተን ብቻ እንድናምን አስገንዝቦናል፡፡ ዮሐ 20 : 31፡፡ እኛም የቶማስን እጅ እጅ አድርገን ዳሰነዋል የሐዋርያትን ዓይን ዓይን አድርገን አይተነዋል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም "ክብሩን አየን.." እንዳለ አባ ሕርያቆስም " ከእርሱ ጋር በላን ጠጣን.." እንዳለ እኛም እንደ ቶማስ " ጌታችን አምላካችን" እንላለን!!!!! በዚህም እኛ "ብፁዓን ነን"!!! እንድናምነው የረዳን አምላካችን ይመስገን!!!! በበጎ ሥራም ደስ እንድናሰኘው ይርዳን!!! በረከተ ሐዋርያት ይደርብን!!! አሜን!!! መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው
إظهار الكل...
“ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤ አሰሮ ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፤ ሠላም እምይዕዜሰ፤ ይህን ፤ ፍስሐ ወሠላም፡፡” መልካም የትንሣኤ ክርስቶስ ሲነሳ በራሳችን ምኞትና የሥጋ ፈቃድ እኛ እንዳንቀበር እንጠንቀቅ ! ዲ/ን ኤርምያስ @mahtotetonetor2
إظهار الكل...
ከእጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም ለዚህ ግሩፕ አባላት። ቀጥታ ቃላት ሳንጨምር ያሉንን ይኸው ~እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ ።ገንዘብ ወደ ገዳሙ አካውንት የምታስገቡ ሁሉ እኛ እሱ የሚያውቃችሁን የእናንተን ስም በጸሎት ሰዓት ለማንሳት አንደክምም ምንም እንኳን ኃጢአተኞች ብንሆንም እግዚአብሔር ይሰማናል ብለን እናምናለን ።የጥቂት እህቶችና ወንድሞች ስም ብቻ ነው የተላከልን የገንዘቡን መጠን ስንመለከት ብዙ ሰዎች እየተረባረቡ ነው በዚህም ከልብ እናመሰግናለን እግዚአብሔር ያክብርልን ።
إظهار الكل...
የሕፃናት ሁሉ ተምሳሌት የስነ ምግባር ቀንድ ሕፃን ሐረገወይን እኛም የበኩላችንን እናድርግ 100,000 ብር እንድትሸለም እናድርግ ሕፃን ሐረገወይን ቀለሙ በ19:00ውስጥ 100,000,000 view
إظهار الكل...
በአል❌ በዓል✅ ትንሳኤ❌ ትንሣኤ✅
إظهار الكل...
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ እና ዮሐንስ ዘደማስቆ ሐዋርያው ጴጥሮስ ጌታ በዐረገ በዓመቱ (34 ዓ.ም.) ቅዱሱን እሳት በመቃብሩ ስፍራ ማየቱን ጽፈዋል። ይህ ተአምር አሁን እስካለንበት ዘመን የቀጠለ ሲሆን፣ ሁል ጊዜም በትንሣኤ በዓል ዋዜማ ቅዳሜ ቀን ይታያል። ስለዚህ የሚያስደንቅ ተአምር ብዙ የማያምኑ ሰዎች በራሳቸው መንገድ ለማጣራት ሞክረዋል። እስኪ ከእነዚህ ውስጥ አንዱን ታሪክ ላጫውታችሁ። በአንድ ወቅት እንዲህ ሆነ… ዕለቱ ቅዳሜ ጠዋት 4 ሰዓት የትንሣኤ ዋዜማ ነው። የእስራኤል አይሁድ ፖሊሶች እና የከተማዋ ከንቲባ  ይህ እሳት ይፈልቅበታል የተባለውን የጌታን መቃብር እውነትነት ማረጋገጥ ስለ ፈለጉ በውስጡ ለእሳቱ መነሣት ምክንያት የሚሆኑ ተቀጣጣይ ነገሮች ካሉ በሚል ለሁለት ሰዓታት ያህል ሦስት ጊዜ ጥብቅ ፍተሻ አደረጉ። ግን ምንም ሊያገኙ አልቻሉም። ቀጥሎም ሁለት መቃብሩን የሚጠብቁ ሙስሊሞችን በማምጣት ልክ የቀድሞዎቹ አይሁድ የጌታን መቃብር እንዳተሙ እነርሱም መቃብሩን ዘግተው በሰም እንዲያትሙት አደረጉ። ይህንም ተከትሎ በቦታው የነበሩ አረብ ክርስቲያኖች ቱርክ እስራኤልን በተቆጣጠረችበት በ13ኛው ክፍለ ዘመን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ በየትኛውም ቦታ ቢሆን እንዳይዘምሩ የተከለከሉትን ቆየት ያለ ዝማሬ በኅብረት ከፍ ባለ ድምፅ መዘመር ጀመሩ። መዝሙሩም:- “እኛ ክርስቲያኖች ነን። ለብዙ መቶ ክፍለ ዘመናትም ክርስቲያኖች ነበርን። እስከ ዘላለምም እንዲሁ እንሆናለን፣ አሜን!” የሚል ነበር። እኩለ ቀንም ሲሆን የግሪኩና የአርሜንያው ፓትርያርክ፣ የግብፁ ሜትሮፖሊታንት እንዲሁም  ቀሳውስት እና ዲያቆናት ወደ ታተመው የክርስቶስ መቃብር መጡ። ከብዙ ጸሎት እና ምስጋናም በኋላ የታተመው የክርስቶስ መቃብር እንዲከፈት አደረጉ። ፓትርያርኩም ሞጣህቱን ብቻ አስቀርተው ከላይ የለበሱትን ልብሰ ተክህኖ በማውለቅ በክርስቶስ የዕድሜ ቁጥር ልክ ሦስት 33 ያልበሩ ሻማዎችን ይዘው ጨለማ ወደ ነበረው መቃብር ገቡ። ምእመናኑም ከውጭ ሆነው በአንድ ድምፅ ኪርያላይሶን (አቤቱ ይቅር በለን) እያሉ በመዘመር ይጠባበቁ ጀመር። ወደ ቅዱሱ መቃብር ገብተው የነበሩትም የግሪኩ ፓትርያርክ ያን በሰው ያልተቀጣጠለ እና የክርሰ‍ቶስን የትንሣኤ ብርሃን የሚያበሥረውን አምላካዊ እሳት ይዘው ብቅ አሉ። ይህን ጊዜ ጎልጎታ በእልልታ ተሞላች የቤተ ክርስቲያኑም ደወል በሐሴት ይደወል ጀመር። ትንሣኤከ ለእለ አመነ ብርሃነከ ፈኑ ዲቤነ እንኳን አደረሰን!!! ዲያቆን አቤል ካሳሁን
إظهار الكل...
ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃኅ እምንዋም። ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን። ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ። (መዝ ፸፰፡፷፭/ ከውጭም ከሀገር ውስጥም በቀጥታ የደወላችሁ ቴክስትም ለእንኳን አደረሰህ መልእክታችሁ ባለመመለሴ ይቅርታ እየጠየቅሁ ለማኅቶተቶኔቶር አባላትና በዓለም ሁሉ ለምትገኙ አመሰግናለሁ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ !
إظهار الكل...