cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

الـــنـــســـاء ســلــفــيــة

قال الشيح صالح آل الشيح حفظه الله المرأة عليها واجب في الدعوة إلى الله تعلى @nisaouselefiya t.me/nisaouselefiya ( التوحيد مصدر لأمن الناس) «من مات وهو يدعو من دون الله ندا دجل النار»

إظهار المزيد
العراق202 587لم يتم تحديد اللغةالفئة غير محددة
مشاركات الإعلانات
175
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

◉ቁርአን ይዞ ኢማምን መከታተል ------------------------------------------ ➜ኢማሙን በተራዊህ ሰላት ሲያሰግድ በቁርአን መከታተል ፍርዱ ምንድን ነው ? 🔖ما حكم متابعة الامام في التراويح في المصحف? 📍◦ لا يجوز. ابداً عليك ان تنصت. لا تتابعه ابداً. إنما عليك أن تنصت للقراءة ولا تقرأ معه. لا تتابع معه في المصحف ولا تقرأ معه اثناء قراءته. كل ذلك مخالفٌ بل يعني يخشى ان لا تصح صلاتك. لانه يجب عليك الانصات وجوباً. يجب عليك ومتابعة الامام بالانصات◦ ▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▬ 🎙فضيلة الشيخ د.صالح السحيمي •┈┈••✾◁◉▷✾••┈┈• የቴሌግራም ቻናላችንን ይ🀄️ላ🀄️ሉ👇 📲🖇 t.me/sefinetunuh
إظهار الكل...
4_5810043273389080090.mp31.21 MB
اذا كانت لقمةٌ في فمك وأُذِّن للفجر فلا تبصقها بل يجوز لك اكل ما اخذته بيدك اما أن تاخذ مما في الارض فلا لقوله عليه الصلاة والسلام "إذا سمع احدكم النداءَ والاناء علي يده فلايضَعْه حتي يقضيَ منه حاجتَه" صحيح ابي داود
إظهار الكل...
ሱረቱል ከህፍ በአላማቺን ምርጥ ቃሪዖቺ ➊ ሰዑድ ሹረይም 👇 https://t.me/Rahatul_QeIb/228 ➋ አሊ ሀዘይፊይ 👇 https://t.me/Rahatul_QeIb/229 ➌ ሙሀመድ አዩብ 👇 https://t.me/Rahatul_QeIb/230 ➍ አደም አልረፊኢ 👇 https://t.me/Rahatul_QeIb/231 ➎ አሊ ጃቢር 👇 https://t.me/Rahatul_QeIb/232 ➏ ስዑድ ጋሙዲ 👇 https://t.me/Rahatul_QeIb/233 ➐ ለዐዩን ኩሺይ 👇 https://t.me/Rahatul_QeIb/234 ➑ አቡበከር ሻትሪይ 👇 https://t.me/Rahatul_QeIb/235 ➒ አብዱል አዚዝ አህመድ 👇 https://t.me/Rahatul_QeIb/236 ➓ አብዱረህመን ሱዳይስ https://t.me/Rahatul_QeIb/238
إظهار الكل...
Rahatulqelb ✔

﷽ ዛሬ ጁመዐ ነው ሱረቱል ካፍ የቻለ ይቅራ ያልቻለ ያድምጥ ራሀቱል ቀልብ 👇

https://t.me/Rahatul_QeIb

كان من دعاء موسى عليه السلام: «اللهم ليِّن قلبي بالتوبة، ولا تجعل قلبي قاسياً كالحجر». 📚الزهد لأحمد بن حنبل (٣٥٠)
إظهار الكل...
#ለእህቴ_አድርሱላት___! #ምርጫ_እንድህ_አይደለም። --------------------------------- አውቃለሁ ይከብዳል ያለ ትዳር ኑሮ፡ የህሌና ፀፀት የውስጥ እንጉርጉሮ፡ ቀን ባለፈ ቁጥር እድሜ ይጨምራል፡ ያውም በዚህ ዘመን ፊትናውም ያስፈራል፡ አወ ብቸኝነት እጂጉን ያስጠላል፡ ጊዜው ሲረዝምብሽ ሊመስልሽ ይችላል!! --------------//-------------------------- #ቢሆንም_ግን_እህት__!! የችግሩን ክብደት እኔ ብረዳሽም፡ በዚህ መጥፎ ተግባር አብሽሪ አልልሽም፡ ደግሞ ለአንችም ቢሆን አያስደስትሽም፡ ለሙስሊሟ ጀግና ይህ አይመጥንሽም፡ -------------------------------------------- ጆይን ብሎ ገብቶ በሊፍት ለመውጣት፡ የማይሆን አስቦ የያዙትን ማጣት፡ ሀፍረትሽን ጥለሽ በሚዲያ መምጣት፡ ተመከሪ እህቴ ይህ ለአንች ነው ቅጣት፡ ተቆጠቢ እባክሽ እህት ተመከሪ፡ ወንጀል አትሰብስቢ ተይ አሏህን ፍሪ!! --------------------------------------------- ዩቲዩብ ላይ ቀርበሽ ትዳር ስትጠይቂ፡ ውበትሽ እንድታይ ደፍረሽ ስትስቂ፡ ፈታኝ መጥፎ ነገር ፎቶ ስትለቂ፡ ወንድን ለመፈተን ተጋልጠሽ ስትዘልቂ፡ ወንጀሉ ከባድ ነው እህት ተጠንቀቂ!! --------------------------------------------- ባል ፍለጋ ብለሽ በሚዲያ አትውጭ፡ አሏህን ለምኝው በአደብ ተቀመጭ፡ ለኢኽዋን ለአህባሽ ልብሽን አትስጭ፡ ትዳር ቀልድ አይደለም ጀግናውን ምረጭ፡ ለኢኽዋን ብትነግሪው የትዳር ንድፍሽን፡ በውስጥ አይመክርሽም አያውቅም ልክሽን፡ ስልጣኔ መስሎት ያረክሳል ክብርሽን!! ---------------//----------------------- #ስለዚህ_እህቴ__!! ቂያማ እየቀረበ እየበዛ ፊትና፡ ሀቁ እየተተወ በዝቶ ፍልስፍና፡ መፍትሔው ተረስቶ ተውሒዲና ሱና፡ የትዳር ጣዕሙ ደስታው ተረሳና፡ ፋራነት ተደርጎ መፅናት እስልምና፡ መሀይሙ በዝቶ አዋቂ አንሷልና፡ ሀራም ግንኙነት ንቃት ሆኗልና፡ ይህ ደግሞ ለእህቴ አይመጥንምና፡ ታገሽ አሏህ አለሽ ፀልይ ለረበና፡ እውነተኛ ውበት ይሔ ነው ቁንጂና፡ አሏህ ይሰጥሻል የሀቅ ሰው ጀግና፡ ቁጥብ ሴት ሁኝ እንጂ አሞተ ቆፍጣና፡ ቀጥ ብለሽ ተጓዥ በኢስላም ጎዳና፡ #እንጂ_ምርጫ_እንድህ_አይደለም! ------------------------------------------ በተውሒድ በሱና በእውቀት የመጠቁ፡ በፀባይ በአደብ እጂጉን የላቁ፡ የሴትን ልጂ ክብር ጠንቅቀው ያወቁ፡ በመንሀጀ ሰለፍ በሀቅ የረቀቁ፡ ሚስትነትሽን አምነው የሚንከባከቡሽ፡ ሱናውን ጠብቀው በደሴታ እሚያገቡሽ፡ እንድህ አይነት ጀግና ጠንካሮች እያሉ፡ ኢኽዋንን ለማግባት ታስቢያለሽ አሉ!? ፖለቲካ ሰብኮ ከሱና እሚያርቅሽ!? ከጠማማወች ጋር ከሚያስተዋውቅሽ!? ለሰላማዊ ሰልፍ ሜዳ ከሚያዘልቅሽ!? ዘወትር ጧት ማታ ከሚጨቃጨቅሽ!? ለውስን ቀን እንጂ ይህ ላያዛልቅሽ!? ሽርክ ቢዲዐ እንጂ ተውሒድ ላይቀልብሽ፡ ተይው ከወድሁ ይሔ ሰው ይቅርብሽ። ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼ ሱሪ ከሚገትት አስመሳይ አልጫ፡ ከፖለቲካ ጋር ተጣብቆ እንደ ሙጫ፡ ከገባሽ በኋላ ከሚጨንቅሽ መውጫ፡ ልንገርሽ አሁኑ ይስተካከል ምርጫሽ፡ ለእውነተኛ ፍቅር ለዘላቂ ኑሮ፡ ሰለፍይ ማግባት ነው ሰለፍይ አፍቅሮ፡ ሱፍይ ኢኽዋን አህባሽ ያረጋል ደንቆሮ፡ #አወ_እንድህ_አይደለም.....!! እየተነዛነዝሽ ከመኖር ዘላለም፡ ውጫዊ ገፅታ ውበትና ቀለም፡ ጭራሹን በድፍረት በሚዲያው አለም፡ ተሳሳትሽ እህቴ ምርጫ እንድህ አይደለም፡ --------------------------------------------- ከኑረዲን አል አረቢ 2014 ➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻➻ https://t.me/nuredinal_arebi https://t.me/nuredinal_arebi
إظهار الكل...
شـبـاب السـلـــفــــيــــيــن

#ሰለፍያ_ቀጥተኛ_የሀቅ_መንገድ_ብሎም_አይነኬ_ፅኑ_ተራራ_ነው ለአስተያዬትና እርማት @Nuredin_al_arebi_Bot @Nuredin_al_arebi_Bot

◾️ሸህ ፈውዛን አላህ ይጠብቃቸውና እንዲህ አሉ። ➡️ ነጃ መውጣት (መዳን) የምትፈልግ ከሆነ እነዚህ ሶስት ነገሮች ላይ አደራ፦ ①) የአላህን ኪታብ "ቁርአን" አጥብቀህ ያዝ ②) ቅናቻውን "የመልእክተኛው መንገድ" ተከተል ③) ቢድአ "በዲን ላይ ጭማሬ" ተጠንቀቅ። 📚 شرح المنظومة الحائية (ص٥٦)
إظهار الكل...
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ ፨፨፨ ይህ ለኸይር ፈላጊወች ወደ ኸይር ሥራ ጥሪ ስለ ማድረግ ይሆናል፨፨፨ ከየት ነው ? ወደት ነው? መልካሙ ሥራስ ምንንድነው ትሉኝ ይሆናል። እንግድያውስ ብዙ ሳትደክሙ ኸይር ስራውም ሳይዘገይባችሁ ወደዛው ላመላክታችሁ ተከተሉኝ። ኸይር ስራው ምን ይሆን ላላችሁ የ አላህን ቤት አብረን እንገንባ ነው ። ቦታውስ የት ነው ? ለምትሉኝም መልሱ ባጭሩ እዝሁ የሰሜን ወሎዋ ውብ ከተማ፣ የበዳዮች አስከፊ ብትር ጠባሳውን ጥሎባት ያለፍችው ወልድያ ነው። እንደምታወቀው ለብዙ አመታት የወልድያ ዩንቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች እና ወልድያ ከተማ ሙስሊሞች ሲታገሉለት የቆየው እና በተለምዶ አውራጎዳና በር ተብለው በምጠራው ዩንቨርስቲው መውጫ ፊትለፊት በምገኘው እና በ1998 ለዩንቨርሲቲው ቀረበ፣ የንግድ ቦታ ነው በሚል ተልካሻ ምክንያቶች የአላህ ቤት መስጅድ የፈረሰበት ቦታ ላይ ዳግም ከብዙ አመታት እልህ አስጨራሽ ትግል በኋላ የ አላህ ፍቃድ ሆኖ የመስጅድ ግንባታ መጀመሩን እዛው የሚገኙ ዑስታዞች እና ወንድሞቻችን አጫውተውኝል ለዚሁ ግንባታ ማስጀመሪያ የዋለው ገንዘብ ከሰው የተገኘ ብድር እንደሆነና ነግረውኛል ፡፡ ሰለዚህም ሁላችንም የአቅማችንን ያህል አስተዋፆ በማድረግ እዳውን ከፍለን የመስጊዱን ግንባታ አጠናክረን ማስቀጠል እንዳለብን ጥሪያቸውን ለሁሉም ሙስልም ማህበረሰብ አስተላልፏል።.... በዚህ ኸይር ስራ ላይ መሳተፍ እንዴት እንችል ይሆን ብላቹ ለተጨነቃችሁም መፍትሄው ይሀውላቹ ብያለው 1. 0942218404 ሀስን ዳውድ 2. 0948879372 ጅማል ሙሀመድ 3. 0922604043 ዑስታዝ ሙ/ሷልህ ብትደውሉልን እና የነየታችሁትን በጥሬገንዘብ፣ ድንጋይ ፣ አሸዋ ፣ ቆርቆሮ፣ ሚስማር፣ አልያም ሲሚንቶ በመግዛት ካላቹበት ሆናችሁ ብትደውሉልን እና ብትሰጡን ተቀብለን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጁ መሆናችንን እየገለጵን ለዚህ መስጅድ ግንባታ ለምታድርጉልን እገዛ አላህ ምንዳውን በጀነት ይክፈላቹ እንላለን።። በዱንያ የወፍ ጎጆ የምታክል መስጂድ እንኳ የገነባ ሰው አላህ በጀነት ቤት ይገነባለታል! ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ሼር አድርጉ ፡፡ ☞ወልዲያ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመአ https://t.me/Daewa_selefya_beuniversity
إظهار الكل...
ፈዋዝ ☞ [ዳዕዋ ሰለፊያ በዩኒቨርሲቲ]

አላማቺን በሱና ላይ የታነፁ ሰኬታማ የሆኑ ተማሪዎችን መፈጠር ነው ! እንድሁም በሁሉም ዩኒቨርሲቲ የሙስሊሞቺን ጀመአ ለማጠናከር, እርስ በርስ ለማስተሳሰር, መረጃ ለመለዋወጥና ለመደጋገፍ አንዲያስቺለን የተከፈተ ቻናል ነው ፡፡ ለአስተያየት ☞ @Fewaz_muslimbot

📌በተሸሁድ ጊዜ መቼነው አመልካች ጣታችንን የምናነሳው? ―――― 📍ኢማሙ አን'ነወውይ አለህ ይዘንላቸውና ከፊል ባልደረቦቻችን አመለካች ጣቱን (إلا الله) የሚለው ንባብ ላይ ሲደረስ አመልልካች ጣቱን ያንሳ ይላሉ። ✔አል_አልላመቱ ሙሐመድ ቢን አሊ አደም አል_ወለውይ በተሸሁድ ጊዜ አመለካች ጣቱን (إلا الله) የሚለው ንባብ ላይ ሲደርስ ያንሳ የሚለው ንግግር የሄ ማስረጃ የለውም።ይልቁንስ ግልፅ የሆኑት ሀዲሶች የሚያሳዩት ሰውየው መጀመሪያ ለተሸሁድ ከተቀመጠበት ጊዜ ጀምሮ ተሸሁዱን እስከሚጨርስ ድረስ(እሲኪያሰላምት) አመልካች ጣቱን ማንሳት አለበት የሚል ነው።እውነታውም ይሄው ነው።አል_ባኽሩል ሙሒጢ አስሰጃጅ ፊ ሸርሒ ሶሒህ ሙስሊም ቢን ሐጃጅ(13/59) አቡ ዑበይዳ https://t.me/AbuOubeida
إظهار الكل...
Abu_Oubeida "channel"

من أحب أن لا ينقطع عمله بعد موته فلينشر العلم {ابن الجوذي رحمه الله /التذكرة(٥٥)

የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን መቅራት ይፈቀድላታልን? ~ ~ በመጀመሪያ “ይፈቀዳል” ወይስ “አይፈቀድም” በሚለው ላይ የዑለማዎች ልዩነት እንዳለ ይታወቅ፡፡ እንዲያውም ብዙሃን ዑለሞች እንደማይፈቀድ ነው የሚገልፁት፡፡ የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን መቅራት አትችልም ያሉ ምሁራን ሁለት መነሻዎች አሏቸው፡፡ እነሱም፡- አንዱ፡- “የወር አበባ ላይ ያለች ሴትና ጀናብተኛ ከቁርኣን ምንም አይቀሩም” የሚለው ሐዲሥ ሲሆን ሁለተኛው፡- የጀናብተኛን ሁኔታ ቂያስ በማድረግ ነው፡፡ “ሁለቱም ትጥበት ወጅቦባቸዋል፤ ጀናብተኛ መቅራት ካልተፈቀደለት የወር አበባ ላይ ያለችዋም አይፈቀድላትም” የሚል ንፃሬ ነው፡፡ እነዚህ ሁለት መነሻዎች ጤነኛ ናቸው ወይ? ሌሎችስ ዑለማዎች በዚህ ላይ ምን ይላሉ? ይህ አቋም ሚዛን የሚደፋ እንዳልሆነ በመግለፅ “የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን እንዳትቀራ የሚከለክላት የለም” የሚሉ ዑለማዎች ቁጥር አንድና ሁለት አይደለም፡፡ “አይፈቀድም” በሚሉ ዐሊሞች የቀረቡት ማስረጃዎችንም ጥንካሬ የሚጎድላቸው እንደሆኑ ይገልፃሉ፡፡ እነዚህ ዐሊሞች በዚህ ረገድ ከሚያነሷቸው ነጥቦች ውስጥ ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡- 1ኛ፡- ከልካዮች ያቀረቡት የሐዲሥ ማስረጃ ደካማ ነው፡፡ በደካማ ሐዲሥ ተንተርሶ በትክክለኛ ማስረጃ ያልተከለከለን ዒባዳ መከልከል አይቻልም፡፡ ሐዲሡን፡- * ኢማሙ አሕመድ፡- “ውድቅ ነው” ብለውታል፡፡ [ተህዚቡ ተህዚብ፡ 1/283] * ኢማሙል ቡኻሪ፡- ደካማነቱን ገልፀዋል፡፡ * ኢብኑ ተይሚያ፡- ሐዲሡን “በሐዲሥ አዋቂዎች ስምምነት ደካማ ነው” ብለዋል፡፡ [አልመጅሙዕ፡ 21/460] * ኢብኑል ቀይም፡- “በሐዲሥ አዋቂዎች ስምምነት ድክመት ያለበት ሐዲሥ ነው” ብለዋል፡፡ [ኢዕላሙል ሙወቂዒን፡ 3/25] * ኢብኑ ሐጀር፡- “በሁሉም መንገዶቹ ደካማ ነው” ብለዋል፡፡ [ፈትሑል ባሪ፡ 1/323-324] * አልባኒ፡- በብዙ ኪታቦቻቸው ሐዲሡ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ለምሳሌ፡- [ዶዒፉ ሱነን ቲርሚዚ፡ ቁ. 98] * ኢትዮጵያዊው ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ዐሊ ኣደምም በዚህ ርእስ ላይ የሚጠቀሱት ሐዲሦች ለማስረጃነት የሚበጁ አይደሉም ብለዋል፡፡ [ዘኺራ፡ 4/570] ኢብኑ ባዝ፣ ኢብኑ ዑሠይሚንና ሌሎችም በርካታ ዐሊሞች በተመሳሳይ የሐዲሡን ደካማነት ገልፀዋል፡፡ 2ኛ፡- ከልካይ ማስረጃ እስካልቀረበ ድረስ በጉዳዩ ላይ መሰረቱ ፍቁድነት ነው፡፡ የወር አበባ ላይ ያለች ሴት በዚህ ረገድ ከሌሎች ሙስሊሞች የተለየ ብይን የላትም፡፡ እሷን ከሌሎች ለይቶ ከቁርኣን የሚከለክል ሰው ግልፅ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ እንደሚታወቀው የሴቶች የወር አበባ ማየት ከነብዩ ﷺ ዘመን በኋላ የመጣ አዲስ ክስተት ሳይሆን ጥንትም የነበረ ነው፡፡ ሆኖም ግን በዚያን ሰዓት ቁርኣን እንዳይቀሩ አልከለከሏቸውም፡፡ “እንዳልተከለከሉ ምን አሳወቀን?” ከተባለ ልክ የወር አበባ ላይ ሲሆን እንዳይፆሙና እንዳይሰግዱ የሚከለክሉ ትክክለኛ ሐዲሦች እንደደረሱን ቁርኣን እንዳይቀሩ ቢከለከሉ ኖሮም በማያሻማ መልኩ ማስረጃ ይደርሰን ነበር ማለት ይቻላል፡፡ 3ኛ፡- አላህ ቁርኣንን በመቅራት አዟል፡፡ ለሚቀራውም ሰው ትልቅ ሽልማትን ሊሸልም ቃል ገብቷል፡፡ ያለ ተጨባጭ ማስረጃ የወር አበባ ላይ ያሉ ሴቶችን ከዚህ ትልቅ የዒባዳ መስክ መከልከል ልክ አይደለም የሚለው ሌላኛው ይህን ሀሳብ የመረጡ ምሁራን መከራከሪያ ነጥብ ነው፡፡ 4ኛ፡- የወር አበባ ላይ ያለችን ሴት ከጀናብተኛ ጋር ማመሳሰልም ልክ አይደለም፡፡ ጀናባ ያለበት ሰው ምርጫው በእጁ ነው፡፡ ከፈለገ ታጥቦ መቅራት ይችላል፡፡ የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ግን ደሙ ሲቆም እንጂ ስለፈለገች አትታጠብም፡፡ በዚያ ላይ ከጀናባ በተለየ የወር አበባ ቆይታ ቀናትን የሚፈጅ ነው፡፡ ስለዚህ ከጀናባ ጋር ማመሳሰሉ ጤነኛ ንፅፅር አይደለም፡፡ የወሊድ ደም ሲሆን ደግሞ ቆይታው የበለጠ ይራዘማል፡፡ ኢብኑል ቀይም “የወር አበባ ላይ ያለች ሴትና ጀናብተኛ ከቁርኣን ምንም አይቀሩም” የሚለው ሐዲሥ ለማስረጃነት የማይበቃ ደካማ እንደሆነ በሰፊው ከተነተኑ በኋላ እንዲህ ይላሉ፡- “ሐዲሡ ሶሒሕ ካልሆነ ከልካዮች ዘንድ በጀናብተኛ ከማነፃፀር ውጭ ሌላ ማስረጃ አይቀራቸውም፡፡ በሷና በጀናብተኛ መካከል ያለው ትክክለኛ ልዩነት ሁለቱን አንድ አድርጎ ለመበየን የሚከለክል ነው፡፡ ይህም በብዙ መልኩ ነው፡፡ አንዱ ጀናብተኛ በፈለገ ጊዜ በውሃም ሆነ በአፈር መጥራት (መጧሀራት) ይችላል፡፡ ስለዚህ ከነጀናባው የሚቀራበት ምክንያት የለውም፡፡ የወር አበባ ላይ ያለችው ግን ከዚህ የተለየ ነው፡፡” ሌሎችም መለያዎችን ዘርዝረዋል፡፡ ከፈለጉ ሙሉውን ይመልከቱት፡፡ [ኢዕላሙል ሙወቂዒን፡ 3/25] 5፡- የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን እንዳትቀራ ማለት በየወሩ ለተወሰኑ ቀናት ቁርኣንን እንዳትማር፣ እንዳታስተምር፣ በመቅራት አጅር እንዳታገኝ መከልከል ነው፡፡ በዚያ ላይ ሒፍዝ ላይ ከሆነች ለመርሳት ልትጋለጥ ትችላለች፡፡ በመጨረሻም “ለመሆኑ የወር አበባ ላይ ያለች ሴት ቁርኣን መቅራት ይፈቀድላታል ያሉ ዑለማዎች እነማን ናቸው?” የሚል ጥያቄ ከተነሳ የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል፡- ★ የማሊኪያ መዝሀብ መቅራት ትችላለች የሚል ነው፡፡ [ዘኺራ ሊል ቀራ፡ 1/379] ★ የዟሂሪያም አቋም ይሄው ነው፡፡ [አልሙሐላ፡ 1/94] ★ የአሕመድም አንድ ዘገባ ነው፡፡ [አልኢንሷፍ ሊልመርዳዊ፡ 1/249] [አልኢኽቲያራቱል ፊቅሂያ ሊብኒ ተይሚያ፡ 27] ★ ከኢማሙ ሻፊዒይ በዚህ ላይ የሚፈቅድና የሚከለክል ሁለት የተለያዩ እይታዎች የተላለፉ ሲሆን አንዳንዶች የሚፈቅደው የቀድሞ አቋማቸው ነው ብለዋል፡፡ ★ የኢብኑ ጀሪር ምርጫም መቅራት ትችላለች የሚለው ነው፡፡ [ሸርሑ ሶሒሕ አልቡኻሪ ሊብኒ በጧል፡ 1/423-424] ቡኻሪ፣ ኢብኑል ሙንዚርና ሸውካኒም ይህንኑ መርጠዋል፡፡ የኢብኑ ተይሚያና የኢብኑል ቀይም አቋም ይሄው እንደሆነም አሳልፌያለሁ፡፡ ከዘመናችን ታላላቅ ዑለማዎች ውስጥ የጥቂቱን ንግግር ላቅርብ፡- ★ ኢብኑ ባዝ፡- “የወር አበባ ላይ ላለች ሴት ቁርኣን መቅራት ይፈቀድላታል፡፡ ከዚህ የሚከለክል ግልፅ ማስረጃ ስለሌለ፡፡ ነገር ግን ሙሥሐፍ (ቁርኣን) ሳትነካ ነው፡፡ ‘የወር አበባ ላይ ያለች ሴትና ጀናብተኛ ከቁርኣን ምንም አይቀሩም’ የሚለው ሐዲሥ ደካማ ነው” ብለዋል። [መጅሙዑ ፈታዋ፡ 16/127] ★ ኢብኑ ዑሠይሚን፡- “የወር አበባ ላይ ላለች ሴት ሐጃ ሲኖር ካልሆነ በስተቀር በአንደበቷ ባትቀራ #በላጭ ነው፡፡ ለምሳሌ አስተማሪ ሆና ተማሪዎችን የምታቀራ ከሆነች ወይም በፈተና ጊዜ ተማሪዋ ለፈተናዋ መቅራት ካስፈለጋትና መሰል ጉዳዮች” ብለዋል። [መጅሙዑ ፈታዋ ወረሳኢል ኢብን ዑሠይሚን፡ 11/234] ልብ በሉ! ከውዝግብ ለመራቅ ያክል የሰጡት ምክር እንጂ መከልከላቸው አይደለም፡፡ “ባትቀራ #በላጭ ነው” አሉ እንጂ “መቅራቷ ሐራም ነው” አላሉም፡፡ ★ የሳዑዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ ዑለማዎች፡- “የወር አበባና የወሊድ ደም ላይ ያለች ሴት ሙስሐፍ ሳትነካ ቁርኣን መቅራቷን በተመለከተ ከሁለቱ የዑለማዎች አቋም ትክክለኛው ችግር የለበትም የሚለው ነው፡፡ ምክንያቱም ይህንን የሚከለክል በተጨባጭ አልተገኘምና” ብለዋል፡፡ [ፈታዋ ለጅነቲ ዳኢማህ፡ ቁ. 3713] ፈትዋዉን የሰጡት ኢብኑ ባዝ፣ ኢብኑ ቀዑድና ዐብዱረዛቅ ዐፊፊ ናቸው፡፡
إظهار الكل...
★ ሸይኽ ዐብዱል ሙሕሲን አልዐባድ፡- “የወር አበባ ላይ ያለችን ሴት ከሒፍዟ ቁርኣን እንዳትቀራ የሚከለከል ማስረጃ አናውቅም” ብለዋል፡፡ [ሸርሑ ሱነን አቢ ዳውድ] ★ ኢትዮጵያዊው ዓሊም ሸይኽ ሙሐመድ ዐሊ ኣደምም እንዲሁ መቅራት እንደምትችል አስፍረዋል፡፡ [ዘኺራ፡ 4/570-571] ★ አልባኒና ፈርኩስም ይህንኑ መቅራት ትችላለች የሚለውን ሀሳብ ከመረጡ ዐሊሞች ውስጥ ናቸው፡፡ ማሳሰቢያ፡- እስካሁን የተወራው ቁርኣንን በእጅ ሳይነኩ በቃል መቅራትን እንጂ ሙስሐፍ መንካትን የሚመለከት አይደለም፡፡ ሆኖም ግን በጓንት ወይም ጨርቅ በመያዝ ወይም እንደ ሞባይል ካሉ መሳሪያዎች ላይ የሚገኘውን የቁርኣን አፕሊኬሽን ተጠቅሞ መቅራት እንደሚቻል በርካታ የዘመናችን ዑለማዎች ገልፀዋል፡፡ ወላሁ አዕለም። (ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 19/2010) https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.