ar
Feedback
ኬልቅያስ

ኬልቅያስ

الذهاب إلى القناة على Telegram

ኬልቅያስ የቴሌ ግራም ቻናል ኦርቶዶክሳዊ የነፍስ ማዕዶችን የሕይወት ቃል ወንጌለ መንግሥት የምስል ( vidio ) ትምህርቶች ፣ ያሬዳዊ መዝሙራትን ፣ የቅዱሳን ዜና ሕይወት ፣ ወቅታዊ የቤተክርስቲያን መረጃዎች፣ የአብያተ ክርስቲያናት እና የገዳማት ታሪክ ፣ የአባቶች ምክር ፣ የጠቢባን የአባቶች አባባል ፣ መንፈሳዊ ጥቅሶች እና ኪነ - ጥበባዊ ልዩ ልዩ አውዶች የሚቀርብበት ነው።

إظهار المزيد
404
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
ሲከተለው በድንገት ያ ሰው ቆመ። አሌክሳንደር ወደ ፊቱ አብርቶ ሲያረጋግጥ መቆሙን አወቀ። እርሱም እርምጃውን ገታ ፈርቶ ቆመ። ተጠራጠረ። ፊቱን ሳያዞር የቆመው ሰው አሌክሳንደር ብርሀኑን በቅርበት ላይ እያበራበት ወደ ኋላው ዞረ። መካከላቸው የነበረው ርቀት በጣም ቅርብ ስለነበረ ያ ሰው እንደዞረ አሌክሳንደር ማንነቱን በቀላሉ ለየው። ሲከተለው የነበረው በዚሁ ደን ውስጥ በሌሊት ብቻውን አጊኝቶት ክፉኛ ደብድቦት ሞቷል ብሎ ትቶት የሄደው ባሪያው ነበረ። እርሱ መሆኑን ሲያውቅ ያለ ፍርሀት ወደ ፊት ተራመደ። እንደ በጎ አጋጣሚ ቆጥሮ መልካም አጋጣሚውን መጠቀም ወደደ። ለብዙ ግዜያት ባሪያውን አጊኝቶ ሊያወራው ቢፈልግም ፍጹም ሊያገኘው ሳይችል ቀርቷል። ዛሬ ግን መንገድ አገናኛቸውና ሊያወራው ተደብቆ ደወል ወደሰማበት የአምልኮ ስፍራ የሚገሰግሰውን ሰው ከቆመበት እንዳለ ወደርሱ አቀና። ባሪያው ወደርሱ እየመጣ ያለውን ሰው ማንነት ባያውቅም ቆሞ ጠበቀው። አሌክሳንደር አጠገቡ ደርሶ ለሰላምታ እጁን ሲዘረጋ ማንነቱን በትክክል አወቀውና እርሱም መዳፉን ጨበጠው። አሌክሳንደር ለቀደመ ጥፋቱ ይቅርታ ሊጠይቅና ከየት እየመጣ መሆኑን ለመጠየቅ ጊዜ ሳያጠፋ በእንግሊዘኛ ሰላም ሲለው ባሪያው ለአክብሮት አጎንብሶ ምላሽ ሳይሰጥ ሰላምታውን ተቀበለ። አሌክሳንደር "I'm glad I found you today by chance after searching hard. I need two things from you. 1. Because of the wrong I did to you in the past 2. If I knew where you are coming from now?" አለው። ባሪያው ብዙ እንዳያደክመው " ወንድሜ ብዙ አትድከም። እኔ ጽድቅም እውቀትም የሌለኝ ሰው ነኝ። ምን እንዳልክ አላወኩም። እንግሊዘኛ አልተማርኩም። ጎዳና ላይ አደኩ ሌባ ሆንኩ እስር ቤት እያልኩ አሁን አዚህ ነኝ" አለው። " what did you say?" አለው አሌክሳንደር። " ኤውልህ ወንድሜ በከንቱ ጊዜ አናጠፋም ቸር ይግጠምህ" ብሎ ባሪያው ጥሎት ሄደ። የኪዳን ጸሎት ተጠናቆ ቅዳሴ ከመገባቱ በፊት ካህኑ በመስቀል ህዝቡን ሲባርኩ የመሪጌታ ባለቤት በቆሙበት ግድግዳውን ደገፍ ብለው አሁን ቤተክርስቲያን ቆመው አመስጋኝ አወዳሽ አስቀዳሽ ሆነው አሁን ካሉበት ከመገኘታቸው ፊት የሆነውን የኋሊት በሀሳብ መቃኘት ጀመሩ። ከደኑ ውስጥ እንዳበደ ሰው ልጃቸው ጥሏቸው ሲሄድ እየተጣደፉ እየተጣሩ እየተማጸኑት ከምንም ሳይቆጥራቸው ወደ ቤት ደርሶ ነጠላ ወስዶ ወደ ቤተክርስቲያን ሲያቀና እርሳቸውም ማመን አቅቷቸው እንደወትሮው የማርያም እለት እንደሚያደርጉት ነጭ ሀበሻ ሀገራዊ ልብሳቸውን ጥበብ ሳይለብሱ ነጠላቸውን ከትከሻቸው ጣል አድርገው ተከትለውት እርሱ በወንዶች መግቢያ ተሳልሞ ሲገባ አረጋግጠው ነጠላቸውን አጣፍተው ለብሰው እርሳቸውም በሴቶች መሳለሚያ ገብተው እንደተጨነቁ አሁን ወጣ አሁን ወጣ እያሉ ሲጨነቁ ኪዳን አለቀ። ኪዳን ጸሎቱን ሲያደርሱ የቆዩት መሪጌታም ሕዝቡን እየባረኩ ነው። በወንዶች ጨርሰው በሴቶች በኩል ሲመጡ ሁሉም ተሳልሞ ሲፈጸም ተባርከው በጆሮአቸው ተጠግተው "መሪጌታ ስሙር በወንዶች በኩል አይተውታል አለንዴ?" አሏቸው። " አላየውትም!" አሏቸው። መሪጌታ አገልግሎት ላይ የሁል ጊዜ ባሕሪያቸው ነው ማንንም አያዩም። የስሙር እናት ደንግጠው ሲወጡ መሪጌታ ወደ መቅደስ ወደ አገልግሎታቸው ገቡ። የስሙር እናት በወንዶች መሳለሚያ ሰው ጠብቀው መልክት ሊልኩ ወደው ቢጠብቁ ከንድ ወጣት ልጅ ከውስጥ ሲወጣ " ናስቲ ልጄ! አንድ ስሙር የሚባል ልጅ ብለህ ውስጥ ትጠይቅልኛለህ?" አሉት ልጁን አላወቁትም። " ኧረ ችግር የለውም እኔ ራሴ ስለማውቀው ጠራሎታለው አጠገቡ ነበርኩ" ሲላቸው። በረጅሙ ተንፍሰው " ስሙርን ታውቀዋለህ? እርግጠኛ ነህ?" ሲሉት " አዎ በደንብ የመሪጌታ ተማሪ ነበርኩ" አለ ወጣቱ። " በቃ ውስጥ ከሆነ ተወው ተባረክ" ብለው ወደ ውስጥ ተመለሱ። ቅዳሴ ተጠናቆ ቀድመው ወተው ስሙርን ጠብቀው አብረው ወደ ቤት ሲገቡ አሌክሳንደር እቤት ተኝቷል። ኋላ ቁርስ በልተው ቆይተው መሪጌታ መጡ። ሌሊት የተፈጠረውን ሁሉ ባለቤታቸው ሲነግሯቸው ሰምተው ዝም አሏቸው። ስ

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠 ከክፍል 170 የቀጠለ 💠💢 ለሁሉም ሁለታችሁም ወደ ቤት ተመለሱ። እኔ ለጥያቄዬ መልስ ሳላገኝ ወደ ኋላ አልመለስም እርምጃዬ ወደ ሙሲቾ ነው" ሲላቸው እናቱ " ምንድነው ጥያቄህ?" አሉት። እንደምትመልሺልኝ ቃል ትገቢያለሽ?" አላቸው። እናቱ ምንም ይሁን ሊመልሱለት " አዎ ቃል ገብቻለው ጠይቀኝ። አንተም እንደምትመለስ ቃል ግባ" ብለውት ተስማምተው ጥያቄውን ጠየቀ " አባዬ በዚህ ሌሊት የሄደው ወደ ሙሲቾ ነው? አይደለም? እንዳትዋሺኝ ቃል ገብተሻል" ሲላቸው የሚሉት ጠፋቸው። መሪጌታ ቃል ያስገቧቸው ትዝ አላቸው። አልነግርም እንዳይሉም ቃል ገብተዋል። ግራ ገባቸው። ቆመው እንዳሉ ከፊትለፊታቸው አንዳች በሰው ቁመት የሚገመት ቅርጽ ያለው ብርሃን ሲያዩ ፈዘው መመልከት ጀመሩ። 💢💠🌿 ክፍል 172 🌿💠💢 የሶስቱም እይታቸው በዚያ ጨለማ መካከል ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ የሆነ ተአምር መመልከት ሆነ። ምንም ማለት ምንም መናገር አልቻሉም። ብቻ ዓይኖቻቸውም ሀሳባቸውም ሁሉ ወደ ሚያዩት ሆነ። የሚመለከቱት ይህ ተአምር እየሆነ የነበረው በነርሱ የቅርብ ርቀት ላይ ሲሆን እያዩት ደኑ መካከል የወረደው ብርሃን ከርቀት ነጸብራቁ ብርሃኑ እየተዋጠ እየደበዘዘ መጣና ከእይታቸው ተሰወረ። ስሙር የሰፈነውን ዝምታ በጥያቄ ሰበረው " እንዴት ያለ አካባቢ ነው? ምን አይነት መንደር ነው?" እንደ ጥያቄም እንደ አድንቆትም። እውነትም አዋሽ ቆላቲ ከዚህ በቀር የሚገልጸው ስለሌለ እንጂ ብዙ ቢል ይወድ ነበረ። ምክንያቱም ስሙር በዚህ አካባቢ የሚያያቸው ብዙ ተፈጥሮአዊ ነገሮች ላስተዋላቸው ምሥጢር ያዘሉ ተአምራውያን ናቸው። አስቀድሞ ኢሄን አይቷል። ሰንሰለታማው ተራራ በየእለቱ ልዩ ውበት ባለው ጉም ሲሸፈን። አዎ ስሙር በዚያ ተመልክቷል የአዋሽ ተራሮችና አካባቢው በቀን ዝናብ ሳይኖር በበጋ አካባቢው በቀስተ ደመና ሲከበብ። ስሙር ጎበዝ ሰአሊ የሳለው እንጂ በእውን በዓይኑ እያየ መሆኑን ማመን እስኪያቅተው ጥቅጥቅ ያለው ደን በፀሐይ ተሸፍኖ ግማሹ በደን የተሸፈነው ተራራ ጥላ ሲያጠላበት አይቷል። እንደመጣ አካባቢ የሚያየው ሁሉ ይደንቀው ስለነበረ አንድ ቀን በደኑ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ በጅ ስልኩ ፎቶ ሲያነሳ ዛፎቹ ላይ በስልኩ ካሜራ ሲያነሳ ያያቸው ምሥጢራዊ ምልከታዎች ሁሉ ትዝ አሉት። በተለይም ፎቶ ሲያነሳ ሰባቱን ሕብረ ቀለም በቀስተ ደመና አምሳል አንድ የተወሳሰበበት ስእል ነገር ላይ ከቦ ያየበትን ሁሌ ልቡ ያደንቃል መላልሶም ስዕሉን ያየው ነበረ። አንዳንዴ የኪዳነ ምሕረት ስዕልም መስሎት አትኩሮ ያየዋል። ከዚያ የሚበልጠው ደግሞ ዛሬ ሆነ። እውነትም ውሸትም ብሎ ለማንገራገር እድል የሚያሳጣ እውነት አብረውት አሌክሳንደርና እናቱ እያሉ ስሙር የሚያስደንቅ ብርሃን በዚያ ምሥጢራዊ መንደር ሲወርድ ተመለከተ። አብረውት የቆሙ እርሱን ፍለጋ የወጡትም ይህን ተመለከቱ። በተለይም ነጩ አሌክሳንደር ያየውን በቃል መግለጽ እያቃተው እንዲህ አለ "I have never seen such a wonderful thing. What did we see in front of us? Who can tell what will happen in this mysterious country? Undoubtedly, being a person who speaks is Ethiopian. Because in a country surrounded by religion, there are many subtle gifts of faith. What can science say about that light? If your father had lived, he would have told us this for sure" ጀመረ ደግሞ!" አሉ የስሙር እናት። ምንድነው አሁን የሚለው?" አሉት ስሙርን። ሳቅ ብሎ "እንዲህ ያለ ድንቅ ነገር አይቼም አላውቅም። በፊታችን ሆኖ ያየነው ምንድነው? እዚህች ምሥጢራዊት ሀገር ላይ የሚሆነውን ማን ሊናገረው ይችላል? ያለ ጥርጥር እናገራለው ሰው መሆን ኢትዮጵያዊነት ውስ ነው ያለው። ምክንያቱም በሃይማኖት የታጠረች ሀገር ውስጥ ብዙ የእምነት ረቂቅ ስጦታዎች ስላሉ። ያን ብርሃን ሳይንስ ምን ሊለው ይችላል። አባትህ ኖረው ቢሆን ግን ይህን በእርግጠኝነት ይነግሩን ነበረ ነው የሚለው" ሲላቸው ፊታቸውን ፈገግታ ሞላው። በጣም ተደንቀው " መሪጌታ ያውቃሉ! አለ አይ ፈረንጆ! መሪጌታ አልክ!" እያሉ ሲደነቁበት ከአዋሽ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ስንዱዋ ቤተክርስቲያን የማለዳ የደወል ድምጿ ተሰማ። ስሙር ደነገጠ። ሰዓት ከስልኩ ላይ ሲያይ ማመን አቃተው ሰዓቱ ሊነጋጋ ጥቂት እንደቀረው አወቀ። 10:15 ሆኗል። " አባዬ የት ነው ያለው? የት ነው እርሱ አሁን?" አለ ስሙር ግራ በመጋባት ከእናቱ ምላሽ በመጠበቅ። የሚያውቁት አንድ ጊዜ የተፈጠረ ነገር ነበረ። እርሱን ግን አሁን ለልጃቸው እንዳይነግሩት ለመርጌታ ቃል ገብተዋል። ቃላቸውን ካፈረሱ ምን እንደሚያገኛቸው ያውቃሉ ፈሩ። የሚያደርጉት ግራ ሲገባቸው " ምንድነው የምትለኝ? ለምን እራሱኑ አጠይቀውም! የወጣሁት ከቤቴ ፍለጋ ነው አጊንቼሀለው። እርሱን ትተን ወደ ቤታችን እንመለስ ዛሬ ማርያም ነች። ሰምተሀል ደውሉም ተደውሏል። እበተስኪያን መሄድ እንጂ ቆሞ ንትርኩ አይረባንም" አሉ እናቱ ቀለል አድርገው ያሳምናል ያሉትን ምክንያት አቅርበው። መልስ አልሰጣቸውም እያወሩት አንድ ሌላ ማረጋገጫ ሲታሰበው ያን ሊያደርግ በቆሙበት ጥሏቸው ወደ ቤት አቀና። እናቱም እንዳበደ ሰው ትቷቸው ሲሄድ " ስሙርዬ! አንተ! ስሙር" እያሉ እየተቿከሉ ተከተሉት። አሌክሳንደር ግን እናትና ልጅ ሲያወሩ ጀምሮ ስላየው ብርሃን በማሰብ በሀሳብ ጭልጥ ብሎ ሄዶ ስለነበረ ከሀሳቡ የነቃው በስሙር እናት ጥሪ ነበረ። እየሮጡ ሲሄዱ አይቷቸው በቆመበት በድንግዝግዙ ውስጥ ሆኖ ፈጥኖ የጅ ስልኩን አውጥቶ አበራና ዓይኑ ማየት የሚቻለው ድረስ አካባቢውን ተዟዙሮ መቃኘት ማድመጥና ማስተዋል ጀመረ። እራሱ ደኑ በአንድ ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ በሆነ ስርአት እንደሚተዳደር እስኪመስለው ድረስ በቆየበት የስራ የመስክ ተለምዶው ከሚያውቃቸው የደን መገለጫነት የአዋሹ ደን ተለየበት። ይህ መገለጫ ከእለት እለት የሚቀያየር ይሆን ብሎም አሰበ። አሁን አውሬዎች ያሉበት አንድ ጫካ እንዴት ነው እንዲህ ጸጥ ያለ የሚሆነው? እያለ በልቡ እያሰበ የሰው ኮቴ የእርምጃ ድምጽ ሰማ። በጣም ፈራ እጅግ ተረበሸ የሚሆነው ጠፋው። ያደረገው የሚሰማው ኮቴ አቅጣጫው ከወዴት እንደሆነ በማድመጥ ክፉ አድራሽ ከሆነ ለማምለጥ ጆሮውን ቀሰረና የድምጹን አቅጣጫ አረጋገጠ። እርሱ ካለበት በግራ በኩል መሆኑን እርግጠኛ ሆኖ በጥንቃቄ ያበራውን ለርሱ ብቻ በቅርበት እንዲታየው እያበራ ድምጹን ወደሰማበት ተራመደ። አንድ ብቻውን ያለ ሰው ወደ ቤተክርስቲያኑ ከቅጣጫ ሲያመራ ተመለከተ። አሌክሳንደር ከባድ ጥያቄ ውስጡ ተፈጠረ። " ኢሄ ሰው ከደኑ ውስጥ በዚህ ሰዓት ከየት ነው የሚመጣው? እዚህ ውስጥ መኖሪያ ቤት የለ? ምንድነው? ብሎ አስቦ ተከተለው። በትክክልም የሚሄደው ወደ ቤተክርስቲያን መሆኑን እርግጠኛ ሆነ። በጁ ምንም አይነት ብርሃን ሳይዝ ነው የሚጓዘው። ያም ሌላ ተአምር ሆኖበት ወደ ሰውዬው በፍጥነት ከኋላው መከተል ጀመረ። ፈርቶ ሸፍኖ የያዘውን የጅ ስልኩን ብርሃንም ለቆ መጠቀም ጀመረ። እያበራ

ሲከተለው በድንገት ያ ሰው ቆመ። አሌክሳንደር ወደ ፊቱ አብርቶ ሲያረጋግጥ መቆሙን አወቀ። እርሱም እርምጃውን ገታ ፈርቶ ቆመ። ተጠራጠረ። ፊቱን ሳያዞር የቆመው ሰው አሌክሳንደር ብርሀኑን በቅርበት ላይ እያበራበት ወደ ኋላው ዞረ። መካከላቸው የነበረው ርቀት በጣም ቅርብ ስለነበረ ያ ሰው እንደዞረ አሌክሳንደር ማንነቱን በቀላሉ ለየው። ሲከተለው የነበረው በዚሁ ደን ውስጥ በሌሊት ብቻውን አጊኝቶት ክፉኛ ደብድቦት ሞቷል ብሎ ትቶት የሄደው ባሪያው ነበረ። እርሱ መሆኑን ሲያውቅ ያለ ፍርሀት ወደ ፊት ተራመደ። እንደ በጎ አጋጣሚ ቆጥሮ መልካም አጋጣሚውን መጠቀም ወደደ። ለብዙ ግዜያት ባሪያውን አጊኝቶ ሊያወራው ቢፈልግም ፍጹም ሊያገኘው ሳይችል ቀርቷል። ዛሬ ግን መንገድ አገናኛቸውና ሊያወራው ተደብቆ ደወል ወደሰማበት የአምልኮ ስፍራ የሚገሰግሰውን ሰው ከቆመበት እንዳለ ወደርሱ አቀና። ባሪያው ወደርሱ እየመጣ ያለውን ሰው ማንነት ባያውቅም ቆሞ ጠበቀው። አሌክሳንደር አጠገቡ ደርሶ ለሰላምታ እጁን ሲዘረጋ ማንነቱን በትክክል አወቀውና እርሱም መዳፉን ጨበጠው። አሌክሳንደር ለቀደመ ጥፋቱ ይቅርታ ሊጠይቅና ከየት እየመጣ መሆኑን ለመጠየቅ ጊዜ ሳያጠፋ በእንግሊዘኛ ሰላም ሲለው ባሪያው ለአክብሮት አጎንብሶ ምላሽ ሳይሰጥ ሰላምታውን ተቀበለ። አሌክሳንደር "I'm glad I found you today by chance after searching hard. I need two things from you. 1. Because of the wrong I did to you in the past 2. If I knew where you are coming from now?" አለው። ባሪያው ብዙ እንዳያደክመው " ወንድሜ ብዙ አትድከም። እኔ ጽድቅም እውቀትም የሌለኝ ሰው ነኝ። ምን እንዳልክ አላወኩም። እንግሊዘኛ አልተማርኩም። ጎዳና ላይ አደኩ ሌባ ሆንኩ እስር ቤት እያልኩ አሁን አዚህ ነኝ" አለው። " what did you say?" አለው አሌክሳንደር። " ኤውልህ ወንድሜ በከንቱ ጊዜ አናጠፋም ቸር ይግጠምህ" ብሎ ባሪያው ጥሎት ሄደ። የኪዳን ጸሎት ተጠናቆ ቅዳሴ ከመገባቱ በፊት ካህኑ በመስቀል ህዝቡን ሲባርኩ የመሪጌታ ባለቤት በቆሙበት ግድግዳውን ደገፍ ብለው አሁን ቤተክርስቲያን ቆመው አመስጋኝ አወዳሽ አስቀዳሽ ሆነው አሁን ካሉበት ከመገኘታቸው ፊት የሆነውን የኋሊት በሀሳብ መቃኘት ጀመሩ። ከደኑ ውስጥ እንዳበደ ሰው ልጃቸው ጥሏቸው ሲሄድ እየተጣደፉ እየተጣሩ እየተማጸኑት ከምንም ሳይቆጥራቸው ወደ ቤት ደርሶ ነጠላ ወስዶ ወደ ቤተክርስቲያን ሲያቀና እርሳቸውም ማመን አቅቷቸው እንደወትሮው የማርያም እለት እንደሚያደርጉት ነጭ ሀበሻ ሀገራዊ ልብሳቸውን ጥበብ ሳይለብሱ ነጠላቸውን ከትከሻቸው ጣል አድርገው ተከትለውት እርሱ በወንዶች መግቢያ ተሳልሞ ሲገባ አረጋግጠው ነጠላቸውን አጣፍተው ለብሰው እርሳቸውም በሴቶች መሳለሚያ ገብተው እንደተጨነቁ አሁን ወጣ አሁን ወጣ እያሉ ሲጨነቁ ኪዳን አለቀ። ኪዳን ጸሎቱን ሲያደርሱ የቆዩት መሪጌታም ሕዝቡን እየባረኩ ነው። በወንዶች ጨርሰው በሴቶች በኩል ሲመጡ ሁሉም ተሳልሞ ሲፈጸም ተባርከው በጆሮአቸው ተጠግተው "መሪጌታ ስሙር በወንዶች በኩል አይተውታል አለንዴ?" አሏቸው። " አላየውትም!" አሏቸው። መሪጌታ አገልግሎት ላይ የሁል ጊዜ ባሕሪያቸው ነው ማንንም አያዩም። የስሙር እናት ደንግጠው ሲወጡ መሪጌታ ወደ መቅደስ ወደ አገልግሎታቸው ገቡ። የስሙር እናት በወንዶች መሳለሚያ ሰው ጠብቀው መልክት ሊልኩ ወደው ቢጠብቁ ከንድ ወጣት ልጅ ከውስጥ ሲወጣ " ናስቲ ልጄ! አንድ ስሙር የሚባል ልጅ ብለህ ውስጥ ትጠይቅልኛለህ?" አሉት ልጁን አላወቁትም። " ኧረ ችግር የለውም እኔ ራሴ ስለማውቀው ጠራሎታለው አጠገቡ ነበርኩ" ሲላቸው። በረጅሙ ተንፍሰው " ስሙርን ታውቀዋለህ? እርግጠኛ ነህ?" ሲሉት " አዎ በደንብ የመሪጌታ ተማሪ ነበርኩ" አለ ወጣቱ። " በቃ ውስጥ ከሆነ ተወው ተባረክ" ብለው ወደ ውስጥ ተመለሱ። ቅዳሴ ተጠናቆ ቀድመው ወተው ስሙርን ጠብቀው አብረው ወደ ቤት ሲገቡ አሌክሳንደር እቤት ተኝቷል። ኋላ ቁርስ በልተው ቆይተው መሪጌታ መጡ። ሌሊት የተፈጠረውን ሁሉ ባለቤታቸው ሲነግሯቸው ሰምተው ዝም አሏቸው። ስሙር ዝምታቸው የበለጠ ጥያቄ ሆኖበት " አባዬ ሳትዋሽ መልስ ፈልጋለው። ሌሊት የት ነው የሄድከው?" አላቸው። ፈገግ ብለው " ለምን ዋሽሀለው! አገልግሎት ነው የሄድኩት። ለዚያ ነው ልታረጋግጥ ቤተክርስቲያን የሄድከው?" አሉት። ዝም አላቸው። እናቱ ጫካው ውስጥ አጊኝተውት በርሱ ምክንያት ያዩትን ሁሉ አጋነው አወሩላቸው። መሪጌታ " እምነት ከመስማት ነው። ልጄ በዚያ ሌሊት ከሄድክበት ያየኸውን ሳይሆን የሰማኸው ካለ እርሱንም አስተውል። ሁሉ አስተማሪ ነው" ሲሉት ስሙር የባሪያው ምክር ትዝ አለውና " አንተ የሰማሁት እንዳለ እንዴት አወክ?" ጠየቀ። " እናትህና አሌክሳንደርም ቢሆኑ ከዚያ ሲያገኙ ምንም አላሉህም?" አሉት። ጥያቄውን ልቡ እየሻከረ ተወው። " አረ ያን ልጅ አንሱትና ምግብ ይብላ!" አሉ መሪጌታ። " ፈረንጆ! አንተ ፈረንጆ!" እያሉ የስሙር እናት ወደ ውስጥ ገቡ። አሌክሳንደር ከእንቅልፉ ተነስቶ ከመሪጌታ ቀርቦ መስቀል ተሳልሞ ወዲያው ስሙርን "You left me in the forest, why did you come home? Of course, it was both good and bad for me. I found the person I had wronged in the forest going to church at night. I apologized and asked him where he was coming from, but he didn't answer either of them, we didn't get along" "ከጫካ ውስጥ ጥለኸኝ ለምን ወደ ቤት መጣህ? በርግጥ ለኔ ጥሩም መጥፎም አጋጣሚ ሆነኝ። ያንን በደል ያደረስኩበትን ሰው ከደኑ ውስጥ ሌሊት ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄድ አገኘሁት። ይቅርታ ጠየኩት ቀጥዬም ከየት እንደሚመጣ ጠየኩት ግን ለሁለቱም መልስ አልሰጠኝም አልተግባባንም" ሲል ስሙር ማመን አቃተው አባቱን ማየት ጀመረ። " አባዬ የት እንዳለ ታውቃለህ? አሁን ያንን ሰው የት ነው የማገኘው?" ጠየቃቸው። " ምን ይረባሀል?" አሉት። " የምጠይቀው ትልቅ ጥያቄ አለኝ" አላቸው። " እዚያው ደን ውስጥ" ሲሉት ስሙር ወዲያው ወጣ። 💠 ይቀጥላል 💠 💢💠ታኅሳስ 15 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠 ከክፍል 170 የቀጠለ 💠💢 ለሁሉም ሁለታችሁም ወደ ቤት ተመለሱ። እኔ ለጥያቄዬ መልስ ሳላገኝ ወደ ኋላ አልመለስም እርምጃዬ ወደ ሙሲቾ ነው" ሲላቸው እናቱ " ምንድነው ጥያቄህ?" አሉት። እንደምትመልሺልኝ ቃል ትገቢያለሽ?" አላቸው። እናቱ ምንም ይሁን ሊመልሱለት " አዎ ቃል ገብቻለው ጠይቀኝ። አንተም እንደምትመለስ ቃል ግባ" ብለውት ተስማምተው ጥያቄውን ጠየቀ " አባዬ በዚህ ሌሊት የሄደው ወደ ሙሲቾ ነው? አይደለም? እንዳትዋሺኝ ቃል ገብተሻል" ሲላቸው የሚሉት ጠፋቸው። መሪጌታ ቃል ያስገቧቸው ትዝ አላቸው። አልነግርም እንዳይሉም ቃል ገብተዋል። ግራ ገባቸው። ቆመው እንዳሉ ከፊትለፊታቸው አንዳች በሰው ቁመት የሚገመት ቅርጽ ያለው ብርሃን ሲያዩ ፈዘው መመልከት ጀመሩ። 💢💠🌿 ክፍል 172 🌿💠💢 የሶስቱም እይታቸው በዚያ ጨለማ መካከል ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ የሆነ ተአምር መመልከት ሆነ። ምንም ማለት ምንም መናገር አልቻሉም። ብቻ ዓይኖቻቸውም ሀሳባቸውም ሁሉ ወደ ሚያዩት ሆነ። የሚመለከቱት ይህ ተአምር እየሆነ የነበረው በነርሱ የቅርብ ርቀት ላይ ሲሆን እያዩት ደኑ መካከል የወረደው ብርሃን ከርቀት ነጸብራቁ ብርሃኑ እየተዋጠ እየደበዘዘ መጣና ከእይታቸው ተሰወረ። ስሙር የሰፈነውን ዝምታ በጥያቄ ሰበረው " እንዴት ያለ አካባቢ ነው? ምን አይነት መንደር ነው?" እንደ ጥያቄም እንደ አድንቆትም። እውነትም አዋሽ ቆላቲ ከዚህ በቀር የሚገልጸው ስለሌለ እንጂ ብዙ ቢል ይወድ ነበረ። ምክንያቱም ስሙር በዚህ አካባቢ የሚያያቸው ብዙ ተፈጥሮአዊ ነገሮች ላስተዋላቸው ምሥጢር ያዘሉ ተአምራውያን ናቸው። አስቀድሞ ኢሄን አይቷል። ሰንሰለታማው ተራራ በየእለቱ ልዩ ውበት ባለው ጉም ሲሸፈን። አዎ ስሙር በዚያ ተመልክቷል የአዋሽ ተራሮችና አካባቢው በቀን ዝናብ ሳይኖር በበጋ አካባቢው በቀስተ ደመና ሲከበብ። ስሙር ጎበዝ ሰአሊ የሳለው እንጂ በእውን በዓይኑ እያየ መሆኑን ማመን እስኪያቅተው ጥቅጥቅ ያለው ደን በፀሐይ ተሸፍኖ ግማሹ በደን የተሸፈነው ተራራ ጥላ ሲያጠላበት አይቷል። እንደመጣ አካባቢ የሚያየው ሁሉ ይደንቀው ስለነበረ አንድ ቀን በደኑ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ በጅ ስልኩ ፎቶ ሲያነሳ ዛፎቹ ላይ በስልኩ ካሜራ ሲያነሳ ያያቸው ምሥጢራዊ ምልከታዎች ሁሉ ትዝ አሉት። በተለይም ፎቶ ሲያነሳ ሰባቱን ሕብረ ቀለም በቀስተ ደመና አምሳል አንድ የተወሳሰበበት ስእል ነገር ላይ ከቦ ያየበትን ሁሌ ልቡ ያደንቃል መላልሶም ስዕሉን ያየው ነበረ። አንዳንዴ የኪዳነ ምሕረት ስዕልም መስሎት አትኩሮ ያየዋል። ከዚያ የሚበልጠው ደግሞ ዛሬ ሆነ። እውነትም ውሸትም ብሎ ለማንገራገር እድል የሚያሳጣ እውነት አብረውት አሌክሳንደርና እናቱ እያሉ ስሙር የሚያስደንቅ ብርሃን በዚያ ምሥጢራዊ መንደር ሲወርድ ተመለከተ። አብረውት የቆሙ እርሱን ፍለጋ የወጡትም ይህን ተመለከቱ። በተለይም ነጩ አሌክሳንደር ያየውን በቃል መግለጽ እያቃተው እንዲህ አለ "I have never seen such a wonderful thing. What did we see in front of us? Who can tell what will happen in this mysterious country? Undoubtedly, being a person who speaks is Ethiopian. Because in a country surrounded by religion, there are many subtle gifts of faith. What can science say about that light? If your father had lived, he would have told us this for sure" ጀመረ ደግሞ!" አሉ የስሙር እናት። ምንድነው አሁን የሚለው?" አሉት ስሙርን። ሳቅ ብሎ "እንዲህ ያለ ድንቅ ነገር አይቼም አላውቅም። በፊታችን ሆኖ ያየነው ምንድነው? እዚህች ምሥጢራዊት ሀገር ላይ የሚሆነውን ማን ሊናገረው ይችላል? ያለ ጥርጥር እናገራለው ሰው መሆን ኢትዮጵያዊነት ውስ ነው ያለው። ምክንያቱም በሃይማኖት የታጠረች ሀገር ውስጥ ብዙ የእምነት ረቂቅ ስጦታዎች ስላሉ። ያን ብርሃን ሳይንስ ምን ሊለው ይችላል። አባትህ ኖረው ቢሆን ግን ይህን በእርግጠኝነት ይነግሩን ነበረ ነው የሚለው" ሲላቸው ፊታቸውን ፈገግታ ሞላው። በጣም ተደንቀው " መሪጌታ ያውቃሉ! አለ አይ ፈረንጆ! መሪጌታ አልክ!" እያሉ ሲደነቁበት ከአዋሽ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ስንዱዋ ቤተክርስቲያን የማለዳ የደወል ድምጿ ተሰማ። ስሙር ደነገጠ። ሰዓት ከስልኩ ላይ ሲያይ ማመን አቃተው ሰዓቱ ሊነጋጋ ጥቂት እንደቀረው አወቀ። 10:15 ሆኗል። " አባዬ የት ነው ያለው? የት ነው እርሱ አሁን?" አለ ስሙር ግራ በመጋባት ከእናቱ ምላሽ በመጠበቅ። የሚያውቁት አንድ ጊዜ የተፈጠረ ነገር ነበረ። እርሱን ግን አሁን ለልጃቸው እንዳይነግሩት ለመርጌታ ቃል ገብተዋል። ቃላቸውን ካፈረሱ ምን እንደሚያገኛቸው ያውቃሉ ፈሩ። የሚያደርጉት ግራ ሲገባቸው " ምንድነው የምትለኝ? ለምን እራሱኑ አጠይቀውም! የወጣሁት ከቤቴ ፍለጋ ነው አጊንቼሀለው። እርሱን ትተን ወደ ቤታችን እንመለስ ዛሬ ማርያም ነች። ሰምተሀል ደውሉም ተደውሏል። እበተስኪያን መሄድ እንጂ ቆሞ ንትርኩ አይረባንም" አሉ እናቱ ቀለል አድርገው ያሳምናል ያሉትን ምክንያት አቅርበው። መልስ አልሰጣቸውም እያወሩት አንድ ሌላ ማረጋገጫ ሲታሰበው ያን ሊያደርግ በቆሙበት ጥሏቸው ወደ ቤት አቀና። እናቱም እንዳበደ ሰው ትቷቸው ሲሄድ " ስሙርዬ! አንተ! ስሙር" እያሉ እየተቿከሉ ተከተሉት። አሌክሳንደር ግን እናትና ልጅ ሲያወሩ ጀምሮ ስላየው ብርሃን በማሰብ በሀሳብ ጭልጥ ብሎ ሄዶ ስለነበረ ከሀሳቡ የነቃው በስሙር እናት ጥሪ ነበረ። እየሮጡ ሲሄዱ አይቷቸው በቆመበት በድንግዝግዙ ውስጥ ሆኖ ፈጥኖ የጅ ስልኩን አውጥቶ አበራና ዓይኑ ማየት የሚቻለው ድረስ አካባቢውን ተዟዙሮ መቃኘት ማድመጥና ማስተዋል ጀመረ። እራሱ ደኑ በአንድ ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ በሆነ ስርአት እንደሚተዳደር እስኪመስለው ድረስ በቆየበት የስራ የመስክ ተለምዶው ከሚያውቃቸው የደን መገለጫነት የአዋሹ ደን ተለየበት። ይህ መገለጫ ከእለት እለት የሚቀያየር ይሆን ብሎም አሰበ። አሁን አውሬዎች ያሉበት አንድ ጫካ እንዴት ነው እንዲህ ጸጥ ያለ የሚሆነው? እያለ በልቡ እያሰበ የሰው ኮቴ የእርምጃ ድምጽ ሰማ። በጣም ፈራ እጅግ ተረበሸ የሚሆነው ጠፋው። ያደረገው የሚሰማው ኮቴ አቅጣጫው ከወዴት እንደሆነ በማድመጥ ክፉ አድራሽ ከሆነ ለማምለጥ ጆሮውን ቀሰረና የድምጹን አቅጣጫ አረጋገጠ። እርሱ ካለበት በግራ በኩል መሆኑን እርግጠኛ ሆኖ በጥንቃቄ ያበራውን ለርሱ ብቻ በቅርበት እንዲታየው እያበራ ድምጹን ወደሰማበት ተራመደ። አንድ ብቻውን ያለ ሰው ወደ ቤተክርስቲያኑ ከቅጣጫ ሲያመራ ተመለከተ። አሌክሳንደር ከባድ ጥያቄ ውስጡ ተፈጠረ። " ኢሄ ሰው ከደኑ ውስጥ በዚህ ሰዓት ከየት ነው የሚመጣው? እዚህ ውስጥ መኖሪያ ቤት የለ? ምንድነው? ብሎ አስቦ ተከተለው። በትክክልም የሚሄደው ወደ ቤተክርስቲያን መሆኑን እርግጠኛ ሆነ። በጁ ምንም አይነት ብርሃን ሳይዝ ነው የሚጓዘው። ያም ሌላ ተአምር ሆኖበት ወደ ሰውዬው በፍጥነት ከኋላው መከተል ጀመረ። ፈርቶ ሸፍኖ የያዘውን የጅ ስልኩን ብርሃንም ለቆ መጠቀም ጀመረ። እያበራ

ከሆንሽ ባለ አእምሮ ሁኚ። እኔን እብዱን እንዳቆሰሉኝ እብዶች አትሁኚ። ታመሽ ሌላውን አታሳምሚ። ድነሽ ሌላውን አድኚ። ተርፈሽ ለሌላው ትረፊ። አልያ ግን ለእሳቱ ተዘጋጂ። ልጅሽ ድኗል እርሱ መንገዱን ይዟል። ተከተይው አልያ በድንገት አደጋ ጣዮች እንዳቆሰሉኝ በድንገት ትወሰጃለሽ። የሞት እራት ሳቶኚ ልጅሽን ምሰይው። ባለ አእምሮ ሁኚ። አመዛዝኚ እውነትን ፈልጊ። የሚያሳድደኝ በስለት ሊቆርጥ ምንም ወዳላወቁት እንደሄደ ምንም ባላወቅሽው ባንቺ ዙሪያ ቆራጮች ቆመዋል። ሳትቆረጪ ከልጅሽ ተባበሪ። የመጨረሻውን መልዕክቴን ላንተ" አለው ወጣቱን " መጽሐፍ ቅዱስ ታነባለህ ተምረሀል? ሉቃ 13:6 አንብላት እንዳታረፍድ። እኔ አሁን ልሂድ" አለ ገና በአግባቡ የሚገባውን ነገር ሳያደርጉለት። " ቆይ ትሄዳለህ!" አሉት የኤርምያስ እናት።የመጣሁበትን ፈጸምኩ። ኢሄ የኔ መንደር አይደለም። ከናንተየሚስማማኝ ምን ነገር አለኝ። የመጣሁት በምክንያት ነው። እንጂ እንዴት እብድ ከጤነኞች ይተባበራል" ብሎአቸው ወደ በሩ ሲያቀና ከውጭ " በዚህ ነው መሰለኝ የሄደው" የሚባባሉ ሰዎች ድምጽ ሰሙ። የኤርምያስ እናት " ሰማህ የሚያሳድዱህን ድምጽ። እዚሁ ቆይ" አሉት። ሽሽቴ ራሴን ለማዳን ብቻ ከሆነ ምን ይረባኛል። ይልቅ ከከብቶቹ ባለቤት ዘንድ ደርሼ በሁል ጊዜ መንጋውን እንዲጠብቅ ላደርግ ይገባል" ብሎ በሩን ሲከፍት አለፍ ብለው የነበሩት ዞረው አዩትና " ኢኸውና ያ እብድ ኑኑኑ" እያሉ ሲመለሱ በሩን በኃይል ዘግቶ ከነርሱ ሸሽቶ ሮጠ። የኤርምያስ እናት ግን ስለርሱና ስላወራው ሁሉ እያሰበች ደንግጣ ባለችበት ቆማ ቀረች። ወጣቱ ዲያ ከዓይኑ እስኪሰወሩ በጨለማው ማየት ባይችልም ተከትለው የሮጡት ሰዎች ድምጽ እስኪጠፋ ወዲያው በር ከፍቶ ቆሞ ሲያይ ቆይቶ ምንም ድምጽ ሲያጣ እንዳልደረሱበት ተረድቶ ወደ ውስጥ ተመሀሰ። ቆመው አገኛቸው ደነገጠ። " አልደረሱበትም ሳያመልጣቸው አልቀረም" ሲላቸው ከሀሳባቸው ነቅተው " እእ" ሲሉት ደግሞ አላቸው። እርሳቸውም እንዴት እንደተገናኙ እያሰቡት " ግን እርሱ ማነው? አይተኸው ታውቃለህ?" አሉት። " ኧሰ እኔ አይቼው አላውቅም። እንዲህ ያለ እብድ ሰምቼም አይቼም አላውቅም። የሚያወራው ሁሉ ያስደነግጣል ያሳዝናል ልብ ይነካል። ጤነኛ የማያወራውን እኮ ነው የሚያወራው" አላቸው። " እብድ ሆኖ እንዴት ስለ ሰው መጨነቅ እንዴት?" አሉት ጨምረው። " እንዲህ አይነት ታሪክ በሃይማኖታችን ውስጥ ከመጽሐፍ አንድ ጊዜ ያነበብኩትን ነው ዛሬ በአካል ያየሁት። አንዳንድ ብርቱዎች በዓለም ሊሳለቁባት እብድ መስለው ከሰው ተለይተው ይኖራሉ" አላቸው። " አንተ ደግሞ በቃ ዘለህ ክርስቲያን ካልሆናቹ ማለት ትወዳለህ" አሉት።ድሮ ቢሆን በጣም ይቆጡ ነበረ። ዛሬ ግን ቃሉን ከመናገር በዘለለ ምንም ቁጣ አላየባቸውም። " እንዴት ከሚያሳድዱት እየሸሸ እኔን አገኘኝ? ለምን? ደግሞ እዚህ ከመጣ በኋላስ ለምን እያስታመምነው ጥሎን ሄደ?" ትልቅ ጥያቄ ፈጠረባቸው። "እርሱማ የሄደው የመጣው እንድናስታምመው ሳይሆን የመጣበትን ሲፈጽም ነው። ቢሆን ነው እንግዲ የቀረውን ሀሳቡን ለርሶ ከመጽሐፍ እንዳነብሎት አዞኝ የሄደው። የመጣው ለአንድ መልዕክት ነው ማለት ነው" ሲላቸው ሀሳቡ እውነት መሆኑን ያለ ጥርጥር ተቀበሉ። "በል ሂድስቲ ያለህን ታነብልኛለህ ሰማሀለው መጽሐፉን ይዘህ ና" ብለውት ወደ ቤታቸው ሲገቡ መጽሐፉን ሊያመጣ ወደ ክፍሉ አቀና። ወዲያው ከብዙ መጻሕፍቶች ላይ ከላይ የተቀመጠውን ጥቁር ሽፋን ያለው ከሽፋኑ ላይ የመስቀል ስእል ያለበትን መጽሐፍ ቅዱስ ይዞ ወደ ቤታቸው ገባ። " ያለህን ቦታ አውጥተህ አንብበው እስቲ" አሉት። ቦታውን ሲፈልግ ቆይቶ " እንዲህ ይላል" ሲላቸው ሀሳባቸውን ሰብስበው ዝም አሉ " ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው።ፍሬም ሊፈልግባት መቶ ምንም አላገኘባትም። የወይን አትክልት ሠራተኛውንም እነሆ ከዚህች በለስ ፍሬ ልፈልግ ሦስት ዓመት እየመጣሁ ምንም አላገኘሁም።ቁረጣት ስለምን ደግሞ መሬቱን ታጎሳቁላለች አለው። እርሱ ግን መልሶ ጌታ ሆይ ዙሪያዋን እስክኮተኩትላትና ፋንድያ እስካፈስላት ድረስ በዚህች ዓመት ደግሞ ተዋት። ወደ ፊትም ብታፈራ ደኅና ነው። ያለዚያ ግን ትቆርጣታለህ አለው። ይላል።" አላቸው። ብቻ በታሪኩ ውስጥ ያልገባቸው ብዙ ቢኖርም መልእክት እንዳለው በቀላሉ ተረዱ። እየተብሰለሰሉ እርምያስ ደወለ። ስልኩን አንስተው " ሄሎ " ሲሉ ምላሽ የለም። የሚሰሙት ከባድ ጩኸት ጫጫታ ነው። እናት ሰማይ ምድሩ ተገለባበጠባቸው። 💠 ይቀጥላል 💠 💢💠ታኅሳስ 11 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠 ከክፍል 166 የቀጠለ 💠💢 "ልጄ ይቅርታ አድርጌልሀለው። የፈቀድከውንም አልከለክልህም። ያሰብከውንም ፕሮግራም በደስታ እቀበላለው። ግን ልጄ እኔ የምልህ ትክክለኛው ሃይማኖት የተቀበልከው ካልሆነ ጥፋትህን ስለማልፈልግ ነው" ሲሉት " አመሰግናለው እናቴ ለሕይወት ያብቃሽ ዘላለም ኑሪልኝ" አላቸው ቀና ብሎ። " ምነው ያ በሆነ ዛሬ ይህን ማንነትህን አባትህ ኖሮ ባየው" አሉና እናቱ ዓይናቸው እንባ አቀረረ። " አምላክ የፈቀደው ሆኗል እናቴ አትዘኚ። በይ መሸብኝ እኔም ልሂድ" ብሎ ሲነሳ ሊሸኙት አብረውት ወጡ። እያወሩ ከጊቢ ወተው እንደወዳጆች እየተጨዋወቱ ጥቂት ሸኝተውት ሲመለሱ ጨለማው ውስጥ ከጁ ባንጊያ የጨበጠ ቡቱቱ የለበሰ እብድ ከፊታቸው ቆመ። ደነገጡ። " አጠገቡ ደርሰው ነው ያዩት ሊጮሁ ሲሉ " ብትጮሂ በዚ ነው..." ብሎ ባንጊያውን ሲያነሳ ዝም ብለው ደንግጠው ቆሙ። 💢💠🌿 ክፍል 171 🌿💠💢 የለበሰውን ቡቱቱ በግልጥ ከጃቸው የያዙትን ባትሪ አብርተውበት በግልጽ አይተውታል። እብድ መሆኑን አረጋግጠዋል። እንዳለውም አንድ ድምጽ ቢያሰሙ ያለውን ከማድረግ እንደማይመለስ ስላሰቡ ባሉበት ምናልባትም በመንገድ የሚያልፍ ሰው እስኪመጣ መጮህ በራስ ላይ የሞት አዋጅ የማወጅ ያክል ተሰማቸው። " እይኝ እስቲ እኔ ማነኝ? ምን እመስላለው? አንቺስ ማነሽ?" አለ ቆጣ ብሎ። ለጥያቄዌ ምንም ስፍራ አልሰጡም የኤርምያስ እናት። ምክንያቱም ከፊታቸው ቆሞ የሚጠይቃቸው ሰው ከአእምሮው ያይደለ እብድ ነው። ዝም አሉት። " መልሱ እንዲህ ነው። እኔ እብድ የማደርገውን የማላውቅ። አንቺ ደግሞ ባለ አእምሮ። ኢሄው ነው። ታዲያ እኔ ለምን አበድኩ በጤነኞቹ መካከል ለምን ተለየው ለምን አበድኩ? አዎ ያበድኩት ለራሴ በእውነት ዓለም ልኑር ብዬ ነው። ባለ አእምሮዎች ከሀሰት በተባበሩበት በፈጠራቸው ላይ ባመጹበት ለምን ጤነኛ ልሁን አብጄ ብቻዬን ልሁን እንጂ። አንቺ አሁን ባለ አእምሮ ነሽ ምን አመዛዘንሽበት? ደሀ አልበደልሽም? ምስኪኑን አላስለቀስሽም? እኔን ግን ቢሰድቡኝ ቢያንቋሽሹኝ እንጂ ማንን እሰድባለው ከማን እደርሳለው? ታዲያ ማነው እብድ? እኔ ወይስ ሰዳቢዎቼ? አንቺ ወይስ እኔ?" አለ ዓይኑን አፍጦ ፍርሀታቸው ጨመረ ሀሳባቸውና እይታቸው ሁሉ ወደ ጨበጠው ስለታማ ነው። " አልገባሽም ማነው እብድ?" ደግሞ ጠየቀ። " አሁን ኢሄን ስለታማ ባንጊያ ከየት አገኘሁት መሰለሽ ከባለ አእምሮዎቹ ከጤነኞቹ። አንዱ ከወዳጁ ጋር ተጣልቶ ሊበቀለው በዚህ ጨለማ ከሰው ተደብቆ የፈጠረው ከሰማይ እያየው የማይናገሩ ያልተጣሉትን ከብቶቹን በዚህ ስለት ቆራርጦ ወዳጁን ሊበቀል ብቻውን እንደኔ እንደ እብድ እያወራ ሲሄድ ተከተልኩት" አለና ዝም ሲል የኤርምያስ እናት በፍርሀት እየሰሙት በማመንና ባለማመን መሀል ሆኑ። " ያ ሆነ! እብዱና ጤነኛው በጨለማው ታገልን። እብዱ ተሳስተሀል አልኩ ጤነኛው ግን ልክ ነኝ ያሰብኩትን ካልፈጸምኩ በሚል ከጁ የጨበጠውን ልቀማው በዝምታ አጠገቡ ደርሼ ትግል ጀመርን የነፍስ የነፍሱን ታገለኝ። እየታገልን ወደቅን። እንዴት ጤነኛ ከእብድ ያታገላል? ስወድቅ መሬቱ ተስማማኝ ስለቱ ግን ተቃወመኝ። ኢኸው በወደኩበት ኢሄ ባንጊያ እንኳ ለስህተት አድልቶ እጄን ቀላኝ!" ብሎ የቆረጠውን ሲያሳያቸው የኤርምያስ እናት የሚፈሰውን ደሙን ሲያዩ ደነገጡ። ደሙን እያዩ መቆየት አቅም አነሳቸው የለበሱትን ሻርብ ወዲያው ከጁ ሊጠመጥሙለት የጨበጠውን ስለት ዘንግተው በቅጽበት ያሰቡትን ያለ ፍርሀት አደረጉ። እብዱ መልስ አልሰጠም ከጁ የለበሱትን ሲጠመጥሙለት " አንቺም እንደኔ አበድሽ! ከእብድ ጋር ተባበርሽ! የማይድን ቁስለኛ አስታመምሽ! ያ ጤነኛ ኢሄን ስለት ይዤበት ስሮጥ እየተከተለኝ ነበረ። በጨለማው አምልጬው ነው እንዳይደርስብኝ አንቺንም እንደኔ በእብደትሽ እንዳይቀጣሽ ሂጂ አምልጪ ሂጂ ወደ ቤትሽ ሽሺ። እኔ ግን ቆሜ እጠብቀዋል። በቃ እሞታለው። በቃ ይግደለኝ" እያለ እንዲሄዱ ሲማጸን ግራ ገባቸው። " ለምንድነው የሚገድልህ? እኔንስ ለምን ይገድለኛል?" ጠየቁት። "ጤነኛው ስላበደ ባለ አእምሮው አእምሮውን ስላጣ። አንደበት የሌላቸውን እንሰሳት አትግደል ባልኩት አብዱን አሳደደኝ። እርሶም ከእብዱ ተባብረዋል ካገኞት...." ሲላቸው በቃ እንደው ግራ ገባቸው። ቡቱቱ ለባሹ ሰውና ንግግሩ አንጀታቸውን አላወሰው። " ና ከእኔ ተከተል።ከኔ ቤት ቁስልህን አጥቤ ጂቢ አደርግልሀለው። ከሚያሳድድህም ትሰወራለህ። ቤቴ ቅርብ ነው። በጣም ደም እየፈሰሰህ ነው። እርዳታ ያስፈልግሀል እባክህን ና" ሲሉት " እኔኮ እብድ ነኝ!" አላቸው። " ና ተከተለኝ" ብለው ከፊቱ ቀደሙ እርሱም ተከተላቸው። ወዲያው ከቤታቸው የውጭ በር ደርሰው " ና ወደ ውስጥ ግባ!" አሉት። " ጊቢ ጨለም ካለው ቦታ ካልሆነ ወደ ቤት መግባት አልችልም። ካበድኩ ቆይቻለው። ቤት መግባት ካቆምኩ ዓመታት አልፈዋል። አሁን ቤት ከገባው ማበድ ነው። እኔ ደግሞ ማበድ እፈራለው። ማበድ አልፈልግም። ጤነኞች እንዲስቁብኝ ከቤታቸው አልገባም" አላቸው ከደጅ ቆሞ። ከርቀት ከጨለማው የሚሯሯጡ ድምጽ የሚያሰሙ በርካታ ሰዎች ሁካታ ሲሰሙ " እሺ እንዳልክ ይሁን ና ግባ" አሉትና ወደ ጊቢ ገባ። እንደገባ ከሰፊው ጊቢ ውስጥ ዛፎች ወደ በዙበት ጥላቸው በጨለማው ከየክፍላቱ በሚበሩት የመብራት ብርሃን ወዳጠሉበት ስፍራ ሲያቀና እርሳቸው በቶሎ ወደ ቤት አቀኑ። በፍጥነት የተቀጣጠለውን ከሰል በማንደጃ ይዘው ቁስሉን ሊተኩሱለት መተኮሻ ጨርቅ በአን ላይ ይዘው ወደ ጨለማው ሲሄዱ ሁሌ ንፍታሌምን በፍቅር የሚመክረው በጊቢው ረጅም ዓመታት የኖረው ትሁት ወጣት አያቸውና ተከተላቸው። ወደ ጨለማው ሲፋጠኑ " በሰላም ነው ምን ሆነዋል?" እየጠየቀ ሲከተላቸው "በሰላም ነው። ና ተቀበለኝ" ብለው ማንደጃውንና መተኮሻውን አቀበሉትና " ወደ አትክልቶቹ ሂድ መጣው ከዚያ አድርስ" ብለውት አልኮል ሊያመጡ ወደ ቤት ተቻኩለው ተመለሱ። ወጣቱ እንደደረሰ ከጁ የያዘውን ማንደጃ አስቀምጦ ምንም ሳያይ በዚያው እንደቆመ የኤርምያስ እናት እየሮጡ መጡ። ፈዞ ቆሞ እያያቸው " እስቲ ፍጠን አብራልኝ" ሲሉት ስልኩን አበራ። ያሰሩለትን ሻርባቸውን በደም ተጨማልቆ ከጁ የሚፈታ እብድ ሲያይ ደነገጠ። የሚናገረው የሚለው ጠፋው። ከአልኮሉ ጋር ይዘው በመጡት ጥጥ ቁስሉን አጠቡለት። " የእብድ ቁስል ቶሎ ነው የሚድነው። የጤነኞቹ ነው የሚመረቅዝ" አለ እብዱ ወጣቱ በፍርሀት ያየዋል። " ቆይ ምን ቆርጦት ነው?" የኤርምያስን እናት ጠየቃቸው። እብዱ መለሰ " በጤነኛው እጁ ወደ ስለታማው ከመሬት ወዳለው ባንጊያ እያሳየው " ጤነኞች ናቸው የቆረጡኝ። ባለ አእምሮዎች ናቸው ያቆሰሉኝ" አለው። አጥበውት በመተኮሻ ሲተኩሱለት " ሰው ያነደዳት እሳት ቲኒሿ ይህን ያክል ካቃጠለች የሚጠብቀን የሰማዩ እሳት እንዴት ይሆን? ያውም እሳቱ መጠኑ ቀንሶ በመተኮሻ! መዘጋጀት ነው በግዜ!" አለ። ሁለቱም እገዛቸውን ቀጠሉ። እብዱ " እየተዘጋጀህ ነው?" አለው ወጣቱን። ዝም አለው። " በቃ ተውት አታክሙኝ ልቁሰል አታድኑኝ ልታመም። ስለናንተ ማስታወሻ ይሆነኛል" አላቸው። የኤርምያስ እናት " ምነው አሳመምንህ እንዴ?" አሉት። " አዎ ከቁስሌ በላይ ካደሙኝ በላይ አመማቹኝ አሳመማቹኝ" አላቸው። " ስለ ልጅሽ የምትጨነቂ እናት

Alexander!" "አሌክሳንደር!" አለው ተገርሞ። ያን ሁሉ ሲያወራው የቆየው አሌክሳንደር እንደሆነና አማርኛ አቀላጥፎ ማውራት እንደሚችል ሲያስብ ማመን እያቃተው " ቆይ እስከ ዛሬ አማርኛ እንደማይችል ሰው መሆን ለምን ፈለክ?" ሲለው አሌክሳንደርን ተከትለው የመጡት እናቱ ደርሰው " ቆይ ምን ሆነሀል ልጄ? ምነው ለኔስ አታስብም?" ሲሉት ደነገጠ። " ምንድነው እማዬ?" አለ የጅ ባትሪ አብርተው አጠገቡ የቆሙትን እናቱን። " ጭራሽ ምንድነው ትለኛለህ? እኔ ልጠይቅህ እንጂ ምንድነው? ምን ሆነሀል?" አሉት። ስሙር መልስ አልሰጣቸውም። እናቱ " እኔማ ሀገር ሰላም ነው ብዬ መች ጉዴን አውቄው። ኢሄ ፈረንጅ ነው ከጉድ ያተረፈኝ። ያውም በስንት ጣጣ" አሉት አለመግባባቱን ጣጣ በሚል ገልጸው። " የምን ጣጣ ነው?" አላቸው ስሙር። " ወደ መኝታ ክፍል ገብቶ ያው በሚያውቀው ይለኛል ይለኛል ምኑን ልወቀው። እርሱ ደግሞ እንደው ስንፍናው ምን ሆነሀል ብዬ ብጠይቀው ሊሰማኝ ነው! ውይ ዲዳ በቃ ዲዳ። መጨረሻ ጎትቶ ከመኝታህ አደረሰኝና እንደሌለህ አሳየኝ። ለሽንት ወተህ ነው ብዬ ማሰቤስ ብጠብቅ አልመጣ ስትልኮ ነው ተያይዘን የወጣነው" አሉት። ስሙር ሲያወራው የነበረው አሌክሳንደር ሳይሆን ሌላ ሰው መሆኑ ሲገባው እርሱ መስሎት በአማርኛ የጠየቀውን አስታውሶ እናቱ ዲዳ ካሉት ውስጥ እራሱን ደመረና ሳቅ አለ። ከዚያ ለእናቱ ምንም ሳይመልስ ሶስቱም እንደቆሙ ስሙርና አሌክሳንደር በፈረንጀኛ የሆነውን ሁሉ ምሥጢር አድርገው ማውራት ጀመሩ። አሌክሳንደር ስሙር የሚያወጋውን ሲሰማ በተደሞ መሆኑን ያስተዋሉት የስሙር እናት አንዳች ምሥጢር እንዳለ ለመጠርጠር ጊዜም አልፈጀባቸውም። ግይ ሳይጠይቁ የልጃቸውን ሲያወራ የሚያሳየውን የሰውነት እንቅስቃሴና የአሌክሳንደርን በጽሞና ጓጉቶ መስማት እየተመለከቱ ለመረዳት ጣሩ። ግን ምንም እንኳን ፍንጭ አጡ። አሌክሳንደር በዝምታ ከመስማት ወደ ጥያቄ አለፈ። ጥያቄውም ያወራውን አብሮት የነበረውን ሰው መልኩን አይተኸዋል የሚል ነበረ። ስሙርም ከድምጹ ውጭ ምኑንም እንዳላየው ነገረው። ሁለቱም ስለ ተፈጠረው ነገር ሲደነቁ ያዩት እናት " በቃ እኔ ሰውም አልመስላችሁም አይደል? ምነው ትችላለህ አንተ እንኳን በምሰማው ብታወራ? አሁን ያወራችሁትን እያንዳንዱን በቋንቋዬ ንገረኝ" አሉት የስሙር እናት። ስሙር ፈገግ ብሎ " እኔ ወደ ቤት አልመለስም ከሙሲቾ ተራራ መውጣት ፈልጋለው ስለው ነው ፈረንጆ አይሆንም እኔና እናትህ አንለቅህም" ያለኝ ኢሄው ነው ያወራነው ነገር። ሲላቸው እናቱ ልጃቸውን ክፉ መንፈስ ቢያገኘው እንጂ በደህናው በዚህ ሌሊት ወደ ሙሲቾ ካልሄድኩ እንደማይል አስበው የአሌክሳንደርን ሀሳቡን መቃወም ደስ አስብሏቸው " እድሜ ይስጥህ ፈረንጆ አንተ አማርኛ ካለመቻል ውጪ ልክ ነህ ጤናህ እንደኔ ልጅ አልተናጋም!" አሉት ዓይን ዓይኑን እያዩት። የሚሉት ሳይገባው እርሱም ፈገግ አለላቸው። ስሙር ግን አንድ ሀሳብ ውስጡ ለተፈጠረው ጥያቄ መልስና ለሚጠራጠረው ነገር እርግጠኛ እንደሚያደርገው አስቦ " ለሁሉም ሁለታችሁም ወደ ቤት ተመለሱ። እኔ ለጥያቄዬ መልስ ሳላገኝ ወደ ኋላ አልመለስም እርምጃዬ ወደ ሙሲቾ ነው" ሲላቸው እናቱ " ምንድነው ጥያቄህ?" አሉት። እንደምትመልሺልኝ ቃል ትገቢያለሽ?" አላቸው። እናቱ ምንም ይሁን ሊመልሱለት " አዎ ቃል ገብቻለው ጠይቀኝ። አንተም እንደምትመለስ ቃል ግባ" ብለውት ተስማምተው ጥያቄውን ጠየቀ " አባዬ በዚህ ሌሊት የሄደው ወደ ሙሲቾ ነው? አይደለም? እንዳትዋሺኝ ቃል ገብተሻል" ሲላቸው የሚሉት ጠፋቸው። መሪጌታ ቃል ያስገቧቸው ትዝ አላቸው። አልነግርም እንዳይሉም ቃል ገብተዋል። ግራ ገባቸው። ቆመው እንዳሉ ከፊትለፊታቸው አንዳች በሰው ቁመት የሚገመት ቅርጽ ያለው ብርሃን ሲያዩ ፈዘው መመልከት ጀመሩ። 💠 ይቀጥላል 💠 💢💠 ታኅሳስ 9 2016 ዓ.ም አሰላ 💠💢

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠 ከክፍል 168 የቀጠለ 💠💢 በር ከፍተው ወደ ውጪ ሲወጡ ስሙር ቀስ ብሎ በመስኮት ዘሎ ወጣ። ቀስ እያለ እሚሄዱበት ድረስ ሊከተላቸው እንዳሰበ ገና ከጊቢ ሳይወጡ ባጭሩ መንገዱ ተቋጨ። አባቱን አጣቸው። ቢፈልግ ቢፈልግ ሊያገኛቸው አልቻለም። በፍጥነት ወደ ቤት በወጣበት ተመለሰና ወደ እናትና አባቱ ክፍል ቀስ ብሎ በዝግታ ገብቶ ሲመለከት አባቱን ከመኝታቸው ተኝተው አገኛቸው። ምንም ሳይል በቀጥታ ወደ ክፍሉ ተመልሶ ተኛ። አባቱ ግን ወደ ምሥጢራዊው የጠቢባን የውዳሴ ደጅ ገሰገሱ። ስሙር 9:ዐዐ ሰዓት ዳግም ነቅቶ አባቱን ሲያያቸው የሉም። አዘነ ነገን ጠብቆ ሊከተላቸው ነገ የዓመት ያክል ራቀበት። ወዲያው ልብስ ደራርቦ ከቤቱ ወጣ። ጨለማው ደኑን አቋርጦ ለመሄድ አይደለም ከጊቢያቸው እንኳ እንዳይወጣ አቅም ቢያሳጣውም ስሙር ግን የጅ ስልኩን አብርቶ በጁ ዱላ ይዞ ወደ ደኑ በሙሲቾ ተራራ መሄጃ አቀና። ገና ደኑ ውስጥ እንደገባ አንድ ሰው ሳያስበው ከኋላው "ቁም" ሲለው ደርቆ ቀረ። 💢💠🌿 ክፍል 170 🌿💠💢 ስሙር ሰውነቱ በድን ሆነ። ከቆመበት መንቀሳቀስ አቃተው።ድምጹን ከፊት ይስማው ከኋላ ከቀኝ ይሁን ከግራ እንኳን በቅጡ አልለየም። ብቻ ቁም ሲባል ቆሞ መገኘቱን ነው የሚያስታውሰው አንድ ነገር። " ከጅ ያለውን የብርሃን መስጫ መብራት አጥፋው" አለ ቁም ያለው ሰው። ስሙር ከጁ የያዘውን ብርሃን ከፍርሀቱ የተነሳ ምኑን ነክቶ እንደሚያጠፋ እንኳን እስኪጠፋው ተደነባበረ። " አይዞህ የከፋ ነገር ባንተ ላይ የሚመጣ ምንም አይኖርም አትፍራ ተረጋጋ" ሲለው ስሙር ቲኒሽ ትንፋሹ መለስ አለለትና ተረጋግቶ በጁ የያዘውን ብርሃን ተረጋግቶ አጠፋው። አካባቢው ጨለማ ተዋጠ። ስሙር ከፍርሀቱ ጋር ተደምሮ ጨለማን ለመጀመሪያ ጊዜ ያየው ይመስል አካባቢው ብቻ ሳይሆን ውስጡም ጭልም አለበት። ጨለማው እንዳለ ሆኖ ስሙር በአካባቢው ታላቅ ጸጥታ ውስጥ ሆኖ የሚሆነውን መጠበቅ ጀመረ። በአካባቢው የሰፈነው ጸጥታ ፍጹም ጸጥ ያለ ከመሆኑ የተነሳ መርፌ እንኳን ከእጅ ቢወድቅ ይሰማል። ስሙር ጆሮው ተቀሰሯል ግን ምንም ድምጽ የለም። ባለበት ቆሞ የስሜት ህዋሳቱን በበለጠ ማሰራት ጀመረ። ከደቂቃዎች በኋላ ከቀኙ የሰው ኮቴ ድምጽ ወደርሱ ሲራመድ ተሰማው። የሰማው የሰው ኮቴ ድምጽ ውስጡ አስተጋባ የንውጽውጽታ ያክል አወከው። የሚሆነውን ከመጠበቅ በቀር ግን ምንም ላለማድረግ እንደቆመ ነው። ወደርሱ እየተጠጋ የመጣው ኮቴ አጠገቡ ደርሶ ከኋላው ቆሞ ድምጹ ጠፋ። ከአሁን አሁን ማጅራቱን የሚመታው እየመሰለው ሲርድ በዝምታ ቆይቶ " ሰላም ላንተ ይሁን ተወዳጅ ወንድሜ ሆይ! በዚህ ድቅድቅ ጨለማ በዚህ የሰው ልጅ ባልሆነ ሰዓት ስለምን ብቻህን ትሄዳለህ? ጉዞህስ ወዴት ነው?" ጠየቀው። ስሙር የሚሰማው ህልም መሰለው። የሰማው ድምጽ በትህትና ዜማ ልብን የሚያሳርፍ ልዩ በፍቅር የተቃኘ የመሰንቆ ድምጽ ይመስላል። ደግሞ ሌላ ቃል እስኪናገር መጠበቅ እንጂ ይህን ጥያቄ ሰምቶ ቅኝቱ በፈረሰ ድምጽ ምላሽ መስጠት ኃጢአት መስሎ ተሰማው። "ስለምን ለመልስ ዘገየህ? ግድ የለህም ንገረኝ" ሲለው ስሙር " ወደ ተራራው" አለ ባጭሩ። በመካከላቸው ያ ፍጹም ጸጥታ ዳግም ሰፈነ። ጸጥታው የፈረሰው " ከተራራው በዚህ ሰዓት ምን ትፈልጋለህ? እንኳን በዚህ ሰዓት ቀንስ ቢሆን ከተራራው ምን ጉዳይ አለ?" በሚል ጥያቄ ነበረ። ስሙር ለዚህ ጥያቄ ተመጣጣኝ ምላሽ ፍለጋ በሀሳቡ ዓለምን አካለለ። ነገር ግን የዚህ ጥያቄ ምላሽ በዚህች ብዙ ጠቢባንን አቅፌ ይዣለው በምትል ከንቱ ዓለም ውስጥ ከቶ አጣ። ሰማየ ሰማያት አየረ ርቀት መነጠቅን ተመኘ። ያ ግን ለርሱ ስላልተሰጠ በሀሳብ አክናፍ በሮ በሮ እዚያው ጨለማ ከዋጠው ከቆመበት ደን ውስጥ ተመለሰ። " ልቤ ከዚያ መድረስን ይመኛል። ያን ስፍራ ካየሁ ጊዜ ጀምሮ ነፍሴ ደጋግማ ብታስበው" አለ መልስ እንደማይሆን ውስጡ እያወቀ። "ያስ ቢሆን በለ አእምሮ ሆነህ ሳለህ ስንት አውሬ ባለበት ብቻህን በድቅድቅ ጨለማ ለምን ትሄዳለህ?" ጠየቀው። ስሙር " ያ ከናፍቆቴ ገዝፎ አልታየኝም። ደግሞም ወደዚያ የሚሄዱት በዚሁ ሰዓት ይህን ቢያደርጉ ምንም እንዳላገኛቸው አምናለው" አለ በትህትና። አስቁሞ በትህትና የሚያናግረው ሰው አላማ ፍጹም ያልገባው ስሙር ጥያቄና መልስ ሲሰጣጡ በመቆየታቸው ፍርሀቱ ቀንሶ "አንተስ በዚህ ድቅድቅ ጨለማ ከዚህ ምን ትሰራለህ? እኔንስ ስለምን ከመንገዴ ታቆመኛለህ?" አለው ፈራ ተባ እያለ። ያስቆመው ሰው በዝምታ ሲያስብ ቆይቶ " የሰው መንደር እረፍት ባጣ እረፍት ፍለጋ ወደ ብቸኝነት ወጣው። እስካሁንም ግን ፍጹም ሰላምንና የጠፋውን እኔን አላገኘዋቸውም። እስካገኛቸው በዚህ ቆያለው። አንተን ያስቆምኩ ግን መንገድህ ትክክል ቢሆንም ጊዜውና ጉዞህ ትክክል ስላልሆነ ነው" አለው። ስሙር ምላሹ የበለጠ ግራ አጋባው። " እኔጋ የቆምከው አንተ አይደለህም? እንዴት ራስህን ታጣዋለህ? የኔስ ጉዞ ምኑ ነው ትክክል ያልሆነው?" ደግሞ ጠየቀው። እንዲህ መለረለት " አዎ አጠገብህ ያለው እኔነት ውስጥ ነው እኔነቴ የጠፋው። የብዙዎቻችን ማንነት የሚጠፋው እዚያው ሰፊው እኛነታችን ውስጥ ነው። ታዲያ ኢሄ ውሳጣዊው ዓለማችን ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ የጠፋውን እኛነታችንን ለማግኘት ትጋት ያሻዋል። ሰነፎች ግን እራሳቸውን ፍለጋ በራሳቸው ዓለም ውስጥ ሲባክኑ ጭራሽ የከፋ ጥፋት ያገኛቸዋል። አንተ ራስህን ነህ? አንተ ካንተ ስር ጠፍተህበት ታውቃለህ?" ግማሹን በጥያቄ ለጥያቄው መልስ ሰጠ። ስሙር የሚሰማው ንግግር ውስጡ ድረስ ዘልቆ ነፍሱን ቀሰቀሳት። ባዶነቱን መዘነበት። በዚህ ድቅድቅ ጨለማ ያገኘው ነፍሰ ገዳይ ሳይሆን ነፍሱን ሊታደግ የተላከ ሐዋርያ እንደሆነ አወቀ። " የኔስ ጉዞ ስህተቱ?" አለው ስሙር። " እንዳልከው ብዙ ከኛ የቀደሙ ተጓዦች ነበሩ። በርካቶቹ በቀን በብርሃን ተጉዘው ከሞትና ጨለማ ደርሰው ሕይወታቸውን ገብረዋል። የበረቱት ግን በጨለማው እንኳ ፀሀይ ሆነው እያበሩ ሕይወት አግኝተዋል። አንተ የቱን ነህ?" መልሶ ጠየቀው። " ሁለተኛዎቹን መሆን እፈልጋለው" መለሰለት። መልሱን እንደሰማ ስሙርን ተቆጣው "በአንዴ እነርሱን መሆን ወደ ሞት እንደመጓዝ አይቀልም። አዎ እነርሱ የፍጥረታትን ፈጣሪ ስላመለኩ ፍጥረታት ተገዙአቸው። ያ ግን ለኛ አይቻለንም። ሙሴን ታውቀዋለህ በበትሩ ባሕር ከፈለ። ኤልያስንስ ቁራ ምግብ ሲያመጣለት እንደነበረ! ዮናስ በአሳ አንበሪ ሆድ ሶስት ቀናትን ውሎ ማደሩን? ዳንኤል ከአናብስት ጋር ማደሩን! ሶስት ሕፃናትስ ወደ እሳት ተጥለው ውኃ እንደሆነላቸው! ሌላም ብዙ ብዙ። እነዚህ ሁሉ ከእዚህ የደረሱት በተጋድሎ ነው። በዚያ ውስጥ ሳናልፍ እነርሱ ከደረሱበት ለመድረስ እንዴት? ከዚያ ተራራ ሳትደርስ ረጅም ጉዞና ብዙ ፈተና ከፊትህ አለ። ለመድረስ ማንነትህ ካስቻለህ አሁን መሄድ ትችላለህ" ብሎት ጥሎት ሲሄድ ሳይንቀሳቀስ ባለበት ቆሞ ያ ሰው የነገረውን ሁሉ ዳግም እያሰላሰለ እራሱን እንደተባለውን በራሱ ውስጥ የጠፋውን እርሱነቱን ፍለጋ ወደ ውስጡ ርቆ ሄደ። ከሀሳቡ ያነቃው "ስሙር!" የሚለው ጥሪና ከትከሻው ያረፈው መዳፍ ነበረ። ስሙር ብሎ ሲጠራው የሚያውቀው ሰው መሆኑን ሲያውቅ ደነገጠ። ለምን በዚህ ጨለማ ከቤት እንደወጣ አጠገቡ የቆመው ሰው በእንግሊዘኛ ሲጠይቀው "

መምጣት ትችላለህ? ነው አትመጣም?" ብሎ ነገሩን በጥያቄ መለሰ። " እኮ ምን አለ ነው የምልህ?" አለ ንፍታሌም። ቢኒያም ድምጹን ቀንሶ " እኚያ እቤት መተው አንተን የጠየቁትን አባትኮ ገዳም አባ ኃይለ ጊዮርጊስ ጋር አየዋቸው። ቶሎ ናና አግኛቸው። እንዳያመልጡህ ብዬ ነው" ብሎት ሳይሰናበተው ስልኩን ዘጋ። " እውነትህን ነው? ሄሎ ሄሎ!" አለና ስልኩን ከጆሮው አንስቶ መዘጋቱን ሲያይ ተቻኩሎ " መሄድ አለብኝ" አላት ሰላምን። ሰላም " የምናወራውን ለጥያቄዬ ምላሽ ሳትሰጠኝ?" አለችው በተማጽኖ። " በአፋጣኝ መሄድ አለብኝ ባይሆን ምናልባት ሌላ ጊዜ ስንገናኝ....በጣም ይቅርታ! በአስቸኳይ ና የሚል መልእክት ደርሶኝ ነው" አላትና ሊወጡ ሲሉ እናቱ ብቅ ብለው " ወዴት ነው? ቆይ እንጂ ምነው ተቻኮላችሁ?" ጠየቁ ንፍታሌም እንደሚቸኩል ነግሯቸው በፍጥነት ሲወጣ ሰላምን ግን ቆይተሽ ትሄጃለሽ ብለው የንፍታሌም እናት አቆዩአት። ንፍታሌም በፍጥነት ገዳም የሚፈልጉትን አባት እስኪያቸው ቸኩሎ ወደ መኪና መንገድ ገሰገሰ። " ሄሎ የኔ ልጅ! ሰላምዬ ደና ነሽ!" አሏት መሪጌታ አመሀ ልጃቸውን በስልክ ሲያወሩ። እርሷም የምትሳሳላቸውን አባቷን ደህንነታቸውን ጠይቃ ከአባቷ ትዕዛዝ ተቀበለች። " ሰላምዬ ይመጣሉ ያልኩሽ እንግዳ ነገ ነው ወዲህ የሚመጡት። ሀገሩን ከዚህ ቀደም መተው ስለማያውቁት አብረሻቸው እንድትመጪ ብዬ ነበረ። ታዲያ መምጣት የምትችይ ከሆነ ብቻ ነው። ካልተቻለ አብሮአቸው የሚመጣ ሰው ሌላ....." ሲሏት " አባዬ እችላለው! አብሬያቸው እመጣለው። የት ነው የማገኛቸው?እንዴት ነው ተገናኝተን መምጣት የምንችለው?" ጠየቀቻቸው። አባቷ እንዴትና የት እንደሚገናኙ ነግረዋት ተሰነባብተው ስልክ ተዘጋ። ንፍታሌም ገዳም እንደደረሰ ለቢኒያም በተደጋጋሚ ቢደውልም ስልክ አልሰራ አለው። በቀጥታ ወደ አባ ኃይለ ጊዮርጊስ በአት አቀና። እንደደረሰ አባ ኃይለ ጊዮርጊስን አጊኝቷቸው ከጃቸው መስቀል ተሳልሞ ሲጨዋወቱ ቆይተው ቢኒያም መምጣቱን ጠየቃቸው። " አዎ እዚህ ነበረ። ከአንድ ቦታ ልኬው ነው ይመጣል" ብለው መለሱለት። ከቆይታ በኋላ ቢኒያም ከተላከበት ሲመጣ ንፍታሌም በደስታ ተቀበለው። አባ ከአጠገባቸው ሲሄዱ ጠብቆ " የታሉ ያልከኝ አባት? ስልክህ ደግሞ ፍጹም አይሰራም" አለ ንፍታሌም። ቢኒያም " እንዴ አላገኘሀቸውም እንዴ? እኔኮ እዚሁ ትቻቸው ከተላኩበት ሄድኩ። ቆይ ቆየኝ ልጠይቃቸው" ሲለው " አትጠይቃቸው ተወው ይቅር በቃ" አለ ንፍታሌም። ቢኒያም ግን ሊጠይቅ ትቶት ወደ ውስጥ ገባ። አባን አናግሯቸው እያዘነ ተመለሰና " አየህ ስደውልልህ ፍጠን ያልኩህ ለዚህ ነበረ። ጠየኳቸው ሄደዋል አሉኝ። ነገ መንገድ ስለሚሄዱ ወደ ሌላ ቦታ ሄደዋል አሉኝ" አለው። ንፍታሌም ስላላገኛቸው ቅር ቢለውም ብዙም ሳያዝን " ይሁን በቃ አትጨነቅ" ብሎት ገዳም አብረው ቆይተው አብረው አባ ኃይለ ጊዮርጊስን ተሰናብተዋቸው ሲሄዱ ንፍታሌምን ለብቻ ጠርተውት አንድ መልእክት ነግረውት የታዘዘውን በሺታ ተቀብሎ ተሰነባበቱ። ቢኒያምና ንፍታሌም ወዲያው ወደ ሮቤ እንደደረሱ እንደሚገናኙ ተቀጣጥረው ተለያዩ። ንፍታሌም ወደ ቤቱ አቅንቶ ከቤት ሻንጣውን አሰናድቶ ወዲያው ወደ ገዳም ተመለሰ። በማግስቱ ማለዳ ንፍታሌምና የማያውቃቸው አባ ኃይለ ጊዮርጊስ ጋር የነበሩ አረጋዊ መነኩሴ ቢኒያም እንዲገናኛቸው የፈለገው ንፍታሌም ግን ያላወቃቸው አባት በጠዋት አብረው ከገዳሙ ወተው ወደ መነኻሪያ ሲሄዱ ለብዙ ቀናት ከማንም ጋር ሳያወራ በዝምታ ያሳለፈው አቤል በማለዳ ወደ ገዳም አባ ኃይለ ጊዮርጊስ ጋር ሲሄድ ከመንገድ ከነንፍታሌም ጋር ተገናኘ። ገና ከርቀት ንፍታሌምን ሲያየው ተጨነቀ። አብረውት ያሉትን አባት አጠገባቸው ሲደርስ ከጃቸው መስቀል ተሳልሞ ንፍታሌምን ሰላም አለውና አረጋዊው " ከወዴት እየሄድክ ነው?" ሲሉት አቤል " እራሴን ፍለጋ እየሄድኩ ነው። እስከዛሬ ራሴን ሳላገኘው ብዙ ፈለኩ። አሁን ግን እራሴን ፍለጋ እየሄድኩ ነው። አባ ራሴን እንዳገኝ ይርዱኝ። ልከተልዎት?" አላቸው። ንፍታሌም ሄድ ብሎ ቆሞ ሲጠብቃቸው አቤል ጥቂት አውርተውት ተከተላቸው። ሶስቱም በአንድነት ወደ መነኻሪያ አቀኑ። ሰዓቱ ማለዳ 12 ሰዓት አቅራቢያ ነው። ቢኒያም ከእንቅልፉ እንደነቃ ስልኩን አንስቶ ለሰላም ደወለ። " ከቻልሽ ዛሬ ባገኝሽ!" አላት። " አልችልም መንገድ እየሄድኩ ነው" ብላው ስልኩን መልሶ ንፍታሌም ጋር ደወለ። " የት ነህ?" አለው። ንፍታሌም " መንገድ እየሄድኩ ነው ምን ያህል እንደምቆይ አላውቅም" አለው። ቢኒያም ንፍታሌምና ሰላም ግንኙነታቸው እንደጠረጠረው እንደሆነና ሁለቱም በምሥጢር ተያይዘው ወደ ሌላ ቦታ እየሄዱ መሆኑን ውስጡ ጠረጠረ። ሰላም ቤቷን ቆልፋ አባቷ ያሏትን ሰው ለማግኘት ወደ ተባለችበት አቀናች። ሮቤ መነኻሪያ ደርሳ ወደ ሀሮ ዱማል ከሚሄደው መኪና ጋር ቆማ እንዳለች አቤል ንፍታልምንና እኚያ ከእብዱ ጋር ያየቻቸውን አረጋዊ አባት ስታይ ክው ብላ ደርቃ ቀረች።........... 💠 ይቀጥላል 💠 💢 ታኅሳስ 8 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ 💢

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠 ከክፍል 165 የቀጠለ 💠💢 "ልጄ ገና ሳይሽ ነው ልቤ እንዲሁ የወደደሽ! ንፍታሌምን ፈልጌው ነው የመጣሁት ስትይኮ ትናንት ድንግጥ ነው ያልኩት። ቀድሞ ትተዋወቁ ነበረ?" አሏት። ንፍታሌምም እግረመንገዱን ለእናቱ መልስ ሊሰጥ " ሰአሊና የመሪጌታ ልጅ መሆንሽን ለምን ባለፈው እንዴት ሳትነግሪኝ?" ብሎ ሲጠይቃት እናቱ እንደሚተዋወቁ የሆነ ግንኙነትም እንዳላቸው ተረድተው ደስ እያላቸው " በሉ ተጨዋወቱ የሆነች ስራ አለችኝ" ብለው ወጡ። የንፍታሌም እናት ልጃቸው ሰላምን እንደተመኙት ሊያገባት መንገድ እንደጀመረ እርግጠኛ ሆነው ፈነጠዙ። የርሳቸውን መውጣትና ንፍታሌም የጠየቃትን ጥያቄ አያይዛ ሰላም አፍና የያዘችውን የውስጧን ፍም እሳት ልቧን የሚያነደውን እሳት አውጥታ በግልጽ ልትነግረው ወስና " ያው አንተም እኔን ለመስማት ብዙ ዝግጁ አልነበርክም። እንጂ እኔ......" ብላ ዝም አለች አቅም አጣች። ውስጧ ያሰበው " እኔ ታሪኬን ብቻ ሳይሆን ራሴንም ላንተ መስጠት ነው ፍላጎቴ። አፈቅርሀለው" ልትለው ነበረ ግን አፏ ተሳሰረ። ንፍታሌም " እንጂ አንቺ....እ ምን?" ሲላት አምጣ " እንጂ እኔማ አንተን..........." 💢💠🌿 ክፍል 169 🌿💠💢 " እኮ እንጂማ አንቺ ምን?" አለ ንፍታሌም ልቡ ደንግጦ። ሰላም አማጠች ግን አቃታት የውስጧን ለማውጣት ከውስጧ ብዙ ታገለች። " እንጂማ እኔ አንተን...." ብላ ዋናውን በልቧ ለዘወትር የምታመላልሰውን ሀሳብ አውጥታ መናገር አቃታት። ንፍታሌም የምትለውን እየጠበቀ ስልኩ ጮኸ። ስልኩን አንስቶ " ሄሎ" አለ። የቤዛ ወንድም ነበረ። ስልኩን ከጆሮው ላይ እንደያዘ ሄሎ ከሚለው ቃል በቀር ምንም ነገር ሳይናገር ለረጅም ደቂቃዎች በስልክ የሚያወራውን ሰው ብቻ ሲሰማ ቆየ። የንፍታሌም ሀሳቡ ሙሉ በሙሉ ወደ ስልኩ መሆኑን በስልክ ከሚሰማው ነገር ስሜቱ ሲለዋወጥ ይታይ ስለነበረ ኢሄ በመጠኑ ለሰላም እፎይታ ሰጣት። የስልክ ንግግሩን እስኪፈጽም ለንፍታሌም የጀመረችለትን እንዴት እንደምትፈጽምለትና ጭንቀቷን እንዴት እንደምትገላገል ታሰላስል ጀመረች። በዝምታ ሲሰማ ቆይቶ " አዎ እኔም የቤዛን እንዲህ በቀላሉ መግለጽ የምችለው አይደለም" አለ ንፍታሌም። ሰላም ሳይታወቃት የሰማችው ከሀሳቧ አባነናት። ንፍታሌም ላይ አፈጠጠችበት። እርሱ ግን ትኩረቱ ሁሉ ወደ ስልኩ ስለነበረ የስሜቷን መለዋወጥ አልተመለከተም። ለተናገረው ከወዲያ ለተሰጠው ምላሽ " አዎ በጣም እንጂ" የሚል ምላሽ ጨምሮ ሲሰጥ ሰላም ክፉ ክፉ ሀሳቦች ወደ ልቧ መጡ። ትታው የነበረውን የንፍታሌምንና የቤዛን ግንኙነት ውስጧ መልሶ በቅናት ተሳለባት። የቤዛ ወንድም ንፍታሌምን በጣም በሚያሳዝን መልኩ ድንገት ዱብዳ የሆነበትን የእህቱን ዳግም ላያገኛት መኮብለል በእንባ ከነገረው በኋላ እያወራው በሄደ ቁጥር ስሜቱን መቆጣጠር አቅቶት ከ35 ደቂቃዎች ያላነሰ ሲያወራው ቆይቶ ማውራት ሲያቅተው እያለቀሰ ስልኩ ተዘጋ። ንፍታሌም በዝምታ ሲሰማው ቆይቶ ማውራት አቅቶት ስልኩ ሲዘጋ ስልኩን ፊት ለፊቱ አስቀምጦ በማዘን አቀረቀረ። ሰላም ቀና ብላ አየችው። በጣም አዝኖአል። የምትለው ጠፋት። በተፈጠረው ልቧ ባሰበው ነገር ቅናት ቢያነዳትም የልቧን ሰው እርሱን አይዞህ ለማለት ደግሞ አብዝታ ተመኘች። ግን ስለ ምንም ሳታወራው እርሷም ዝምታን መረጠች። የንፍታሌም እናት ያሰቡት ሳይሆን ቀርቶ ያላሰቡት ሆነ። ንፍታሌም በየመሀሉ ሰላም ቀና ብላ ሰርቃ እያየችው በሀሳብ ጭልጥ ብሎ ጠፋ። መከፋቱ ማዘኑ በዝምታ ሊያቆያት አልቻለም። " ንፍታሌም!" አለችው። ድምጿ አጠራሯ የተለየ ነበረ። ንፍታሌም ከሀሳቡ ነቅቶ ቀና ብሎ አያትና " ይቅርታ ቲኒሽ ተረብሼ ነው" ሲላት የበለጠ ያላት ነገር ቀድማ ካሰበችው ጋር ተጨምሮ አወካት። ፍርሀቷ ሁሉ ለቋት " ምንድነው የረበሸህ? ምን ተፈጥሮ ነው?" አለችው። በቤዛ ወንድም አነጋገር በጣም የተከፋው ንፍታሌም ነገሩን ለሰላም መልሶ ለመንገር እንኳን አቅም አቶ " ተይው እስቲ ከባድ ነው" ሲላት እንዳሰበችው ሆኖ እየደበቃት እንደሆነ በማሰብ " አንድ ነገር ልጠይቅህ?" አለችው። አነጋገሯ ቲኒሽ የቁጣ ስሜት ይታይበታል። ንፍታሌም ዓይን ዓይኗን እያየ " ምንድነው ምጠይቂኝ?" አላት። ሰላም ጥቂት ዝም ብላ የምትለውን መላልሳ በውስጧ አውጥታ አውርዳ "የሴት ጓደኛ አለህ? ትዳር ለመያዝ አስበሀል?" ጠየቀችው። ይህ ጥያቄ የብዙ ወዳጆቹ ጥያቄ ሲሆን መልሱን እርሱ እራሱ ስለማያውቀው ምን ብሎ እንደሚነግራት ግራ ገባውና ማሰብ ጀመረ። ምን ብሎ እንደሚመልስላት እያሰበ ሌላ ጥያቄ ውስጡ ተፈጠረ። " ለምንድነው የጠየቀችኝ" ብሎ አሰበና " ምን አይነት ጥያቄ ነው? በምን ምክንያት ጠየቅሽኝ?" መልሶ ጠየቃት። እርሷ ግን ወዲያው ምላሽ ሰጠች " ምናልባትም የረበሸህ ነገር እርሱ ከሆነ.....ማለቴ ከሴት ጓደኛህ ጋር የተፈጠረ ነገር ኖሮ ከተረበሽክ ብዬ ነው" ስትለው " የለም አይደለም" አላት። " አልመለስክልኝም" አለችው። "ምኑን?" አላት። ሰላም " የሴት ጓደኛ አለህ? ወደ ትዳር መች ልትገባ ነው?" አለችው መልሱን ለማወቅ ጓጉታ። "እ.." አለ መልሱን ለማሰብ ጊዜ እየወሰደ። " የሴት ጓደኛ አለኝ አዎ። ትዳር እንግዲህ እንደ እግዚ...." ሳይጨርስ " የሴት ጓደኛ አለህ?" አለች ማመን አቅቷት ተስፋም ቆርጣ። ሰላም በትክክልም ንፍታሌም ከቤዛ ጋር የፍቅር ግንኙነት ይኖረዋል ብላ እርግጠኛ ሆነች። ለጥያቄዋ በሰጣት ምላሽም ሰላም ተስፋዋ ጨለመባት። ንፍታሌምን ካላገኘችው ሕይወቷ ፍጹም ባዶና ደስታ የተለየው የጨለማ ዘመን ከፊቷ ተገልጦ ታያት። መልሳ ደግሞ እርሱን መተው ያለርሱ መኖር እንደማትችል ሰላም አሰበችና በሳቧና የርሱ ምላሽ ሲጋጭባት ሳይታወቃት ተከፍታ " ጓደኛህ አዚሁ የሮቤ ልጅ ነች? ታዲያ ለምን አታስተዋውቀኝም?" አለችው። ንፍታሌም " ምን ችግር አለው ካገጠጠመን አስተዋውቅሻለው። በብዛት እኔም አልፎ አልፎ ነው የማገኛቸው። ከብዙዎቹ ጋር የማይረሳ ትዝታ አለን። የማይረሳ የአገልግሎት ዘመን አብረን አሳልፈናል። ግን ሁሉም አሁን በየምክንያቱ በሕይወት አጋጣሚዎች ወደተለያየ ስፍራ ተበታትነን ቀረን። ብዙዎቹን በአካል አላገኛቸውም" ሲላት ሰላም አንዳች ልዩ የደስታ ስሜት ከፊቷ ታየ። ሀሳቡ እርሷ እንደተረዳችው ሳይሆን የንፍታሌም ምላሹ አብረውት ስላደጉ ሴት ጓደኞቹ ስለ አብሮአደጎቹ እንደሚላት ስታውቅ በረጅሙ ተንፍሳ " የኔ ጥያቄ እንደዛ አይደለም። የሴት ጓደኛ ያልኩ ለነገ የትዳር ሕይወትህ ያጨሀት ማለቴ ነው" ስትለው ንፍታሌም ቀድሞ እንዳልተረዳት ሁሉ ፈገግ ብሎ አያት። ሰላም ሌላ ደስታ ውስጧን ሞላው። ሁለቱም ዓይን ለዓይን ተገጣጠሙ። እርሱ ቀድሟት አቀረቀረ። መልሱን እየጠበቀች ድጋሚ ስልኩ የጥሪ ድምጽ አሰማ። ቢኒያም ነበረ። የማንሻ ምልክቱን ተጭኖ " ሄሎ ዶ/ር ቢኒያም!" አለው። ቢኒያም ድምጹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ " ኤውልህ አክብሮቱ ይቆየኝ።እኔ አሁን ገዳም ነኝ። መምጣት ከቻልክ በፍጥነት ብትመጣ ብዬ ነው የደወልኩልህ። ቶሎ ና።" አለው። " እንዴ ምን ሆነሀል? እንዴት እንደዛ ተቻኩለህ ወተህ ገዳም ሄድክ? ደግሞ እንዲህ አጣድፈህ የምትጠራኝ በምን ምክንያት ነው? ምን ገጥሞህ ነው? ምንድነው?" አለው ንፍታሌም። ቢኒያም ማብራሪያ መስጠት አልፈለገም " አሁን

10:30 አካባቢ ከሙሲቾ ተራራ ግርጌ ሲቃረቡ ሁለቱም በተመሳሳይ የፍርሀት ስሜት ልባቸው ራደ። ያን ተቋቁመው ወደ ፊት አንድ እርምጃ እንኳን መራመድ አልቻሉም። ባሉበት ቆሙ። አንድ ልዩ ስፍራ ላይ መቃረባቸውን ግን ነፍሳቸው አውቃለች። ከርቀት በዘንባባ የተከበበ ከፍ ያለ ስፍራ አዩ። ሁለቱም በፈገግታ ተያዩና ወደ ስፍራው ተጠቋቆሙ። " እንሂድ እንሂድ " ተባብለው በፍርሀት ወደ ፊት ዳግም ገሰገሱ። ከፊታቸው የሚያዩትን ስፍራ ውበቱን ታላቅ ጸሐፊ ቀንዱን አንስቶ ምን ቃላትን ቢመርጥ በቃላት የዚያን ስፍራ ውበት መግለጽ አይቻለውም። ሁለቱም በሚያዩት አንዳች ልዩ ደስታ ተሰማቸው። ስሙር በቻይና ያን የተንጣለለ ውብ የምርምር ተቋም ጊቢ ዛሬ ካየው ፈጽሞ እንደማይወዳደር አሰበ። አሌክሳንደርም እስከዛሬ ካያቸው ከጎበኛቸው ሁሉ ይህ ልዩ ስሜት ፈጠረበትና ከኪሱ ስልኩን አውጥቶ ሰዓት ሲያይ 11:05 ሆኗል። የስልኩን መተግበሪያዎች መምረጥ ጀመረ። የፎቶ ማንሻውን ከፍቶት የስልኩን የፊት ሰሌዳ ሲያይ ጨለመበት። ከስልኩ መስሎት ዘግቶ ከፈተው ያው ነው። ደንግጦ ለስሙር ነገረው። የስሙርንም ሞከሩ ያው ነው። የስልኩ ሰሌዳ ላይ አፈጠጡ። በጨለመው ሰሌዳ አፍጠው በጨለማው ውስጥ አንዳች እንዲህ ነው የማይባል የሚያስፈራ ነገር ወደነርሱ ሲመጣ አዩት።ጊዜ አላጠፉም። ስልኩን ዘግተው አዩ ምንም የለም። በስልካቸው ያዩትን አልተጠራጠሩም አመኑ። በፍጥነት በመጡበት እግሬ አውጪኝ አሉ። ሲሄዱ ሰባት ሰዓት ከውሱን ደቂቃዎች የተጓዙትን መንገድ ቁልቁለቱን ከፍርሀት ጋር ሆኖባቸው ሳያውቁት አምስት ሰዓት ገደማ ብቻ ተጓዙት። በተለይም እየጨለመ በመምጣቱ ከደኑ ውስጥ አደጋ ጣዮች ያገኙናል በሚል ተፋጥነው ወደ ቀያቸው ገሰገሱ። በላብ ተነክረው የስሙር እናትና በቅርበት ያሉ ጎረቤቶች ተጨንቀው ከደጅ ቆመው ስሙርና አሌክሳንደር ከምሽቱ 4:10 ሰዓት ሲሆን እቤት ደረሱ። የስሙር እናት ልጃቸው ሲመጣ የሚሉት ጠፍቷቸው እንባቸውን እየጠራረጉ የጎረቤት ሰዎች ብዙ ብዙ ሲሏቸው ጥለዋቸው ገቡ። ስሙር የዋሉበትን ለጠየቁት መልሶ ወደ ቤት ቀድሞ ሲገባ አሌክሳንደር ተከትሎት ገባ። እንደገቡ ከመቀመጫ ላይ ቁጭ ብለው በረጅሙ ተነፈሱ። " ምነው ልጄ ምነው?" አሉት እናቱ ዓይናቸውን እየጠራረጉ። " ከሙሲቾ ተራራ ሄደንኮ ነው" አላቸው። ተቆጡ በጣም። " ዘንዶው ቢውጣችሁስ? አልያም ንቡ ነድፎ ከዚያ ቢያስቀራችሁስ?" አሉት በቁጣ። " ቆይ አባዬስ?" ጠየቃቸው። " እንዴት ዋላችሁ?" እያሉ ገቡ አባቱ። መሪጌታ ስሙርና አሌክሳንደር ከጫካው ውስጥ ሲያልፏቸው እርሳቸው ሕይወቱ ከተለወጠች ብቸኛ ሰው ጋር በጨለማው ውስጥ ከደኑ ውስጥ ነበሩ። ሲገቡ ተነስተው ተቀበሏቸውና እራት ቀርቦ በልተው ተጨዋውተው ሁሉም ወደየ መኝታቸው አቀኑ። ስሙር ከመጣበት ቀን ጀምሮ አንድ ነገር አስተውሏል። አባቱ ሌሊት ተነስተው ወዴት እንደሚሄዱ ባያውቅም ከወጡ እንደማይመለሱ አረጋግጧል። የሚሄዱበትን ለማወቅ ይቺን ሌሊት ሊጠቀማት ወስኖ ወደ መኝታው አቀና። ከተኛበት ሰዓት ጀምሮ በየሰዓቱ እየተነሳ አባቱን ሲከታተላቸው ቆየ። ሌሊት 6:00

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠 ከክፍል 164 የቀጠለ 💠💢 "ተሸነፍኩ ስላሸነፈችኝ ምድርና ስለ ጠቢባኗ ዘመርኩ ተማረኩ" አለው በቋንቋው አቀላጥፎ እየነገረው። ስሙር ፍጹም አመነው። አሌክሳንደር "ያን እለት ነው ያንተ አባት ልጃቸው ለመሆንና የዚህች ሀገር ኗሪ ለመሆን የወሰንኩት። ከሁሉ በላይ ደግሞ የነዚያን ጠቢባን ሃይማኖተኞች ሃይማኖት ተቀብዬ አምላካቸውን ላመልክ ወሰንኩ። ከእንግዲህ ወደ ተሸነፈ ከንቱ መሰሎቼ ጥበብ አልመለስም። አባትህ ያስተምሩኛል ኢትዮጵያዊና ክርስቲያን ሆኜ እኖራለው" አለው በእንግሊዘኛ። ስሙር እየሰማው ሳያውቅ አለቀሰ። ከተቀመጠበት ተነስቶ አሌክሳንደርን አቅፎት ባንተ መንገድ አብረን እንጓዛለን። እኔም እንዳንተ ሀሳብህ ሀሳቤ ነው። መሪጌታ ለኔም ላንተም አባት ናቸው" አለው ለአሌክሳንደር። " አመሰግናለው " አለ አሌክሳንደር። ተቃቅፈው እንዳሉ አሌክሳንደር ከርቀት ባሪያውን አየው። " ያውና ያ ገደልኩት ብዬ የጣልኩት ሰው" ሲለው ስሙር ዞረ። ወዲያው ባሪያው ከእይታ ሲሰወርባቸው ሁለቱም ወደ ደኑ ባሪያውን ፍለጋ አቀኑ። 💢💠🌿 ክፍል 168 🌿💠💢 ሁለቱም ተከታትለው አሌክሳንደር ባሪያውን ዝክረ ጻድቅን ባየበት አቅጣጫ ተከታትለው ሮጡ። ወዲያው ወደ ደኑ መግቢያ ገቡ። በዚያ ፍጥነት ይሰወርብናል ብለው ባያስቡም ከወዴት እንደገባ አጡት። ለደቂቃዎች ተዘዋውረው ፈለጉት ዙሪያ ገባቸውን ተዘዋውረው ቃኙት ያን ሰው ግን ደግመው ሊያገኙት አልቻሉም። ወዲያው ስሙር አሌክሳንደር አስመስሎበት እንጂ ምንም አይነት ሰው እንዳላየ እርግጠኛ በመሆን በውስጡ ያሰበውን አውጥቶ ነገረው። አሌክሳንደር ግን ለስሙር በትክክል ያንን ሰው በትክክል እንዳየው እርግጠኛ ሆኖ አረጋገጠለት። ስሙር አካባቢውን ደኑ ውስጥ ዓይኖቹን እያንከራተተ ሌላ ጥያቄ ተከሰተበት። " ቆይ ለምንድነው ግን ይህ ሰው ወደዚህ ስፍራ የመጣው? ነው ኢሄ ሰው በዚህ አካባቢ የቆየ ነበረ? አዲስ ከሆነ እስከ ዛሬስ የት ነው የቆየው? በትክክል እውነት አይተኸው ደግሞ ከሆነ ለምን ከኛ ሊሸሽ ፈለገ?" በእንግሊዘኛ ነጩን ጠየቀው። ጥያቄውን ሲሰማ እራሱ አሌክሳንደር ያላሰበው መሆኑ በራሱ እንዲገረም አደረገው። ከዚህ በቀር ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ምንም ምክንያት አጣ። ሁለቱም የዝክረ ጻድቅ የባሪያው ነገር ግራ ገባቸው። የበለጠ ለስሙር የሰማው ታሪክና ያየው ነገር የበለጠ ግራ አጋባው። ጨምሮ ፈረንጁን ጠየቀው " እነዚያ አየዋቸው ያልከው ነጫጭ ልብስ የለበሱትስ እነማን ናቸው? ከአባቴና ከዚያ ሰው ጋር ሆነህ ያየሀቸው ወደነርሱ የመጡት በማን ምክንያት ይሆናል? በአባቴ ወይስ አሁን በተሰወረብን ሰው ምክንያት?" ጠየቀው። አሌክሳንደር ከዝምታ በቀር ለዚህም መልስ አጣ። ስሙር ሌላ ጥያቄ ጨመረለት " ነጫጭ የለበሱት ሰዎች ወዴት ነው የሄዱት ነው ያልከኝ?" አለው። አሌክሳንደር " እነዚያ ልዩ ኃይል የተላበሱ ሞት ከፊታቸው ሊቆም የማይቻለው በዓይኔ በብረቱ እያየዋቸው ወደዚ ወደ ምሥጢራዊው ተራራ ነው የሄዱት ከዓይኔ እስኪሰወሩ ድረስ ሳያቸው ነበረ። እነርሱ የተለዩ ናቸው። እርምጃቸው ግርማ ሞገሳቸው ሁሉኮ ነው የሚለየው። እነርሱን በቃል መግለጽ አይቻልም። ልክ እነደነርሱ ሁላ መንደራቸውም የማትደፈር ቅጥር በልዩ ኃይል የተከበበች የጥበብ መንደር ነች" አለ አሌክሳንደር። ስሙር በፈረንጁ የስሜት አገላለጽ ከፊቱ ያለችውን የምሥጢር ተራራ ለማወቅ የበለጠ ጓጓ ልቡ ተነሳሳ። " አሌክሳንደር!" አለው ስሙር ያሰበውን ሊያማክረው። ወደርሱ ዞሮ ሲያየው " ትክክለኛ ያ የምሥጢር ስፍራ ከዚህ በቅርበት ላይ የሚታየው ተራራ ነው እርግጠኛ ነህ?" ጠየቀው ጠቋሚ ጣቱን ወደ ሙሲቾ ተራራ እየጠቆመ። " በትክክል እርሱ ነው። እነዚያ በረድ የመሰለ ነጭ ለባሾች ያቀኑት በርሱ አቅጣጫ ነው። የስራ ባልደረቦቼም ተልዕኮአቸውን ለመፈጸም ለቀናት ቆይተው ጥበባቸው በጥበብ ተሽሮባቸው አፍረው በከንቱ ደክመው የተመለሱት ከዚያ ተራራ ነው። እነርሱ ከተራራው ግርጌ እንጂ ያውም ከተራራው እንዳልደረሱ ሲመለሱ ከነበርኩበት ሳያዩኝ ተደብቄ ሲያወሩ ሰምቻቸዋለው። አዎ ያ ሶስት ቅርጾች ያሏቸው ተራሮች ያ ምሥጢራዊ ልዩ ኃይል ያለው ቦታ ነው" አለው። በቃ ቀስ እያለ የስሙር ልቡ በቆመበት እግር አውጥቶ ወደዚያ ተራራ ሲሮጥ ተሰማው። " ና እኔና አንተ ወደዚያ ተራራ እንሂድ። በዚያ ተራራ ከሚኖሩት እነዚያ ነጭ ልብስ ከሚለብሱት መንደር እንድረስ። ና እኔና አንተ ወደዚያ መንደር ጉዞ እንጀምር!" አለውና አሌክሳንደርም ተስማምቶ ወደ ሙሲቾ ተራራ በአንድ ሀሳብ አንድ ልብ ሆነው ጉዞ ጀመሩ። ከአዋሽ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን አቅራቢያ ወደ ተራራው ጉዞ ሲጀምሩ ከረፋዱ 4 ሰዓት አካባቢ ነው። ሁለቱም ከፊታቸው የአካባቢው ሰው እንኳ ታሪኩን በሰማው ከመተረክ በቀር ብዙው ሰው ወዳልሄደበት ምሥጢራዊ ተራራ የመሪጌታ ልጅና አሌክሳንደር ተያይዘው ካሰቡት ሊደርሱ ከፊታቸው ወዳለ ጥቅጥቅ ያለ ደን አሻግረው ምሥጢራዊውን ተራራ እያዩ ጉዞ ጀመሩ። እንደ ቀላል ተስማምተው የጀመሩት መንገድ እንዳሰቡት አልጋ በአልጋ አልሆነላቸውም። በረጃጅም ዛፎች የተሞላው ለዓይን የሚማርከው ደን መልክአ ምድሩ ተራራማ በመሆኑ ውበቱ ከድካም ሊታደጋቸው አልቻለም። ሁለቱም በጉዞአቸው ውስጥ እግረ መንገዳቸውን ዝክረ ጻድቅን ከመፈለግ አልቧዘኑም ነበረ። ሁለቱም ገና እሩቅ ሳይጓዙ ነበረ ከላይ የለበሱትን ጃኬታቸውን አውልቀው በጃቸው የያዙት። ግንባራቸው ላይ ላብ ችፍ ብሏል። ተራራውን በቀላሉ እንደፈለጉት ሊወጡት አልቻሉም በተራመዱ ወደ ፊት በተጠጉ ቁጥር ተራራው ድካሙ እየጨመረ መጣ። ድካሙ መመለስ ቢያስመኛቸውም ከተራራው እልፍኝ የተሸሸገው ሥውር ምሥጢር ደግሞ አጓጉቶ ብርታት ሰጣቸውና ወደ ፊት ገሰገሱ። ከድካማቸው የተነሳ ማውራት አቁመዋል። የየራሳቸውን ሀሳብ በውስጣቸው እያመላለሱ ፊትና ኋላ ሆነው ተከታትለው ይሄዳሉ። ደኑ ወደ ተራራው በወጡ ቁጥር ጸጥታው እየጨመረ እየጨመረ ነው የሚሄደው። ኢሄ በራሱ በጣም አስፈሪ ነበረ። አቅጣጫው እንጂ ተራራው ከዓይን እይታ ውጪ ከሆነባቸው ሰዓታት አልፈዋል። በጽናት ወደ ፊት ድካሙን ዋጥ አድርገው እየሄዱ ነው። በግምት ለ አራት ሰዓታት ገደማ ያክል ተጉዘው በጣም ደክሞአቸው ከደኑ ውስጥ ሁለቱም ጥቂት ሊያርፉ እየፈለጉ ወደ ፊት ሲጓዙ ስምንት ሰዓት አካባቢ ላይ አካባቢውንና መላውን የሚያናውጽ ታላቅ አስፈሪ ድምጽ ተሰማ።ሁለቱም ድምጹን ሲሰሙ ባሉበት ቀጥ ብለው ቆሙ። ፈሩ በጣም ደነገጡ። የሰሙት ድምጽ የአንበሳ መሆኑን ሁለቱም ተረድተዋል። ድምጹን የሰሙት ከቅርባቸው ቢመስልም ከርቀት እንደሆነም ልባቸው አውቋል። አውቀውም ግን ማመን አልፈለጉም። ፍርሀት ናጣቸው። ዓይን ለዓይን ተፋጠው ቀሩ። ያን ድምጽ ሰምተው ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ጆሮአቸው እንደቆመ ድምጽ ሲፈልግ የደኑ ጸጥታ ወደ ቀደመ ፍጹም ጸጥታው ተመለሰ። ድንጋጤው ድካማቸውን ሁሉ አራቀላቸው። " እንሂድ " አለው ስሙር። ወደ ፊት አቀኑ። አንደቀድሞው ያለ ፍርሀት ባይሆንም ኮሽ ባለ ሁሉ ድንግጥ እያሉ የፊታቸውን እያሰቡ ወደ ፊት ተጓዙ። ሁለቱም ዳግም ድካም ይሰማቸው ጀመረ። ደኑን አቋርጠው መገስገሱን ተያያዙት። አንድ ከብት የጠፋበት ሰው አጊኝተው የሚሄዱበትን አቅጣጫ ጠይቀው አረጋግጠው አለፉት።

አድርጌ የምናፍቀውን ላገኝ ወጣው። ከእንግዲህ በዓለም ልኖር ነፍሴ እንቢ አለች መድኃኒቷን ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ነፍሴ እርሱን ናፍቃ ከጥላቻ ከኃጢአት መንደር ወደ አፍአ ምድር ወደ ጸሎት ዋሻ ልገሰግስ እግሮቼን እንደቦኅር እግሮች እንዲጸኑ ከሕይወት መንገድ ጉዞ አስጀመርኳቸው። ከእንግዲህ ስበድለው የኖርኩትን በእንባ እየታጠብኩ ይቅርታን የምለምንበት በጣም ቲኒሽ ዘመን ስለቀረችኝ ያን ላደርግ ወጥቻለው። እንዳታለቅሱ እንዳታዝኑ እኔ የምሄደው ወደ ሕይወት ነው። ይልቁኑ እርሱን ደስ እንዳሰኙት በጽናት እንደነርሱ ሥጋዬንና የዓለምን ምኞት ሁሉ ሰቅዬ በድል ፈተናውን መከራውን አልፌ ለክብር እንድበቃ በአምላኬ ፊት ጸልዩልኝ። እማዬም ከእንግዲህ የምጽአት የሞት ቀን እርሷ እንደሌባ በድንገት የምትሆን ናትና ለጉዞ ራስሽን አሰናጂ ከእንግዲህ ሌላው ሁሉ ከንቱ ስለ ሆነ ስለማያልፈው ራስሽን አዘጋጂ። አንተም ተወዳጁ ወንድሜ ሆይ ባለህበት በአሁኑ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ። እንደኔ እንደትናንቱ በዋዛ ፈዛዛ በማይረባው የዓለም ነገር ዘመንህ አይለፍ። መኖር ጀምር። ባላችሁበት ስለኔ ጸልዩ ሰላመ እግዚአብሔር ለናንተ ይብዛላችሁ። ወደ ደጋጎቹ በአት ሳይገባኝ ሕይወትን ፍለጋ ወደ ጽድቅ መንደር ሄጃለው። ስለኔ አትጨነቁ ከእንግዲህ ስለርሱ እናንተንና ዓለሙን ሁሉ ትቼ ሄጃለው" እያቆራረጠ ሳግ እያነቀው በእንባ እየታጠበ አንብቦ ሲጨረስ እናቱ መልስ ሳይሰጡት ከአጠገቡ ተነስተው ወጡ። ተደነቀ " እቴቴ! እቴትዬ!" ተጣራ አልቆሙም ካለበት ክፍል ጥለውት ሄዱ። እርሱም ሊከተላቸው ተነሳና ወደ እህቱ ፎቶ ግራፍ ተራምዶ ካለበት አውርዶ አቅፎ ስሞ መልሶ አስቀምጦ " እኔስ ከእንግዲህ ወዴት ነኝ?" አለ ወደ እህቱ ፎቶ ግራፍ ዞሮ እንዳለ። መልስ አላገኘም። አንድ ነገር ወደ ልቡ መጣ። " እኔም እንዳንቺ ልጨክን? ሚጣዬ እኔም በሄድሽበት መንገድ ልከተልሽ?" አለና ፈዞ ሲያያት ቆይቶ " አምላኬ ሆይ አንተ ምራኝ" ብሎ ከክፍሉ ወጣ።....... 💠 ይቀጥላል 💠 💢💠ታኅሳስ 1 2016 ዓ.ም ባሌ ጎባ 💠💢

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠 ከክፍል 162 የቀጠለ 💠💢 አብረው በእንባ ቆዩና " ለመንግሥቱ ያብቃሽ ጽናቱን ያድልሽ ሂጂ በዚህ መንገድ የሄዱ ሁሉ ከሕይወት ደርሰዋል። በጸሎት በርቺ" አላት። " ግንኮ አሁን ገና 9:40 ነው" አላት። " አንተን መምህሬን ልሰናበት ነው በዚህ ሰዓት ወዳንተ ክፍል የመጣሁት ሲነጋጋ ማንም ሳይነሳ ነው የምሄደው" ብላው ተሰነባብተው ወደክፍሏ ተመለሰች። ንፍታሌም ቁጭ ብሎ አነጋ። 11:30 ሲሆን በሩ ተንኳኳ።የቤዛ ወንድም ነው። ቀስቅሶት ተነስቶ ጸሎት አድርሶ በራሳቸው መኪና ሊሄድ ሹፌሩ መኪናዋን አንስቶ ንፍታሌም ምሥጢሩን በልቡ ይዞ የቤዛን እናት ተሰናብቶ ወደ መኪናዋ ገባና የቤዛን ወንድም ቻው ብሎት ወጣ። መኪናዋ ከጊቢ እስክትወጣ ከበረንዳ  ቆሞ አይቶ መኪናዋ ስትወጣ የቤዛ ወንድም ወደ ቤዛ ክፍል ንፍታሌም ሊሄድ ሲነሳ ሲጠራት ዝም ማለቷ አኩርፋ መስሎት ወደ ክፍሏ ገባ። የለችም ደነገጠ ከመኝታዋ ላይ ወረቀት አየና አንስቶ ገልጦ ማንበብ ጀመረ። 💢💠🌿 ክፍል 167 🌿💠💢 የቤዛ ወንድም ቆሞ ባለበት የጻፈችውን አንብቦ እዚያው መኝታዋ ላይ ስሜቱን መቆጣጠር አቅቶት ቁጭ አለ። በተቀመጠበት አቀርቅሮ ያነበበውን ደግሞ በኅሊናው ደጋገመውና አስታወሰ።ቤዛን ዳግመኛ እንደማያገኛት ታናሽ እህቱን ከእንግዲህ እንደማያያት ከዚህ በላይ ደግሞ ያለችበት አድራሻዋን ማወቅና ድምጿን እንኳ መልሶ እንደማይሰማው ሁሉ ሲያስብ ቁጭ ብሎ ባለበት ሳያውቅ እንባው ጠብ ጠብ አለ። እንባውን ሲያፈስ ቆይቶ ካቀረቀረበት ቀና ሲል ከእህቱ ፎቶግራፍ ጋር ተፋጠጠ። ከንደኛው ፎቶግራፍ ከእውቅ ባለስልጣን እጅ በከፍተኛ የትምህርት ውጤት ሽልማት ስትቀበል ሲሆን አንደኛው ደግሞ አባቷ ከመሞታቸው በፊት አብረው የተነሱት ነበረ። ሁለቱንም በየተራ እያፈራረቀ ሲያይ ቆይቶ ስለ ሁለቱም ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። የቤዛ ወንድም ለእህቱ ልክ እንደ እናት ነው። ማንም የማያውቀውን ምሥጢሯን ሳይቀር ነው የምታዋየው። ወንድሟ ያን ሲያስታውስ ዛሬ ግን ከማንም እኩል ላደረገችው እንግዳ ሆኖ ምንም ሳትለው መልሶ ላያገኛት መሄዷን ሲያስብ ሆድ ባሰውና ለሞተው አባቱ ደግሞም ጥላቸው ለሄደች ለራቀች እህቱ ከክፍሏ ውስጥ ከመኝታዋ ተቀምጦ ለረጅም ደቂቃዎች በእንባ ሲታጠብ ቆየ። ከቆይታ በኋላ ነው እናቱ ከክፍሉ ሲያጡት ልጃቸውን ቤዛን ለመጠየቅ ወደርሷ ክፍል መጡ። "ሚጡዬ! ሚጣ! ኧረ ሚጣ!" እየተጣሩ ወደ ክፍሉ ተቃረቡ። ምላሽ አላገኙም። ደርሰው የክፍሉን በር ከፍተው ሲገቡ ልጃቸው ቁጭ ብሎ ሲያለቅስ አገኙት። በጣም ደነገጡ። እናቱ እንደገቡ ተደናግጦ ከዓይኖቹ እንባን ጠራርጎ " እቴትዬ ጊቢ! ምነው በጠዋት ተነሳሽ?" ጠየቃቸው። ሄደው አጠገቡ ከቤዛ መኝታ ላይ ተቀምጠው እጃቸውን ትከሻው ላይ አሳርፈው " የናንተ የልጆቼ ፊት ላይ እንባ ማየትን ያክል ልቤን የሚያውከው ነገር በዚህ ምድር የለም። የምኖረው በናንተ ነው። አልቅሳችሁ ማየት ተክዛችሁ መመልከት አልፈልግም። ዛሬ ያ ሆነ። አንተ ልጄ በዚህ በማለዳ ከእህት ክፍል ሆነህ ተደብቀህ ስታለቅስ እናትህ መጣሁ። ልጄ ምን ሆነሀል? የኔ የጤናዬ ጉዳይ አሳስቦህ ነው? ነው የእህትህ ተጎሳቁላ መምጣት? ምንድነው ንገረኝ" አሉት። "እቴቴ እንደ ዛሬ ቀን ጨልሞብኝ አያውቅም። ኢሄ ስሜት ባለፈው ለቀናት ቤዛን ያጣናት ጊዜ እንኳን ተሰምቶኝ አያውቅም። ዛሬ እኔን እንዲህ ተሰማኝ እኔ ከእናትና እህቴ ተለይቼ መኖር እንደማልችል። ያንን ሳስብ የዓይኖቼ ሸለቆዎች ደመናን አዘሉ በመከፋቴም እንባን አዘነቡ" አለ ያደራረቀውን ፊቱን በአዲስ እንባ እያራሰ። የበለጠ አንጀታቸው ተላወሰ። " ኢዬን አምላክም አያድርገው! እኔም ያለናንተ እንደማልኖር ስለሚያውቅ ፈጣሪዬ ኢሄንን በኔ አያደርግም። አንለያይም እኔንም እህትህንም አታጣንም" ሲሉት የእናቱን ልጆቻቸው ጥለዋቸው እንደማይሄዱ እርግጠኛ ሆነው ማውራት አይቶ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ይህን ያህል መከፋቱ እርሳቸውንም ቢያስከፋቸውም ጠንከር ብለው ልጃቸውን ለማጽናናት ራሱን እያሻሹት ወደ ራሳቸው ይዘውት አቅፈው " የኔ ልጅ እርግጠኛ ሁን ያሰብከው አይሆንም። አንተና እህትህ ገና ጦራችሁኝ ብዙ ዘመን ኖሬ ነው የምለያችሁ። ያኔም ቢሆን ሚጣዬ አለችልህ" አሉት ጸጉሩን እያሻሹት። የበለጠ ንግግራቸው ሆድ እያስባሰው ለቅሶው እየባሰ እየጨመረ ሲመጣ " እንዴ ምንድነው አሁን በሰላም ሀገር እንዲህ የሚያደርግህ?" አሉት። በውስጡ ልንገር አልናገር እያለ ሲያመነታ ቆይቶ ንግግራቸው ሀዘኑን እያባሰው ሄዶ ድንገት የውስጡ ምሥጢር ከስሜቱ ጋር ገንፍሎ ወጣ። " ከእንግዲህ በዚህ ቤት ስለ ልጆቿ የምትሳሳ አንዲት እና የምትወደው ወንድ ልጇ ብቻ ስለሚወዷት ልባቸው ሁሌ እያሰቡ እያነቡ ይኖራሉ። ያ ስለሆነ።ያቺ የዚህ ቤት ድምቀት ከእንግዲህ ፈክታ ስለማትታይ" አለ። እናቱ " ለምን ሲባል? ሚጣዬ አባቷ ያለ ምክንያት ቤዛ ያላት መስሎሀል? ምንም እንኳ ሰውነቷ ጎስቁሎ ወደኛ ብትመለስም እርሷ እኔና አንተ እስካለን ውስጧ ደስተኛ ነው። ሥጋ ባዳ ሆኖ ፊቷ በችግር ቢጎሰቁልም ሰውነቷ ቢከሳም እርሷ በውስጧ ደስታ እንደቀድሞው ሁለንተናዋ እንዲመለስ አልጠራጠርም። እርሷ ትፈካለች!" አሉት። " እርሷ ሳትኖር ኢሄ መሆን አይችልም። ከእንግዲህ እኛ ያለንበት እርሷ አውቃ ትኖራለች እንጂ ያለችበትን ላናውቅ ርቃ ሸሽታ ሄዳለች እቴቴ" አለ። እናቱ የሚለው በትከክል ገባቸው። " ቤዛ ሄደች ነው የምትለው?" ጠየቁት። እርሱ ያነባል እርሳቸው ግን ሲጠይቁት ከመደናገጥ ጋር አግርሞት ይታይባቸው ነበረ። ቀና ብሎ አይቷቸው " አዎ እርሷ ከእንግዲህ እንደማናገኛት እንዳንፈልጋትም አሳስባ ወደ ምትናፍቀው ወደ ወደደችው ሄዳለች" ብሎ የጻፈችውን መልዕክት ያዘለ ወረቀት አሳያቸው። እናቱ እንደፈራው አልሆኑም። በዝምታ ቆይተው ዓይን ዓይኑን እያዩት " ቤዛ ይህን እንደምታደርግ እርግጠኛ ነበርኩ በዚህ ፍጥነት ግን ትሄዳለች ብዬ አላሰብኩም። ልጄ እናት ልትሆነኝ ቀደመች። ሁሉን ትታ የፈጣሪዋ ለመሆን ቆረጠች። ዓለምን ናቀች እራሷን ካደች። አዎ ዛሬ አንጀቴን አስሬ ልቤን አጠነክራለው አላነባም የምወዳት ልጄ ወጣትነቷን ውበቷን እወቀቷን ሁለንተናዋን ቆርጣ ስትተው በንግግሯ ውስጥ አይቼባታለው። ትሂድ አዎ ያን መንገድ የሚጓዙት ጠነሰካሮች ናቸው። ከእንግዲህ ልመናዬ እርሷን እንድመስል እርዳኝ። በፈተና አጽናት የሚል ነው"ሲሉት ማመን አቃተው። " ልጄ ለመሆኑ የጻፈችው ምን ይላል? የምትሄድበትንም አድራሻ አላስቀመጠችም?" አሉት ወደርሱ እንዲያነብላቸው ዓይን ዓይኑን እያዩ። ጉሮሮውን ጠራርጎ ሊያነብላቸው ሳለና ወረቀቱን አስተካክሎ ጀመረ። " የምጽፈው አጠረኝ ለመልዕክት ብቻ ይቺን ከተብኩ" ይላል ርዕሱ። " ለሚወዱት ሰው መለየትን በቃል መግለጽ አይደለም አብሮ መኖርን እንኳን ስውቦ የውስጥን ሁሉ ለመግለጽ ቃል ያጥራል። እማዬና ወዱ ወንድሜ አንድም ቀን ኢሄ በሕይወቴ ይፈጠራል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበረ። እኔ ከናንተ እለያለው ብዬ። ለካ ፍቅር የሚወዱትን ስለወደዱት መተው ነው። ዛሬ ያ ሆነ። በጣም የምወዳችሁን እናንተን በመስቀል ላይ ስለ እኔና ስለ ዓለም ሁሉ ደሙን ስላፈሰሰው በፍጹም ፍቅር ስለወደደን አምላክ የሚወደኝ ቢኖር እራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ እንዲል የበረቱትን አብነት

ጥያቄ ምላሽ ስጠው። አትታወክ እረፍት እንድታገኝ ወደ እረፍት ሂድ። ንሰሐ ግባ" ይላል ወረቀቱ። ግራ ገባኝ። ከታች ያለውን ሳነብ እንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ። እያለቀስኩ ዳኛው ገቡና በችሎቱ ያለው ሁሉ ሲነሳ ተነስቼ ችሎቱ ጀመረ። በዚያ ችሎት እውነት ስለፍቅር ዋጋ ስትሰጥ ተመለከትኩ። ያለ ጥፋታቸው ታላቁ ሰው በተሰበሰበው ሁሉ ፊት አንገታቸውን ደፍተው አየው። ያለ ስማቸው ስም ሲሰጣቸው ሳያስተባብሉ አሜን ብለው በርሳቸው ላይ የሚባለውን በዝምታ ሲቀበሉ ተመለከትኩ።እንዳቀረቀሩ ቀና ሲሉ ከሕዝብ መሀል ዓይናቸው የሚያርፈው እኔ በደለኛው ላይ ነበረ። አቃተኝ ራሴን አዛው ላጋልጥ ነጻ ላወጣቸው ፈለኩ ግን ከደረሰኝ ወረቀት ላይ የተጻፈልኝ አደራ ያዘኝ። እያየዋቸው እያዩኝ በዚያ ችሎት እንደወንጀለኛ ፍርድ ተፈረደባቸውና ፖሊሶች ችሎቱ አልቆ ይዘዋቸው ሄዱ። ካለሁበት ቁጭ ብዬ እያነባው ያቺ ተበዳይ በኔ ነገዋን የተነጠቀች ወጣት ከተቀመጥኩበት እያለቀስኩ አይታኝ ወጣች። በቃ ከዚያን እለት ጀምሮ ውስጤ እረፍት አጣ። ለታሰሩት ሰው ምግብ የሚያመላልስ አንድ ልጅ አደረኩላቸው። እርሳቸው ግን መልሰው የሚልኩልኝ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ለጥያቄዬ ምላሽ እየሆነ መጣ። ፍቅርን ያሳዩኝ ሰው ወደራሳቸው ሳቡኝ ምክራቸው ለወጠኝ። እረፍት ፍለጋ ወደ ገዳም ከማላውቅበት ሄድኩ። የበለጠ እረፍት የሚገኝበት ሃይማኖት ኢሄ እንደሆነ በመሄዴ በገጠሙኝ ነገሮች ተረዳው" ብሎ የነበረውን ነገር ሁሉ አንድ በአንድ ለእናቱ ነገራቸው። " ከዚያ ጊዜ በኋላ መጠነኛ የውስጥ ሰላም ቢኖረኝም ስለበደልኳት ሕይወቷን ስላመሳቀልኩባት ልጅ ማሰቤ መጨነቄ ግን ቀጠለ። በርሷ ላይ ያን ሳደርግ ትልቅ ድርሻ የነበራት የርሷው ጓደኛ በገንዘብ ተታላ በከፈልኳት ጓደኛዋን ለኔ አሳልፋ ሰታኝ በዚ ምክንያት የሆነውን ደግሞም እኚያ ንጹ ሰው በኛ ምክንያት ወይኒ ቤት መውረዳቸውን ሰምታ ራሷን እንዳጠፋች ሰማው። የበለጠ ጸጸቴ ጨመረ። የቀረኝን አንድ ኑዛዜ ደፍሬ በደሌን ልናዘዝ የያዝኩት ሃይማኖት አቅም ሰጠኝ። በጉዞዬም ይህን ያክል ማይባል ብዙ ነገር አገኘውበት። የበደልኳትን ልጅ በይቅርታ ፊቷ ቀረብኩ ለካ ኢሄ ሃይማኖት የበደሉንን ይቅር እንደምንል አንተም ይቅር በለን በሚል የምሕረት የይቅርታ ጸሎት ላይ የታነጸ ኖሯል የፈራኋት ልጅ ምንም እንዳልተበደለ ሰው ለኔ ይቅርታ አደረገች። በዚያ የአባ ትህትናን ቃል አደራ ገሚሱን ፈጸምኩ የቀረኝን ፍለጋ በቀደም እንዳልኩሽ ሰሜት እርሳቸው ጋር ሄድኩ።" አላቸው እንባው እየወረደ። እናቱ ታሪኩን ሰምተው ምንም ሳይመልሱ ፈዘው እያዩት ዝም አሉ። " ኢሄ ነው በኔ የሆነው። ዛሬ በዚህ ሃይማኖት ያቺን ተበዳይ ሴት ሚስቴ አድርጌ እየኖርኩ ነው እማ! እንደ ሀሳቤ አንቺን እናቴን አክብሬ ለደስታሽ ሁሉንም ነገር በፕሮግራም ላሳውቅሽ ሀሳብ ነበረኝ። ግን አንቺ ሁሉንም በድንገት አወቅሽ። ቢሆንም አሁንም የምወዳትን ሚስቴን እኔንም ልጃችንንም እንድትመርቂን ቲኒሽ ፕሮግራም አስቢያለው። ስላሳዘንኩሽ ሁሉ ይቅርታሽን ላገኝና ፍቃዴን እንዳትከለክይኝ ስለ ፍቃድሽ እንዲሆን ልጠይቅ ደግሞ ዛሬ ያው ወዳንቺ መጥቻለው። እማዬ ይቅር በይኝ መርቂኝ!" ብሎ ከእናቱ ጉልበት ተደፍቶ ተንበርክኮ ተማጸነ። " ልጄ ይቅርታ አድርጌልሀለው። የፈቀድከውንም አልከለክልህም። ያሰብከውንም ፕሮግራም በደስታ እቀበላለው። ግን ልጄ እኔ የምልህ ትክክለኛው ሃይማኖት የተቀበልከው ካልሆነ ጥፋትህን ስለማልፈልግ ነው" ሲሉት " አመሰግናለው እናቴ ለሕይወት ያብቃሽ ዘላለም ኑሪልኝ" አላቸው ቀና ብሎ። " ምነው ያ በሆነ ዛሬ ይህን ማንነትህን አባትህ ኖሮ ባየው" አሉና እናቱ ዓይናቸው እንባ አቀረረ። " አምላክ የፈቀደው ሆኗል እናቴ አትዘኚ። በይ መሸብኝ እኔም ልሂድ" ብሎ ሲነሳ ሊሸኙት አብረውት ወጡ። እያወሩ ከጊቢ ወተው እንደወዳጆች እየተጨዋወቱ ጥቂት ሸኝተውት ሲመለሱ ጨለማው ውስጥ ከጁ ባንጊያ የጨበጠ ቡቱቱ የለበሰ እብድ ከፊታቸው ቆመ። ደነገጡ። " አጠገቡ ደርሰው ነው ያዩት ሊጮሁ ሲሉ " ብትጮሂ በዚ ነው..." ብሎ ባንጊያውን ሲያነሳ ዝም ብለው ደንግጠው ቆሙ።...... 💠 ይቀጥላል 💠 💢💠ኅዳር 27 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠 ከክፍል 159 የቀጠለ 💠💢 ሌላው ያልነገርኩሽ እማ" አለ ኤርምያስ ወደ እናቱ እያየ። " ቀና ብለው አዩት። " እንዳልኩሽ ዋጋ የከፈሉልኝ አባ ትህትና ያልኩሽ አባት መምህሬም መንገድ መሪዬም ሆነውኝ ወድጄ ፈቅጄ የክርስትና ሃይማኖትን በመቀበል ተጠምቄያለው። ኢሄም ከሆነ ቲኒሽ ቆየ" ሲላት እናቱ  ሕጻኑን አስቀምጣው በንዴት " ምን?" አለችው። 💢💠🌿 ክፍል 166 🌿💠💢 ኤርምያስ ሳይግባቡ እናቱ በእንባ ታጅበው የርሱን ልጅ አያት የሚሆኑትን ተወዳጁን የራሄል ልጅ ንፍታሌምን ቁጭ አድርገው ሃይማኖቱን በመለወጡ እጅግ አዝነውበት ጥለውት ቤቱን ለቀው የወጡበትን ሁኔታ እያሰበ ከቀናት በኋላ አመሻሽ ላይ ወደናቱ መኖሪያ ቤት እየሄደ በሀሳቡ የትናንት የቀደመ አስቸጋሪ ማንነቱን እያስታወሰ ለዚህ ለዛሬ ማንነቱ ዋጋ ከፍለው የሰሩትን አባ ትህትናን በልቡ እያመሰገነ ከርሳቸው የተቀበለውን እርሱም ለሌላው ያለ ዋግ እንዲሰጥ ያሳሰቡትን አደራቸውን ለመፈጸም ልቡን እያበረታ ለመታመን ቃል እየገባ አባ ትህትና ዋጋ እንደከፈሉለት እርሱም በሕይወቱ ለሰዎች በሚችለው ሁሉ ዋጋ እየከፈለ ሊኖር ለራሱ በራሱ የልቡ እልፍኝ ውስጥ ራሱን ምስክር አድርጎ ለራሱ ቃል ገባ። ቀኑ እየጨላለመ ነው ብርሃኑ ድንግዝግዝ ብሏል። እርሱና ባለቤቱ ራሄል ከሚኖሩበት አቅራቢያ ከሚገኘው የእናቱ ቤት በሀሳብ ከራሱ ጋር እያወራ ምንም ሳይታወቀው የሄደ ሳይመስለው ከራሱ እያወራ ከእናቱ ቤት ደረሰ። ያ ለማንም የማይጨነቅ ክብር የሌለው ከዓመታት በፊት የነበረው ማንነቱ ዛሬ ፍጹም ተለውጦ የቤተሰቡን በር እንኳን አንኳኩቶ ወላጅ እናቱን ስላዘኑበት ምን ብሎ ከፊታቸው በድፍረት እንደሚቆም በማሰብ ፍርሀት ልቡን አርዶት ከበራቸው ቆሞ ሲያስብ ቆየ። " ቆይ ገብቼ እንዴት ነው የማወራት? ምን እላታለው? አምላኬ ሆይ እናቴን ለማሳዘን ምክንያት ሆንኩኝ ይቅር በለኝ" አለ። ያሰበውን ሳያውቅ በስሜት የሚሰማው አጠገቡ እንዳለ ሁሉ ድምጹን አሰምቶ። ጭንቀቱ አልለቀቀውም። እናቱ ቁጡ ስለሆኑ ግራ ተጋብቶ በሀሳብ ውስጥ እንዳለ " የኔ ልጅ እንዲህ ለሰው መጨነቅ የእናቱን በር እንኳን ከፍቶ ለመግባት አቅም እስኪያጣ ያደረሰው ኢሄ ስብእና ኬት የተገኘ ነው?" ኤርምያስ ደንግጦ ዞረ። እጃቸውን እንደምትበር ወፍ ዘርግተውታል ማመን እያቃተው ተጠጋቸው እናቱ አቀፉት ለረጅም ደቂቃዎች ከእናቱ እቅፍ በልጅነት ደስታ ቆየ። እናቱም አንዳች ቃላት ሊገልጹት አቅም በሌላቸው የእናትነት ፍቅር ጠፍቶ እንደተገኘ ልጅ በናፍቆት ስፍስፍ ብለው በእቅፋቸው አቆዩት። እንዳቀፉት የቀደመ ስሙን ጠርተው "መቼም ቢሆን ለኔ ልጄ ነህ። ሃይማኖትህን ተታለ ብትቀይርም እናትነቴ የመይቀየር ነው። ደግሞ ልብ ገዝተህ ወደ ቤተሰቦችህ ትክክለኛው ሃይማኖት እንደምትመለስ ተስፋ አደርጋለው" ሲሉት " ማንነው እናቴ እኔኮ ኤርምያስ ነኝ። አሁን የጠራሽው ሰው ሞቷል የለም። አሁን በእቅፍሽ ያለው አዲሱ ልጅሽ ነው። በሕይወት ያለው በሕይወት ዘላለም እንድትኖሪ የሚናፍቀው ልጅሽ" አላቸው። በመንገድ የሚያልፉት ጉድ እስኪሉ እናቱ አቅፈውት ቆዩና " በል ውስጥ ገብተን እናወራለን እንግባ" አሉትና ወደ ውስጥ ገቡ። የቤተሰቦቹ ጊቢ ዙሪያውን በቤት የተከበበ የሚከራዩ ብዙ ክፍሎች ያሉበት ሲሆን የነርሱ ቤት ከመሀል ይገኛል። ከዓመታት በፊት እነርሱ ጊቢ የሚገቡ ሴት ተከራዮች በኤርምያስ ምክንያት ከአንድ ወር በላይ ከይቀመጡም ወዲያው ይለቁ ነበረ። እነርሱ ጊቢ የሚገቡ ወንዶችም ቢሆኑ በርሱ ምክንያት እንብዛም የሚቆዩ አልነበሩም። ገና ጊቢ ሲገባ ኢሄን ሁሉ አስታወሰና በጣም ይጠላው ወደ ነበረ እነርሱ ጊቢ ብዙ ዓመት ወደ ኖረው ሰው ክፍል " መጣው ሂጂ ጊቢ እናቴ" ብሏቸው አቀና። ከክፍሉ ደጃፍ ደርሶ ገርበብ ያለውን በር ሲያንኳኳ አንድ አጭር ጠይም ወጣት ከውስጥ ወጣ። ኤርምያስ አቀረቀረ። ወጣቱ ገና ሲያየው " አንተ ነህ ያንኳኳኸው? እኔ አላምንም!" ብሎ ስሙን ሲጠራው ቀና ብሎ " ያ ማንነትም ስምም ዛሬ የለም። የረጅም ጊዜ ምኞትህ ሆኗል። ኤርምያስ እባላለው። ከክርስትናው መንጋ ተቀላቅያለው" ሲለው ወጣቱ ዘሎ ተጠመጠመበት። ብዙ አወሩ ብዙ ተነጋገሩ ድጋሚ ሊገናኙ ኤርምያስ ተሰናብቶት ወደናቱ ቤት ሄደ። ሲገባ እናቱ ሻይ እያፈሉ ነው። " እማዬ ምን እየሰራሽ ነው?" አለ ኤርምያስ " የምትወደውን ምግብ በሻይ በልተህ እንድትሄድ..." ሳይጨርሱ " ውይ አልበላም ፆም ነው" ሲላቸው ወሽመጣቸው ቁርጥ አለ። ተስፋ በመቁረጥ እርሱ ወዳለበት መጡ። አጠገቡ ተቀምጠው " ሃይማኖትህን ለመለወጥህ ምክንያትህ ምንድነው?" ጠየቁት። " ፍቅር" አለ ኤርምያስ። " በዚያች ሴት ምክንያት?" አሉት ራሄልን መስሏቸው። " አይደለም! አንድ የፍቅር ሰው! እኚያ ታላቅ ሰው አባ ትህትና" አለ። " እንዴት ለሚሞት ዘላለም ለማይኖር ሰው ስትል ሃይማኖትህን ትለውጣለህ?" አሉት ቆጣ ብለው። ዝም ብሎ ቆይቶ " ትክክለኛ ሰዎች መንገዳቸው ትክክል ነው። እነርሱ ደግሞ በሕይወታቸው ይሰብካሉ። ኑሯቸው አምላካቸውን ደስ የሚያሰኝ የሚያያቸውን ሰውም በተግባር የሚያስተምር ነው" አለ። " አንድ ሴት አይቀረኝ በዚያ መካከል ነው ጊቢ እያለው የማትመስለኝን ልጅ በፍቅሯ የተነደፍኩት። እርሷን ለማግኘት መንገዱ ቀላል አልሆነልኝም። ፍቅሬ ጭራሽ ጨመረ። የበለጠ ወደድኳት። ውስጤ በዝሙት እሳት ተቀጣጠለ። ሌሎች ሴቶች አልመስልህ አሉኝ። ያቺን ሴት ፈጣሪ አይደለም ሰው በማይወደው መንገድ እራሷን እንድትስት አድርጌ ወደ ምፈልገው ስፍራ ወሰድኳት። ያን አሳት ፍላጎቴን ፈጸምኩ። እርሷ ግን ምንም አታውቅም ነበረ። ስትነቃ የሚፈጠረውን በማሰብ በሌሊት አውጥቼ ከመንገድ ጣልኳት። የምትሆነውን ግን በርቀት እንከታተል ነበረ። አንድ ሰው በሌሊት ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄድ ወድቃ አገኛት አላለፋትም አንስቶ ወደ ቤቱ ወሰዳት እንጂ። በዚያ ሌሊት ነው የምወደው ልጄ ንፍታሌም የተጸነሰው። ልጅቱ ወደ ትምህርቷ ከቀናት በኋላ ተመለሰች። በትምህርቷ ጎበዝ የነበረችው ልጅ ቅስሟ ተሰበረ በዚያም ምንም አልተሰማኝም። ከወራት በኋላ ከጊቢ አጣኋት። ብዙ ፈለኩ አጠያየኩ ምንም። ከቆይታ በኋላ ጎባ እንደምትኖር ሰማው። የምትኖረው ደግሞ ሌሊት ካነሷት ሰው እህት ቤት ነበረ። ቆይቶ ባንድ በገጠማት አጋጣሚ ያን ሌሊት ያነሳትን ንጹ ሰው ከሰሰችው። ያ ሰው መነኩሴ ነበረ። አባ ትህትና ያኔ ወደዚህ የመጣው በአጋጣሚ ነበረ። ተመልሶ ሄዶ ከቆይታ በኋላ ሲመለስ ባለበት እንዲያዝ በወጣ ትዕዛዝ እኔ እያለው እርሳቸው ተይዘው ለፍርድ ቀረቡ። በምን እንዳወቁ አላውቅም ያኔ ለፍርድ ሲቀርቡ ልጅቷን መድፈሬን እኔ መሆኔን ያውቁ ነበረ። ሙሉ ስሜን እስከ አያቴ ድረስ። ጥፋቴ ጸጸት አላሳርፍ እያለኝ ስኖር በድንገት ያቺን ወጣት የደፈራት ሰው ተከሷል የፍርዱ ቀንም እንዲህ ነው ሲባል ሰማው። እማዬ በሁለት ሀሳቦች ላይ መወሰን አቅቶኝ ተቸገርኩ። በቦታው ከፍርዱ ከችሎቱ ብገኝ ድንገት እታወቅና እታሰር ይሆን ብዬ ፈራሁ። እንዳልቀር ስለኔ ዋጋ የሚከፍለውን ሰው ማየት ተመኘው። በመጨረሻ ወስኜ ሄድኩ። ከችሎቱ ተገኝቼ ከበስተኋላ ከተቀመጥኩበት አንድ ወጣት ብጣሽ ወረቀት አቀበለኝ። ገልጬ አነበብኩት። ከርሳቸው የተጻፈ ነው። ደፋሪው እኔ መሆኔን እንደሚያውቁ ተረዳው። " ለአእምሮህ

አደከምካት ብሎህ ነው እንግዲ ቻለው!" ሲሉት ሳላም " ኧረ እኔ ምን ደከምኩ በዚህ መጠን...."ሳትጨርስ ንፍታሌም "መጠኑ አይደለም። አስፈላጊ አልነበረም ነው የኔ አባባል" አለ። ሰላም ደግማ መልስ አልሰጠችም። ቢኒያምና ንፍታሌም ሰለቆይታቸው እየተጨዋወቱ የንፍታሌም እናት ቆንጆዋን ሰላምን በየደቂቃው ሰርቀው እያዩአት ደርባባነቷን እያደነቁ ለቢኒያም አስቸኳይ መልዐሰክት በስልክ ተደውሎ ተነግሮት ተቻኩሎ እንደሚመለስ ተናግሮ ወጣ። የንፍታሌም እናት በቢኒያም መሄድ ወደር የለሽ ደስታ ተሰማቸው። ምክንያቱም ሰላምና ልጃቸው የበለጠ እንዲያወሩ አጋጣሚው ምቹ ነው ብለው ስላሰቡ። " አዚሁ ሮቤ ነው የምትኖሪው?" ጠየቋት። ንፍታሌም የእናቱ ጥያቄ ምቾት አልሰጠውም። " አዎ እዚሁ ነው የምኖረው!" አለች ሰላም። " እሰይ ይሁን! የት አካባቢ ነው የቤተሰቦችሽ ቤት? የማን ልጅ ነሽ? ቤተሰቦችሽንስ አውቃቸው ይሆን?" አሏት በስስት ዓይን ዓይኗን እያዩ በጥያቄ ላይ ጥያቄ ደራርበው። ሰላም " የኔ ቤተሰቦች እንኳን ወደዚህ ወደ ቆላ አዋሽ ቆላቲ የሚባል ቦታ ነው አሁን የሚኖሩት" ስትል ንፍታሌም አዋሽ ቆላቲ የሚለው ቃል እንደመብረቅ የነጎድጓድ ድምጽ አስደነገጠው። ቃሉን የት እንደሰማው ለማስታወስ ሞከረ። ወዲያው ትዝ አለው። ከቤዛ ወንድም ጋር ሆነው ከፈረንጆች አጠገብ ከአንድ ባለኮከብ ሆቴል ውስጥ እንደሰማው አስታወሰ። " አባቴ መሪጌታ አመሀ ይባላል" አለች ሰላም ቀጥላ። ንፍታሌም የበለጠ ደነቀው። ነጮቹ አመሀ ብለው ሲያወሩ ሀገር ወዳድነቱን ቆራጥነቱን ኢትዮጵያዊነቱን ደግሞም እነርሱን መሞገቱን በመጨረሻም እንዳስጠነቀቃቸው የሰቡት ቀርቶ ያላሰቡት ሆኖ መመለሳቸውን በቁጭት ሲያወሩ በሰማቸው ጊዜ ሰፊው የወሬአቸው ምዕራፍ አመሀ የሚል እንደነበረ አስታወሰ። አመሀ እያሉ ሲደነቁበት ደግሞም ሲበሳጩበት የነበረው ሰው ደግሞ አሁን የሰላም አባት ሆኖ ሰማው። ንፍታሌም ግራ ገባው። የሰላምና የእናቱ ጨዋታ አጓጓውና ሊወጣ የነበረውን ሀሳቡን ትቶት ሊቆይ ወሰነ። እናቱ ሰላም ስለርሷ የጠየቋትን እንደመለሰች ጥያቄ ጨመሩ። " ተማሪ ነሽ? ነው ባለትዳር?" ንፍታሌም ደነገጠ። " ሰላም ትምህርት መጨረሷን የተማረችውን የትምህርት ደረጃ። ለጥቂት ጊዜ በሞያዋ መስራቷንና ትዳር እንዳልያዘች መለሰች። ንፍታሌምም እናቱም በሰሙት በአንድ ነገር ተደነቁ። ሰላም በሞያዋ አዲስ አበባ ከአንዱ ትልቅ የቤተክርስቲያን ሕንጻ አሻራዋን እንዳሳረፈችና በቤተክርስቲያኑ መንፈሳዊ ስዕላቱን የሳለችው እርሷ መሆኗን ስትነግራቸው በውስጣቸው እጹብ አሉ። የንፍታሌም እናትም አያይዘው " ልጄም በልጅነቱ ስዕል ይስል ነበረ" አሉ እንደምንም የሁለቱን ነገር ወደ ማስተሳሰር ለማምጣት ብለው። " አይ እማዬ የኔ ዝም ብሎ በተለምዶ ነው። የርሷ በጣም ትልቅ ጥበብና በዕውቀት የዳበረ ነው። ያውም መንፈሳዊ ስዕላትን ለመሳል መመረጥና የአምላክ ፍቃድ ያስፈልገዋል። ሰላም በእውነት አንቺ በጣም እድለኛና ትልቅ ሰው ነሽ!" አለ ንፍታሌም። እናቱ ስለሰጠው ምስክርነት ልጃቸውን በውስጣቸው መረቁት። የበለጠ የውስጣቸው ጥያቄ መልስ እንዲያገኝና ሁለቱን ለማቀራረብ " ልጄ ገና ሳይሽ ነው ልቤ እንዲሁ የወደደሽ! ንፍታሌምን ፈልጌው ነው የመጣሁት ስትይኮ ትናንት ድንግጥ ነው ያልኩት። ቀድሞ ትተዋወቁ ነበረ?" አሏት። ንፍታሌምም እግረመንገዱን ለእናቱ መልስ ሊሰጥ " ሰአሊና የመሪጌታ ልጅ መሆንሽን ለምን ባለፈው እንዴት ሳትነግሪኝ?" ብሎ ሲጠይቃት እናቱ እንደሚተዋወቁ የሆነ ግንኙነትም እንዳላቸው ተረድተው ደስ እያላቸው " በሉ ተጨዋወቱ የሆነች ስራ አለችኝ" ብለው ወጡ። የንፍታሌም እናት ልጃቸው ሰላምን እንደተመኙት ሊያገባት መንገድ እንደጀመረ እርግጠኛ ሆነው ፈነጠዙ። የርሳቸውን መውጣትና ንፍታሌም የጠየቃትን ጥያቄ አያይዛ ሰላም አፍና የያዘችውን የውስጧን ፍም እሳት ልቧን የሚያነደውን እሳት አውጥታ በግልጽ ልትነግረው ወስና " ያው አንተም እኔን ለመስማት ብዙ ዝግጁ አልነበርክም። እንጂ እኔ......" ብላ ዝም አለች አቅም አጣች። ውስጧ ያሰበው " እኔ ታሪኬን ብቻ ሳይሆን ራሴንም ላንተ መስጠት ነው ፍላጎቴ። አፈቅርሀለው" ልትለው ነበረ ግን አፏ ተሳሰረ። ንፍታሌም " እንጂ አንቺ....እ ምን?" ሲላት አምጣ " እንጂ እኔማ አንተን..........." 💠 ይቀጥላል 💠 💢💠ኅዳር 25 2016 ዓ.ም ባሌ ሮቤ 💠💢

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠🌿 ክፍል 165 🌿💠💢 " እንዲህ የሚያስተክዝህ የሚያሳስብህ ነገር ምንም አልገባኝም። ቆይ ምን ሆነሀል?" አሉት የንፍታሌም እናት። ንፍታሌም በማለዳ ቤተክርስቲያን ደርሶ ከተመለሰ በኋላ እጁ ላይ አንድ መጽሐፍ ይዞ ቁጭ ብሎ ሲብሰለሰል አይተውት። መልስ አልሰጣቸውም ዝም አለ። ዝም ያለው ሰምቶ እንዳልሰማ ሆኖ መስሏቸዋል። እርሱ ግን በሀሳብ ጭልጥ ብሎ ሰውነቱ እንጂ እርሱነቱ አልነበረም። " አንተን አይደለንዴ የማናግረው" ሲሉት አጠገቡ ደረሰሰው ከሀሳቡ ነቅቶ " ምንድነው ምን?" አላቸው። ያኔ ነው በትክክልም እንዳልሰማቸው የተረዱት። አጠገቡ ተቀምጠው " ልጄ ምን ሆነሀል? የመጡት እንግዳ በድንገት መሄድ ሲያስቆጣህ አኩርፈህ ማታ በቅጡ እንኳን ሳታወራኝ እኔም ደክሞህ ነው ከመንገድ የመጣኸው ብዬ ዝም አልኩህ። ዛሬ ደግሞ እንዲህ የምትብሰለሰልበት ምን ምክኒያት ኖሮህ ነው?" አሉት። ንፍታሌም ከአጠገቡ የተቀመጡትን እናቱን እንደተጨነቁ ስለገባው " የማስበው ብዙ ነገር ነበረ ሌላ የሚያስኮርፍ የሚያናድደኝ ግን ምንም አይኖርም። አንቺ አትጨነቂ" አላቸው ፈገግ ብሎ። " የመነኩሴው ማታ እንደነገርኩህ ነው። ባላሰብነው በድንገት ነው ጩኸት ሰምተን ወተን ስንመለስ ያጣናቸው። ኢሄ አሁን በኛ ያስፈርዳል? አሁን ቢኒያም እንዴት ተጨንቆ እንደነበረ ብታይ። የሚይዘው የሚጨብጠው ጠፋው። ንፍታሌም ሲመጣ ምን ይለኛል? እያለ ሲጨነቅ ነበረ" ሲሉት ቀበል አድርጎ " አይ እማዬ እኔ የተናደድኩመስሎሽ ነው እንጂ አልተናደድኩም። ደግሞ መሆን ያለበት ነው የሆነው። እግዚአብሔር ያለው ሆነ ምን ያናድደኛል? እኔ ስለ ሌላ ጉዳይ ነበረ ሳስብ የነበረው። እርሱም ቢሆን ያን ያህል ለኔ መጨነቅ አልነበረበትም" ሲላቸው እናቱ ፈገግ ብለው " ያው ደውሎ ሲነግርህ አደራ ጥለህበት የለ አደራዬን በላው ብሎ ነዋ" ብለው መጠነኛ ሳቅ እያቆራረጡመሳቅ ጀመሩ። " ሆሆሆ!" ይሉና በየመሀሉ ይስቃሉ። ንፍታሌም የሳቃቸው ምክንያት ምንም አልገባ ቢለው " ምነው እማ በሰላም ነው? በምንድነው እንዲህ የምትስቂው?" ጠየቃቸው። " እንዲሁ ነው! ሌላ ያልነገርኩህ ቢኒያም መነኩሴውን ፍለጋ መውጣቱን ነው" ብለው እንደገና ሰቁ። " የት ብሎ ነው የሚፈልጋቸው? ድከም ቢለው ነው" አላቸው። " ብቻውን እኮ አይደለም" አሉ በድጋሚ በአግርሞት እየሳቁ። " እና ከማን ጋር ነው?" አላቸው በርሱ ምክንያት ሌላ ሰው መድከሙ እያሳዘነው። "ልጄ!" አሉ እናቱ በስስት እያዩት " ቢኒያምና እኔ መነኩሴውን ስናጣቸው ግራ ገብቶን እያለን በር ተንኳኳ" ሲሉት " አይ እማዬ የጠየኩሽን ንገሪኝ እንጂ ከማን ጋር ነው?" አላቸው። " መነኩሴው መስለውኝ ነበረ ቢኒያም ከበሩ ላይ ከፍቶ ሲቆይብኝ ተነስቼ ወደርሱ ሄድኩ ከበሩ ላይ ስታወራው የነበረችው ቆንጅዬ ልጅ ለቁንጅናዋ ወደር የላትም። እንደዚያ ያለች ቆንጆ አይቼ አላውቅም። ገና ሳያት ደነገጥኩ። የበለጠ ደግሞ ንፍታሌምን ፈልጌው ነበረ ስትለኝ ልቤ ተርክክ አለ። ኋላ ስናወራትኮ ነው እርሷ መነኩሴውን ከመንገድ እንዳየቻቸውና ሁለት ሆነው እንዳለፏት ስትነግረን ቢኒያም እንዴት ያለች ውብ ልጅ አይቻት እንኳ ሳልጠግብ ከቢኒያም ጋር ተያይዘው ከመነኩሴው ሊደርሱ በረሩ" አሉት። የነገሩት ነገር ንፍታሌም ጋር አንዳች ስሜትና ጥያቄ ይፈጥርበታል ብለው አስበው ነበረ። አልሆነም። ሰምቶ ዝም አለ። እናቱ ዝምታው ውስጣቸውን አበገነው። " ልጅቷ ግን ለምንድነው የፈለገችህ?" ጠየቁት። " መች አውቂያት ለምን እንደፈለገችኝ አውቃለው?" ብሎ ጥያቄን በጥያቄ መለሰ። " ከምታውቃቸው ሴቶች በቃ እንደው በጣም ቆንጆዋን አስታውስ። እርሷ ነች" ሲሉት አባባላቸው በጣም ገርሞት ከት ብሎ ሳቀባቸው። " አውነቴን ነው ምን ያስቅሀል? እንደርሷ ያለ ውብ የለም። የውበት መለኪያ ነች። ቁንጅናዋን ለመግለጽ ቃል ያጥራል። እኔማ ወዲያው አግብታ ይሆን ብዬ አሰብኩ" አሉና ውስጣቸው ወዳሰናዳው አጀንዳ ወሬያቸውን ጎተቱት። " ማንነቷን ስላላወኩ ታግባ አታግባ አላውቅም" አላቸው። "አውቀህ ነው የምትጠመው ታውቃታለህ" ብለው ለንፍታሌም ተክለ ሰውነቷን መልኳን አለ ያሉትን ሰላምን ይገልጣታል ብለው ያሰቡትን ውብ ቃላት ሁሉ ተጠቅመው " እርሷ አሁን እኔ ካልኩትም በላይ ቆንጅዬ ነች" ሲሉት " እማ ላንቺ ቆንጆ የሆነች ለኔኮ ላትሆን ትችላለች። እኔ ያልኳትም እንደዛው ላንቺ....." ብሎ ሳይጨርስ " ኢሄ እንዳልከው አይነት አይደለም። እርሷን ውበቷን ሰው ሁሉ የሚስማማበት ነው። ለማንም ቆንጆ ነች እርሷ። ምንም አልጎደላትማ" ሲሉት " አሁን የርሷን ነገር እንተው። እኔም ወደ ጎባ ደርሼ መጣለው" ሲላቸው በጣም ተናደው " ፈልጋህ ነው የመጣቸው በጣም ወድጃታለው። እንደው ካላገባች ብትቀርባት። በዚያ ላይ እርጋታዋ። ኧረ የርሷ ሁለንተናዋ ውበት ነው" ሲሉት " ምን!" አላቸው። " አዎ ያው እንዲያው ሰንብቶ መኖር አይቀር የመኖር አንዱ ምዕራፍ ደግሞ ትዳር ነው። እንደርሷ ያለች ጸባየ መልካም ውብ ቆንጆ ደግሞ ተፈልጎም አይገኝም። ከሆነልህ አዎ እርሷን ብታገባ ብዬ ነው። ያውም አሰስካሁን አንዱ ካልቀደመህ ነው" ሲሉት የመጨረሻው ንግግራቸው እረፍት ሆኖት " ልክ ነሽ እማ። እስካሁን አትቆይም ኢሄኔ አግብታለች። ባይሆን እንኳን ታጭታ ነው የሚሆነው" አላቸው። ወዲያው የውጭ በር ሲንኳኳ ቀድሞ እርሱ ሲኖር በር የማይከፍቱት እናቱ ተቻኩለው ወጡ። ከበር ሲደርሱ በዝምታ ፈገግ ብለው ቆሙ። ቢኒያምና ሰላም ናቸው። " ሰላም አደራችሁ! ትናንት በዚያው እንደወጣችሁ ስትቀሩኮ አሳሰባችሁኝ። ደና ናችሁ!" ሲሏቸው ቢኒያም ለሰላምታ መዳፉን ዘረጋ። ጨብጠውት ሰላምም እንዲሁ ስታደርግ የንፍታሌም እናት " እንዴት ነሽ የኔ ቆንጆ ብለው" ጨብጠው ጉንጮቿን ሳሟትና ሶስቱም ተከታትለው ወደ ውስጥ ገቡ። " ኑ ግቡ ግቡ" እያሉ እናቱ ቀደሙ። ቀጥሎ ቢኒያም ገባ። ንፍታሌምን ሲያየው የጨው ሀውልት ሆነ። ተከትላው ሰላም ገባች። እርሷም የልቧን ሰው ከፊቷ ተሰይሞ ብቻ ያይደለ በፍቅሯ ከልቧ የተቀመጠውን ንፍታሌምን ገና ስታየው ሰውነቷ ተብረከረከ። " ኑ ወደዚህ ድረሱ። ነይ እዚጋ" ብለው ሰላም ከንፍታሌም አጠገብ እንድትቀመጥ ሲያመላክቷት " ዶ/ር እንዴት አለህ!" ብሎ ንፍታሌም ለሰላምታ ሲነሳ ቢኒያም ወደርሱ ተራመደ። አጠገቡ ደርሶ የናፍቆታቸውን ተቃቅፈው ቆዩ። ሲያበቁ ከቢኒያም ጀርባ የቆመችው ሰላምን " ሰላም! እንዴት አለሽ ደና ነሽ!" ብሎ ንፍታሌም መዳፉን ዘረጋ ሰላምም እንዲሁ ለምላሽ እጇን ዘርግታ " እግዚአብሔር ይመስገን!" አለችው ተጨባበጡና ቢኒያም ከንፍታሌም አጠገብ ሲቀመጥ ሰላም ከቢኒያም ጎን ተቀመጠች። ንፍታሌም ሰላምን ሰላም ሲላት እናቱ ስሟን አውቆ ነው ነው ለሰላምታ ነው ሰላም ያላት በሚል ብዙ ግራ ተጋቡ። " በሉ ተጫወቱ ሻይ ነገር ላፍላላችሁ" ሲሉ ቢኒያም " አይ አያስፈልገንም ሮብ እኮ ነው እማዬ" አለ ቢኒያም ንፍታሌም እናቱን እማዬ እንደሚለው ሁሉ እርሱም እንደናቱ ጠርቷቸው። " አይ የኔ ነገር ዘንግቼዋለው" አሉና እርሳቸውም ፈንጠር ብለው ስለሰላምና ልጃቸው ሊታዘቡ ተቀመጡ። በጨዋታቸው ውስጥ " ያደረከው ነገር ልክ አልነበረም። እንግዳው በአጋጣሚ ሳታውቁ ከሄዱ ሌላ ሰው ማድከም እንደገና ማስጠነቅህ ስተት ነው" አለው ቢኒያምን። እናቱ ቀበል አድርገው " አይ ቢኒያም እርሷን

ሰውዬ እንደው አድላችን አላግባባን" ሲሉ ይዞት የመጣው ልጅ አቀርቅሮ በአነጋገራቸው ሳቀ። ወዲያው ስሙር ወደ ውጭ ወጣና አሌክሳንደርንም ልጁንም ሰላም ብሏቸው ልጁ ተሰናብቶ ሲሄድ ስሙርና አሌክሳንደር ከጊቢ ተያይዘው ሲወጡ የስሙር እናት ተጣርተው " ኤው ስሙርዬ አትመነው። እነዚ ሰዎች አካላቸው ነጣ እንጂ የሰይጣን ቁራጮች ናቸው። ወይ ዱላ ነገር በጅህ ትይዝ እንዴ!" ሲሉት ሳቅ ብሎ " ኧረ አያስፈልግም አሁን ምንም አይፈጠርም አትጨነቂ እማዬ" ብሏቸው ሄደ። ቆንጆ ለእይታ የሚያመች ቦታ መርጠው ስሙርና አሌክሳንደር አብረው ቁጭ ባሉበት ይጨዋወቱ ጀመረ። አሌክሳንደር ስራውን ምን ይሰራ እንደነበረና ትልልቅ በዓለም ላይ ያሉ የሚጎበኙ ስፍራዎችን ተዘዋውሮ እንደጎበኘ በዚህ ስራውም ደስተኛ ሆኖ ለረጅም ጊዜ እንደሰራ በአጋጣሚም ወደዚህ አካባቢ ለተለየ ተልዕኮ እንደመጣና ኢሄን ስፍራ ገና ሲያየው የተሰማውን ስሜት የነበረውን የደስታ ያገኘውን እርካታ ሁሉ አንድ በአንድ ነገረው። በተለይም ተልዕኳቸውን ለመፈጸም ወደዚህ ስፍራ ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ከመጡ በኋላ በዚህ ደን ውስጥ ከነርሱ ጋር ስለነበረው ቆይታ ሁሉ እያነሳ አወጋለት። ስሙር ከአሌክሳንደር የሚሰማው ከሚያወራበት ስሜት ጋር ተደምሮ እውነት ቢመስለውም ሊያምነው ግን አልወደደም ውስጡ ላለማመን ታገለው። በትግል ውስጥም እያለ እዚህ የመቅረቱ ምክንያት ምን እንደሆነ ውስጡ ጥያቄ ፈጠረበት። ነገር ግን አልጠየቀውም። አሌክሳንደር አውርቶ እስኪያበቃ ጥያቄውን አቆይቶ ይሰማው ነበረ። በደኑ ውስጥ በነበራቸው ቆይታ ደኑንና በውስጡ ያሉትን ለማጥናት የነበሩት ልዑካን መሳሪያ ታጥቀው ደኑን ማሰስ እንደጀመሩ ነገረው። ወዲያው የአሌክሳንደር ስሜት ተለዋወጠ። ዓይኑ እንባ አቅሮ አንደበቱን ቃል አጠረውና ጥቂት ዝም አለ። ስሙር የበለጠ ለመስማት ጓጓ። " ከእለታት በአንዱ ቀን መሳሪያዬን ታጥቄ ወደ ንጊት ተቃርቧል በጨለማው ውስጥ ስንቀሳቀስ አንድ ሰው ብቻውን አገኘው ከሰውነት የራቀ በደል ፈጸምኩበት የሞተ መስሎኝ ጥዬው ሄድኩ። ያ ሰው ሽፍታ መስሎኝ ነበረ ያን ያደረኩበት" ብሎ ከሚያምሩት ዓይኖቹ እንባ ወረደ። ስሙር የበለጠ ፍጻሜውን ለመስማት ልቡ ተሰቀለ። " ጥዬው ሄድኩ ደኑን አካልዬ በድንግዝግዝ አውሬ በልቶታል ብዬ በዚያው ስመለስ አንድ ሰው ተጨምሮ ያን ሰው ሲያስታምመው አየው። እንዳልሞተ ተረዳው። ሁለቱንም በያዝኩት መሳሪያ እስከወዲያኛው ላሰናብታቸው ፈለኩና መሳሪያዬን አቀባበልኩ ካለሁበት ተደብቄ ማነጣጠር ጀመርኩ። ሳነጣጥር ከእይታ ይጠፉብኛል ቀና ብዬ ሳያቸው ግን ይታያሉ። ብዙ ደከምኩ። የበለጠ እልህ ተጋባው ከቆይታ በኋላ ወደነርሱ ተጠግቼ ልቶክስ ሳነጣጥር ከነርሱ ሌላ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ተመሳሳይ ሶስት ሰዎች ከእይታዬ ውስጥ ገቡ" አለና እንዴት ያንን ተአምር እንደሚተርክለት ግራ እየተጋባ " ያንን አጋጣሚ በትክክል እንኳን እንዳልተርክ ጊዜና ለመግለጽ አቅም ያጥረኛል። ከዚያ በቃ መሳሪያዬ አልተኮስ አለኝ ተቸገርኩ። ሳነጣጥር የማየውን ቀና ብዬ ስመለከት ሌላ ይሆንብኛል በተለይ የነዚያ ነጭ ልብስ የለበሱ ሰዎች ነገር ከአእምሮ በላይ ነው" እያለ የገጠመውን ሳይጨምር ሳይቀንስ አንድ በአንድ ተረከለት። 💠አንባብያን ታሪኩን ክ.122 ላይ ታገኙታላችሁ💠 ያን ቀን ቆሜ እያየዋቸው እነዚያ ነጫጭ የለበሱ ሰዎች ወደዚያ ምሥጢራዊ ተራራ ሲጓዙ ቆሜ እንዲህ አልኩ "Ethiopia is a mysterious country. The God of these religious people is great. It is absolutely inscrutable beyond conscience. My heart would love to find a path that leads me to this great divine mystery rather than the purpose for which it came. From these there is no hatred but peace"" ኢትዮጵያ ምሥጢራዊት ሀገር ነች። የእነዚህ ሃይማኖተኞች አምላካቸው ታላቅ ነው። ፈጽሞም የማይመረመር ከኅሊና በላይ ነው። ከመጣውበት አላማ ይልቅ ወደዚህ ታላቅ መለኮታዊ ምሥጢር መንገድ የሚመራኝ ባገኝ  ልቤ ይወዳል።ከእነዚህ ዘንድ ሰላም እንጂ ጥላቻ የለም በፍቅር  ገዳያቸውን የሚያሸንፉ ኃያላን ናቸው።"አልኩ ተሸነፍኩ ስላሸነፈችኝ ምድርና ስለ ጠቢባኗ ዘመርኩ ተማረኩ" አለው በቋንቋው አቀላጥፎ እየነገረው። ስሙር ፍጹም አመነው። አሌክሳንደር ያን እለት ነው ያንተ አባት ልጃቸው ለመሆንና የዚህች ሀገር ኗሪ ለመሆን የወሰንኩት። ከሁሉ በላይ ደግሞ የነዚያን ጠቢባን ሃይማኖተኞች ሃይማኖት ተቀብዬ አምላካቸውን ላመልክ ወሰንኩ። ከእንግዲህ ወደ ተሸነፈ ከንቱ መሰሎቼ ጥበብ አልመለስም። አባትህ ያስተምሩኛል ኢትዮጵያዊና ክርስቲያን ሆኜ እኖራለው" አለው በእንግሊዘኛ። ስሙር እየሰማው ሳያውቅ አለቀሰ። ከተቀመጠበት ተነስቶ አሌክሳንደርን አቅፎት ባንተ መንገድ አብረን እንጓዛለን። እኔም እንዳንተ ሀሳብህ ሀሳቤ ነው። መሪጌታ ለኔም ላንተም አባት ናቸው" አለው ለአሌክሳንደር። " አመሰግናለው " አለ አሌክሳንደር። ተቃቅፈው እንዳሉ አሌክሳንደር ከርቀት ባሪያውን አየው። " ያውና ያ ገደልኩት ብዬ የጣልኩት ሰው" ሲለው ስሙር ዞረ። ወዲያው ባሪያው ከእይታ ሲሰወርባቸው ሁለቱም ወደ ደኑ ባሪያውን ፍለጋ አቀኑ። 💠 ይቀጥላል 💠 💢💠 ኅዳር 24 2016 ዓ.ም ባሌ ጎባ 💠💢

👤👤👤👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤👤👤👤 👤👤 ህቡዕ ገጽ 👤👤 👤 ህቡዕ ገጽ 👤 💢💠 ከክፍል 158 የቀጠለ 💠💢 " አባዬ ሁሉንም አየሁ ይበቃል በቀረኝ እድሜ አምላኬን ማገልገል እፈልጋለው። ጣና ካሉት በአንዱ ገዳም ለመኖር ወስነናል" አላቸው። መሪጌታ ልዩ ፈገግታ በፊታቸው ታየ። ስሙርን አቅፈው ሳሙት። ደስ አላቸው። ስሙር በድጋሚ አንዳች ነገር ያለፈ አይነት ስሜት ተሰማው። ከአባቱ ጋር ወደ ፊት አቀኑ። መሪጌታ ከጫካው እንደወጡ ግባ ብለውት ወደ ቄስ ዲበኩሉ ቤት ሲያቀኑ ስሙር የኋሊት ወደ ዋሻዋ አቅጣጫ ተመለሰ። እንደደረሰ ከፍልፍሉ የተፈጥሮ ዋሻ በር ታላቁ ወንዝ ይፈሳል በየት ብሎ ወደ ዋሻው እንደሚሄድ ግራ ገባው። ስሙር ጨለማ የዋጠው ዋሻ ውስጥ አንዳች ነገር ሲገባ ያየ መስሎታል። ጫማውን አውልቆ ወደ ወንዙ በባዶ እግሩ ሲገባ ጨለማው ውስጥ ያለው ሰው ወደ ጥግ ልጥፍ ብሎ ቆመ። 💢💠🌿 ከፍል 164 🌿💠💢 የፈረንጅ ሀገር ትልልቅ ስመ ጥር በብርሃን ፈርጥ ያጌጡ ህንፃዎችን የቃኘ ሰው ወደ ጨለማው ዋሻ እየፈራ ሱሪውን ወደ ላይ ሰብስቦ በወንዙ ውስጥ እየተራመደ ልቡ እያመነታ ከመግቢያው ደረሰ። ስሙር የዋሻው መግቢያ በር ላይ ደርሶ ተሻግሮ የመጣበት ወደ ውስጥ የመግባት ድፍረቱ እንደ ጉም ተኖ ሲጠፋበት በፍርሀት ሆኖ ቆሞ ማሰብ ጀመረ። ስልኩን ከለበሰው ጂንስ ሱሪ ኪስ ውስጥ አውጥቶ ነስልኩን መብራት አብርቶ በቀኝ እጁ እንደጨበጠ ክንዱን በመዳፉ ስልኩን እንደያዘ ወደ ዋሻው ውስጠኛው ክፍል ዘረጋ። እንዳሰበው አልሆነለትም የስልኩ ብርሀን ጨለማውን ረቶ የዋሻውን የውስጠኛ ክፍል ገልጦ የሚያሳየው መስሎት ነበረ። ግና አልሆነም የስልኩ ብርሃን በጣም አነስተኛ የዋሻውን አካል ብቻ በገሚሱ በድንግዝግዝ ያሳየው ስለሆነ የልቡ አልደርስ አለ። ስልኩን እንዳበራ ወደ ውስጥ ሊገባ አሰበና ፍርሀት አሸኘፈው። ስሙር ወዲያው ወደ ኋላው ሊመለስ ወሰነ። ከውስጥ ከዋሻው ውስጣዊ ክፍል የነበረው ሰው ግን የስሙርን እያንዳንዱን እንቅስቃሴና ተግባሩን ከጨለማው ውስጥ ሆኖ ይከታተለው ነበረ። ስሙር ጥርት ያለውን ንጹ ውኃ በእግሩ እያንቦጫረቀ ከደቂቃዎች በፊት የመነጋገሪያ ስልኩን በጨበጠው መዳፉ የወንዙን ውኃ እየጨለፈ እየረጨ ተሻግሮ ጫማውን አጠለቀና በቀጥታ ታይቶ የማይጠገበውን የአዋሽን መልክአ ምድር የተፈጥሮ ውበት ደግሞ አስደማሚ የስነ ተፈጥሮ ትዕይንት እየቃኘ ወደ ቤተሰቡ ቤት አቀና። ከዋሻው ውስጥ የነበረው ሰው በቅርብ ርቀት ሆኖ ስሙር ወዴት እንደሚሄድ ከዋሻው ወቶ ተደብቆ ይከታተለዋል። ስሙር የዚህችን ሀገር ውብ ገጸ በረከት የእግዜር ስጦታ ልብ ሲል የነጮቹን መንደርና በዚያ የኖራቸውን ዓመታት በልቡ ይረግማል። አንዳንዴም ራሱን ይጠይቃል " ሰው ለምንድነው ወደ ነጮች በረከቱን ትቶ የሚሰደደው?" ይላል ራሱን። በዚህ ጥያቄው ውስጥ በነጮቹ ሀገር ያሳለፈውን በትዝታ ይቃኛል። በተለይም ከዚያ ዓለም አቀፍ የምርምር ማዕከል ውስጥ የነበረውን ጊዜ ፍጹም ማስታወስ እንኳ አይፈልግም ነበረ። አሁን ግን በእናት አባቱ ቤት በሚናፍቃት ሀገሩ መሆኑን ሲያስብ ደስታው ወደር ያጣል። " እማዬ!" እያለ እየተጣራ ወደ ቤት ገባ። " ስሙርዬ አለው መጣህ? አባትህስ ጥለውህ የት ጠፉ?" አሉት እናቱ። " ሰው ጋር ደርሼ መጣለው ጉዳይ አለኝ አለ" አላቸው። ስሙርን ሲከታተለው የነበረው ሰው ከመሪጌታ ቤት መግባቱን ሲያይ ወደነበረበት ተመልሶ ሄደ። የስሙር እናት ከጓዳ የነበረውን ስራቸውን ጨርሰው ወደ ሰሎን መዳፋቸውን እየጠራረጉ ብቅ ብለው " የኔ ልጅ በአባትህ እንዳትከፋ። እንግዲ እርሳቸው እንኳን ትናንት የመጣኸው አንተ እኔም እድሜዬን አብሪያቸው ኖሬ የማውቀው እግዜር ቅርባቸው መሆኑን ብቻ ነው። እርሳቸው ምሥጢር ናቸው። አንዳንዴ ስናደድ ዘላብድና ወይ ተቆጥቼ እናገራቸውና ወዲያው ዋጋዬን ሳገኝ እታረማለው" አሉት ፈገግ ብለው። ስሙር ደነገጠ። " ማለት እንዴት? የምን ዋጋ ነው?" አላቸው እናቱን። " አይ ልጄ የመዳፈሬን ነዋ። እርሳቸውን አስቀየምኩ ማለት ኬት መጣ ሳልለው የእግዜር በትር ይመታኛል። ታዲያ የርሱ ናቸው ማለት አይደል!" አሉት ፈገግታቸው ጨምሮ። ስሙር የበለጠ በአባቱ ተደነቀ። " እማዬ ቆይ ግን እንዴት ነው ወደዚህ ለመምጣት የቻላችሁት? ከሰሜን ተነስቶ ኢሄን ቤተሰብ ባሌ ጠረፍ ከእንዲህ ያለ ቦታ ያመጣው ምንድነው ይባላል?" አላቸው ስሙር እናቱን። " እስቲ ተወው! ለዚህም ነው አባትህ ምሥጢር ናቸው የምልህ! ልጄ እንዲሁ አንድ ቀን ተነስተው ከዚህ መውጣት አለብን አሉኝ ደነገጥኩ ነገሩም እንደማይሆን ነገርኳቸው። እንደው አቡዬ ጠርተዋቸው ይሁን አላውቅም። እኔም እዚህ ብንሆን ደስ ይለኛል። ግን ከዚህ መሄድ አለብን ብለው ሙጥኝ አሉ። ሞቴን ሞት ያድርገው አሻፈረኝ አልኳቸው። ይገርምሀል ወዲያው ምን ሀሳቤን እንደለወጠው ሳላውቅ መሪጌታን ተከትዬ ሁለቱን ወንድሞችህንና ሰላምን ይዣት ወደማላውቃት ባሌ መጣው። ስንቱን ከተማ አልፈን መሪጌታ ከዚህ ጫካ መሀል ኑሮአችን እንዲሆን ፈለጉ ያሉት ሆነ። ስሙርዬ መሪጌታ አቡዬ ጠርተዋቸው ነው እሚሆነው። አሁን በቅርብ ምን ሆነ መሰለህ!" አሉ በመዳፋቸው አፋቸውን እየጠረጉ " የሆኑ ፈረንጆች ወዲህ ወደ ላይ አንድ የምሥጢር ተራራ አለ። ሙሲቾ ይባላል። ፈረንጆቹ በጣም የሚመላለሱበት ወርቅ ነው ምን ይሁን አለ አሉ። ከነዚያ ፈረንጆች ጋር መሪጌታ ገጥመውልህ ጭራሽ ቤት ድረስ ጋብዘዋቸው ምሳ ማብላት የአካባቢው ሰው ሁሉ ተመሳጥረው ጽላታችንን ለነጮቹ ሊሸጡ ነው ብሎ መሪጌታን አገለላቸው። ወዳጆቻቸው ካህናት ጭምር አንዳንዶቹ አሟቸው። መሪጌታ እበተስኪያንም እንዳይገባ ቁልፍም ይቀበሉልሀል" አሉት አወራራቸው የተረት ያክል አጓጊ ነው። ስሙር " ከዚያስ?" ጠየቃቸው። " ከዚያማ አንድ ቀን ማለዳ ቄሱ የበተስኪያኑን በር ቢሉት ዲያቆኑ ቢታገል ማን ይክፈተው" አሉት በተደሞ። " እንዴ ለምን ቁልፍ ጠፍቶ ነው?" ስሙር ጠየቃቸው። " ምን ቁልፍ ይጠፋል። ሲከፍት የኖረው ቁልፍማ ስራውን ሰራ። ጋኑም ተከፈተ። መሸንቆሪያውንም ከፍተውትኮ ነው በሩ እንቢ ያለው። ኋላ ስንታቸው ያቃታቸውን መሪጌታ በስማም ብለው ከፈቱት አሉ" አሉና ያዩትን እየነገሩት የሚመስሉት እናቱ ነገሩን አሉ በሚል አጠናቀቁት። " ስሙርዬ ስሰማ ኮራው ደስ አለኝ። ያኔ ያገለሏቸው የገፏቸው ጊዜ ነጭ ጃንጥላ አመጣልሀለው ስራህን አሳየኝ ብዬ ለአቡዬ ተስዬ ነበረ። ሰማኝ የጠየኩትን አሳየኝ። ለአባትህ ስነግራቸው የአንቺ ጸሎት ነው የሰራው አሉኝ። እንዲህ ነው የአባትህ ነገር የአቡዬ ነገር አይሆንላቸውም" አሉት ስሙርን። ስሙር ልዩ ልዩ ጥያቄ በውስጡ ተፈጠረ። ስለ አባቱ ውስጡ ብዙ ነገር ማሰብ ጀመረ። " አባዬ ልጅ ሆኜም አስታውሳለው አንድ ጊዜ ከውስጤ የማይጠፋ አንድ እስካሁን የሚደንቀኝ ነገር በርሱ ሲሆን አይቻለው። በድንገት ነበረ ያየሁት በጣም ደንግጬ ነበረ። እንዳየሁት ሲያየኝ ለማንም ምንም እንዳልነግር ቃል አስገባኝ ምሥጢር ሆኖ በልቤ ተቀምጧል። አዎ እማዬ እውነት ነው አባቴ ልዩ ነው" አለ ስሙር ሁለቱም የየራሳቸውን የሚያውቁትን አስታውሰው እያደነቁ እየተጨዋወቱ የጋሽ በለጠ ልጅ አሌክሳንደርን ይዞት መጣና ከደጅ " እዚህ ቤት!" እያለ ሲጣራ የስሙር እናት " እመት ማነው!" እያሉ ወጡ። " ውይ እናንተ ናችሁ እንዴ? ግቡ። ለነገሩ አንተው ከነገርከው እንጂ ኢሄ