ar
Feedback
Top Mereja

Top Mereja

الذهاب إلى القناة على Telegram

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Top Mereja

تُعد قناة Top Mereja (@topmereja) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 21 338 مشتركاً، محتلاً المرتبة 10 174 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 1 514 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 21 338 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 04 أكتوبر, 2025، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -234، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 0، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 0‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً N/A‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 0 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 0 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የ Twitter አድራሻ : http://twitter.com/BoleMereja?t=watBbei5PnmgrUd80qQrnw&s=09 ዩቲዩብ : https://youtube.com/channel/UCXcMdhLzUAPeRAxW48JFClQ

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 05 أكتوبر, 2025) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.

21 338
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-547 أيام
-23430 أيام
أرشيف المشاركات
በትግራይ ክልል ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ለማፍረስ ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ አካላት አለመጠየቃቸው ቅሬታ አስነሳ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዋጁ መሠረት የጊዜያዊ አስተዳደሩን አፈጻጸም ሪፖርት አለማቅረባቸው ጥያ
በትግራይ ክልል ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ለማፍረስ ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ አካላት አለመጠየቃቸው ቅሬታ አስነሳ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዋጁ መሠረት የጊዜያዊ አስተዳደሩን አፈጻጸም ሪፖርት አለማቅረባቸው ጥያቄ አስነስቷል የማሻሻያ አዋጁ የትግራይ ክልል ወደ መደበኛ የሕግ ሥርዓት እንዲገባ ይረዳል ተብሏል ባለፉት ሁለት ዓመታት በጊዜያዊ አስተዳደር ሥር በቆየው ትግራይ ክልል በቀደመው ጊዜ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን ለማፍረስ የተንቀሳቀሱ አካላት ሳይጠየቁ መቅረታቸው ላይ ቅሬታ ቀረበ፡፡ በአዋጁ መሠረትም ጠቅላይ ሚኒስትሩም የጊዜያዊ አስተዳደሩን አፈጻጸም በተመለከተ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ሪፖርት ሳይቀርቡ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ዕድሜ ማራዘም አስፈላጊ አይደለም የሚል ቅሬታም በፓርላማ ቀርቧል፡፡ ቅሬታው የቀረበው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማክሰኞ መጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም. ባደረገው 21ኛ መደበኛ ስብሰባ፣ የፌዴራል መንግሥት በክልል ጣልቃ እንዲገባ የሚፈቅድለትንና በሥራ ላይ ያለውን አዋጅ ቁጥር 359/1995 ለማሻሻል የቀረቡ የማሻሻያ ድንጋጌዎች ላይ፣ ለ25 ደ... ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.ethiopianreporter.com/139854/ @BoleMereja

ሰበር ዜና ‼️ እንኳን ደስ አላችሁ። የሸኔ ዋና መሪ እና አዛዥ ተገደለ። በወለጋ ጫካ ባለው ቤቱ መስዕዋትነት ተቀበለ። ሙሉ መረጃውን ከስር ባለው ሊንክ ተመልከቱ 👇 https://youtu.be/YLV6IO86yUo

" በትግራይ ያለው የፓለቲካ ሁኔታ ለድህንነቴ ያሰጋኛል ! " - የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዱባይ ይገኛሉ
" በትግራይ ያለው የፓለቲካ ሁኔታ ለድህንነቴ ያሰጋኛል ! " - የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዱባይ ይገኛሉ። በዱባይ ሆነውም ' bird story agency ' ለተባለ ሚድያ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል። ለህክምና በዱባይ እንደሚገኙና በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ የገለፁት ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው አስከ አሁን በኋላፊነታቸው እንደሚገኙ በመግለፅ መንግስታዊ ስራዎች እየተከታተሉና እየፈረሙ እንደሚገኙ ገልፀዋል። " በቀጣይ ትግራይን ማንም ይምራት ብዙ አያሳስብም "  ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ማንኛውም የትግራይ መሪ ከፌደራል መንግስት በመቀራረብና በመመካከር የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በማክበር ግዝታዊ አንድነትና ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ መስራት አለበት " ብለዋል። የፌደራል መንግስት ለፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተገዢ በመሆን ከፌደራል መንግስት ውጪ ያሉ ታጠቂዎች ከትግራይ  እንዲወጡ መስራት አለበት ሲሉ አስገንዘበዋል። በትግራይ ላለው የፓለቲካ ቀውስ መፈጠር የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችን ተጠያቂ  ያደረጉም ሲሆን " ይህንን ሀቅ በመቀበል ለዚህ ውድቀት የዳረገንን አስተሳስብ መቀየር የትግራይ ችግር ይፈታል " ብለዋል። " ያለው በእድሜ የገፋ አመራር በ20 እና በ30 ዓመት ዕድሜ ውስጥ ለሚገኙ ለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ቦታውን መልቀቅ አለበት " ሲሉ አክለዋል። " ትግራይ ደጋግመው ወደ ስህተት በዘፈቁዋት አመራሮች መመራት የለባትም " በማለትም አሳስበዋል። ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በትግራይ ያለው የፓለቲካ ቀውስና አካሄድ ለድህንታቸው እንደሚያሰጋቸው በዚሁ ቃለ ምልልድ ወቅት ገልጻዋል። ይህም ክልሉን መልሰው የመምራት ዕድላቸው መሟጠጡ አመላካች ነው ተብሏል። @BoleMereja

ጥብቅ ማስጠንቀቂያ!!!! SCAM ALERT!!! ነገሩ እንዲህ ነው። በዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥን የሚተላለፍ ባለ 240 ክፍል ተከታታይ ድራማ ለመስራት በ18 ወር ኮንትራት ተዋንያንን መቅጠር እፈልጋለሁ
+3
ጥብቅ ማስጠንቀቂያ!!!! SCAM ALERT!!! ነገሩ እንዲህ ነው። በዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥን የሚተላለፍ ባለ 240 ክፍል ተከታታይ ድራማ ለመስራት በ18 ወር ኮንትራት ተዋንያንን መቅጠር እፈልጋለሁ የሚል መልእክት መስተዋት ፊልም ፕሮዳክሽን ነኝ በሚል ስም የኢትዮጵያ ተዋንያን እና ፊልም ሰሪዎች ማህበር የቴሌግራም ቡድን ላይ ይለቀቃል። በሌላም መንገድ አይታቻሁት ይሆናል። ጉዳዩን የነገረችን ለትወና እድል ጉጉት ያላት ወጣት ሲቪ እና አድራሻዋን ከፎቶ ጋር አድርጋ ትልክላቸዋለች። አሁን ደግሞ Emotion እና Pause ያለው የራቁት ፎቶ ላኪ ይሏታል። "አልገባኝም🤔" ስትላቸው አቦል ቲቪ ላይ ድራማ የሚሰሩ ናቸው ያሏትን ሁለት ሴቶች ፎቶ ይልኩላትና እንደዚህ ተነስተሽ ላኪ ይሏታል። ፎቶዎቹ የወሲብ ስሜት ላይ ያሉ አይነት ነው። ፎቶዎቹን እንድታምኚ ያህል ነው የላክንልሽ ብለው ካሳዩዋት በኋላ አጥፍተውታል። ንግግራቸውም በቡድኑ ቴሌግራም ሳይሆን በግል የማጣደፍ አይነት ነበር። ልጅቷ ለወንድሟ ነግራው መረጃው እኔ ጋር እስኪደርስ ድረስ ልጅቷ አምናቸው ነበር። እንዳሉት ፎቶ ልካ ቢሆን ሳታውቀው ፎቶዋ በወሲብ ግዢ ቴሌግራም ውስጥ ተለቆ ገንዘብ(ወንጀል) ይሰራባት ነበር ወይም ሌላ። ይህ መሰሉ ነገር የተለመደ እና አደገኛ ማጭበርበር (SCAM) ነው። እውነታዎችን ያዙ! 1. አቦል ቴሌቪዥን ጠይቄአለሁ መስተዋት ፊልም ፕሮዳክሽ ከሚባል ተቋም ጋር የረዥም ተከታታይ ድራማ ውል የለንም ብለዋል። 2.የኢትዮጵያ ተዋንያን እና ፊልም ሰሪዎች ማህበር የሚባል ህጋዊ ተቋም የለም። ያለው የኢትዮጵያ ፊልም ሰሪዎች ማህበር፣ የፊልም ፕሮዲዩሰሮች ማህበር ፣የኢትዮጵያ ተውኔት ባለሞያዎች ማህበርና የኢትዮጵያ ቲያትር ባለሞያዎች ማህበር እና አላቲኖስ የኢትዮጵያ ፊልም ሰሪዎች ማህበር ናቸው። 3. በቴሌግራም የሚያነጋግራችሁ Mestewat Aragaw bot በታዋቂዋ ተዋናይት እና ሙዚቃ ባለሞያዋ መስተዋት አራጋው ነው። ቅጥፈት ነው። 4. ኦዲሺን ወይም የተዋናይ ምልመላ የሚያደርግ የፊልም ተቋም የቢሮ አድራሻ ወይም ስልክ ወይም የሆነ ታዋቂ ሰው የታመነ ቦታ ይኖረዋል። ይሄኛው ከቴሌግራም ሊንክ ውጪ አድራሻ የለውም። 5. ለተትወና ምልመላ የራቁት ፎቶ ላኩልን የሚል የፊልም እና የተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ፕሮዲዩሰር የለም። የት ሆኖ ሊሰራው ነው ስታስቡት? ካለም አትላኩ። ካለም ይሄን ፀያፍ ጥያቄ አጋልጡ። ተዋናይ ለመሆን የቱንም ያህል ብትጓጉ ራሳችሁን እየጠበቃችሁ። ተዋናይ ለመሆን የሚያስችሉ በርካታ ህጋዊ መንገዶች አሉ። ተማሩ ፣ በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ችሎታችሁን ለማሳየት ጣሩ። ተዋንያን የሚፈልጉ ያላችሁበት ድረስ ይመጡላችኋል። ያጋጠመሽን ከማስረጃው ጋር ያጋራሽኝ እህት ተባረኪ። እግዜር ጠብቆሻል ❤🙏 መልእክቱን እያጋራችሁ እያደረጋችሁ ሴቶቻችሁን ከውርደት ጠብቁ!!! ©Meaza Worku ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

ሰበር መረጃ ‼️ ዋናው አዋጊ መሪ ጀነራል ተማረከ። ያሳደገውን ህዘብ የወጋ ፣ ከሃዲ የጦር መሪ በስተመጨረሻም ተያ። ሙሉ መረጃውን ከስር ባለው ሊንክ ተመልከቱ 👇 https://youtu.be/MBJL8ThpFX0

ልዩ መረጃ ‼️ የሲዳማ ክልል ፕሬዘዳንት ከአገር ሸሽተው እንዳያመልጡ ለአገሪቷ ኢሚግሬሽን ትእዛዝ ተሰጠ። በከፍተኛ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በፌደራሉ መንግስት ግምገማ ላይ ያሉት አቶ ደስታ ሌዳሞ
ልዩ መረጃ ‼️ የሲዳማ ክልል ፕሬዘዳንት ከአገር ሸሽተው እንዳያመልጡ ለአገሪቷ ኢሚግሬሽን ትእዛዝ ተሰጠ። በከፍተኛ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በፌደራሉ መንግስት ግምገማ ላይ ያሉት አቶ ደስታ ሌዳሞ ምርመረቻው ተጣርቶ ሲጠናቀቅ በክልሉ አዲስ የአመራር ሹም ሽር ይካሄዳል ተብሏል። አርቲስት ቶክቻው ለሲዳማ ህዝብ በመቆርቆር ያደረገው ትግል የሚደነቅና የሚያስመሰግነው ነው። @BoleMereja

መረጃ ! በደሴ ከተማ አስተዳደር ዛሬ መጋቢት 23/2017 ዓ.ም ከጧቱ 2:00 ሰዓት ላይ በደሴ ከተማ ልዩ ስሙ ፒያሳ ሜጠሮ መቃኛ አካባቢ የደሴ ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ አባል የሆነው ዋና ሳጅን ገብ
መረጃ ! በደሴ ከተማ አስተዳደር ዛሬ መጋቢት 23/2017 ዓ.ም ከጧቱ 2:00 ሰዓት ላይ በደሴ ከተማ ልዩ ስሙ ፒያሳ ሜጠሮ መቃኛ አካባቢ የደሴ ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ አባል የሆነው ዋና ሳጅን ገብሬ  እውነቱ በተመደበበት ቀጠና መኖሪያ አቅራቢያ ነዋሪ የሆኑትን ሸህ ሙሀመድ ሠይድ እና ባለቤታቸውን ወ/ሮ ጀሚላ መሀመድን በያዘው ክላሽን ኮፍ መሳሪያ በተኮሰው ጥይት ሸህ መሃመድ ሰይድ ሲገደሉ ባለቤታቸው ቆስለው በደሴ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በህክምና ላይ  እንደሚገኙ በደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ 2ኛ ዋና ፖሊሰ ጣቢያ ኀላፊ  ም/ኢ/ር ፀጋ አባተ ገልፀዋል። ገዳዩ በአሁን ሰዓት በ2ኛ ዋና ፓሊስ ጣቢያ በህግ ቁጥጥር ስር የሚገኝ ሲሆን የድርጊቱን መንስኤ እንዳልታወቀ ፖሊስ አስታውቋል። @BoleMereja

ልዩ መረጃ ‼️ በአማራ ክልል ጎጃም የመከላከያ ዋና  አዋጊ ተደመሰሰ። በመሃል ከተማ ውስጥ በድንገት ጉድ ሰሩት። ሙሉ መረጃውን ከስር ባለው ሊንክ ተመልከቱ 👇 https://youtu.be/bPJRrq5VGQQ

በየካቲት ወር ብቻ ከፍጥነት ወሰን በላይ ያሽከረከሩ 2806 አሽከርካሪዎች ተቀጡ! የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን የትራፊክ ቁጥጥርና ኩነት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በየካቲት ወር 2017
በየካቲት ወር ብቻ ከፍጥነት ወሰን በላይ ያሽከረከሩ 2806 አሽከርካሪዎች ተቀጡ! የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን የትራፊክ ቁጥጥርና ኩነት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም ባካሄዳቸው የቁጥጥር ሥራዎች አንዱ በሆነው ‘በሕግ ከተወሰነው የፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር’ ላይ 2 ሺሕ 806 አሽከርካሪዎች በሕግ ከተወሰነው የፍጥነት ወሰን በላይ ሲያሽከረክሩ በመገኘታቸው የእርምት ርምጃ መውሰዱን አስታውቋል፡፡ ዳይሬክቶሬቱ ያከናወነውን ሥራ አስመልክቶ በሪፖርት እንደገለፀው፤ በየካቲት ወር 3 ሺሕ 102 አሽከርካሪዎች ላይ ምርመራ ለማድረግ ዐቅዶ፤ 2 ሺሕ 806 አሽከርካሪዎች በሕግ ከተወሰነው የፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከራቸው የእርምት ርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡ በዚህም የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ከፍተኛው ከሕግ ከተወሰነው የፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር የተገኘበት ሲሆን ልደታ እና ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተሞችም ይከተላሉ ተብሏል፡፡ በከተማዋ በቀን በአማካይ አንድ ሰው በመንገድ ትራፊክ አደጋ ምክንያት ሲሞት ከሁለት እስከ ሦስት ሰው ላይ የአካል ጉዳት እንደሚደርስ የገለጸው ዳይሬክቶሬቱ፤ ለዚህም እንደምክንያት ከሚጠቀሱት ውስጥ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር አንደኛ ምክንያት መሆኑን አስታውቋል ሲል አሃዱ ሬዲዮ ነው የዘገበው። @BoleMereja

ልዩ መረጃ ‼️ ከነገ ሰኞ ጀምሮ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና ፌደራል ፖሊስ ወደ ትግራይ ክልል ከተሞች እንደሚገባ የወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ። የፌደራል መንግስቱ ለዚህ ውሳኔ የደረሰው ከትላንቱ በጀነራል ታደሰ ወረደና በጠ/ሚር አብይ አህመድ ውይይት በተደረሰ ስምምነት እንደሆነ ነው ያገኘነው መረጃ የሚያመላክተው። የትግራይ ይሄ  ህዝብ ከሻዕብያና ከሻዕብያ ተላላኪ ሽብር ፈጣሪ  ቡድኖች ለመከላከል የፌዴራል ፖሊስ ና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በዋና ከተማ መቐለ፣ ዓዲግራት፣ ዓድዋና ሽሬ ዜጎችን ዋስትና ለማረጋገጥ ሙሉ ሀይል ይገባሉ። @BoleMereja

የደመወዝ ጭማሪ‼️ ለዐቃቢ ሕግ ከ35% - 50% የደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም ጭማሪ (ማሻሻያ) ተደረገ። 35%-- 24000+11000 35%-40%~20400+11000 40%-50%~ 18000+11000 ጭ
የደመወዝ ጭማሪ‼️ ለዐቃቢ ሕግ ከ35% - 50% የደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም ጭማሪ (ማሻሻያ) ተደረገ። 35%-- 24000+11000 35%-40%~20400+11000 40%-50%~ 18000+11000 ጭማሪ ተደርጓል። @BoleMereja

እስካሁን ከ1700 በላይ ሰዎች ሞተዋል! በሚያንማር የተከሰተውን ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ እስካሁን ከአንድ ሺህ ስድስት መቶ በላይ ሰዎች መሞታቸውን ቢቢሲ ዘግበቧል። @BoleMereja
እስካሁን ከ1700 በላይ ሰዎች ሞተዋል! በሚያንማር የተከሰተውን ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ እስካሁን ከአንድ ሺህ ስድስት መቶ በላይ ሰዎች መሞታቸውን ቢቢሲ ዘግበቧል። @BoleMereja

ሰበር ዜና ‼️ የባህርዳር ከተማ መውጫ እና መግቢያ መንገድ ተዘጋ። ዋና ከተማዋ ተከባለች። ሙሉ መረጃውን ከስር ባለው ሊንክ ተመልከቱ 👇 https://youtu.be/7KHL1A_pYh4

አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች “በሽብር ወንጀል” ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀረቡ‼️ የፌደራል ፖሊስ “በሽብር ወንጀል ጉዳይ” ጠርጥሬያቸዋለሁ ያላቸውን አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተ
አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች “በሽብር ወንጀል” ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀረቡ‼️ የፌደራል ፖሊስ “በሽብር ወንጀል ጉዳይ” ጠርጥሬያቸዋለሁ ያላቸውን አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞችን፤ በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት አቀረበ። ጉዳዩ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ፖሊስ በጠየቀው የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ላይ ብይን ለመስጠት ለመጪው ሰኞ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። የፌደራል ፖሊስ የጊዜ ቀጠሮውን የጠየቀው፤ በስምንት ተጠርጣሪዎች ላይ እያካሄደ ያለውን የምርመራ ስራ “በሰው እና በሰነድ ማስረጃ በስፋት ለማጣራት” በሚል ነው። ከስምንቱ ተጠርጣሪዎች ውስጥ ባለፈው ሳምንት እሁድ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ በተሰራጨ ዝግጅት ላይ “የሀሰት ታሪኳ” ቀርቧል የተባለው ብርቱካን ተመስገን ትገኝበታለች። @BoleMereja

ሰበር ዜና ‼️ የመከላከያ ልዩ ኮማንዶ መቀሌ ገባ ! ።የተፈራው ነገር ሆነ! ጥቃት ፈፀመ። ሙሉ መረጃውን ከስር ባለው ሊንክ ተመልከቱ 👇 https://youtu.be/nWEpLJRXMSA

የአዲስ አበባ ባንኮች እስከ ምሽት 3 ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ ተጠየቀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የንግድ ቢሮ ባንኮች እስከ ምሽት 3 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እንዲሰጡ ለብሔራዊ ባንክ ጥያቄ አቅርቧል። የንግድ ቢሮው  እንዳለዉ እንደማንኛውም አገልግሎት ሰጪ የንግድ ተቋማት ዋና ዋና መንገድ ላይ የሚገኙ ባንኮች እስከ ምሽቱ 3 : 30 ድረስ አገልግሎት የሚሰጡበት አሰራር እንዲዘረጋ የትብብር ጥያቄ የቀረበዉ። ዋና ዋና መንገድ ላይ የሚገኙ የንግድ ተቋማት እስከ ምሽቱ 3:30 ድረስ እንዲሰሩ ከተወሰነ ብዙ ባንኮችም በዚሁ መስመር ላይ የሚገኙ በመሆኑ የአገልግሎት ሰዓታቸውን ማራዘም ለንግድ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ ያደርጋል ያደርጋል መባሉን ቅዳሜ ገበያ ሰምታለች። ይህን ተከትሎ ቢሮው በቀጥታ ባንኮችን የማዘዝ ስልጣን ስለሌለው የትብብር ጥያቄው በደብዳቤ ለማዕከላዊ ባንኩ ማቅረቡን ነዉ ለመረዳት የተቻለዉ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ደምብ 185/2017 የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ምሽት 4 ሰዓት ድረስ በመንገድ ዳር የሚገኙ የንግድ ተቋማት ደግሞ ምሽት 3:30 ድረስ እንዲቆዩ የሚያስገድድ ደምብ ከመጋቢት 10 ጀምሮ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል። ቅዳሜ ገበያ

ሰበር መረጃ ‼️ በዘመነ ካሴ የሚመራው የጎጃም ፋኖ ታሪክ ሰራ። ታይቶ የማይታወቅ ከባድ ማጥቃት መፈፀም። አራት ኦራል ወታደር ተደመሰሰ። ሙሉ መረጃውን ከታች ባለው ሊንክ ያገኙታል 👇 https://youtu.be/Up-C-wL3F5k

"መንግሥት የብርቱካንና መሰል ጓደኞቿን እገታ ቢያንስ ለችግሩ እውቅና ሰጥቶና ሕዝብን አስተባብሮ ወደ መፍትሔው መሔድ ሲገባው ማድበስበስን በመምረጡ እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ችግሩ ሥር ሰዶ ከእለት እለት
"መንግሥት የብርቱካንና መሰል ጓደኞቿን እገታ ቢያንስ ለችግሩ እውቅና ሰጥቶና ሕዝብን አስተባብሮ ወደ መፍትሔው መሔድ ሲገባው ማድበስበስን በመምረጡ እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ችግሩ ሥር ሰዶ ከእለት እለት እየከፋ ሄዷል፡፡ መጋቢት ፰ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል እየተጓዘ በነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ላይ በኦሮሚያ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን፣ ወረ ጃርሶ ወረዳ፣ ልዩ ስሙ አሊዶሮ በተባለ ቦታ አሽከርካሪውን ጨምሮ መላ ተሳፋሪዎች መታገታቸውንና ለማስለቀቂያ የሚኾን በነፍስ ወከፍ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እየተጠየቀባቸው መኾኑን ሰምተናል፡፡" - መኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄና እናት ፓርቲ ዛሬ በጋራ ካወጡት መግለጫ @BoleMereja

ሰበር ዜና ‼️ ጀነራል ዉጊያ ለመምራት በሄዱበት ግምባር ተከበቡ። አቃታቸው ተጨማሪ ጦር እንዲላክ ታዘዘ።ሙሉ መረጃውን ለማየት👇 https://youtu.be/m350uqwHMoA

ተወዳጁ ድምፃዊ አብዱ ኪያር ከደረሰበት አደጋ አገግሞ አሁን በከዘራ ታግዞ መራመድ መጀመሩን እና በቅርቡም ያለምንም እርዳታ መራመድ እንደሚጀምር ገለጸ። "አልሓምዱሊላህ በከዘራ ድጋፍ መራመድ ጀምሬያለ
ተወዳጁ ድምፃዊ አብዱ ኪያር ከደረሰበት አደጋ አገግሞ አሁን በከዘራ ታግዞ መራመድ መጀመሩን እና በቅርቡም ያለምንም እርዳታ መራመድ እንደሚጀምር ገለጸ። "አልሓምዱሊላህ በከዘራ ድጋፍ መራመድ ጀምሬያለሁ" በሚል በቪድዮ ያሰራጨው አብዱ፣ ጉዳት ከደረሰበት በኋላ ደግሞ የእናቱም ሃዘን ተደርቦበት እንደበር የሚታወቅ ሲሆን "ከአገር ውስጥ ፣ ከተለያዩ አገራት ፣ በአካል ፣ በስልክ ፣ በኢሜይልና በተለያየ መንገድ ያፅናናችሁኝ ያበረታችሁኝና የፀለያችሁልኝ ወንድምና እህቶቼ እጅግ በጣም አመሰግናለሁ። " ብሏል። "አልሓምዱሊላህ ከሀዘኔ ተፅናንቻለሁ ከህመሜም አገግሜ አሁን አጥንቴ ገጥሞልኝ በከዘራ እየታገዝኩ በደንብ እየረገጥኩ እራመዳለሁ።" በሚል መልዕክት ያስተላለፈው አብዱ "በሚቀጥሉት ቀናት በደምብ ተለማምጄ በቅርብ ያለምንም እርዳታ መራመድ እጀምራለሁ። በድጋሚ ሁላችሁንም አመሰግናለሁ።" በማለት መልዕክት አስተላልፏል። ድምጻዊው ልክ የዛሬ ወር ባስተላለፈው መልዕክት "በቀደም ሊፍት ወድቆብን ከከባድ አደጋ ተረፍኩ። ዛሬ ደግሞ የናቴን ሞት ተረዳሁ። ፈተናው እየበዛብኝ ነው። ሁላችሁም በፆማችሁ እና በፀሎታችሁ አስታውሱኝ" ሲል ጥሪ አቅርቦ እንደነበር ይታወሳል። @BoleMereja